Search Results for 'ዳያስፖራ'

Home Forums Search Search Results for 'ዳያስፖራ'

Viewing 12 results - 1 through 12 (of 12 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    ለኢንቨስትመንት ዘርፍ ተጨማሪ አቅም የሚሆነው ሲዳማ ባንክ

    ቀደም ሲል “ሲዳማ ማይክሮፋይናንስ ተቋም” በመባል የሚታወቀው የብድርና ቁጠባ ተቋም “ሲዳማ ባንክ አክሲዮን ማኅበር” ሆኖ በባንክነት ለመደራጀት በሐምሌ ወር 2014 ዓ.ም ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ አግኝቷል።

    አዲስ አበባ (አዲስ ዘመን) – በአንድ ሀገር የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ ውስጥ የጎላ ሚና ካላቸው ባለድርሻ አካላት መካከል የፋይናንስ ተቋማት በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳሉ። እነዚህ ተቋማት በሀገራዊ የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ ውስጥ ካላቸው ሚና መካከል አንዱ ለኢንቨስትመንት ተግባራት የፋይናንስ ምንጭ መሆናቸው ነው።

    የብድርና ቁጠባ ተቋማትን ጨምሮ ባንኮችና የመድን (insurance) ድርጅቶች በአነስተኛም ሆነ በትልልቅ የኢንቨስትመንት ተግባራት ላይ ለተሰማሩ ግለሰቦች፣ ማኅበራትና ኩባንያዎች የሥራ ማከናወኛ የገንዘብ ምንጮች እና የንብረት ዋስትናዎች ሆነው ይሠራሉ። ውጤታማ የኢንቨስትመንት ተግባራት አስተማማኝ የፋይናንስ አቅርቦት የሚፈልግ በመሆኑ በኢትዮጵያም ሆነ በሌላው ዓለም ያሉ የኢንቨስትመንት ሥራዎች ከእነዚህ የገንዘብ ተቋማት ተሳትፎ ውጭ የሚታሰቡ አይደሉም።

    ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የበርካታ ዜጎችን ሕይወት በበጎ የለወጡት የብድርና ቁጠባ ተቋማት ለአነስተኛና መካከለኛ የኢንቨስትመንት ሥራዎች ውጤታማነት የነበራቸው ሚና ከፍተኛ እንደሆነ አይዘነጋም። በኢትዮጵያ የብድር እና ቁጠባ ተቋማት ደንበኞች ቁጥር ከባንክ ደንበኞች ቁጥር በብዙ እጥፍ የላቀ ነው። ይህም ለአብዛኛው ሕዝብ የብድር አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት እነዚህ ተቋማት እንደሆኑ አመላካች ነው። አንጋፋ የሚባሉት የብድርና ቁጠባ ተቋማት የፋይናንስ አቅማቸው ከብዙ አዳዲስ ባንኮች ጭምር የተሻለ ነው። ዛሬ በትልቅ ስምና አቅም የሚታወቁ ብዙ የኢንቨስትመንት ድርጅቶች መነሻቸው እነዚህ የብድርና ቁጠባ ተቋማት ናቸው።

    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የብድርና ቁጠባ (የማይክሮፋይናንስ) ተቋማት አስተማማኝና ፍትሐዊ በሆነ አሠራር እንዲሠሩና ሕዝባዊ ተዓማኒነት እንዲኖራቸው እንዲሁም ባንክ ሆነው ለመንቀሳቀስ የሚስችላቸው ሕጋዊ ማዕቀፍ እንዲኖራቸው የሚያስችል መመሪያ ከሁለት ዓመታት በፊት ማውጣቱ ይታወሳል። የብድርና ቁጠባ ተቋማቱ ያላቸውን ግዙፍ የደንበኛና የፋይናንስ አቅም ትልልቅ በሆኑና የተሻለ ትርፍ ሊያመጡ በሚችሉ ኢንቨስትመንቶች ላይ እንዲያውሉት የተዘጋጀው ይህ መመሪያ፤ ብዙ የብድርና ቁጠባ ተቋማት ወደ ባንክ እንዲሸጋገሩና ወደ መደበኛ የባንክ ሥራ እንዲገቡ እያስቻለ ነው።

    በዚሁ መመሪያ መሠረት ቀደም ሲል “ሲዳማ ማይክሮፋይናንስ ተቋም” (Sidama Microfinance In­stitution) በመባል የሚታወቀው የብድርና ቁጠባ ተቋም “ሲዳማ ባንክ አክሲዮን ማኅበር” (Sidama Bank S.C.) ሆኖ በባንክነት ለመደራጀት በሐምሌ ወር 2014 ዓ.ም ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ አግኝቷል። ባንኩ 1,988 ባለአክሲዮኖች ያሉት ሲሆን፥ የተፈረመ ካፒታሉ አንድ ቢሊዮን 447 ሚሊዮን ብር ነው። ከዚህ ውስጥ ከ583 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆነው ገንዘብ የተከፈለ ካፒታል ነው።

    የሲዳማ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀ መንበር አቶ አብርሃም ማርሻሎ ባንኩ ከብሔራዊ ባንክ የሥራ ፈቃድ ማግኘቱን ተከትሎ በባንክ ዘርፍ ተግባራት ላይ ለመሰማራት የሚያስችሉትን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን እንዳከናወነ ይናገራሉ። አቶ አብርሃም በዚህ ረገድ ስለተከናወኑ ተግባራት ሲገልፁ “የባንኩ የውስጥ አሠራር የሚመራባቸውን መመሪያዎችን የማዘጋጀት፤ በብሔራዊ ባንክ መስፈርት መሠረት ውስጣዊ አደረጃጀቶችን የማሟላት፣ ከባንክ ዘርፉ ወቅታዊ እድገት ጋር የሚጣጣምና ባንኩን ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያስችል የኮር ባንኪንግ ሶፍትዌር ግዢ ለመፈፀምና ባንኩ የሚመራበትን የአምስት ዓመታት ስትራቴጂካዊ እቅድ ለማዘጋጀት ቅድመ ዝግጅት ተግባራትን የማጠናቀቅ፣ የሠራተኞችን አቅም በስልጠና የመገንባትና ተቋሙን በብቁ ሰው ኃይል የማጠናከር፣ በመጀመሪያ ዙር የተሟላ የባንክ አገልግሎት የሚሰጡ 10 ቅርንጫፎችን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የማዘጋጀት እንዲሁም በብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ሂሳብን ጨምሮ የመጠባበቂያና የክፍያ ሂሳቦችን የመክፈት ተግባራት ተከናውነዋል” ሲሉ ያብራራሉ።

    እንደ እርሳቸው ገለፃ፥ ባንኩ ባለፈው የበጀት ዓመት 142.3 ሚሊዮን ብር ዓመታዊ ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ 177 ሚሊዮን ብር በመሰብሰብ ከእቅድ የበላይ የሆነ አፈፃፀም አስመዝግቧል። ይህም ካለፈው ዓመት የባንኩ አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር የ58 በመቶ ብልጫ እንዲኖረው አድርጓል። 48 ሚሊዮን ብር ለማትረፍ አቅዶ 83 ሚሊዮን ብር በማትረፍ በባንኩ ታሪክ የተሻለ ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል። በጠቅላላው 165 ሚሊዮን ብር ተቀማጭ ገንዘብ በመሰብሰብም ከቀዳሚው ዓመት አፈፃፀም የ29 በመቶ እድገት አሳይቷል።

    በብድር አቅርቦት ረገድ ደግሞ ባንኩ የሰጠውን ብድር በ86.6 ሚሊዮን ብር (በ29 በመቶ) በማሳደግ ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሰጠውን ብድር 462.5 ሚሊዮን ብር ማድረስ ችሏል። “የባንኩ የተበላሽ ብድር ምጣኔ 3.6 በመቶ ሲሆን፣ ይህም ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው የአምስት በመቶ ምጣኔ አንፃር ሲታይ የሲዳማ ባንክ የተበላሸ የብድር ምጣኔ ጤናማ እንደሆነ አመላካች ነው” ይላሉ።

    የሲዳማ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ታደሰ ሐጢያ ባንኩ ማይክሮፋይናንስ ተቋም በነበረበት ጊዜ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የሕብረተሰብ ክፍሎች ሲያገለግል እንደነበር አስታውሰው፤ አገልግሎቱ አዋጭና ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ በብሔራዊ ባንክ ሕጋዊ ማዕቀፍ መሠረት ባንኩ ይህን አገልግሎቱን እንደሚቀጥልም ይናገራሉ። ባንኩ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አንዱ የባንክ አገልግሎትን በገጠርና በከተማ ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ መሆኑም ይህን አገልግሎቱን የማስቀጠል አካል ነው።

    እርሳቸው እንደሚሉት፥ ተቋሙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ አድርጓል። ቀደም ካለው ጊዜ ጀምሮ የባንኩን አገልግሎት የሚጠቀሙ በእርሻ፣ በሆቴልና በሌሎችም የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች አሉ። የተቋሙ በባንክ አሠራር መደራጀት ደግሞ ይህን አገልግሎት ለማስፋትና ለማዘመን ተጨማሪ ዕድልና አቅም ይፈጥራል።

    ተቋሙ ወደ ባንክ ሲሸጋገር ብሔራዊ ባንክ ያስቀመጠውን አነስተኛ መነሻ ካፒታል ለማሟላት የአክስዮን ሽያጭ ያከናወነ ሲሆን፣ የተፈረሙ አክሲዮኖች ተከፍለው እንዲጠናቀቁ በማድረግ ከመደበኛ የባንክ ሥራዎች በተጨማሪ ዓለም አቀፍ የባንክ ሥራዎችን ለማከናወን እየሠራ ይገኛል። “ወደ ባንክ ሥራ ስንገባ የጠንካራ የፋይናንስ አቅም ባለቤት መሆን ያስፈልጋል፤ አለበለዚያ አቅም ካላቸው ከሌሎች ባንኮች ጋር ለመወዳዳር አስቸጋሪ ይሆናል። ለትልልቅ የኢንቨስትመንት ሥራዎች ብድር ማቅረብም ሆነ በፋይናንስ ገበያው ላይ ተፎካካሪ መሆን አይቻልም” ይላሉ። ይህን ለማሳካትም የተፈረሙ አክሲዮኖች እንዲከፈሉና የኮርባንኪንግ (Core Banking) ሥራን ለመጀመር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ አቶ ታደሰ ያስረዳሉ።

    የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገበያ እንዲገቡ መፈቀዱ መልካም ዕድሎችና ፈተናዎች እንደሚኖሩት የሚገልጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፥ መልካም ዕድሎችን መጠቀም ከተቻለ ፈተናዎቹን መቀነስና ተወዳዳሪ መሆን እንደሚቻል ነው የተናገሩት። የባንኮቹ መግባት የሀገር ውስጥ ባንኮች ውድድሩን ለመቋቋም ራሳቸውን እንዲያጠናክሩ፣ በዚህም ተገልጋዩ ሕብረተሰብ ተጠቃሚ እንደሚሆን ይገልጻሉ። የኢትዮጵያ ባንኮች በካፒታል አቅምም ሆነ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ በሚጠበቅባቸውና ወቅቱ በሚፈልገው ልክ እየተንቀሳቀሱ አለመሆናቸውን ተናግረው፥ እነዚህን ክፍተቶች በማስተካከል ለውድድር መዘጋጀትና ለተገልጋዩ እርካታ መሥራት እንዳለባቸው ይመክራሉ። ከዚህ አንፃር ሲዳማ ባንክ ትልቅ አቅም ያላቸውን ባለሀብቶችን እንዲሁም ዳያስፖራውን ማሳተፍን ጨምሮ ያሉትን መልካም አጋጣሚዎች ሁሉ ተጠቅሞ በባንክ ኢንዱስትሪው ዘርፍ ተወዳዳሪ ለመሆን ማቀዱን አቶ ታደሰ ገልፀዋል።

    ሲዳማ ባንክ ለኢንቨስትመንት ዘርፍ የሚኖረውን አዎንታዊ አስተዋፅኦ በተመለከተም አቶ ታደሰ ሲናገሩ፥ “ገበያው አዋጭ በመሆኑ ባንኩ ለኢንቨስትመንት ሥራዎች የፋይናንስ ምንጭ የመሆን አቅም አለው። ቀደም ሲልም የባንኩን አገልግሎት የሚጠቀሙ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች አሉ። ወደፊትም ባንኩ ይህን ተግባሩን በስፋት አጠናክሮ ይቀጥላል” ብለዋል።

    ሲዳማ ባንክ በማይክሮፋይናንስ ደረጃ ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የሕብረተሰብ ክፍሎችን ሲያገለግልና ለግለሰቦች እንዲሁም በአነስተኛና ጥቃቅን የንግድና ኢንቨስትመንት ሥራዎች ላይ ለተሰማሩ ማኅበራት የፋይናንስ ምንጭ ሆኖ ቆይቷል። ብዙ ግለሰቦችና ማኅበራትም በተቋሙ የብድርና ቁጠባ አገልግሎት ሥራቸውን አሳድገው ዛሬ ትልልቅ ኢንቨስተሮች ለመሆን በቅተዋል።

    የሲዳማ ክልል የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝደንት አቶ መስፍን ቂጤሳ እንደሚናገሩት፣ ተቋሙ በግል ንግድ ላይ ለተሰማሩ በርካታ ግለሰቦችና ድርጅቶች ባለውለታ ነው። እርሳቸውም ከባንኩ ጋር ያላቸው ደንበኝነት የቆየ መሆኑን አስታውሰው፥ “ከባንኩ የወሰድነው ብድር በጣም ጠቅሞናል፤ ትርፋማ ሆነን እንድንሠራ አግዞናል” በማለት የባንኩ የብድር አገልግሎት ለውጤታማነታቸው አጋዥ እንደሆናቸው አስረድተዋል።

    “አካባቢው በቡና ምርት የታወቀ ስለሆነ ባንኩም ለቡናው ዘርፍ ትልቅ ድጋፍ እያደረገ ነው” የሚሉት አቶ መስፍን፤ ለቡና አብቃዮችና ነጋዴዎች እንዲሁም ለተደራጁ ማኅበራትም የፋይናንስ ዕድል እንደሚያመቻች ይገልፃሉ። በቀጣይም ከባንኩ ጋር ያላቸውን ደንበኝነት አጠናክረው፥ በይርጋለም የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተፈጠረውን መልካም ዕድል በመጠቀም ቡናን እሴት ጨምሮ ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል።

    “ከዚህ ቀደም የነበረው የባንኮች ተደራሽነት ውስን ስለነበር ብድር ለማግኘት ችግሮች ነበሩ። ሲዳማ ባንክ ለኢንቨስትመንት ሥራዎች ብድር በማቅረብ ጥሩ ዕድል ይፈጥራል፤ ለልማት በተለይ ለኢንቨስትመንት ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ የሚገኝ ባንክ ነው። ጥሩ ተስፋ ያለው ባንክም ነው” በማለት አቶ መስፍን ባንኩ ለኢንቨስትመንት ዘርፍ ስለሚኖረው አስተዋፅዖ ይናገራሉ።

    በግል የንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩት ወይዘሮ አየለች ዱካሞም የባንኩ ደንበኛ ናቸው። “ቀደም ሲል የሲዳማ ማይክሮ ፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ ነበርኩ” የሚሉት ወይዘሮ አየለች፥ ተቋሙ ባንክ ከሆነ በኋላ ከባንኩ ብድር መውሰዴ ሥራዬን ሰፋ አድርጌ እንድሠራ አግዞኛል። ብዙ ሰው ከሲዳማ ባንክ ብድር እየወሰደ እየሠራ ነው፤ እየተለወጠም ነው። ከባንክ ጋር መሥራት ጥቅሙ ብዙ ነው” ሲሉ ይገልጻሉ። ሲዳማ ባንክ በጥቃቅንና አነስተኛ የንግድ ሥራዎች ላይ ለተሰማሩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ትልቅ ድጋፍ ሲያደርግ እንደነበር አስታውሰው፤ ከባንኩ ብድር ወስደው ከአነስተኛ የንግድ ሥራ ተነስተው ለትልቅ ደረጃ የበቁ ሰዎችን እንደሚያውቁም ነው የጠቀሱት። ወደፊትም ከባንኩ ጋር ብዙ ሥራዎችን የመሥራት እቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

    ሲዳማ ባንክ Sidama Bank

    Semonegna
    Keymaster

    ከኢትዮጵያ ዳያስፖራ የተግባር ምክር ቤት የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

    ሀገራችን ኢትዮጵያ ተገዳ የገባችበትን የህልውና ጦርነት በጋራ ለመመከት በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊን ከሕዝባቸው ጎን በቆራጥነት በመቆም የሀገርን ሉአላዊነት ለማስከበር በሚደረገው ዘመቻ የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    ይህ የህልውና ጦርነት በውጭ ሀገር የምንገኘውን ኢትዮጵያውያን እንቅልፍ የነሳና ሀገራችን እንደ ሀገር እንዳትቀጥል በወያኔ ጁንታ ቡድን፣ በአልሸባብ፣ እና በሸኔ እንዲሁም በውጭ ሀገር የሚገኙ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በቅንጅት የከፈቱብን ጦርነት ብሔራዊ ክብራችንና የሚነካ የሀገራችንን ሰላም የሚያውክ በመሆኑ በእጅጉ አሳስቦናል።

    ስለዚህ መንግሥት በሆደ ሰፊነት ቀደም ሲል የወሰዳቸውን ቁርጠኛ የሰላም ፍላጎቶቹን በማድነቅ የሰላም ድርድሩ ውጤታማ እንዲሆን ሙሉ ድጋፍ ስንሰጥ መቆየታችን እንደተጠበቀ ሆኖ፤ በአሸባሪነት የተፈረጀቱ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ከሰላም ይልቅ ጦርነትንና እልቂትን መርጠው የከፈቱብንን የአጥፍቶ መጥፋት ጦርነትን በጥብቅ አውግዘን መንግሥት እየወሰደ ያለውን እርምጃ እንደግፋለን።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ የተግባር ምክር ቤት የአሸባሪውን ጁንታ ቡድን እንዲሁም አልሸባብና ሸኔን ማውገዝ ብቻ ሳይሆን ለሀገር ሕልውናና ለሕዝባችን ሰላምና ጥቅም ስንል ከመንግሥትና እንዲሁም ከመከለከያ ሠራዊታች ጎን በመቆም የዜግነት ድርሻችንን ለመወጣት የትግባር ምክር ቤቱ ዝግጁ መሆናችንን እናረጋግጣለን።

    በእርግጥ ዲያስፖራው ዛሬም ነገም ለሀገሩ ለወገኑ ድጋፉን አጠናክሮ እንደቀጠለ ቢሆንም በሀገራችን ውስጥ በተፈጠረው ሀገር የማዳን ዘመቻ በዘር፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ እምነት ሳንከፋፈል ከስሜታዊነትና ከኩሪፊያ በመውጣት ለነገዋ ኢትዮጵያ የተሻለ ነገር ለማምጣት፣ የተሻለችውን ኢትዮጵያ ለማየት ትግሉን የሚጠይቀውን ማንኛውንም ድጋፉ እንድናደርግ ምክር ቤታችን በድጋሚ በመላው ዓለም ለሚገኙ የኢትዮጵያዊያንና ለኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ ጥሪ ያቀርባል።

    መንግሥት ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ከፍታ ለማድረስ፣ ችግሮችን በውይይት በመፍታት፣ ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት፣ የሀገራችንን ፖለቲካ ለማዘመን፣ ውስጣዊ ችግሮቻችን በተገቢው መንገድ ለመፍታት ግጭቶችና የጦርነትን ውድመት እንዳይቀጥል በቁርጠኝነት ተነሳስቶ ለሀገረ መንግሥት ግንባታው መሠረት ለመጣል ፖለቲካዊ ችግሮችን በአግባቡ ፈትሾ ሁሉን አቀፍ ውይይትና ድርድር ማድረግ፤ በሀገሪቱ ምክር ቤት በአሸባሪነት የተፈረጁትን ቡድኖች ወደ ዘላቂ ሰላም የጠረንጴዛ ድርድር እንዲቀመጡ ወስዶት የነበረውን የሰላም ጥረት አሁንም ወደፊትም እንዲቀጥል ምክር ቤታችን መደገፉን ይቀጥላል።

    ነገር ግን ከጦርነት በተሻለ ሰላምን መምረጥ ትርፋማነቱ ቢያዋጣም አሸባሪውና ጎጠኛው የጁንታው ቡድን የአማራና አፋርን ሕዝብ በመውረር የትግራይን ሕዝብ አግተው በሰላማዊ ሕዝብና በመሠረተዊ የልማት ተቋማት ላይ ያደረሱትን መጠነ ሰፊ ውድመት መልሰን ለማቋቋም እርብርብ በምናደርግበት ወቅት የሀገርን ሉአላዊነት አደጋ ላይ ለመጣል ለሦስተኛ ዙር የተከፈተብን ታሪክ ይቅር የማይለው ጦርነት በእጅጉ አስቆጥቶናል። ስለዚህ፦

    1ኛ የአማራና የአፋር ክልልን በመውረር ሲዋጉና አመራር ሲሰጡ የነበሩትን እንዲሁም እድሚያቸው ለውትድርና ሞያ ያልደረሱ የትግራይ ህፃናትን በመመልመል ለጦርነት ያሰልፉትን የወያኔ ጁንታ አመራሮች ተለይተው በጦር ወንጀለኝነትና በሀገር ክህደት ክስ ተመሥርቶባቸው በአስቸኳይ ለፍርድ እንዲቀርቡ መንግሥትን እንጠይቃለን።

    2ኛ ሀገራችን በገጠማት የሰላም ማጣት ችግርና ተገዳ ከገባችበት የህልውና ጦርነት በተጨማሪ የሕዝብ ሞትና የሥነ ልቦና ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉ የሐሀት ቅስቀሳና የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ በሚያደርጉ ቅጥረኛ ሚዲያዎች፣ አለአግባብ ለመበልፀግ የኢኮኖሚ አሻጥር በሚፈፅሙ ነጋዴዎች፣ በተለይ የመንግሥት ሙሰኞችና ሌቦች ላይ ያለምንምንም ይቅርታ ጠንካራ እርምጃ መንግሥት እንዲወስድ እናሳስባለን።

    3ኛ መንግሥት የሚቻለው ሁሉ ጥረት በማድረግ ለሀገር ጠቀሜታ ሲል ዘላቂ መፍትሔ የሚያመጡ አካሄዶችና አዳዲስ ስልቶችን (strategies) መንደፍ አለበት። በተለይ ከዲያስፖራው ማኅበረሰብ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዞ በጋራ የዓለም አቀፉን ሕብረተሰብ በተሳሳተ ፕሮፖጋንዳ የሚያውኩትን የሚዲያ ተቋማትን ተጠያቂ ለማድረግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለድፕሎማቶቹን ጥብቅ መመሪያ እንዲሰጥና ለተግባራዊነቱም ልዩ ክትትል እንዲያደርግ በጥብቅ እናሳስባለን።

    በመጨረሻም ምክር ቤቱ ወደፊት ከሚያደርጋቸው የድጅታል ዲፕሎማሲ ትግል በተጨማሪ ጦርነቱን በአጭር ጊዜ ለመጨረስ በሚደረገው የህልውና ጦርነት የዘማቹ ሠራዊት ደጀን በመሆን ጠንካራ ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ መሆናችንን ለኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት እናረጋግጣለን።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ የተግባር ምክር ቤት (ኢዳተም)

    Anonymous
    Inactive

    ሲቢኢ ኑር (CBE Noor) ― የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሚሰጠው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ራሱን የቻለ ስያሜና አርማ ሥራ ላይ አዋለ

    አዲስ አበባ (CBE) – የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሚሰጠው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ‘ሲቢኢ ኑር’ (CBE Noor) የተሠኘ ስያሜና አርማ ሥራ ላይ ማዋሉን የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ግንቦት 28 ቀን 2012 ዓ.ም በተዘጋጀ የማስተዋወቂያ መርሀ-ግብር ላይ ይፋ አድርገዋል።

    ባንኩ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎትን በተጠናከረ መልኩ ለሕብረተሰቡ ለማዳረስ እየተገበረ ካለው መጠነ ሰፊ የማሻሻያ ተግባራት ጋር ተያይዞ አዲሱ ስያሜና አርማ ሥራ ላይ መዋሉን አቶ አቤ ሳኖ በመርሀ ግብሩ ላይ ተናግረዋል።

    አዲሱን ስያሜ እና አርማ በማዘጋጀት ሂደት በርካታ አማራጮች የቀረቡ መሆኑን አቶ አቤ አስታውሰው፥ ‘ኑር’ የሚለው አረብኛ ቃል ‘የብርሀን ፍንጣቂ’ የሚለውን ትርጓሜ የያዘ ሲሆን በአማርኛ መኖር የሚለውን መልካም ተስፋን የሚያመለክት በመሆኑ ለአገልግሎቱ ፈላጊዎች ተስፋን የሚሰጥ እንዲሁም ባንኩ ያለውን ራዕይ አመላካች ቃል ስለሆነ የባንኩ የሸሪዓ አማካሪዎችና የባንኩ ከፍተኛ የሥራ አመራር አስተያየት ሰጥተውበት ስያሜው መመረጡን ገልፀዋል።

    ባንኩ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎቱን ለማሻሻል የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑን የተናገሩት አቶ አቤ፥ በእምነታቸው ምክንያት ወለድ ለማይፈልጉ ደንበኞች አገልግሎቱን እንዲያገኙ በማድረግ ረገድ ባንኩ አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን አክለው ገልፀዋል።

    የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ እ.ኤ.አ. በ2011 ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መመሪያ ማውጣቱን ተከትሎ እ.ኤ.አ. ከህዳር 2013 ጀምሮ በተመረጡ 23 ቅርንጫፎች በተለየ መስኮት አገልግሎቱ መሰጠት መጀመሩን በንግግራቸው ያስታወሱት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት፥ በአሁኑ ጊዜ በ1574 በላይ ቅርንጫፎች በመስኮት ደረጃ እንዲሁም ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ብቻ ለመስጠት በተከፈቱ ከ53 በላይ ቅርንጫፎች አማካኝነት አገልግሎቱ በመሰጠት ላይ መሆኑን ገልፀዋል።

    ባንኩ የሸሪዓ መርህን የሚከተሉ የተለያዩ የባንክ አገልግሎቶችን ለሕብረተሰቡ በማድረስ ላይ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ አቤ እ.ኤ.አ. ግንቦት 2020 መጨረሻ ድረስ በወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ጠቅላላ የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑ 30.3 ቢሊዮን ብር መድረስ መቻሉን አመላክተዋል።

    አቶ አቤ በገለፃቸው፥ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎትን የሚጠቀሙ ደንበኞች ብዛትን 2.7 ሚሊዮን መድረሱንና ባንኩ በተለያዩ የሥራ መስኮች ለተሰማሩ ደንበኞች 3 ቢሊዮን ብር የፋይናንስ አገልግሎት ማቅረቡን አስረድተዋል።

    አቶ አቤ ባንኩ በማኅበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት፣ ዕውቅናና አመኔታን ያተረፉ፣ በዘርፉ በቂ የትምህርት ዝግጅት፣ ጥልቅ ዕውቀትና የካበተ ልምድ ያላቸው አምስት አባላት ያሉት የሸሪዓ መማክርት ኮሚቴ እ.ኤ.አ. ከ2019 ጀምሮ ሰይሟልም ነው ያሉት።

    የሸሪዓ አማካሪዎችን መሰየሙ ባንኩ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎቱን የሸሪዓ እሴትን በጠበቀ መልኩ ለመስጠት እንዳስቻለው የገለፁት አቶ አቤ የሸሪዓ መርህ መከበሩን የሚያረጋግጡ የውስጥ ቁጥጥር አሠራሮችን የመተግበር፣ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሂሳብ መዝገብ የመለየት እና መመሪያዎችን የማርቀቅ ተግባርም ማከናወኑን አክለው ገልፀዋል።

    አቶ አቤ በንግግራቸው መጨረሻ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለደንበኞቹ የተሻለ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የማቅረብ ትልቅ አላማ እንዳለው እና በቀጣይ የቁጠባ እና የፋይናንስ አማራጮቹን በማስፋት፣ አዳዲስ አሠራሮችን በመተግበር እና ይበልጥ ዘመናዊ በማድረግ የባንክ አገልግሎቱን ለሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል አመቺና ተስማሚ በሆነ መልኩ ለማቅረብን ያለውን ቁርጠኝነት ገልፀው፥ ደንበኞችና መላው ሕብረተሰብ የወቅቱ የጤና ስጋት ከሆነው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እራስንና ቤተሰብን በመጠበቅ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በሆነዉ ሲቢኢ ኑር (CBE Noor) ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሸሪዓ መርህን በመከተል በሚሰጠው ‘ሲቢኢ ኑር’ (CBE Noor) በተሰኘው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት፦

      • ከወለድ ነፃ የተቀማጭ ገንዘብ አገልግሎት
      • ለበይክ የተቀማጭ ገንዘብ አገልግሎት (ለሀጅ እና ኡምራ ተጓዦች)
      • ዘካ የተቀማጭ ገንዘብ አገልግሎት (ዘካ ለሚያወጡ)
      • የፋይናንስ አገልግሎት
      • የዓለም አቀፍ ንግድ ድጋፍ
      • የዳያስፖራ የቤት መግዣ/መሥሪያ ብድር እና
      • ሌሎችንም አገልግሎቶች

    ከ50 በላይ በሆኑ አገልግሎቱን ብቻ ለመሥጠት በተከፈቱ ቅርንጫፎች እና ከ1574 በላይ በሆኑ ቅርንጫፎች በተለየ መስኮት ይሰጣል፡፡

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    CBE Noor

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ለሀገር እና ለሕዝብ አርአያነት ያለው ታላቅ ተግባር ያከናወኑ ኢትዮጵያውያንን በየዓመቱ ዕውቅና የሚሰጠው የበጎ ሰው ሽልማት በ2012 ዓ.ም. ለሚያካሄደው ስምንተኛው መርሐ-ግብሩ የእጩዎችን ጥቆማ ከየካቲት 1 ቀን 2012 ዓ.ም. አንስቶ ከሕዝብ መቀበል እንደሚጀምር መርሐ-ግብሩን የሚያዘጋጀው የበጎ ሰው ሽልማት ድርጅት አስታውቋል።

    ለስምንተኛው የበጎ ሰው ሽልማት መርሐ-ግብር ከየካቲት 1 እስከ የካቲት 30 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ በአስር ዘርፎች እጩዎችን እንደሚቀበል ድርጅቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ያሳወቀ ሲሆን ዘርፎቹም፥ መምህርነት፣ ሳይንስ (ሕክምና፣ ቴክኖሎጂ፣ ፊዚክስ፣ ምህንድስና፣ ኬሚስትሪ፣ አርክቴክቸር፣ ወዘተ)፣ ኪነ ጥበብ/ሥነ-ጥበብ (በወግ ድርሰት)፣ በጎ አድራጎት (እርዳታና ሰብዓዊ አገልግሎት)፣ ቢዘነስና ሥራ ፈጠራ፣ መንግሥታዊ የሥራ ተቋማት ኃላፊነት፣ ቅርስና ባህል፣ ማኅበራዊ ጥናት፣ ሚዲያና ጋዜጠኝነት፣ እና ለኢትዮጵያ እድገት አስተዋጽዖ ያበረከቱ ዳያስፖራዎች ናቸው።

    ካለፈው ዓመት ሰባተኛው የበጎ ሰው ሽልማት አንስቶ በሽልማት ዘርፎች ውስጥ የተካተተው ለአገራችን እድገት አርአያነት ያለው አስተዋጽኦ ያበረከቱ ዳያስፖራዎች እውቅና የሚያገኙበትን ዘርፍ ጨምሮ እስካሁን ሥራ ላይ ባዋልናቸው ዘርፎች በሙሉ ጥቆማ ማድረግ ይቻላል።

    በተለይ የማኅበራዊ ጥናት ዘርፍ ባለፉት ሁለት ዓመታት በቂ እጩዎች ባለመጠቆማቸው ሽልማቱ ስላልተካሄደ፣ በዚህ የሙያ ዘርፍ ያሉ ደርዝ ያለው ሥራ የሠሩ ኢትዮጵያውያንን ለማክበርና አርአያነታቸውን ለማጉላት ሕዝቡ በተለይም ለሙያው ቅርብ የሆኑ ሁሉ ጥቆማቸውን እንዲያቀርቡ ድርጅቱ ጠቁሟል። እንዲሁም በኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበባት ዘርፍ በዘንድሮው መርሐ-ግብር ከሥነ-ጽሑፍ መስኮች አንዱ በሆነው የወግ ድርሰት ላይ ትኩረት ይደረጋል። የወግ ድርሰት ኢ-ልቦለዳዊ በሆነ የሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የሚመደብ፣ ጥበባዊ በሆነ የአጻጻፍ ብቃት የሚቀርብ ሲሆን፥ በርካታ አንጋፋና ወጣት ደራሲያን የድርሰት በረከታቸውን አቅርበውበታል። ስለዚህ የዘርፉን ጥበባዊነት ለማጉላትና ደረሲያኑንም ለማበረታታት የዘንድሮው የበጎ ሰው ሽልማት የኪነ-ጥበባት ዘርፍ የሙያ መስክ ተደርጎ ተመርጧል።

    ባለፉት ሰባት የሽልማት ወቅቶች፤ አገራችን የምትኮራባቸውና የላቀ አርአያነት ያለው ተግባር ያከናወኑ ሰዎችን እውቅና የተሰጣቸው ከሕዝብ በቀረቡ ጥቆማዎች መሰረት ነው። የበጎ ሰው ሽልማትን ለዚህ ያበቃውም በሽልማቱ ሂደት በውጭ ሀገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የሕዝብ ተሳትፎ በመኖሩና ይህም ከዓመት ዓመት እያደገ በመሄዱ ስለሆነ ይህ ተሳትፎ አሁንም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ድርጅቱ ጠይቋል። ጠቋሚዎች እጩዎችን በሚጠቁሙበት ጊዜ እጩው ግለሰብ ለአገርና ለሕዝብ ያከናወኑትን ተግባር በዝርዝር እንዲገልጹልንና የሚገኙበትንም አድራሻ መጠቆም እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

    ስለዚህ ይህን የበጎ ሰው ሽልማት ዓላማን ከግምት ውስጥ በማስገባት ከላይ በተገለጹት መስኮች ለጥቆማ በተመደበው የአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያውያን ለዚህ ሽልማት ብቁ ናቸው የሚላቸውን እጩዎች እንዲጠቁሙ ጥሪ ተደርጎላቸዋል። ጥቆማ የምንቀበለው በስልክ፣ በቫይበር (Viber)፣ በቴሌግራም (Telegram)፣ በኋትስአፕ (WhatsApp)፣ በኢ-ሜይል (email) እና በፖስታ ነው። አድራሻዎቹም፦

    ስልክ፦ 0977-23-23-23 (ቫይበር፣ ቴሌግራምና ኋትስአፕን ጨምሮ)
    ኢሜይል፦ begosewprize@gmail.com
    ፖስታ፦ 150035፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ናቸው።

    የበጎ ሰው ሽልማት ዓላማ ለሀገራችን ለኢትዮጵያ መልካም የሚሠሩ፣ ሀገራዊ ተልዕኳቸውን በብቃትና በልዩ ልዕልና የሚወጡ፣ የሕዝቡን ኑሮ ለማሻሻል ለውጥ አምጪ ተግባር የፈጸሙ፤ በብዙ ሰዎች የማይደፈረውን ተግባር በተነሣሽነት የከወኑ፣ ለድጋፍ ፈላጊ የማኅበረሰብ ክፍሎች ትኩረት በመስጠት ሀገራዊ ኃላፊነት ወስደው የሠሩ፣ የሀገሪቱ ታሪክ፣ ቅርስ፣ ባሕል፣ እንዲጠበቅ፣ የሀገሪቱ ሥልጣኔ ከፍ እንዲል የሠሩ ኢትዮጵያውያንን በማበረታታት፣ ዕውቅና በመስጠትና በመሸለም ሌሎችን በጎ ሠሪዎች ለሀገራችን ማፍራት ነው።

    ከሕዝብ የሚቀርበው ጥቆማ ከተጠናቀቀ በኋላ አስፈላጊው ማጣራት ተደርጎ፣ ለመጨረሻው ውድድር ተመርጠው ስማቸው ለዳኞች የሚላከውን እጩዎች ማንነት፣ ሕዝብ እንዲያውቀው ለማድረግ፤ አውቆም ለሀገርና ለሕዝብ ባበረከቱት አስተዋጽዖ እንዲያከብራቸው ዝርዝራቸውን በመገናኛ ብዙኃን አማካይነት ይፋ ይደረጋል።

    የመጨረሻውን የየዘርፎቹን የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚ ምርጫ የሚያደርጉት ለእያንዳንዱ የሽልማት ዘርፍ በዳኝነት የተመረጡ ባለሙያዎች ናቸው። ዳኞቹ በእውቀታቸውና በሙያቸው አንቱ የተባሉ፣ የረጅም ጊዜ ልምድ ያላቸውና በታማኝነት ምርጫውን ያከናውናሉ ተብለው የታመነባቸው ናቸው። ለእያንዳንዱ ዘርፍም አምስት ዳኞች ተመርጠው ምርጫውን ያከናውናሉ።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የበጎ ሰው ሽልማት

    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያቀረበውን ይህን ከወለድ ነፃ የዳያስፖራ የቤት መግዣ የፋይናንስ አገልግሎት በውጭ የሚኖሩ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ሌሎች በዚህ አገልግሎት መጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ ሊጠቀሙበት ይችላሉ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ኢትዮጵያ ውስጥ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለማድረግ የሚያስችል ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ይፋ አደረገ። አገልግሎቱ ሙስሊሙን ህብረተሰብ ጨምሮ ሌሎች የወለድ አገልግሎትን የማይፈልጉ ዳያስፖራዎችም እንዲጠቀሙበት የተዘጋጀ ነው።

    የባንኩ የጥራት ቁጥጥር ምክትል ፕሬዚዳንት ወይዘሮ እመቤት መለሰ አዲሱን ከወለድ ነፃ የዳያስፖራ ፋይናንስ አገልግሎት አስመልክተው በሰጡት አስተያየት “ለመኖሪያ ቤት መግዣ የሚውለው ከወለድ ነፃ የዳያስፖራ ፋይናንስ አገልግሎት ከዚህ ቀደም ከቀረቡትና ዳያስፖራውን ከሚመለከቱ የባንክ አገልግሎቶች በተለየ መንገድ ይተገበራል” ብለዋል።

    ዳያስፖራው ወዲዓ’ህ የቁጠባ ሒሳብን በመጠቀም ቢያንስ 20 በመቶ የሚሆነውን ገንዘብ በእንግሊዝ ፓውንድ፣ በአሜሪካን ዶላርና በዩሮ መቆጠብ ከቻለ፣ የፋይናንስ ጥያቄውን ለባንኩ በማቅረብ መስተናገድ እንደሚችል ወይዘሮ እመቤት ተናግረዋል።

    ግንባታው የተጠናቀቀና ጅምር ቤት ለመግዛት የሚውለው የፋይናንስ አገልግሎት በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የመኖሪያ ቤት ችግር እንቅፋት እንዳይሆንባቸው ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ታስቦ ለዳያስፖራው የተዘጋጀ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎት ነው። የፋይናንስ አገልግሎቱን መስፈርቶች ማሟላት የሚችሉ ዳያስፖራዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ወይም በሚኖሩበት አገር በሚገኝ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ቀርበው የወዲዓ’ህ ቁጠባ ሒሳብ በመክፈት መቆጠብ የሚችሉ ሲሆን፣ ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ቅድመ ክፍያ በአንድ ጊዜ ወይም በተለያዩ ጊዜያት በመቆጠብ መክፈል ይችላሉ። ለቤት መግዣ የሚውለውን ፋይናንስ እስከ 20 ዓመት በሚደርስ የቆይታ ጊዜ ከፍለው መጨረስ እንዲችሉም ተመቻችቷል።

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያቀረበውን ይህን ከወለድ ነፃ የዳያስፖራ የቤት መግዣ የፋይናንስ አገልግሎት በውጭ የሚኖሩ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ሌሎች በዚህ አገልግሎት መጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ እንዲጠቀሙበት ወይዘሮ እመቤት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ከወለድ ነፃ


    Semonegna
    Keymaster

    ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ዳያስፖራዎች ልዑካን ቡድን አባላት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን በሙያቸው እንዲያግዙ ጥሪ ማቅረባቸውን ተክተሎ የመጡ ናቸው።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– በኢትዮጵያ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሲካሄድ የቆየው መንግስት ቴክኖሎጂ ለመጠቀም ያለውን ዝግጁነት የሚለይና ለችግሮች የመፍትሄ አቅጣጫ የሚያስቀምጥ አውደ-ጥናት ተጠናቀቀ።

    በአውደ ጥናቱ የመንግስት አግልግሎት አሰጣጥ፣ ቴክኖሎጂ ለመጠቀም ያለው ዝግጁነት፣ የፋይናንስ አስተዳደር ስርዓት ክፍተት ተለይተውበታል – ሚኒስቴሩ እንደዘገበው።

    የጤና አስተዳደር፣ የታክስ አሰባሰብ ስርዓት፣ የመረጃ ግንኙነት (ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን) ቴክኖሎጂ ደኅንነት፣ በባንክ አገልግሎት፣ በኢንሹራንስ አገልግሎት፣ ትምህርት ሚኒስቴር፣ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ በኦዲት አገልግሎት፣ የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት፣ የውሃ አወጋገድ ላይ ክፍተቶች ተለይተዋል።

    አሜሪካ ውስጥ ቨርጂንያ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ (Virginia International University; Fairfax, VA) መምህር በሆኑት ዶ/ር ተፈራ በየነ የተመራው ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ልዑክ ክፍተቶቹን ከለዩ በኋላ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።

    ከ7ሺህ 800 በላይ አዳዲስ አነስተኛና መካከለኛ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች በመላው አገሪቱ ሊቋቋሙ ነው

    ባለሙያዎቹ በኢንሹራንስ፣ በህክምና ቴክኖሎጂ፣ በዲፕሎማሲ፣ በኢንፎርሜሽን ኮሙኑኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ በአሜሪካን ሀገር በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች ከፍተኛ ልምድ ያካበቱ ኢትዮጵያዊያን ናቸው።

    ሚኒስትሮች፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የፋይናንስ ዳይሬክተሮች እና ሌሎችም ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው አካላት ከቡድኑ ጋር ለ1 ሳምንት ክፍተቶችን እና ጉድለቶችን የመለየት ሥራ ሲሠሩ ቆይተዋል።

    የሚመለከታቸው አካላት በየዘርፉ የሚደረጉ ማስተካከያዎችን በኃላፊነት ወስደው ወደ ተግባር የመቀየር ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል። በማጠቃለያው ላይ፥ ልዑካኑ የኢትዮጵያ መንግስት ወይም የሚመለከተው መንግስታዊ ተቋም ዕድሉን ከሰጠን የሀገራችንን ችግር ለመፍታት በቂ አቅም አለን ብለዋል። ወደፊትም በማንኛውም መልኩ ሀገራቸውን ለማገዝ ቃል ገብተዋል።

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታዎች ሹመቴ ግዛው (ዶ/ር) እና ጀማል በከር ልዑካኑ ሀገራቸውን ለመረዳት ያላቸውን ቁርጠኝነት በማድነቅ ምስጋና አቅርበዋል።

    የልዑካን ቡድኑ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን በሙያቸው እንዲያግዙ ጥሪ ማቅረባቸውን ተክተሎ የመጡ ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ትውልደ ኢትዮጵያዊያን


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ የተከፈተው ቆንስላ ጽ/ቤት ቆንሱል ጄኔራል አምባሳደር እውነቱ ብላታ ቆንስላ የጽ/ቤቱ መከፈት በሚኒሶታ ግዛት ለሚኖሩ በሺዎች ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ዳያስፖራ አባላት ምቹ ሁኔታና መነቃቃትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

    ዋሽንግተን፥ ዲሲ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዴሪ) መንግስት በሀገረ አሜሪካ በሎስ አንጀለስ ከተማ (ካሊፎርንያ ግዛት) ከሚገኘው ቆንጽላ ጽ/ቤት ቀጥሎ ሁለተኛውን ቆንጽላ ጽ/ቤት በሴይንት ፓል ከተማ (ሚኖሶታ ግዛት) ከፍቷል።

    ቆንስላ ጄኔራል ጽ/ቤቱ የተከፈተው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ባሳለፍነው ዓመት ነሃሴ ወር ላይ በአሜሪካ ባደረጉት ጉብኝት በገቡት ቃል መሠረት ነው።

    በመክፈቻ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የኦሮሚያ ክልል መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ብርቱካን አያኖ፣ የሴይንት ፓል ከተማ ከንቲባ ሚስተር ሜልቪን ካርተር፣ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም በርካታ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የዳያስፖራ አባላት ተገኝተዋል።

    ክቡር አቶ ለማ መገርሳ እንደገለጹት የቆንስላ ጽ/ቤቱ መከፈት ለአካባቢው ብሎም በመላው አሜሪካ የሚኖረውን ዳያስፖራ ለማገልግል የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል። ዳያስፖራው በኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው የኢኮኖሚና ፖለቲካ ለውጥ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ፣ ለዚህም የኢትዮጵያ መንግስት ከምንጊዜውንም በላይ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።

    አዲስ የተከፈተው ቆንስላ ጽ/ቤት ቆንሱል ጄኔራል አምባሳደር እውነቱ ብላታ በበኩላቸው የጽ/ቤቱ መከፈት በሚኒሶታ ግዛት ለሚኖሩ በሺዎች ለሚቆጠሩ የዳያስፖራ አባላት ምቹ ሁኔታና መነቃቃትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

    የሴይንት ፖል ከተማ ከንቲባ ሚስተር ማልቪን ካርተር በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር ከቆንስላ ጄኔራል ጽ/ቤቱ ጋር ተቀራርቦ ለመሥራትና አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። የካቲት 23 ቀን 2011 ዓ.ም. (ማርች 2 ቀን 2019) በከተማ ደረጃ “የኢትዮጵያ ቀን” ተብሎ እንዲከበር መወሰኑንም ጠቁመዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤምባሲ፤ ዋሽንግተን፥ ዲሲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ቆንስላ ጽ/ቤት


    Semonegna
    Keymaster

    ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ከየካቲት 10 ቀን 2003 (እ.ኤ.አ.) ጀምሮ የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶችንና አባል ለመሆን ብቁ የሚያድርጓትን የማሻሻያ እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የሚያስችላትን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየሠራች መሆኑን ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ።

    በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የባለ ብዙ ዘርፍ የንግድ ግንኙነትና ድርድር ዳይሬክተር አቶ ሙሴ ምንዳዬ የዓለም ባንክ የንግድና ክልላዊ ትብብር ዳይሬክተር ጋር ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደትን እና የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጠና ስምምነትን ለማጽደቅ እያደረገች ባለው እንቅስቃሴ ዙሪያ በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በተወያዩበት ወቅት ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እና በድርድሩ ሂደት የሚገጥሟትን ችግሮች ተቋቁማ ወደ ድርጅቱ እንድትቀላቀል ለማድረግ በርካታ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

    ምንም እንኳን ኢትዮጵያ በተከታታይ የኢኮኖሚ እድገት ብታስመዘግብም የግል ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስት ያለው ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ ነው

    አቶ ሙሴ አያይዘው በአሁኑ ወቅት መንግስት በተለይም በአገልግሎት ንግድ ሰጭ ተቋማት ላይ እየሠራቸው ያሉት የማሻሻል (ሪፎርም) ሥራዎች እና የቴሌኮም ድርጅትን የቁጥጥር/ርጉላቶሬ/ መስሪያ ቤት የተለያዩ ዘርፎች ለግሉ ሴክተር ለማስተላለፍ በሚኒስትሮች ምክር ቤት መጽደቁ ሀገሪቷ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የምታደርገውን ድርድር ሊያግዝ የሚችል መልካም አጋጣሚ ነው ያሉ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም. 4ኛውን የሥራ ቡድን ስብሰባ ለማካሄድ የተለያዩ ዶክመንቶችን የማዘጋጀት ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ተናግረዋል።

    በዓለም ባንክ የማክሮ፣ ንግድና ኢንቨስትመንት ዳይሬክተር ወ/ሮ ካሮሊን ፍረንድ (Caroline Freund) በበኩላቸው ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በዓለም የንግድ ድርጅት ድርድር እና በአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣና ዙሪያ የሚሠራቸው ሥራዎች መልካም መሆናቸውን ገልጸው ወደፊት ለሚደረጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድርኮች እንዲሁም ዘመናዊና ደረጃውን የጠበቀ ቢሮና መሠረተ- ልማት እንዲኖር ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል።

    እ.ኤ.አ. ጥር 1 ቀን 1995 በ124 አገራት የአባልነት ፊርማ የተመሠረተውን የዓለም ንግድ ድርጅት (World Trade Organization)፣ በአሁኑ ሰዓት ዋና መቀመጫውን ጄኔቭ ከተማ፣ ስዊዘርላን አድርጎ 164 አገራትንም በአባልነት አቅፏል።ኢትዮጵያም የዚህ ድርጅት አባል ለመሆን ከየካቲት 10 ቀን 2003 (እ.ኤ.አ.) ጀምሮ የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶችንና አባል ለመሆን ብቁ የሚያድርጓትን የማሻሻያ እርምጃዎችን ስትወስድ ቆይታለች።

    ምንጭ፦ በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የዓለም ንግድ ድርጅት


    Semonegna
    Keymaster

    መቀዛቀዝ የታየበትን የህዝባዊ ተሣትፎ ለማነቃቃት የተለያዩ መድረኮችን በቀጣይነት እንደሚያዘጋጅ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሣትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ አብርሃም ገልጸዋል።

    አዲስ አበባ (ዋልታ)– የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሣትፎ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ባለፉት 6 ወራት 484 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡን አስታውቋል።

    ጽህፈት ቤቱ በበጀት ዓመቱ እስከ አንድ ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ እየሠራ ሲሆን በቀጣይ የተጠናከረ አፈጻጸም ለማስመዝገብ እንደሚንቀሳቀስ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማኅበር እና የህዳሴው ግድብ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ባዘጋጁት ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጿል።

    መቀዛቀዝ የታየበትን የህዝባዊ ተሣትፎ ለማነቃቃት የተለያዩ መድረኮችን በቀጣይነት እንደሚያዘጋጅ የህዳሴው ግድብ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ አብርሃም ገልጸዋል።

    ቪዲዮ፦ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የግንባታ ድጋፍ ዙሪያ ከኢትዮጵያውያን የዳያስፖራ አባላት ጋር የተደረገው ውይይት

    ከዚሁ ጋር በተያያዘም ጥር 22 ቀን 2011 ዓ.ም. ከንቅናቄ መድረኮች አንዱ የሆነው ሁሉም የዳያስፖራ አካላት የሚገኙበት መድረክ በራስ ሆቴል መድረክ አዘጋጅቶ ከተለያዩ ሀገራት ከመጡ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት ጋር በቀጣይነት እና በተሻለ ሁኔታ ግድቡን ሊደግፉ በሚችሉበት መንገድ ላይ ውይይት አድርጓል።

    ዳያስፖራው ባለፉት ሰባት ዓመታት 46 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ማድረጉ የተገለጸ ሲሆን ሃገሪቱ ካላት ዲያስፖራ ቁጥር አንጻር ድጋፉ አነስተኛ መሆኑ ተጠቁሟል። በመሆኑም በተለይም በምዕራብ አውሮፓ የሚገኙ ዲያስፖራዎች የሚጠበቅባቸውን ያህል ድጋፍ ስላላደረጉ ትኩረት አድርጎ እንደሚሠራ የዳያስፖራ ማኅበሩ ዋና ዳይሬክተር አቶ አብርሃም ስዩም አስታውቋል።

    ለዚህም ዳያስፖራው ለህዳሴው ግድብ አዲስ የዳያስፖራ ተሳትፎ ንቅናቄ ለመፍጠር እና በዳያስፖራው ዘንድ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ ያለውን ብዥታ ለማጥራት መድረክ ፈጥሮ ውይይት ማድረግ አስፈላጊ እንደነበርና፣ የራስ ሆቴሉ ውይይትም የዚሁ ዋነኛ አካል እንደነበር ተገልጿል። በተመሳሳይ ሁኔታም በዕለቱ የተለያዩ የህዝብ አደረጃጀቶች የሚሳተፉበት የንቅናቄ መድረክ በካፒታል ሆቴል ተካሂዶ ነበር።

    ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከሁለት ዓመት በኋላ ኃይል ማመንጨት እንደሚጀምር የተገለጸ ሲሆን ከአራት ዓመት በኋላ ተገንብቶ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።

    ምንጭ፦ ዋልታ ሚዲያ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦  

    ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ


    Semonegna
    Keymaster

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ጥር 6 ቀን ለኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች በሰጡት ገለጻ አስካሁን ባለው ሂደት ኢትዮጵያዊያን ዳያስፖራዎች በቀረበላቸው ሀገራዊ ጥሪ አማካኝነት በዳያስፖራ ትረስት ፈንድ በኩል 1 ነጥበ 9 ሚሊዮን ዶላር አዋጥተዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በዳያስፖራ ትረስት ፈንድ አንድ ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር መሰብሰቡን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ጥር 6 ቀን 2011 ዓ.ም. አስታወቁ። እስካሁን ባለው ሂደት በትረስት ፈንዱ አማካኝነት 12 ሺህ 9 መቶ ዳያስፖራዎች መዋጮ አድርገዋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው የ2011 ዓ.ም. አገራዊ በጀትን በአስጸደቁበት ወቅት ኢትዮጵያዊ ዳያስፖራ ሁሉ በአገሩ ልማት ላይ እንዲሳተፍ በቀን የ1 ዶላር መዋጮ መጠየቃቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ዳያስፖራው ለጠቅላይ ሚነስትሩ የሰጠው ምላሽ አጥጋቢ እንዳልሆነ ሲነገር ቆይቷል።

    Commercial Bank of Ethiopia to start diaspora mortgage loan to ease Ethiopians’ home ownership

    ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ጥር 6 ቀን ለኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች በሰጡት ገለጻ አስካሁን ባለው ሂደት ዳያስፖራው በቀረበለት ፈንድ አማካኝነት 1 ነጥበ 9 ሚሊዮን ዶላር አዋጥቷል።

    በመዋጮውም 12 ሺህ 900 ዳያስፖራዎች እንደተሳተፉ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ከዚህም ውስጥ 10 ሺህ 300 የሚሆኑት በአሜሪካ የሚኖሩ ናቸው። 1ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶላሩ ከእነዚህ በአሜሪካ ከሚኖሩ ዳያስፖራዎች መሰብሰቡን አክለዋል።

    በአሜሪካ ካሉ ግዛቶች መካከል ሜሪላንድና ካሊፎርኒያ እንደቅደም ተከተል ከፍተኛ መዋጮ የተገኘባቸው አካባቢዎች መሆናቸውንም ገልጸዋል።

    በዓለም ላይ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዳያስፖራዎች ቢኖሩም መዋጮው እምብዛም ያልሆነበት ምክንያት መተማመኑ ባለመፈጠሩ መሆኑንም ጠቅላይ ሚንስትሩ አስገንዝበዋል።

    The case of Ethiopian diaspora, their interest to invest in Ethiopia and bureaucratic bottlenecks

    የሚዋጣውን ነገር በሚታይ ነገር ላይ በማዋል መተማመንን ለመፍጠር እንደሚሠራ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በፈንዱ የተሰበሰበው ገንዘብ ግን 10 ሚሊዮን ዶላር አስኪደርስ ጥቅም ላይ እንደማይውል ገልጸዋል።

    ይህ የሚሆነውም በክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች መካካል ፍትሃዊ ክፍፍልን ለመፍጠር መሆኑንም ጠቁመዋል።

    የኢትዮጵያውያን ዳያስፖራ ትርስት ፈንድ የተቋቋመው በነሀሴ ወር 2011 ዓ.ም. በጠቅላይ ሚኒስትሩ ዋና ሰብሳቢነት ሲሆን፥ በዋነኝነት በተለያዩ የአርሜሪካ ግዛቶች የሚኖሩ 15 ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በአማካሪ ካንስል አባልነት ያቀፈ ቡድን በበላይነት ይከታተለዋል።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ ድረ-ገጽ: EDTF

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ዳያስፖራ ትርስት ፈንድ


    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ በቅርቡ ሥራውን በይፋ የሚጀምርበት በዳያስፖራው ማህበረሰብ እና በባለድርሻ አካላት ዘንድ ተልዕኮው በግልፅ ታዉቆ በጋራ እና በቅንጅት ሥራው እንደሚሰራ መገለጹን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመልክታል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የኢትዮጵያውያንን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን አገራዊ ተሳትፎ ለማረጋገጥና መብታቸውን ለማስከበር በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስር የተቋቋመው የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ሥራ ለመጀመር የመዋቅርና የሕግ ማዕቀፍ ሥራን ማጠናቀቁን አስታወቀ።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት እና ምክትል ዳይሬክተር አቶ መሐመድ እንድሪስ ታህሳስ 26 ቀን 2011 ዓ.ም. ለአገር ውስጥ እና ለዉጭ አገር መገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ የመዋቅርና የሕግ ማዕቀፍ ሥራን ማጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡ የኤጀንሲው ወደ ሥራ መግባት ዳያስፖራው በአገሩ ጉዳይ ብርቱ ተዋናይ እንደሚያደርገው ተናግረዋል።

    በዉጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን መብትና ጥቅሞችን ለማስጠበቅ የዳያስፖራ ምዝገባ እና መረጃ አያያዝ ስርዓት መዘርጋት፣ ዳያስፖራው በዕውቀትና በተክኖሎጂ ሽግግር አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ማስቻል እንዲሁም በኢንቨስትመንት፣ በንግድና በቱሪዝም ተሳትፎውን ማጎልበት የኤጀንሲው ዋና ዓላማዎች መሆናቸውን አስረድተዋል።

    ተጨማሪ፦ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ እና ለመሥርት ያላቸው ፍላጎትና የሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶች (ቪዲዮ)

    ኤጀንሲው በቅርቡ ሥራውን በይፋ የሚጀምርበት በዳያስፖራው ማህበረሰብ እና በባለድርሻ አካላት ዘንድ ተልዕኮው በግልፅ ታዉቆ በጋራ እና በቅንጅት ሥራው እንደሚሰራ መገለጹን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመልክታል።

    የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይህን ኤጀንሲ ለማቋቋም የወሰነው በጳጉሜን ወር 2010 ዓ.ም. ሲሆን፥ በዚያን ጊዜ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አቶ መለስ ዓለም በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በትውልድ ሀገራቸው እድገት ላይ የራሳቸውን አስተዋጽዖ ለማድረግ ከምን ጊዜውም በበለጠ እንደተነሳሱ ገልጸው ነበር።

    በተለያዩ የውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ከሦስት እስከ አምስት ሚሊዮን እንደሚገመትና ከእነዚህም ውስጥ አብዛኛዎቹ በሰሜን አሜሪካ እና አውሮፓ እንደሚኖሩ ዘገባዎች ያመለክታሉ። እ.ኤ.አ ከ2009 በፊት ኢትዮጵያ ከእነዚህ የዳያስፖራ አባላት የምታገኘው ገቢ (remittance) ከ400 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በታች እንደነበረና ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን ይህ አሀዝ እየጨመረ መምጣቱ ተጠቁሟል።

    በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች ወደ ትውልድ ሀገራቸው የሚልኩት የገንዘብ መጠን ከአራት ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ እንደሆነና ይህም ሀገሪቱ ከወጪ ንግድ (ኤክስፖርት) ከምታገኘው ገቢ ጋር ሲነጻጸር በአንድ ቢሊዮን ዶላር አካባቢ ብልጫ አለው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አባባ – የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ ጥቅምት 12 ቀን 2011 ዓ.ም በይፋ ገንዘብ መሰብሰብ መጀመሩን የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከሁለት ወር በፊት ለኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበረሰብ የትረስት ፈንዱ እንዲቋቋም ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበው እንደነበረ ይታወሳል።

    በይፋ የተቋቋመው ትረስት ፈንድ ጥቅምት 12 ቀን ገንዘብ መሰብሰብ መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገልጸዋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ አማካሪ ምክር ቤት ተቋቁሞ በይፋ ሥራ እንዲጀምር ላደረጉት ትጋትና ጥረት አባላቱን በኢትዮጵያ ሕዝብ ስም አመስግነዋል።

    በአሁኑ ወቅት በትረስት ፈንዱ ገንዘብ የማሰባሰብ ሥራ የመጀመሪያ ደረጃ ላይ እንዳለና ከዚህም በኋላ ብዙ ሥራ መሥራት እንደሚገባ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት።

    ———————————————-

    ———————————————-

    የትረስት ፈንድ አማካሪ ምክር ቤቱ የፈንዱን አቅምና ውጤታማነት ለማሻሻል በትጋት መሥራት እንዳለበትም ዶክተር አብይ ተናግረዋል።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበረሰብ የሚሰጡትን የተወሰነ ገንዝብ በአንድ ወይም በሁለት ጊዜ ጠቅልለው በመክፈል በጣም ወሳኝ ለሚባሉ ፕሮጀክቶች የሚያስፈልገውን ድጋፍ እንዲያፋጥኑም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠይቀዋል።

    በቀን ከአንድ ዶላር በላይ መስጠት ለሚችሉ ዜጎች ድጋፋቸውን በፍጥነት እንዲያድርጉና ዓለም አቀፉ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማኅበረሰብ ከትረስት ፈንድ ምክር ቤቱ ጋር ትብብራቸውን እንዲያደርጉ ዶክተር አብይ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

    የኢትዮጵያ የዳያስፖራ ትረስት ፈንድ የዳይሬክተሮች ቦርድ የተመረጡ ሲሆን ስም ዝርዝራቸው በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግም መጠቆማቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የላከው መግለጫ ያስረዳል።

    ፈንዱ የዳያስፖራውን ተሳትፎ ለማቀናጀትና የልገሳውን ገንዘብ ለማሰባሰብ የሚያስችል እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን የባንክ ሒሳብ ቁጥሩም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000255726725 (አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ) ነው። ከዚህ የባንክ የሒሳብ ቁጥር በተጨማሪ ተቋሙ በኢንተርኔትም ገንዘብ እንደሚያሰባስብና ኦፊሴላዊ ድረ ገጹም “https://www.ethiopiatrustfund.org” እንደሆነ ክስር በተመለከተው ጋዜጣዊ መግለጫ አሳውቋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በተለያዩ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን እንዲወጡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው ባደረጉት ንግግር ጥሪ ማቅረባቸው ይታወቃል።

    በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በቀን ቢያንስ 1 የአሜሪካ ዶላር በመለገስ ለተለያዩ የልማት ሥራዎች ድጋፍ እንዲያደርጉ መጠየቃቸው የሚታወስ ነው።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ ተቋም ምክር ሰጪ ካውንስል መግለጫ (ጥቅምት 10 ቀን 2011 ዓ.ም)

    የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ዳያስፖራ ፈንድ ተቋም ሰኞ ጥቅምት 12 ቀን 2011 ዓ.ም (October 22, 2018) ለሕዝብ መዋጮ መሰብሰቢያ ይከፈታል።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ፈንድ ተቋም ምክር ሰጪ ካውንስል (ኢዲቲኤፍ) ሰኞ ጥቅምት 12 ቀን 2011 ዓ.ም (October 22, 2018) ለሕዝብ መዋጮ መሰብሰቢያ ያዘጋጀዉን ዝግጅት ለሕዝብ ይፋ አድርጎ ሥራዉን በኦፊሴላዊ ድረ-ገጽ https://www.ethiopiatrustfund.org እንደሚጀምር በደስታ ያስታዉቃል።

    ባለፉት ሳምንታት ካውንስሉ የዲያስፖራ ፈንዱን ሕጋዊና መንግስታዊ ደንቦችን በተከተለ መንገድ ፈንዱን ለመመስረት በትጋት ሠርቷል።

    የፈንዱ ካውንስል ምክር ቤት በዓለም ያሉ ዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን ክቡር ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ በቀን 1 ዶላር ለህዝብ አርዳታ አዋጡ ያሉትን ጥሪ ተመልከቶ መዋጮ ለመስጠትና ፈንዱን በስራ ላይ ለማዋል ከፍ ያለ ጉጉት አንዳላቸው ይገነዘባል።

    ይህን ፍላጎት ለሟሟላትና ፈንዱን በሥነ ስርዓት ሥራ ማስጀመር ምክር ቤቱ ለትርፍ ያልተቋቋመ የበጎ አድራጎት ድርጅት ማቋቋም የባንክ ሂሳብ ቁጥር መክፈት ከኢንተርኔት ክፍያ ስርዓቶች እና ሌሎች የፋይናንስ መድረኮችን ጋር መደራደር አና የተለያዩ ደንቦችን ሟላትና አስተዳደራዊ እና የአፈፃፀም ሂደቶችን ለመቆጣጠር እና ግልጽነትን ለማረጋገጥ ምክር ቤቱ እነዚህን ሥራዎች በፍጥነት መወጣት ችሏል።

    ካውንስሉ ዓለምአቀፍ ዲያስፖራዎች ማኅበረሰቦች ለፈንዱ ላሳዩት መታገስና የማያወላዉል ድጋፍ ከፍተኛ ምስጋናዉን ያቀርባል።

    ካውንስሉ የኢትዮጵያ ዲያስፖራን የኢትዮጵያ ወዳጆች እና ሌሎች ነፃነት ዲሞክራሲ ሰብአዊ መብቶችን እና መልካም አስተዳደርን በኢትዮጵያ ማበልፀግ የሚፈልጉን ሁሉ በቀን 1 ዶላር መዋጮቻቸዉን በአንድ ጊዜ በጠቅላላው 365 የአሜሪካን ዶላር እንዲከፍሉ ባክብሮት ይጠይቃል። ይህንም በማድረግ አስፈላጊ ፕሮጀክቶችን ባፋጣኝ ለማስጀመር ይቻላል።

    ስለ ፈንዱ ለመማር እና መዋጮ ለማድረግ ወድዚህ ድህረ ገፅ ይሂዱ (ይጫኑ) https://www.ethiopiatrustfund.org/

    ልዩ ማስታወሻ – የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ በሚል ስም አንዳንድ በግል የተደራጁ ሰዎች ገንዘብ ለመሰብሰብ ጥረት እንደሚያደርጉ የፈንዱ ምክር ቤት ይረዳል። ነገር ግን ኦፊሴላዊ የሆነው በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እ.ኤ.አ. ነሐሴ 9, 2018 በካውንስሉ የተቋቋመው ኤድቲኤ (EDTF) ብቸኛና መደበኛ በሕግ የታወቀው ነው።

    የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ

Viewing 12 results - 1 through 12 (of 12 total)