Search Results for 'ባሕር ዳር'

Home Forums Search Search Results for 'ባሕር ዳር'

Viewing 15 results - 16 through 30 (of 31 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    ባሕር ዳር (ሰሞነኛ) – ዶክተር መሐሪ ታደሰ ወልደጊዮርጊስ አቶ አየነው በላይን በመተካት የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሆነው ተሾሙ።

    ዶክተር መሐሪ ታደሰ ወልደጊዮርጊስ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የሁለተኛና ሦስተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በአሜሪካው ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኖርዝ ቴክሳስ (The University of North Texas) ተከታትለዋል። በዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቴክሳስ አት ኦስተን (The University of Texas at Austin) እና በሌሎችም በተመራማሪነት ማገልገላቸውም ታውቋል። የተለያዩ የምርምር ሥራዎችን በአሜሪካና ካናዳ ማቅረባቸውም በግለ ታሪካቸው ተብራርቷል።

    ዶክተር መሐሪ የተለያዩ ዓለማቀፍ የሙያ ማኅበራት አባል መሆናቸውም ነው የተገለጸው። የአሜሪካ የስታትስቲክስ ማኅበር (American Statistical Association)፣ የአሜሪካ የትምህርት ጥናት ማኅበር (American Educational Studies Association)፣ የተቋማዊ ጥናት ማኅበር፣ የከፍተኛ ትምህርት ጥናት ማኅበር፣ የደቡብ ምዕራብ የትምህርት ጥናት ማኅበርና የቴክሳስ የትምህር ጥናት ማኅበር አባል እንደሆኑም ነው የተገለጸው።

    ከ13 ዓመታት የአሜሪካ ቆይታ በኋላ ባለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ በተለያዩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በምርምርና የተለያዩ ትምህርቶችን በማስተማር እንደቆዩም ተገልጿል፤ በተለያዩ የመንግሥት ተቋማት በኃላፊነት ደረጃ ማገልገላቸውም ነው የተነገረው።

    ዶክተር መሐሪ ታደሰ ወልደጊዮርጊስን ልምዳቸውንና የአመራር ብቃታቸውን ግምት ውስጥ በማስገባት የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ታኅሳስ 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ማካሄድ በጀመረው መደበኛ ጉባኤው የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አድርጎ ሾሟቸዋል።■

    ከአማራ ክልል ሳንወጣ፥ በደብረ ብርሃን ከተማ የሚገነባው የበላይ ባለ ኮኮብ 5 ሆቴልና ቢዝነስ ሴንተር ፕላን በዘርፉ ባለሙያዎች ተገመገመ። የፕሮጀክቱ ዲዛይንና አማካሪ የሆኑት አቶ ነቢዩ ሰለሞን እንዳብራሩት፥ ሆቴሉ በ3,690 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ እንደሚያርፍ፣ 3 ደረጃቸውን የጠበቁ የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ 120 የመኝታ ክፍሎች፣ 2 ሬስቶራንቶች፣ ባር፣ ጂም እና ሌሎች አገልግሎቶችን የሚሰጡ ክፍሎች እንደሚኖሩት፣ ዲዛይኑ አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ያደረገ እንደሆነ ገልጸዋል።

    የደብረ ብርሃን ከተማ ህንጻ ሹም ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አምሳሉ መኮንን በበኩላቸው በቀረበው ዲዛይን መሠረት ገንቢ አስያየት በመስጠት ሆቴሉ ከታሰበው በላይ ተሻሽሎና ዳብሮ እንዲሠራ ባለሙያዎች የድርሻቸውን አንዲወጡ አሳስበዋል።

    የውይይቱ ተሳታፊዎችም የቡና ስኒ በዲዛይኑ ላይ መካተቱ ከደብረብርሃን ጋር ምን ያገናኘዋል? የሠራተኞች ማረፊያ ክፈል፣ ሕፃናት መዝናኛ፣የመዋኛ ገንዳ መካተት አለበት የሚሉና እና ሌሎችም በርካታ ሀሳብ አስተያየቶች ተሰጥተዋል። በመድረኩ ከደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ፣ ከኢንቨስትመንት፣ ከህንጻ ሹም፣ ከህንጻ ዲዛይን አማካሪዎች፣ ከባህል ቱሪዝም ጽሕፈት ቤቶች የመጡ የሥራ ኃላፊዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

    የበላይ ባለ 5 ኮኮብ ሆቴልና ቢዝነስ ሴንተር ከ2 መቶ ሚሊየን ብር በላይ በጀት እንደተያዘለት የመሠረት ድንጋው ሲጣል መገለጹ የሚታወስ ነው።

    ምንጮች፦ የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት እና የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ዶክተር መሐሪ ታደሰ

    Semonegna
    Keymaster

    “ሀገራችንን ኢትዮጵያን አጣብቆ የያዘውን መንግሥታዊ ኃይል ቢዳከም፣ እነዚህ የታሪክም የፓለቲካ መሠረት ያላቸው ልዩ ልዩ ቅራኔዎች በየቦታው ቢፈነዱ፣ በሕዝብ መካከል የእርስ በእርስ ግጭቶች ቢበራከቱ በብዙ አቅጣጫና ውስብስብ የብሄር ቅራኔዎች፣ ሌሎች ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና፣ ማኅበራዊ ችግሮች የተጠመደች ሀገራችንና የኢትዮጵያ ሕዝብ ወዴት ሊወስዱ እንደሚችሉ ከግምት ማስገባት አስፈላጊና ወሳኝ ይሆናል።”

    ሳይቃጠል በቅጠል
    በጋራ ሀገራችን ላይ ያጠላውን የመበታተንና የሕዝብ ለሕዝብ እልቂት ለመቀልበስ የመፍትሄዎች አካል እንሁን!
    (ነአምን ዘለቀ)

    በሀገር ውስጥ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ በሙሉ፣ የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የልዩ ልዩ የቋንቋና ባህል ማኅበረሰቦችን ለምትወክሉ ልሂቃንና ምሁራን፣ የሃይማኖትና የፓለቲካ ድርጅቶች መሪዎች፣ በሀገር ውስጥና በዲያስፓራ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖች፣ አክቲቪስቶች፣ የሚዲያ ባለሙያዎችና የማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች በሙሉ፦

    ሰሞኑን በአገራችን በኢትዮጵያ ልዩ ልዩ አካባቢዎች በደረሱ ጥቃቶች ሳቢያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊና ንጹሃን ወንድሞች፣ እህቶች፣ አባቶች፣ እናቶች፣ አዛውንት፣ ሕጻናት ሳይቀሩ፣ የሃይማኖት አገልጋዮች ጭምር በግፍ ተገድለዋል፣ ቆስለዋል፣ ተፈናቅለዋል። አብያተ ክርስቲያናትና መስጊዶችም ተቃጥለዋል። ብዙ ግፍ ተፈጽሟል። ሕይወታቸውን ላጡ ንጹሃን ዜጎች ወገኖቼና ለቤተሰቦቻቸው፣ ለዘመዶቻቸው በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰማኝን ጥልቅ ሃዘን እገልጻለሁ።

    የሰው ልጆችን ከእንስሳት የሚለየን ረቂቅ ሕሊናን፣ ርሕራሄን፣ ሰብዓዊነት ነው። ከአራት አስር ዓመታት በላይ በተሰበኩ፣ ላለፉት በርካታ ወራት ደግሞ በተካረሩና ጥላቻን መሠረት ባደረጉ የተዛቡና ቁንጽል የታሪክና የፓለቲካ ትርክቶች ሳቢያ ለደረሰው እጅግ አሳዛኝ ጥቃትና የኢትዮጵያውያን ሕይወት መቀጠፍ የራሳቸው ሚና እንደነበራቸው የሚያጠያይቅ አይደለም።

    እነዚህን አሰቃቂና ዘግናኝ ድርጊቶች የፈጸሙ ሁሉ ተጠያቂ መሆን አለባቸው፣ መንግሥት እነዚህን ኢ-ሰብዓዊ ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች በሕግ ፊት ማቅረብ አለበት።

    ከጥቂት ወራት በፊት በልዩ ልዩ ሚዲያዎች በተደጋጋሚ ሃሳቤን ለመግለጽ እንደሞከርኩት ከአንዳንድ የኦሮሞና የአማራ፣ የሕብረ ብሔር ኢትዮጵያውያን ልሂቃን፣ እንዲሁም በልዩ ልዩ ሚዲያዎችና ሶሻል ሚዲያዎች፣ አክቲቪስቶች፣ የብሔርም የሕብረ ብሔርም የፓለቲካ ድርጅት መሪዎች ሲሰነዘሩ የቆዩ ትንኮሳዎች፣ ጠብ አጫሪ ተግባራት፣ እንቅስቃሴዎች በልዩ ልዩ ማኅበረስቦች መካከል ለዘመናት የነበረውን ተጋምዶ፣ ትስስር፣ ትብብር፣ ፍቅር፣ ወልዶ ተዋልዶ አብሮ መኖር የነበረውን እንዳልነበር እያራከሰ እያኮሰሰ የደረሰበትን አሳዣኝ ዝቅጠት ከንፈር እየመጠጥን ስንታዘብ ሰንብተናል። በእኔ እበልጥ እኔ እበልጥ፣ እልህ ተጋብተውም እንዱ እንዱን ለመብለጥ የቃላት ጦርነቶችና፣ ከሁሉም ጎራ የሚሰራጩ የተዛቡ ትርክቶች፣ በሶሻል ሚዲያ የቃላት ሰይፍ መማዘዝ፣ ጥላቻን በሕዝብ መካከል መርጨት በስፋት ሲደረጉ የቆዩበት ሁኔታ፣ በስፋት በተሰራጩ የታሪክም የፓለቲካም የተዛቡ ትርክቶች፣ እጅግ ሲጋነኑ የነበሩ ቁንጽል መረጃዎች፣ ፊው የተዛመቱ የፈጠራ ወሬዎችን ጨምሮ በማኅበረሰቡ መካከል፣ በተለይም ለዘመናት ኢትዮጵያን እንደ ሀገር በመገንባት ትልቅ ድርሻ ያላቸውን በኦሮሞና የአማራ ሕዝቦች መካከል ትልቅ ክፍተት እንዲፈጠር፣ የተወሰኑ የሕዝብ ክፍሎች ውስጥም ጥላቻ አየሰፋ፣ እየተጠናከረ እንዲመጣ አፍራሽ አሰተዋጽኦ በማድረግ ከሰሞኑ ለተቀሰቀስው ከጥላቻ የመጣ ጥቃት፣ እጅግ አሳዛኝና እሰቃቂ ድርጊቶች ሚና እንደነበራቸው መታወቅ ያለበት ይመስለኛል።

    በተለይ በሕዝብ ቁጥር ትልቅ በሆኑት ብሔሮች በአማራና በኦሮሞ መካከል ቅራኔን፣ ጥላቻን፣ ጥርጣሬን የሚያጠናክሩ ትንኮሳዎች፣ በየመድረኩ፣ በጀርመን በእሥራኤል፣ በሌሎችም የዲያስፓራ የተቃውሞ ሰልፎች የተሰነዘሩ የጥላቻ፣ እንዱ ሌላውን በንቀት የሚያንኳስሱ ቃላቶችና ድርጊቶች፣ የተሳሳቱና የተዛቡ ትርክቶች በስፋት ሲካሄዱ እንደነበር የሚካዱ ሊሆኑ አይችሉም። ከዚህ አፍራሽና እጅግ ስስና ተሰባሪ የሆነውን የሀገሪቱን ሁኔታ፣ ተዋናዮቹ ግለሰቦች ብቻ ሳይሆኑ፣ ከግለሰቦች ጀርባ የሚገኙ የዶ/ር መረራ ጉዲናን አጠቃቀም ለመዋስ “የሚጋጩ ህልሞች” እንዲሁም ቅዠቶች፣ ሃሳቦችና ትርክቶች፣ በእነዚህ ትርክቶች ዙሪያም የተሰለፉ ሚሊዮኖች መኖራቸውን እነዚህ ሚዲያዎች፣ ሶሻል ሚዲያዎችና፣ አክቲቪስቶችና የፓለቲካ ልሂቃን ከግምት ውስጥ ሊያስገቡት አልቻሉም፤ ለማስገባትም አልተፈለገምም ነበር።የሴራ መልዕክቶች፣ ባልተጣሩና ለማጣራትም ምንም ጥረት ባልተደረገባቸው በዜና መልክ የሚቀርቡ የፈጠራም የተጋነኑም ወሬዎች በተለይ ሀገር ውስጥ በመሬት ላይ ለሚገኘው የገፈቱ ቀማሽ ሰላማዊ ሕዝብ የማይበጀው መሆኑ መረዳት ያስፈልግ ነበር።

    ያደራጁት ኃይል በእጃቸው በሌለበት፣ አማራጭ ራዕይና ፕሮግራም ባላዘጋጁበት፣ አገርን ሊያረጋጋ፣ ሕዝብን ከጥቃት ሊከላከል የሚችል ወታደራዊና የጸጥታ ኃይሎችን ባላሰለጠኑበት፣ በማይመሩበት፣ ለዚህ ደግሞ መንግሥታዊ አቅሙም፣ ችሎታም፣ ስትራቴጂካዊ ጥናቶች ሆነ ቅደመ ዝግጅቶች ማንም ምንም በወጉ ባላሰቡበት፣ ባልተዘጋጁበት ሁኔታ በስልጣን ላይ የሚገኘውን ብዙ ተግዳሮቶች የገጠመው ነገር ግን ለውጥን ለማምጣት ደፋ ቀና ሲል የቆየውን የለውጡን አመራር በከፍተኛ ርብርብ ለማዋከብና ለመሸርሸር የተሄደበት ርቀት ትልቅ ታሪካዊ ስህተት ይመስለኛል።

    ሀገራችንን ኢትዮጵያን አጣብቆ የያዘውን መንግሥታዊ ኃይል ቢዳከም፣ እነዚህ የታሪክም የፓለቲካ መሠረት ያላቸው ልዩ ልዩ ቅራኔዎች በየቦታው ቢፈነዱ፣ በሕዝብ መካከል የእርስ በእርስ ግጭቶች ቢበራከቱ በብዙ አቅጣጫና ውስብስብ የብሄር ቅራኔዎች፣ ሌሎች ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና፣ ማኅበራዊ ችግሮች የተጠመደች ሀገራችንና የኢትዮጵያ ሕዝብ ወዴት ሊወስዱ እንደሚችሉ ከግምት ማስገባት አስፈላጊና ወሳኝ ይሆናል። እንደ ሀገር መኖር አለመኖር፣ እንደ ሀገር መቀጠል ወይንም አለመቀጠል የምንችልበት ወይንም የማንችልበት የታሪክ መጋጠሚያ ላይ ደርሰናል። በአንድ አካባቢ የሚጀመር እሳት፣ ወደ ሌላ አካባቢ ሊዛመት እንደሚችል ወደ ሰደድ እሳት ሊያድግ፣ ሊሸጋገር ወደሚችል ደረጃ እንደሚደርስ ብዙ እውቀትና ማሰብ የሚፈልግ አይመስለኝም። በሌላም በኩል ደግሞ የእርስ በእርስ ግጭቶች እየተቀጣጠሉ፣ አድማሳቸው እየሰፋ ሊሄድ እንደሚችል፣ በአንድ አካባቢ የተነሳ ግጭትና የግጭቱ ጥቃት ስለባ የሆኑ ወገኖች በሌላ አካባቢ በሚገኙ የአጥቂዎች ወገኖች ላይ የብቀላ ጥቃት፣ የብቀላ ብቀላ አድማሱ አየሰፋ፣ እየተዛመተ፣ ማንም ምድራዊ ኃይል ሊቆጣጠረው ወደማይችል ምድራዊ ሲኦል ሊለወጥ የማይችልበት ምክንያት አይኖርም።

    ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ፦

    ዛሬ ትላንት አይደለም። ትላንት የሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች፣ የአብዛኛው የዲያስፓራ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ትኩረትና የትግሉ ግብ፣ የትግሉም ዒላማ በሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሲዘወር በነበረ ግፈኛና ጨካኝ አገዛዝ ላይ ያነጣጠረ እንደነበር የሚካድ አይደለም። ከጎንደር እስከ ሐረር፣ ከባሌ ዶሎ እስከ ወሎ፣ ከሐረር እስከ ባሕር ዳር የኢትዮጵያ ሕዝብ ከኦሮሞ እሰክ አማራው፣ ከጋምቤላ እሰከ ሶማሌ፣ ከአዲስ አባባ እስከ አምቦ ትግሉ ከመንግሥት ኃይሎች፣ ከጨቋኝና ግፈኛ ገዥዎችና የመጨቆኛ መሥራሪያዎቻቸው፣ ተቋማቶቻቸው ጋር ሲያፋፍም የነበረ፣ አለፍ ካለም የእነሱ ጥቂት ደጋፊዎች ላይ ያነጣጠረ እንደነበር የማይረሳ ነው።

    ዛሬ ግን ቅራኔው፣ ግጭቱ፣ ጥላቻው የጎንዮሽ በሕዝብ መካከል ሆኗል፤ በማኅበረሰቦች መካከል ሆኗል። ትልቁ አደጋ ይህ ከሰሞኑ የተከሰተውና ነጥሮ የወጣው እውነታ ከዚህ ጋር የተያያዘ መሆኑ የሚያጠራር፣ የሚያሻማ ሊሆን አይችልም። ዛሬ ቅራኔው ለዘመናት አብረው በኖሩ ማኅበረሰቦችና በሕዝብ መካከል መሆኑ ነው። ይህ እውነታ በስፋትና በጥልቀት በበርካታ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚታይ እጅግ አደገኛ ሂደት መሆኑ ግልጽ አየሆነ ነው።

    ይህን ልዩና እጅግ አስጊ ሁኔታ ለመለወጥ ከፍተኛ ጥንቃቄ፣ ዘዴዎች፣ ብልሃቶች ይጠይቃል። መንግሥታዊ የማድረግ አቅም የመኖር አለመኖር ብቻ ሳይሆን የመንግሥት እርምጃዎች፣ የመንግሥት ድርጊቶች ሊፈጥሩ የሚችሉትን አሉታዊ የሆነ የአንድ ወይንም የሌላ ወገን የአጸፋ ምላሽ ለመቋቋም የሚያስችል፣ ያልተጠበቁ ትላልቅ አደጋዎች በሕዝብ ላይ እንዳይደርሱም እስቀድሞ ችግሮቹ በቀጥታ የሚመለከታቸውና ከችግሩ ጋር ተፋጠው የሚገኙ የመንግሥት መሪዎችና ልዩ ልዩ የመንግሥታዊ ተቋማት ሃላፊዎች ሊደረግ ብቻ የሚችል የቢሆንስ ትንታኔም የሚያስፈልገው ነው። የመንግሥት መሪዎች ወደ ስልጣን ያመጣቸው ፓርቲና ሕዝብ ውስጥ ያላቸው ቅቡልነት፣ ስትራቴጂካዊ አስተሳሰብ ዝግጁነት፣ በየጊዜው የሚፈተሽ ዕቅድና ይህንኑ የማስፈጸሚያ/የ ማድረግ አቅም የሚሰጡ ልዩ ልዩ የመሣሪያዎች ሳጥን በአግባቡና በብቃት ማዘጋጀትን የሚጠይቁ ናቸው። ድርብርብና በየደረጃው የሚከናወኑ ተግባራት ያሉበት ውስብስብ ሁኔታ ነው። በመንግሥት ብቻ ሳይሆን፣ በአገር ሽማግሌዎች፣ በሃይማኖት አባቶች፣ በልሂቃን፣ በልዩ ልዩ ኃይሎችና ባለድርሻዎች በጋራም፣ በተናጠልም ሥራዎችን ይጠይቃሉ።

    የኢትዮጵያን ሰላምና፣ ደህንነት፣ መረጋጋት የሚፈልጉ ዜጎች ሁሉ ይህን አስጊና አደገኛ በሕዝባችን ደህንነት፣ በሕዝባችን አብሮነት፣ በኢትዮጵያ ሃገራዊ ህልውና ላይ የተደነቀረ ከባድ አደጋ ለመሻገር ከተፈለገ ይህን አደጋ ከሚያባብሱ፣ ከሚቀጣጥሉ ቃላት፣ ቅስቀሳዎች፣ ቁንጽልና በቅጡ ያልታሰቡባቸው፣ ያልተጠኑም በርካታ የሀሰትም ወሬዎች፣ የተዛቡና በምንም መልኩ መቼም ሙሉና ሁለንተናዊ እይታን ሊሰጡ የማይችሉ ትርክቶች በሚዲያና በማኅበራዊ ሚዲያዎች ከማሰራጨት መቆጠብ የግድ ይሆናል። በምትኩ የሚዲያዎች ሚና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ተስፋ መስጠት፣ ማኅበረሰቦች እንዲቀራረቡ የበኩላቸውን ሚና መጫወት ያለባቸው ይመስለኛል። ግጭት ሳይሆን ውይይት፣ ቅራኔን ሳይሆን መግባባት እንዲመጣ ገንቢ ጥረቶች ማድረግ የሁሉም የፓለቲካ ልሂቃንና የሚዲያዎች፣ በሀገር ቤትም በውጭ ሀገርም የሚገኙ የብሄርም የሕብረ ብሄርም ዓላማ ያነገቡ አክቲቪስቶች ታሪካዊ ሃላፊነት ነው ብዬ አምናለሁ። በተለይም እሳቱ የማይደርስባቸው፣ በእነሱም በቤተሰቦቻቸው፣ በዘመዶቻቸው ላይ ጭምር ሊደርስ የሚችል የማይመስላቸው በውጭም በሀገር ውስጥም የሚገኙ የየብሔሩ ልሂቃን፣ የየብሔሩና በሕብረ ብሔርም ኢትዮጵያዊነትና ዜግነት ፓለቲካ የተደራጁ አክቲቪስቶች ሁሉ ቆም ብለው ማሰብ የሚገባቸው ወቅት አሁን መሆኑን በጥብቅ ለማሳሰብ እፈልጋለሁ።

    የሚቀጥለው እሳት ወደ ሰደድ እሳት እንዳያመራ ሳይቃጠል በቅጠል እንዲሉ ለትላልቆቹ የፓለቲካ ልዩነቶች መፍትሄ ማፈላለግ ያስፈልጋል። የተጀመረው አዝጋሚና ብዙ ተግዳሮቶች የገጠመው የለውጥ ሂደት ከእናካቴው እንዳይቀለበስ ሁሉም የድርሻውን ማበርከት አለበት ብዬ አምናለሁ። ይህን አጋጣሚ ለመጠቀም ያቆበቆቡ፣ ይህን ሁኔታ ለመጠቀም ሰሞኑን በሀዘን የተመለከትነውን ጥቃት በማጦዝ፣ በማራገብ ጮቤ የረገጡ፣ ልዩ ልዩ ዘዴዎችንም በመጠቀም ከተለያዩ የፓለቲካም፣ የሚዲያም ተዋናዮች ጀርባም በመሆን ቅራኔዎችና ችግሮች እንዲሰፉ፣ እንዲባባሱ የእነማን ዘርፈ ብዙ ጥረት እንደሆነ የሚጠቁሙ በርካታ መረጃዎች በየጊዜው እንደሚያሳዩ ለአብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ ይመስለኛል። ከመሸጉበት ለማንሰራራት፣ ብሎም የኢትዮጵያን ሃገረ መንግሥት ማዕከል ዳግም ለመቆጣጠር ያላቸውን ቀቢጸ-ተስፋ ዕውን ለማድረግ፣ የለመዱትንም ግፈኛ መንግሥታዊ ሽብርና መንግሥታዊ ዘረፋ በመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ኪሳራ ለማስቀጠል ሙከራቸውን ከማድረግ ወደ ኋላ የማይሉ እኩይና ከታሪክ የማይማሩ ያረጁ ያፈጁ ከ21ኛው ክፍለ ዘመን የፓለቲካ አስተሳሰብ ጋር እራሳቸውን ማለማመድ፣ ካለፈው ወንጀሎቻቸውና ውድቀታቸው መማር የማይችሉ ድኩማን የፓለቲካ ድርጅች እንዳሉ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍንትው ብሎ የሚታይ ሃቅ ነው ብዬ እገምታለሁ።

    እነዚ ህይሎች የራሳቸውን ጥቅምና ያጡትን የበላይነትና ፈላጭ ቆራጭነት ከማየት በስቲያ፣ በሕዝብ ላይ ጭነው ከነበሩት የበላይነት ባሻገር ለሕዝብ መከራ፣ ለሰው ልጆች ጉስቁልና ቁብ የማይሰጣቸው ናቸው። የሚሊዮኖች ኢትዮጵያውያን ደምና እንባ ለ27 ዓመታት አንደ ጎርፍ እንዲፈስ ያደረጉት እነዚህ የፓለቲካ ዓመታት ይህን እኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት የጋራ አገራችን ኢትዮጵያ አገራዊ ትርምስ ውስጥ ብትገባ ፈጽሞ የማይጨነቁበት መሆኑን ሲጀምሩም የተነሱበት የፓለቲካ ዓላማ፣ ታሪካቸው፣ እስካሁንም የቀጠሉበት አንደበታቸው፣ የተካኑበት መሰሪነትና ተንኮል ያረጋግጣል። “እኛ የኢትዮጵያ አዳኞች ነን” በሚል ሽፋንና ነገር ግን የማዕከላዊ መንግሥትን ሙሉ በሙሉ የመቆጣጠር ቀቢጸ-ተስፋቸው እሁንም በትዕቢትና በትምክህት ተወጥረው በሚያደርጉት እንቅስቃሴ አገራችንን ወደ ሁለንተናዊ ትርምስ ጎዳና ሊያስገባ የሚችል ዕድል እንዳንሰጣቸው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ ነቅቶ መጠበቅ እንዳለበት በጽኑ አምናለሁ።

    የኢትዮጵያ ምድር ከጥንት ከሺህ ዓመታት በፊት ዛሬ የሚገኙ ሕዝቦች ያልነበሩበት፣ አንዱ በአንድ ዘመን ከደቡብ ተነስቶ ሌሎችን ማኅበረሰቦች አስገብሮ መሬት ሲይዝ፣ በሌላ ዘመን ሌላው ይህኑ አጸፋ ሲያደርግ፣ ሲስፋፋ፣ በአመዛኙ ደግሞ የየብሔሩ ገዢዎች፣ በዓለም ላይ እንደነበሩ ገዥዎች ሁሉ የተደረጉ ሂደቶች ናቸው። ሌሎች የዓለም ሃገሮች ከተመሠረቱበት የሀገራት ምሥረታ ሂደት ምንም የሚለየው የለም። ባርያ ፈንጋዩና አስገባሪው ደግሞ የአንድ ብሔር አንድ ቋንቋ የሚናገሩ ብቻም አልነበሩም። በልዩ ልዩ የታሪክ ምዕራፎች የየማኅበረሰቡ/ብሄሩ ንጉሶችና ገዢዎች፣ አስገባሪዎች፣ ተስፋፊዎች በመሆን ተፈራርቀዋል። የልዩ ልዩ ብሔሮች/ማኅበረሰቦች ገዢዎች ከመሃል ወደ ደቡብ፣ ከደቡባዊ ከምሥራቃዊ ኢትዮጵያ ተነስቶ እስከ መሃላዊ የዛሬዋ ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን እስከ ሲሜናዊና ሰሜን ምሥራቃዊ የሀገሪቱ ክፍሎች በመዝመት በመስፋፋት ሲፈራረቁበት የቆዩበት የረጅም ዘመናት ሂደት ነው። የረጅም ዘመናት ታሪካችን እያንዳንዱ ማኅበረሰብና በየዘመኑ፣ በሰፊው የታሪካችን ምዕራፎች የነበሩ የብሔርም የሕብረ-ብሔርም ገዥዎች በቀደሙት ዘመናት አጣኋቸው ያላቸውን መሬቶች ለማስመለስ ዳግም በኃይል ሲስፋፋ የነበረበት ውጥንቅጥና አባይን በጭልፋ እንደሚባለው ረጅምና ተጽፎ ያላለቀ፣ ተጽፎም ሊያልቅ የማይችል፣ የብዙ ዘመናት የመጥበብ፣ የመስፋት ሂደቶችና ተደጋጋሚ ኡደቶች ብቻም አልነበሩም። የንግድ ልውውጥ፣ የማኅበራዊ ግንኙነቶች፣ የቋንቋና ባህል መወራርስና መዳቀል የነበሩበትም ሂደት ነበር። ለዳር ድንበርና ለሕዝብ ክብር ለኢትዮጵያ አገራዊ ግንባታ በኦሮሞም፣ በአማራም፣ በአፋር፣ በትግሬ፣ በወላይታ፣ ጉራጌ በሌሎችም የቋንቋና የባህል ማኅበረሰቦች ባፈሯቻቸው በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሀገራዊ እርበኞች፣ አንጸራቂ ጀብድ በፈጸሙ፣ ታላላቅ ጀግኖችና የጦር መሪዎች መስዋዕትነት የተገነባ ሕብረ-ብሔራዊ ኢትዮጵያ ማንነትና ሃገራዊነት የታሪክ ሂደትም ነው። ይህ ውስብስብ የታሪክ ሂደት በ150 ዓመት ታሪክ ትንሽ አጭር መነጽር ሊታጠር፣ ሊገደብ የማይችል ሰፊ የዘመናት የታሪክ ባህርን በጭልፋ በሰፈረ፣ እጅግ ቁንጽል የሆነ የነፍጠኛ የሰባሪ የገባር/የአስገባሪ ትርክትና እንድምታ የማያይወክለው፣ የማይገልጸው ሰፊና ጥልቅ የሆኑ የታሪኮቻችን ገመዶችና ክሮች የልዩ ልዩ ማኅበረስቦች መስተጋብሮች፣ ግንኙነቶችና፣ የሂደቶች ውጤት ነው።

    ዋናው፣ ትልቁ ሃቅ ግን ከዚህም ከዚያም ወገን ማንም የታሪካችን ሙሉ እውቀት፣ ሙሉ መረጃ እንኳን በዚህኛው በወዲያኛውም ሕይወቱ ሊኖረው አይችልም። ታላላቆቹና በዓለም ደረጃ የሚታወቁት የታሪክ ጸሐፍት እነ አርኖልድ ቶዬንቢ (Arnold J. Toynbee)፣ ኤድዋርድ ጊበን (Edward Gibbon)፣ ዘመናዊና ትላልቅ ስም ያላቸው ኒያል ፊርግሰን (Niall Ferguson)፣ ፈርናንድ ብራውዴል (Fernand Braudel)፣ ሌሎችም ታዋቂ የታሪክ አጥኚዎች የሀገራቸውንም ሆነ የዓለምን ታሪክ በሚመለክት የጻፏቸው ሁሉንም የታሪክ ምዕራፎች፣ ሁሉንም ታሪካዊ ክንውኖች፣ ሁሉንም ታሪካዊ መረጃዎች፣ ሁሉንም ታሪካዊ ሂደቶች አጣርተው በሙሉ፣ ፍጹም በሆነ እውቀት/ዩኒቨርሳል የታሪክ ዘይቤም የታሪክ ሙሉ እይታ ሊኖራቸው እንደማይችል የታወቀ ሃቅ ነው። የብዙ አገሮች ታላላቅ የታሪክ ጸሐፊዎች በእያንዳንዱ የታሪክ ምዕራፍ አስከ ዛሬ የሚወዛገቡባቸው በርካታ የታሪክ ኩነቶች፣ የታሪክ ትርጓሜዎች፣ የታሪክ ዘይቤዎች እንዳሉ ራሱ የኢትዮጵያን ታሪክ በራሳቸው ልክ ለሚፈልጉት የፓለቲካ አጀንዳ ቀንጭበውና ቆንጽለው የሚያቀርቡ የየብሔሩ ልሂቃን የሚያጡት ሃቅም አይደለም።

    እነዚህ አጨቃጫቂ፣ አወዛጋቢ የሆኑት በሁሉም ወገን ቁንጽል የሆኑና ማንም በምንም መልኩ ሙሉ በሙሉ በሚያስብል ደረጃ እንደበርክታ የታሪክም የማኅበራዊ ሳይንስ የመነጩ ጥናትችና ትርክቶች ሙሉ እይታ፣ ሙሉ እውቀት፣ ሙሉ ግንዛቤ፣ እንደሌላቸው ይታወቃል። የተፈጥሮ ሳይንስ በተለይም ከአንስታይን የሬላቲቪትይ የፊዚክስ ቲዎሪ (Albert Einstein’s Relativity Theory) ግኝት በኋላ ሁሉን አዋቂና ሁሉን ተንባይ ነኝ የሚለው ማንነቱ ላይ በደረሰብት ቀውስ ሳቢያ የሳይንሱ ማኅበረሰብ የሚቀበለው በአመዛኙ ፍጹም የሆነ፣ ሙሉ የሆነ እውቀት፣ ዩኒቨርሳል የሆነ እርግጠኝነት፣ የትንበያ አቅምም እንደሌለ ነው። ሌሎች ታላላቅ የሳይንስ ፈላስፎች ኢ-እርግጠኝነት (Uncertainty principle) የሚል ስያሜ የሰጡት የተፈጥሮ ሳይንስ ንጉስ የሆነው ፊዚክስ ተፈጥሮን ሙሉ በሙሉ፣ ሁሉን ለማወቅና የሚሆነውንም ለመተንበይ የማይችል፣ በእጅጉ ያለውን ውሱንነት ያጠናከሩ፣ ልዩ ልዩ የእውቀት ዘርፎችም ከኢኮኖሚክስ እስከ የፓለቲካ ሳይንስ የእውቀት ዘርፎች ጠቅላይ ሊሆኑ፣ ሙሉና የወድፊቱንም በፍጹም እርግጠኝነት ሊተነብዩ እንደማይችሉ፣ ልዩ ልዩ የእውቀት ዘርፎች በተወሰነ አውድ፣ በተወሰነ ካባቢ ውሱን ለሆነ ግንዛቤና እውቀት፣ ለውሱን ችግሮች መፍቻ ዘይቤዎች/መሣሪያዎች ብቻ እንደሆኑ፣ የወደፊቱም የመተንብይም ሆነ ያልፈውን የታሪክም የማኅበረሰብን ውጥንቅጦች በሁለንተዊና ጠቅላይ/ዩኒቨርሳል በሆነ መልኩ ለማወቅ እንደማይቻል እንዱ ሌላውን ሲገለብጡ፣ የኖሩ ንደፈ ሃሳቦች፣ ጽንሰ ሃሳቦች (theories)፣ የዓለም እይታዎች (paradigms)፣ ልዩ ልዩ የማኅበረሰባዊና የተፈጥሮ ሳይንስ ፍልስፍናዎች፣ እንዲሁም የዘይቤዎች (methods/models) የትየለሌ መሆናቸው የሚያረጋግጡት ይህንንኑ ነው። በብዙዎች ዘንድ በዚህ ጉዳይ ላይ ሰፊ ግንዛቤና መግባባት የተደረሰ ይመስለኛል።

    ስለዚህ የኢትዮጵያ ልሂቃን በተለይ በፓለቲካው ትልቅ ሚና ያላችሁ የታሪክና የህብረተሰቡን ችግሮች ሁሉ በሚመለከት አለን የምትሉት ግንዛቤ ውሱንነት መቀበል። ትህትና ብትህውትነት (humbleness and humility) እኛ ሁሉን እናውቅለታለን ብለው ለሚገምቱት ሕዝብና ማኅበረሰብም የተሻለው ምልከታ ይመስለኛል። ምክንያቱም ፍጹም እወቀት፣ ፍጹማዊ እውነት አለኝ ለማለት በማይቻልበት እጅግ ሰፊና ጥልቅ የተፈጥሮ፣ የታሪክ፣ የማህብረሰብም ሂደቶች፣ ጉራማይሌዎች፣ ጓዳ ጎድጓዳዎች፣ ጉራንጉሮች፣ ዥጉርጉር ሁኔታዎችና ሂደቶች የነበርን ሕዝቦች በመሆናችን። የሰው ልጆች ሕይወትም ሆነ የዓለም ሕዝቦች ታሪክ አካል የሆነ የኢትዮጵያ ታሪክ (ታሪኮች) ግራጫ ቀለም ያላቸው እንጂ ነጭና ጥቁር ባለመሆናቸው የኋላ ታሪኮቻችን፣ የሚጋጩ ትርክቶች ያን ወይንም ይህን ቁንጽል የታሪክ ጠብታ ይዞ ሙሉ እውቀት ባለቤት ነኝ፤ በሞኖፖል እውቀት እኔ ጋር ብቻ የሚል ስሜት ያላቸው የየብሄሩ ልሂቃን ቁንጽ የታሪክ ትርጉሞች/ትርክትን መሠረት አድርገው የሚሰነዘሩ ሽኩቻዎች የሕዝብ፣ የማኅበረሰብ ቅራኔዎች፣ ጥላቻና፣ ግጭቶች፣ ጥቃቶች መንስዔም እየሆነ የመጣበት ይህ እጅግ አሳዛኝ ሁኔታ እሁን ላይ መቆም ይገባዋል። ለአገርና ለሕዝብ የተሻለው፣ የሚበጀው መንገድም ይህ ይመስለኛል። ሁለተኛው አማራጭ ሕዝብን ማጫረስ፣ ሀገርን ማፍረስ፣ ሁሉም በእሳት የሚጫወት ተዋናይ በሰደድ እሳቱ ወላፈን እራሱም ሆነ በምድር ላይ የሚገኙ የሚወዳቸውም ሳይቀሩ የመለብለብ፣ የሚጠበስ ምድራዊ ገሃነም ብቻ ናቸው።

    የኦሮሞም የአማራም ከዚያም የደቡባዊና የምሥራቃዊ ኢትዮጵያን፣ እንድሁም የኦሮሞን ታሪክ በአግባቡ አላካተተም ወይንም አይወክልም የሚባለው የግዕዝ ስልጣኔ ታሪክ፣ ሌላም ካለ ሁሉም ወገን የኔ የሚላቸው ትርክቶች፣ ልዩ ልዩ ታሪኮች ወይንም የሚጣጣሙበት ወይንም የሚቀራረቡበት መንገዶችና ዘዴዎች መፈለግ፤ ወይንም ደግሞ ተመሳሳይ የታሪክ አረዳድ ያልነበራቸው አገሮች፣ የሚጋጩ ትርክቶች አገራዊ ትርምስ የፈጠሩባቸው የሌሎች ሀገሮችን ሕዝቦች ልምድ ቀስሞ ከሁሉም የተውጣጣ፣ ይህንኑ የሚያጠና ባለሙያዎች የሚገኙበት ኮሚሽን የሚቋቋምበት ሁኔታ ቢመከር ምናልባት አንዱ የመፍትሄ አካል ሊሆን ይችላል። ምክንያቱም ቀደም ሲል እንደተነሳው የአገራችን ትላልቅ የፓለቲካ ቅራኔዎች አንዱ ከአለፉ ታሪኮቻችን የታሪክ አረዳድና አተረጓጎም ልዩነቶች፣ የሚጋጩ ትርክቶች ላይ የሚመነጩ በመሆናቸው ከፍተኛ ትኩረትና ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል እላለሁ።

    ሁሉም አሸናፊ የሚሆንበት፣ ማንም ተሸናፊ የማይሆንበት በሀገሪቱ ዋና ዋና ችግሮች ዙሪያ መፍትሔ ተኮር ውይይቶች በየደረጃው የሚደረጉበት ሁኔታዎች መፈለግ አስፈላጊ ይሆናል። ሁሉም ባለድርሻዎች አገሪቷን እሁን ላይ ከገጠማት የህልውና አደጋ ለመታደግ ከለውጡ መሪዎች ጋር በመነጋገር፣ በለውጡ መሪዎችም በኩል ጉልህ ድምጽ ያላቸውን ባለድርሻዎች፣ የየብሄሩን ልሂቃንና የፓለቲካ ኃይሎች ሁሉ ፍላጎታቸውን በግልጽ ወደ ጠረጴዛው እንዲያቀርቡ፣ ውይይቶች እንዲደረጉ፣ ሰጥቶ የመቀበል፣ ብሎም ሀገራዊና ብሄራዊ መግባባት ላይ መድረስ እንዲቻል መድረኮችን የማመቻቸት ጊዜው አሁን ነው የሚል የሚል ሃሳብ አቀርባለሁ።

    የሁሉም ዜጎችና የቋንቋና የባህል ማኅበሰቦች ጥቅምና መብቶች ያልተከበሩባት ኢትዮጵያ የማንም የየትኛውም ብቸኛ ማኅበረሰብ/ወይንም ብሔር መብት፣ ፍትህና ጥቅም ለዘለቄታው ሊከበርባት እይችልም። የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የሌሎችም ማኅበሰቦች ልሂቃንና የፓለቲካ ኃይሎች ቆም ብለው የማንም የማትሆን አገር ሁላችንም ወደ ምድራዊ ሲኦል የሚወስድ መንገድ ከመግፋት እጅግ የተሻለው አመራጭ ለሁሉም ጥቅም፣ ለሁሉም እኩልነት፣ መብቶች፣ ለሁሉም ድምጽና ክብር፣ ለሁሉም የምትመች ኢትዮጵያን እንድትሆን ተነጋግሮ፣ ተግባብቶ፣ ፍኖተ ካርታውን፣ የጨዋታውን ሕግ፣ ሂደቱን፣ የሥነ ምግባር ደንቡን… ወዘተ የሚመለከቱ እንዲሁም ዋና ዋና ፓለቲካዊ ልዪነቶች ላይ ዉይይቶች በማድረግ፣ ወደ መግባባት ላይ ለመድረስ ማሰብ ያለባቸው ጊዜ አሁን ይመስለኛል። ይህ ጥሪ ለኦሮሞ፣ ለአማራ፣ ለሶማሌ፣ ለአፋር፣ ለትግራይ ለሌሎችም ማኅበረሰቦች ልሂቃን፣ የፓለቲካ ኃይሎች፣ እንዲሁም የሕብረ ብሔር የኢትዮጵያዊነት የዜግነት የፓለቲካ ኃይሎች በሙሉ ለህሊናም፣ ለታሪካችሁም እጅግ የተሻለው አማራጭ መሆኑን በአንክሮ ማሰብ ወቅቱ አሁን ይመስለኛል።

    በሁሉም አካባቢዎች የሚገኙ ሕብረ ብሔር ኢትዮጵያውያን የዜግነት መብቶችና ጥቅሞች ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲስተናገድ፣ እንዲከበሩ፣ እንዲረጋገጡ የሚያስችል ሂደት መጀመርም አለበት። የየትኛውም ብሔር የበላይነት (hegemony)፣ በየትኛውም አካባቢ ይህ የኔ ለእኔ ብሔር ብቻ ነው ሌላው ዜጋ መጤ ነው፣ ሰፋሪ ነው… ወዘተ የሚሉ የተዛቡና ብዙ ሚሊዮን ዜጎችን በገዛ አገራቸው ባይተዋር ያደረጉ፣ ስጋትን፣ የነገን ተስፋ አለማየት፣ ከሰሞኑ ደግሞ በንጹሃን ዜጎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች ሕይወት ያስቀጠፉ አስተሳሰቦችና ሥነ ልቦናዎች የሚለወጡበት ሁኔታ በቅጡ መታሰብ፣ መፍትሔም ማግኘት አለባቸው። በተጨማሪም ይሄ “የኔ ብሔር፣ ይሄ የኔ አካባቢ ብቻ ነው”፣ የሚሉ ኢ-ፍትሃዊ የሆኑ ጸረ-ዴሞክራሲያዊ አመለካከቶች “የኔ” ለተባለውም ብሔር ሕዝብ ጥቅምንም መብቶችንም ለዘላቂው ሊያስከብርና ሊያስቀጥል አይችልም። ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በሌለበት፣ የሕግ የበላይነት ባልተረጋገጠበት፣ ተጠያቂነትና ግልጽነት የሌሉዋቸው የፓለቲካ ስርዓቶች በስመ ብሄር፣ ወይንም በሀገራዊ ብሄርተኝነት ስም ወደ ስልጣን የመጡ ፈላጭ ቆራጭ አምባገነኖች ብሄሬ በሚሉት ሕዝብ ላይ ያደረሱትን መከራ፣ ስቃይና፣ እልቂት በታሪክም አሁን ላይ በዘመናችንም ከበቂ በላይ ሁላችንም የታዘብን፣ ያየን ይመስለኛል።

    በአንድ ሀገር ውስጥ ግማሹ የበኩር ልጅና አንደኛ ዜጋ፣ ገሚሱ የሀገሪቱ ሕዝብ ደግሞ የእንጀራ ልጅና ሁለተኛ ዜጋ፣ ከዚያም ወረድ ብሎ በስጋት በፍርሃት፣ ያለዋስትና እየኖረ የሚቀጥልባት ኢትዮጵያ እንደ እንድ የጋራ አገር፣ በጋራ አብሮ ለመኖር ሊያዘልቁ የሚያስችሉ አይሆኑም። ይህን እስከፊና ለ26 ዓመታት የተንሰራፋ፣ ዛሬም ሊደገም፣ ተጠናክሮ ሊቀጠልበት የሚሞከርበት፣ ብዙ ሚሊዮኖች አማርኛ ተናጋሪ ይሁኑ እንጂ ከኦሮሞ፣ ከጉራጌ፣ ከወላይታ፣ ከትግሬ፣ ከከንባታ፣ ጋሞ፣ ከሶማሌ አፋር፣ ከሌሎችም ማኅበረሰቦች ቅይጥና ቅልቅል የሆኑ፣ ወይንም በሥነ ልቦናም፣ በአመለካከትም፣ የትኛውም ብሔር ሳጥን ውስጥ ሊገፉና ሊከተቱ የማይችሉ፣ ነገር ግን ሁሉንም ብሔሮች/ማኅበረሰቦች የሚወዱ፣ አብሮ የኖሩ፣ አፍቅሮ፣ ተጋብቶና ተዋልዶ፣ በልዩ ልዩ ማኅበራዊና ሰዋዊ ገመዶች የተሳሰረ፣ በደም በአጥንት የተለሰነ የልዩ ልዩ ማኅበረሰቦች የተገኙ “ከአስገባሪነት”፣ “ከነፍጠኝነት”፣“ከሰባሪነት” ጋር ምንም ግኙነት የሌላቸው፣ ከኢትዮጵያዊነት ሌላ ቤት የሌላቸው፣ ብዙ ሚሊዮን ዜጎቻችን በአዲስ አበባ አካባቢዎች፣ በሐረር፣ በድሬ ዳዋ፣ በባሌ፣ በአዳማ፣ በአሰላ፣ በአዋሳ፣ በልዩ ልዩ ሌሎች የሀገሪቱ የከተማ፣ ከተማ ቀመስና የገጠር አካባቢዎች ሁሉ ሙሉ መብቶቻቸው፣ ደኅነታቸው፣ በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይም በኦሮሞ፣ በደቡብ በሌሎችም አካባቢዎች መከበር፣ መረጋገጥ የሚቻልበት ሁኔታዎች፣ ውይይቶች፣ ድርድሮች፣ መግባባቶች መደረስ ይኖርበታል።

    በሀገርም ውስጥ በውጭም የምትገኙ የምታውቁኝም የማታውቁኝም ወድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ፦

    ታላቁ የአሜሪካን ፕሬዝደንት አብረሃም ሊንከን (Abraham Lincoln) የአሜሪካ ጥቁ ር ሕዝቦችን ከባርነት ለማላቀቅ በተደረገው የደቡብ ባሪያ አሳዳሪ ኮንፌደሬት ሠራዊትና የሰሜኑ የአንድነት ሠራዊቶች ከዛሬ 160 ዓመታት በፊት ባደረጉት የእርስ በእርስ ጦርነት ወቅት እንደተናገረው እርስ በእርሱ ተከፋፈለ ቤት ሊቆም/ሊዘልቅ አይችልም (“A house divided against itself cannot stand”)። አሁን እየታየ ባለው በሕዝብ ውስጥ የሚገኝ ቅሬኔና ትላልቅ ህመሞችና ስንጥቆች ሳቢያ የሁላችንም የጋራ ቤት የሆነችው ሀገረ ኢትዮጵያ በዚህ ሁኔታ ህልውናዋ መቀጠል አይችልም። ፍትሃዊነትና ልከኝነትን (just and fair) ማዕከል አድርገን አገራዊ የፓለቲካ ችግሮቻችንን ካልፈታን፣ ይህ ብዙ ሚሊዮን ዜጎቻችንን መብት አልባና አንገት አስደፊ ያደረገ፣ እስከፊና አሳፋሪ ሁኔታ እንደ አገር አብሮ ለመኖር አያስችለንም። ይህን አስከፊና ከሀገሪቱ ችግሮች አንዱ የሆነ አስተሳሰብና ሕጎች ለመለወጥ ሂደቶች መጀመር አለባቸው። ተጠያቂነት፣ ግልጽነት፣ ስልጣን የተገደበበት፣ ሕዝብ በርካታ አማራጮች ቀርበውለት በነጻ ርዕቱአዊ ምርጫ ሊወስን የሚችልበት የሕግ የበላይነትና ለአገራችን ውስብስብ ችግሮች መድኅን ሊሆን የሚችል ፌደራላዊም ዴሞክራሲያዊም የሆነ የፓለቲካ ሥርዓት ለዘላቂው ለሁሉም የቋንቋና የባህል ማኅበሰቦች፣ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ዜጎች ሊበጅና ሊጠቅም የሚችለው። በአንድ ጎን በየአካባቢው የሚገኙ የማኅበረሰቦች የስልጣን ምንጭነት፣ የባህል ቋንቋቸው እኩልነት የሚረጋገጥበት፣ በሌላ በኩል ደግሞ ሁሉም የኢትዮጵያ ዜጎች በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ሙሉ መብቶች የሚከበሩበት፣ የሚረጋገጡበት መንትዮሽ ግብ ሊያጣጥም፣ ሊያስታርቅ የሚችሉ የመፍትሔ ሃሳቦች፣ ሌሎች መሰል አመራጮችንም ማፈላለግ የአገሪቱ የፓለቲካ ልሂቃንና የተደራጁ ኃይሎች በጥልቀት ሊያስቡበት የሚገባ አንገብጋቢና ከቀዳሚዎቹ የፓለቲካ ችግሮቻችን አንዱ ይመስለኛል።

    የ20ኛ ክፍለ ዘመን ታላቁ የሳይንስ ሊቅ አልበርት አንስታይን (Albert Einstein) ከእምሮዋዊ አቅምና እውቀት፣ የወደፊቱን የማለም ምናባዊ ኃይል የበለጠ ነው (“Imagination is more important than knowledge”) እንዳለው ወቅቱ እውቀት አለን የምትሉ ልሂቃን ምናባዊ አቅማችሁን በመጠቀም የሀገራችንን የፓለቲካ ችግሮችና ተግዳሮቶች በውይይት፣ በድርድር፣ ለመፍታት ማሰብን በረጅሙ ማለምን ይጠይቃችሁሃል። ፓለቲካ የዕድሎች ጥበብ (“politics is the art of the possible”) ጭምር ነው ይባላል። ይህ አሻግሮ ማየትን፣ ተግዳሮቶችን ወደ መልካም ዕድሎች፣ አደጋዎችን ወደ ጥሩ አጋጣሚዎች ለመለወጥ ምናባዊ እቅምን መጠቀምንም የሚጠይቅም ጭምር ስለሆነ ይመስለኛል። ዊኒስተን ቸርችል (Winston Churchill) ታላቅ ከመሆን ጋር ታላቅ ኃላፊነትነትም አብሮ ይመጣል፣ ትልቅ ዋጋም ያስከፍላል (“The price of greatness is responsibility”) እንዳለው የብሄርና የሕብረ ብሄር የፓለቲካ ልሂቃን የሀገራችን የፓለቲካ ኃይሎች ለሀገራዊ ሰላም፣ ለሕዝብ መረጋጋት፣ ለፍትሃዊ የፓለቲካ ሥርዓት ምሥረታ፣ እናንተም ትልቅ ለመሆን ለምትችሉበት፣ በርዕቱአዊ ነጻ ምርጫ አማራጭ የፓለቲካ ፕሮግራሞቻችሁን አቅርባችሁ ካሸነፋችሁ 105 ሚልዮን ሕዝብ ለመምራት ለምትችሉበት ዴሞክራሲያዊ የፓለቲካ ሥርዓት በጋራ መሥርቱ። ቆምንለት ለምትሉት ብሄር/ብሄረሰብም ደኅነትና ሰላም፣ ጥቅምና መብቶች፣ እንዲሁ ለመላው ሕዝብ፣ ለሁሉም ኢትዮጵያውን ዜጎች፣ ለሁላችንም የጋራ ሀገር በታላቅ ኃላፊነት መንገድ ለመንቀሳቀስ መወሰን ብልህነትና አስተውሎት ነው። በታሪክ ፊት፣ በሕግም ፊት፣ በህሊናችሁም ተጠያቂ አያደርጋችሁም። በሰማይም እንዲሁ። ሀገር ከሌለ፣ ሀገር ውስጥ ሰላም መረጋጋት ከጠፉ ስልጣንም፣ ጥቅምም፣ ታላቅነትም፣ ማንም ምንም የሚያገኝበት ሁኔታ ሊኖር እንደማይችል፣ ሁሉም ሊጠፋፋ የሚችልበት ሀገራዊ ትርምስ ውስጥ እንደ ዋዛ ፈዛዛ ሊገባ እንደሚቻል በዛሬ ዘመን የተወለዱ የሊቢያን፣ የሶርያን፣ የመንን ሕዝቦች መከራና ስቆቃ እያዩ ያደጉ ታዳጊ ወጣቶች እንኳን የሚገነዘቡት እውነታ ነው።

    ሀገራችን ኢትዮጵያ የምትገኝበት አጠቃላይ ሁኔታ እጅግ እንደሚያሳስበው እንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ፣ ሰሞኑን በተከሰተው የንጹሃን ዜጎቻችን ሕይወት መቀጠፍ፣ መቁሰልና መፈናቀል እንደሚያሳዝነው አንድ ሰብዓዊ ፍጡር፣ ለአማራ ወይንም ለኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም የቋንቋና የባሕል ማኅበረሰቦች፣ ዜጎች በፍትህ፣ በሕግ የበላይነት፣ በማኅበራዊ ፍትህ፣ በዴሞክራሲ ፌደራላዊ የፓለቲካ ሥርዓት የሚኖሩባት ኢትዮጵያ እውን እንድትሆን የበኩሉን አስተዋጽኦና ትግል እንዳደረገ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ዶ/ር አብይ አህመድ፣ ለምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንንለአቶ ለማ መገርሳለአቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ ሌሎችም ለውጡን የመሩና በመምራት ላይ የሚገኙ የኢህአዴግ አመራሮች ይህን ጉዳይ በጥብቅ እንዲያስቡበት ከሀገሪቱ ልዩ ልዩ ባለድርሻ አካላት፣ የብሔርም/ዘውግም፣ የሕብረ ብሔራዊ የፓለቲካ አመለካከትና ፕሮግራም ያላቸው ልሂቃንና ተጽዕኖ ፈጣሪ ባለድርሻዎች ሁሉ በአግባቡ የሚሳተፉበት ብሔራዊ የውይይት፣ የምክክር መድረኮች ማመቻቸት ሰዓቱ የደረሰ ይመስለኛል። መግባባትና እርቅ የሚደረስበት፣ እንዲሁም ወደ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሊያራምዱ የሚችል ፍኖተ ካርታ በሁሉም ባለድርሻዎች ተሳትፎ ወደ ስምምነት የሚያደርሱ መድረኮች የማመቻቸት ሂደት እንዲጀመር የግሌን ሃሳብ እንደ እንድ ኢትዮጵያዊ ለማቅረብ እወዳለሁ።

    የሀገራችንን ችግሮችና ወቅታዊ ሁኔታ በሚመለከት በማዘጋጀት ላይ ያለሁትን የግሌን ሰፋ ያለ ምልከታ በቀጣይ አቀርባለሁ። ፍትህ፣ ሰላም፣ የሕግ የበላይነት፣ የሕዝብና የሀገርን ጥቅም ማስቀደም በሀገራችን እንዲሰፍን፣ መቻቻልና አብሮ መኖር እንዲለመልም ቸሩ አምላክ ይርዳን!!

    ነአምን ዘለቀ
    ቨርጂኒያ፡ አሜሪካ

    ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለችበት የፓለቲካ ቀውስ የሚያሳስበው ሁሉ ሊያነበው የሚገባ

    Semonegna
    Keymaster

    በተማሪዎች አቀባበል ዙሪያ ከባሕር ዳር ከተማ ወጣት ማህበራት ጋር ምክክር ተደረገ

    ባህር ዳር (ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ) – የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች በ2012 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ወደ ዩኒቨርሲቲው ለሚመጡ ተማሪዎች አቀባበል በማድረግ ዙሪያ ከዘጠኝ በላይ ከሚሆኑ የባህር ዳር ከተማ ወጣት ማኅበራት ጋር በዩኒቨርሲቲው የጥበብ ህንፃ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ምክክር አደረጉ።

    የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርሜሽን ስትራቴጂክ ኮምንኬሽ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዘውዱ እምሩ እንዲሁም የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ ገድፍ የባህር ዳር ወጣቶች በዩኒቨርሲቲው ፀጥታ ጉዳይና የተማሪዎችን ደህንነት ከመጠበቅ አንፃር እያበረከቱት ያለውን አስተዋፅኦ አድንቀዋል። አቶ ብርሃኑ አክለውም ዩኒቨርሲቲውም የሥራ ዕድሎችን በመፍጠርና የወጣቶችን አቅም በመገንባት የሚጠበቅበትን እንደሚያደርግ ጠቁመው ወጣቶችም የባህር ዳር ከተማና የዩኒቨርሲቲው ስም በበጎ እዲነሳ አሁንም ከዚህ ቀደም ሲያደርጉት የነበረውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አደራ ብለዋል።

    ከባህር ዳር ከተማ የተወጣጡ የወጣት ማኅበራት ተወካዮች እንደገለጹት፥ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የሞባይልና የላፕቶፕ ዘረፋዎች የሚደርስባቸው ተብለው የተለዩ ዋና ዋና የሚባሉ መስመሮች የመንገድ መብራቶቻቸው የጠፉ እና አንዳንዶችም መስመር ሊዘረጋላቸው የሚገባ ስለሆነ ዩኒቨርሲቲው ከመብራት ኃይል እና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እንዲሠራ ጠይቀዋል። አክለውም፥ ወጣቶቹ በባህር ዳር ከተማም ሆነ በዩኒቨርሲቲው ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር እንዳይኖር ተግተው እንደሚሠሩ ተናግረዋል። በመጨረሻም፥ በተማሪዎች አቀባበል ዙሪያ ለተነሱት ጥያቄዎች በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች መላሽ ተሰጥቷል።

    ምንጭ፦ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    Anonymous
    Inactive

    አብረው ማልቀስ እንጅ አብረው መቆም የማይችሉ ማሽንኮች ተፈልፍለው ሀገሬን ዕረፍት ነሷት። ለቅሶ ቤት ለመድረስ አዛኝ ቅቤ አንጓች ሁላ ከአለባበሱ እስከ አነጋገሩ አሳምሮ ይግተለተል እንደሆነ እንጅ፣ መቃብር ላይ ለመላቀስ ቀብር ለማስፈጸም ይደምቃል እንጅ ቁም ነገር ላይ ነጥፎ በጠመንጃ መፈላለጉን ትውልዱ ጀብድ አድርጎታል። እየሳቁ መግደል ሕገ-መንግሥቱ ሆኗል። የመግለጫ ቃል በማዥጎድጎድ የሸፍጥ ኑሮውን ተክኖታል።

    ሀገሬን ምን ነካት?
    አባይነህ ካሴ (ዲ/ን)

    ከሰቀቀናሟ ዕለተ ቀዳሚት ሰኔ 15 እስከ ዛሬዋ ዕለተ ሰኑይ ሰኔ 17 ቀን 2011 ዓ.ም. ሕይወታቸውን በጥይት ላጡት ሁሉ እግዚአብሔር ነፍሳቸውን በቅዱሳን እቅፍ በገነት ያኑርልን፤ ለሐዘንተኞች በሙሉ ሁሉም ሟቾች የኢትዮጵያ ቤተሰቦች ናቸውና ለኢትዮጵያውያን ሁሉ አረጋጊው መንፈስ ቅዱስ አጽናኝ መልአክን ይዘዝላችሁ። ሞት ማንም ይሞታል፤ ብርቆች ሲሞቱ ግን ራሱ ሞት ያነጋግራል።

    ከሩቅ ከአድማሱ ሥር የብርሃን ብልጭታ ሲታየን ‘ሊነጋ ነው’ ስንል፣ የሳቀልንን ወገግታ ተከትለን በተስፋ ዓለም ስንፏልል፣ ደረስንብህ ስንለው ብርሃናችን ወዴት ሔደብን? በጥሩር ፀሐይ ሰማይ ሥር የውኃ ሽታ ያዘለ ነጭ ባዘቶ ደመና ሊያዘንብልን ነው ስንለው እንዳንጋጠጥን መና ቀረ። በርኅቀት ሳይሆን በርቀት ተሰወረ። እኛን ቀርቶ ሊቃውንቱን አደናገረ። መጣ ያልነው እጃችን ገባ ያልነው ሁላ እየጣለን በረረ። ማር ያልነው ከምን ጊዜው መረረ፣ ወተት ስንለው የነበረው ከመቼው ጠቆረ፣ ሰላም ምነው ኢትዮጵያችንን አፈረ?

    ‘እኔ፣ እኔ፣ እኔ’ ከሚለው ባሕር ‘እኛ፣ እኛ፣ እኛ’ የሚል የቡድን ውሽንፍር ውስጥ ገባንና ኢትዮጵያን፣ ሀገሬን ረሳናት። እርሷም እነዚህ ከንቱዎች እንኳን ለእኔ ለራሳቸው የማይሆኑ ገልቱዎች ብላ መታዘቡን ቀጥላለች። የደሟን እንባ ወደ ውስጧ ሕቅ ብላ ታነባለች። ከላይ ከላይ ደማቅ ፈገግታ እያሳየች። የጣቷ አንጓዎች እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ ሲሉ ሲገዳደሉ ዝም ብላ ታለቅሳለች። የጠጒሮቿ ዘለላዎች በራሷ ላይ ሲሻኮቱ በሐዘኗ በግናለች፤ በክፉ ጦር ልቧን ተወግታለች። ሀገሬን ምን ነካት? ምንስ ነው የሚበጃት?

    አብረው ማልቀስ እንጅ አብረው መቆም የማይችሉ ማሽንኮች ተፈልፍለው ሀገሬን ዕረፍት ነሷት። ለቅሶ ቤት ለመድረስ አዛኝ ቅቤ አንጓች ሁላ ከአለባበሱ እስከ አነጋገሩ አሳምሮ ይግተለተል እንደሆነ እንጅ፣ መቃብር ላይ ለመላቀስ ቀብር ለማስፈጸም ይደምቃል እንጅ ቁም ነገር ላይ ነጥፎ በጠመንጃ መፈላለጉን ትውልዱ ጀብድ አድርጎታል። እየሳቁ መግደል ሕገ-መንግሥቱ ሆኗል። የመግለጫ ቃል በማዥጎድጎድ የሸፍጥ ኑሮውን ተክኖታል።

    በተመቸ ግርድፍ ቃል ወንድምን በመዝለፍ ድንበር በመዝለል ከልክ በላይ በማለፍ አጥንት የሚወጋ የቃል ጦር በማላጋት እና በመወራወር ሀገር መቁሰሏን ማን የወደዳት ተረዳላት? ንክንኩ ድንጋይ ይፈልጣል፤ የመከራ መዓት በአፍላጋቱ ይጓፍጣል፤ አላውቅም የሚል ጠፍቶ ሁሉም ሁሉን ያውቃል። አዎ ሁሉ ዐዋቂ ሲሆን ሁሉም ይታመማል ያን ዕለት ያን ሠዓት መድኃኒት ይጠፋል።

    ለሞቱት አሟሟት የሰማነው ትርክት ልብ አያሳርፍም፤ ገና አበቅ አለበት። እርሱ ሲጠራ የሚታይ ለጊዜው ግን የተሸፈነ እውነት እንዳይኖር ያሰጋል። ከአንድ ወገን ብቻ የሚሰማ በጥፍር የሚያቆም ንግግርም ቢሆን ታማኝነቱ ምን ጊዜም ከአጠራጣሪነት አይዘልልም። ጊዜ እያወጣ የሚያሰጣው እውነት ይኖራል።

    ወታደር ዘር የለውም፤ ‘እኔ የኢትዮጵያ ወታደር ነኝ’ ሲል የነበረውን መልካም ወላዲቷ አምጣ የወለደችውን ጀግና እንደዋዛ ማጣት አለው ብዙ ንዴት፣ አለው ብዙ ቁጭት። ገዳይ የተባሉት ወይ በተኩስ ልውውጥ፣ ወይ ራስን በመግደል እየተባለ ሞታቸው ይነገራል። አይታመንም ባይባልም ተጠግቶ ላየው ምኑም አያሳምንም።

    አንደኛ፡- ብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ባሕር ዳር አጠገብ ዘንዘልማ በሚባለው አካባቢ መገደላቸው መነገሩ ጥርጣሬውን ከፍ ያደርገዋል። እኒህ ሰው ተሳዳጅ (fugitive) ሆነው ባለበት ጊዜ አብሯቸው ከነበሩም እንኳ ከጥቂት ተከታዮች በስተቀር ብዙ አጃቢዎች እንደማይኖሯቸው ይታወቃል። ዘንዘልማ ከባሕር ዳር ከተማ ዓባይን ተሻግሮ ያለ አካባቢ እንደመሆኑ በርከት ያለ አጃቢ ይዘው ሊሻገሩ ይችላሉ ብሎ መገመት አይቻልም። በሦስት ምክንያት፥ አንደኛ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር ባለችው ከተማ ውስጥ ተሰውረው ቆይተው ነበርና። ሁለተኛ በድልድይ የሚሻገሩ ከሆነ ከፍተኛ ጥበቃ እንደሚደረግበት በመገመት በርከት ብሎ ለማለፍ ቀርቶ ራሳቸው ላለፉበት መንገድ እንኳ ያነጋግራል። ሦስተኛ በድልድይ ካልተሻገሩ ወይ በዋና ወይ በታንኳ ምናልባትም በጨለማ ዓባይን አቋርጠው ሊሆን ይችላል። ይህም በርከት ለማለት የሚመች አይደለም።

    እኒህ ሰው የነገሩ ሁሉ መነሻ እና አቀነባባሪ ተደርገው ስማቸው እየተነሳ ይገኛል። እንደዚህ ያለውን ቀንደኛ በከበባ መያዝ ሲገባ ወደ መግደል የተሔደበት መንገድ ሌላ ጥያቄ ከማስነሳት አያድንም። በዚህ ላይ ሰውዬው ሲታኮሱ ጥይት አልቆባቸው እንደነበር መረጃ ተሰጥቷል። ይህ ከሆነ ደግሞ አስጊነታቸውን በብዙ ደረጃ ቀንሶት ነበርና ለመያዝ የበለጠ ምቹ እንደነበር ያመላክታል። የተባሉት ሁሉ ትክክል ከሆኑ መረጃ ማጥፋት ዓይነተኛ ተልዕኮ ለነበረው ዘመቻ (operation) ብቻ የተፈጸመው ድርጊት ትክክል ይሆናል። ሰውዬው በአካል ቢያዙ የሚያወጡት መረጃ እንደሚኖር በመስጋት በሕይወት ከሚቆዩ ሞታቸውን ማቅረቡ ተመርጦ ሊሆን ይችላል። ራሳቸውን ገደሉ ሳይሆን የተባለው በተኩስ ልውውጥ ተገደሉ ነው። ቀባብቶ ማምጣት ሊኖር ይችላል። እውነትን መልሶ በማቋቋም ‘አይ ሰውየው ራሳቸውን ነው የገደሉት’ የሚል ዜና ከመጣ ደግሞ ነገሩ ዘወርዋራ የሆነበትን ምክንያት ማወቁ ይሻላል።

    ሁለተኛ፡- የአቶ ምግባሩ ከበደ ሞት። ሌላው ተስፋ ሊሰጥ ወደ እውነተኛው መረጃ ሊያደርስ ይችል የነበረው የምግባሩ ከበደ ሞት መረጃ የማጥፋቱን ሥራ አቀላጥፎታል ብሎ ላለማሰብ የሚከለክል ነገር የለበትም። ይህ ሰው በሠዓታት ውስጥ ቅርብ ሀገር እስራኤል ደርሶ ሊታከም ይችል እንደነበር መገመት የማንችልበት ዘመን ላይ አይደለንም። መሞኛኘት እንዳይሆን እንጅ ወዲያው የጸጥታ ቁጥጥር እንደተደረገ ሲነገረን አምሽቷል። በሄሊኮፕተር በታገዘ መንገድ ለተሻለ ሕክምና መወሰድ ነበረባቸው። ይህ ለምን አልሆነም?

    ሦስተኛ፡- የጀኔራል ሰዓረ መኮንን ጠባቂ ሞት*። ‘ተይዘዋል’ እየተባለ በየዜና ማሠራጫው ሲነገር የነበረው ሰው ‘ራሱን ገድሏል’ ወደሚል ዜና የተቀየረበት መንገድ እንድንጠረጥር እንጅ እንድንተማመን የሚያደርገን አይደለም። ራሱን የገደለን ሰው ተይዟል ብሎ ዜና የሚሠራባት ምክንያት ሴራን (conspiracy) ያሻትታል እንጅ ቅቡልነት አያስገኝም። [* የአገሪቱ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄነራል ሰዓረ መኮንንና ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንን ጄነራል ገዛኢ አበራን ተኩሶ ገደለ የተባለው የጄነራል ሰዓረ ጠባቂ ራሱን ያጠፋው ወዲያው መሆኑን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር እንደሻው ጣሰው ዛሬ በሰጡት መግለጫ መናገራቸው ይታወሳል። ማምሻውን ደግሞ ፌደራል ፖሊስ በብሄራዊው ቴሌቪዥን ኢቢሲ ራሱ የሰጠውን መግለጫ አስተባብሎ ጠባቂው በሕይወት እንደሚገኝ አስታውቋል። – ቢቢሲ ዜና አማርኛ]

    አራተኛ፡- በዚያ ጭንቅ ሰዓት ጀኔራል ሰዓረ ቤት መሆናቸውም ሌላው ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው። ከቤቱ ሆኖ “የመንግሥት ግልበጣ” የተባለን ነገር የሚከታታል ጀኔራል አለ ብሎ ለመናገር አያስደፍርም። ሰውዬውም እንደዚህ ዓይነት ጠባይ የለባቸውም፤ ሀገር ሳታርፍ የሚያርፉ ሰው አልነበሩምና። በቢሯቸው ሆነው ከፍተኛ የአመራር ሥራ ሊሠሩ በሚገባበት ሠዓት ቤታቸው የተኙበት ምክንያት ምንድን ነው? እውን ነገሩን አውቀውት ነበርን?

    አምስተኛ፡- ጉምቱዎቹ ባለሥልጣናት ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን በግል ጉዳይ፣ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ገዱ አንዳርጋቸው ለሥራ ብለው አንዱ አሜሪካ ሌላው ጀርመን እግራቸው በረገጠበት ቀን የመሆኑ ግጥምጥሞሽስ እንዴት በዋዛ ይታለፍ ዘንድ ይችላል?

    እነዚህ ሁሉ ሲጠቀለሉ አቅጣጫቸው ሌላ ያሳያል። ከተነገረን ምህዋር በዘለለ ሁኔታ አንዳች የተቀነባበረ ሴራ ካልነበረ በቀር ወንድም በወንድሙ ላይ እንደዚህ ዓይነት ጭካኔ ያሳያል ብሎ መገመት ይከብዳል። ገና ደብዛዛ መረጃ ላይ ተቀምጠን ጣት ወደ መጠቋቆሙ መሔዱ አያዋጣም። ይሄኛው መንገድ ሌላ ጥፋት ያመጣልና።

    በዶ/ር አምባቸው መኮንን፣ በምግባሩ ከበደ፣ በእዘዝ ዋሴ፣ በጀኔራል ሰዓረ መኮንን፣ በብርጋዴር ጀኔራል ገዛኢ አበራ፣ በብርጋዴር ጀኔራል አሳምነው ጽጌ ሞት በእጅጉ አዝነናል። ስማቸው ባልተነገረን በሌሎችም ሰዎች ሞት በእጅጉ አዝነናል። በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን የምትታየን ኢትዮጵያ ናት። ቁስል የሆንባት እስኪ እንራገፍላት።

    ምንጯ ደፈረሰ እንጅ አልነጠፈም። እስኪጠራ መታገስ ዋጋ ቢያስከፍልም ድፍርሱን ጠጥቶ ከመታመም ታግሶ ጥሩውን መጠጣት ጥምን ይቆርጣል፣ ጤናም ይጠብቃል። በደፈረሰ ውኃ ውስጥ ምን እንዳለ ማወቅ አይቻልም። ሲጠራ ግን ይለያል። የሦስቱን ቀን ሁናቴ በጥሞና እንየው፣ ድፍርሱን ለማጥራት ጊዜ እንስጠው። ለመኮነኑ አንቸኩል። ለመቧደንም አንጣደፍ። እነዚህ ከላይ የተነሡት እና ሌሎችም ጥያቄዎች ሲመለሱ የሚወገዘው ይወገዛል።

    ይህ ጥቁር ደመና መግፈፉ አይቀርም። እስከዚያው ግን ጨለማ መንገሡን ተቀብሎ ለብርሃኑ መትጋት መውጣት እና መውረድ ብቻ ነው አማራጩ። የዘሩን ዘጋተሎ አምዘግዝጎ ወዲያ ጥሎ፣ የሀገርን ሕመም ለመታመም አብሮ ቆስሎ የእናት ልጅ የእናቱን ልጅ ሲደክመው አዝሎ፣ ወድቆ እንዳይቀር ውኃ በልቶት ጉልበቱ ዝሎ፣ እየቆረሰ አጉርሶ እየቀደደ አልብሶ፣ ወደ ብርሃን መውጫው ሥር ካልተጓዘ በማለዳ፣ ተከፍሎ አያልቅም የእናት ሀገር የአደራ ዕዳ።

    አባይነህ ካሴ (ዲ/ን)

    ሀገሬን ምን ነካት?


    Anonymous
    Inactive

    በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ለአንድ ተማሪ ሞት ምክንያት የሆነውን ድርጊት የከተማው ነዋሪዎች እና የክልሉ መንግስት አወገዙ።
    —-

    ባሕር ዳር (አብመድ) – በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ለአንድ ተማሪ ሞት ምክንያት የሆነውን ድርጊት የከተማው ነዋሪዎች እና የክልሉ መንግስት አወገዙ። የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች ስለ ችግሩ እና ስለ ቀጣይ የተማሪዎች ሰላም ተወያይተዋል።

    ድርጊቱን ያወገዙት ተወያዮቹ ችግር ፈጣሪዎቹን በማጋለጥ ለጸጥታ አካላት እንደሚሰጡም ቃል ገብተዋል። እስካሁን በድርጊቱ የተጠረጠሩ ተማሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ነው በውይይቱ የተገለፀው።

    ውይይቱን የተከታተለው ጋሻዬ ጌታሁን እንዳደረሰን መረጃ ሌሎች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የጸጥታ ስጋት እንዳይደርስባቸው ከጎናቸዉ እንደሚሆኑ ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል።

    በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ እሁድ ግንቦት 18/2011 ዓ.ም የአንድ ተማሪ ህይወት ሲያልፋ ሶስት ተማሪዎች ቆስለዉ በህክምና ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል። የችግሩ መንስኤ እስካሁን እንዳልታወቀም ነው ማብራሪያ የተሰጠው።

    የክልሉ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤትም የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና ሕዝብ በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪ ላይ በደረሰዉ የሕይወት መጥፋት ከልብ ከማዘን ባሻገር ድርጊቱን አጥብቀው እንደሚያወግዙት ገልጿል።

    የክልሉ መንግሥት ከሕዝቡና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ጥቃት አድራሾችን ተከታትሎ ለሕግ እንደሚያቀርብም ነው ያስታወቀው።

    ለሟች ቤተሰቦች፣ ለጓደኞቹና ለዩኒቨርሲቲው ማሕበረሰብም መጽናናትን ተመኝቷል።

    ምንጭ፦ አብመድ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    Semonegna
    Keymaster

    ለመሆኑ እንቦጭን ለማስወገድ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎች የሚሠሩ የአረም ማስወገጃ ማሽነሪዎች ምን አገልግሎት እየሰጡ ነው? አሁን ሥራ ላይ ያሉት የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽኖች ቁጥርስ ምን ያክል ነው?

    ባሕር ዳር – በጣና ኃይቅ ላይ የተከሰተውን የእንቦጭ አረም ለማስወገድ አራት ማስወገጃ መንገዶች በአማራጭነት አገልግሎት ላይ እንዲውሉ ምክረ-ሐሳብ ይቀርባል። ከእነዚህ ማስወገጃ መንገዶች እስካሁን ሁለቱ (የሕዝብ ጉልበት እና ማሽነሪዎች) ጣና ሐይቅ ዙሪያ አገልግሎት ላይ እየዋሉ ነው።

    ለመሆኑ እንቦጭን ለማስወገድ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎች የሚሠሩ የአረም ማስወገጃ ማሽነሪዎች ምን አገልግሎት እየሰጡ ነው? አሁን ሥራ ላይ ያሉት የማሽኖች ቁጥርስ ምን ያክል ነው? ስንል የአማራ ክልል የአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣንን ጠየቅን።

    በዚህ ወቅት አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት ሁለት ማሽኖች ብቻ እንደሆኑ የነገሩን በአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን የጣና ሐይቅ ሥርዓተ ምኅዳር ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ መዝገቡ ዳኘው ሁለቱ ማሽኖች ካናዳና እሥራኤል ሀገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና በአማጋ ኃላፊነቱ ተወሰነ የግል ማኅበር ድጋፍ የተገዙ ናቸው ብለዋል።

    “በባሕር ዳር እና ጎንደር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት (ዩኒቨርሲቲዎች) እየተዘጋጁ ያሉ የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽኖች መኖራቸውን አውቃለሁ” ያሉት አቶ መዝገቡ፥ እስካሁን ድረስ ግን ከተቋማቸው ጋር ርክክብ ፈፅመው ወደ ሥራ አለመግባታቸውን ገልጸዋል።

    አብመድ የተሰሩት ማሽኖች ለምን ርክክብ ተፈፅሞ አገልግሎት መስጠት አልጀመሩም ሲል ሁለቱን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አነጋግሯል። የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ከሙላት ኢንድስትሪያል ኢንጂነሪንግ ጋር በመተባበር የሠራው የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽን ጥቅምት 24 ቀን 2011 ዓ.ም. የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በተገኙበት ቢመረቅም ይህ ዜና እስከሚጠናቀርበት ጊዜ ድረስ አገልግሎት አይሰጥም።

    “ማሽኑ አገልግሎት ለመስጠት ምንም ዓይነት ችግር የለበትም፤ በቅርቡም ለሦስት ወራት ያክል የሙከራ ትግበራ ከተደረገ በኋላ ከሚመለከተው አካል ጋር ርክክብ ይደረጋል” ያሉት የቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ሰይፉ አድማሱ የዘገየው ማሽኑን ለማንቀሳቀስ የሚሠራ ራሱን የቻለ የሰው ኃይል አደረጃጀት ባለመኖሩ ቅጥርና ምልመላ ለመፈፀም ጊዜ በመውሰዱ መሆኑን አስታውቀዋል።

    ከሙላት ኢንዳስትሪያል ኢንጅነሪንግ ጋር በመተባበር ለባለሙያዎቹ ስልጠና ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ያስታወቁት ዶ/ር ሰይፉ ስልጠናው ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ ተግባር እንደሚገቡም ገልፀውልናል። ማሽኑን በዘላቂነት ለማስተዳደርና ሥራውን ለማስተባበር ራሱን የቻለ ተቋማዊ አደረጃጀት እንደሚያስፈልገውም ገልጸዋል።

    በጎርጎራ ወደብ አካባቢ የሚገኘው ሌላው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአረም ማስወገጃ ማሽንም ከአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን ጋር ርክክብ ያልተፈፀመበት ማሽን ነው። የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር ኢንጅነር ሰለሞን መስፍን “ለአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን ርክክብ እንዲፈፀሙ ደብዳቤ ልከናል” ብለዋል። የተዘጋጀው ማሽን አገልግሎት ለመስጠት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ፥ ማሽኑን የሚያንቀሳቅስ የሰው ኃይል (ኦፕሬተር) ማዘጋጀት የአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን ድርሻ እንደሆነም አስታውቀዋል።

    የአካባቢ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን በበኩሉ ማሽኖቹን ለመረከብና የሰው ኃይል ለመቅጠር በተግር ሲሠሩ ማየት እፈልጋለሁ ብሏል።

    በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና በሙላት ኢንድስትሪያል ኢንጅነሪንግ የተዘጋጀው ማሽን ከ19 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ እንደተደረገበትም ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። በዚህ ሳምንት ውጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ የተገዛ ሌላ የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽን ጣና ሐይቅ ላይ ደርሶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

    ምንጭ፦ አብመድ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የእንቦጭ ማስወገጃ ማሽን


    Semonegna
    Keymaster

    ዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር ደጀን ከተማ ውስጥ (አማራ ክልል) የሚያስገነባው ሲሚንቶ ፋብሪካ አጠቃላይ ወጪው 8.8 ቢልዮን ብር እንደሆነና ግንባታው በ24 ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተጠቁሟል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር በአማራ ክልል ደጀን ከተማ ላይ ሲሚንቶ ፋብሪካ ለመገንባት ከሁለት የውጭ ሀገር ድርጅቶች ጋር የሦስትዮሽ የሥራ ስምምነት ተፈራረመ።

    አክስዮን ማኅበሩ አክስዮን ማኅበሩ ስምምነቱን የተፈራረመው መቀመጫውን ኮፐንሃገን ከተማ (ዴንማር) ያደረገውና ዓለምአቀፍ የምህንድስና (ግሎባል ኢንጂነሪንግ) ኩባንያ ከሆነው “FLSmidth & Co. A/S” እና መቀመጫውን ያንግጆ ከተማ፣ ቻይና (Yangzhou, China) ያደረገው ሌላው ዓለምአቀፍ የምህንድስና ኩባንያ “Hengyuan Group” ጋር አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሸራተን አዲስ ሆቴል ውስጥ ነው ነው። በስምምነቱ መሠረት “FLSmidth & Co. A/S” የግንባታ መሣሪያዎችን ሲያቀርብ፣ “Hengyuan Group” ደግሞ የግንባታውን ሥራ ያከናውናል። የፋብሪካው ግንባታ አጠቃላይ ወጪውም 8.8 ቢልዮን ብር እንደሆነና ግንባታው በ24 ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ተጠቁሟል።

    ቪድዮ፦ በ8.8 ቢልዮን ብር በደጀን ከተማ (አማራ ክልል) የሲሚንቶ ፋብሪካ ሊገነባ ነው።

    የዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር ለሚገነባው ፋብሪካ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውንም የአክስዮን ማኅበሩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል ጠቁመዋል።

    በስምምነቱ ወቅት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝደንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፦ “ይሄ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለክልሉ ልማት ትልቅ አጋዥ ይሆናል የሚል እምነት አለን፤ ስለዚህ ገንቢዎቹም፣ አቅራቢዎቹም፣ ሁላችሁም ደጀን ላይ ይህንን ሲሚንቶ ፋብሪካ ለማፋጠን በምታደርጉት ጥረት የአማራ ክልል ሕዝብና መንግስት ሁልጊዜም ቢሆን ከጎናችሁ ይሆናል” በማለት የክልሉን መንግስት ደጋፍ አረጋግጠዋል።

    የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንም በበኩላቸው የመሠረት ድንጋይ ማስቀመጥ ብቻ ትርጉም እንደሌለውና፣ ይልቁንም በፍጥነት ተገንብተው ወደማምረት ሥራና ለኅብረተሰቡ የሥራ ዕድል ፈጠራ መግባት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

    የሲሚንቶ ፋብሪካው ወደ ሥራ ሲገባ በቀን 5 ሺህ ቶን ክሊንከር እና በዓመት 2.25 ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ እንዲያመርት፣ ለዚህም 655 ሰዎችን በቋሚነት የሚቀጥር ሲሆን፥ ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ሥራ ሲጀምር ደግሞ የሠራተኞቹን ቁጥር ወደ 1,500 ለማሳደግ ታቅዶ እንደሚገነባ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

    ዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር በህዝብና በግል ባለሀብቶች ባለቤትነት በአክስዮን የተቋቋመ የንግድ ድርጅት ነው። ዋና መሥሪያ ቤቱም የአማራ ክልላዊ መንግስት ዋና ከተማ በሆነችው ባሕር ዳር ከተማ ውስጥ ነው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ዓባይ ኢንዱስትሪያል የልማት አክስዮን ማኅበር


    Anonymous
    Inactive

    አቶ በረከት አቶ ታደሰ ባሕርዳር ይዳኛሉ
    የቀድሞዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኢሕድን)ና የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) መሥራቾች አቶ በረከት ስሞዖንና አቶ ታደሰ ካሳ የታሰሩትም፣የሚዳኙትም አማራ ክልል እንደሆነ የክክሉ ባለሥልጣን አስታወቀ።የአማራ መስተዳድር የሥነ-ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ኃላፊ አቶ ዝግአለ ገበየሁ ለጋዜጠኞች እንደነገሩት ሁለቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት የታሰሩት ጥረት የተሰኘዉን የኩባንዮች ስብስብ በማክሰራቸዉ ነዉ።ድሮ ኢሕዴን፣ በመሐሉ ብአዴን፣ በቅርብ ደግሞ አዴፓ በሚሉ ምሕፃረ-ቃላት የሚጠራዉ የአማራ ክልክል ገዢ ፓርቲ የመሠረተዉና የሚቆጣጠረዉ ድርጅት የአስራ-ሠባት አምራችን ነጋዴ ኩባንዮች ባለቤት ነዉ።

    አውዲዮውን ያዳምጡ።
    Deutsche Welle

    Semonegna
    Keymaster

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለተለያዩ ትምህርት ቤቶች ከሚያደርገው ድጋፍ በተጨማሪም በሌሎች የማኅበረሰብ-አቀፍ አገልግሎቶች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ዩኒቨርሲቲው አቅዶ እየሠራ መሆኑን ተገልጿል።

    ጂንካ ከተማ፣ ደቡብ ኦሞ ዞን (ሰሞነኛ) – ጂንካ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ተገንብተው በ2010 ዓ.ም. ወደ ሥራ ከገቡት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አንዱ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው ምንም እንኳን ከተመሰረተ አጭር ጊዜ ቢሆንም የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት በርካታ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል።

    ዩኒቨርሲቲው በማኅበረሰብ-አቀፍ አገልግሎት (community-based service) በደቡብ ኦሞ ዞን ውስጥ ለሚገኙ 18 ሁለተኛ ደረጃ እና አንድ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በጥቅሉ ለ19 ትምህርት ቤቶች 510 ኮምፒዩተሮችን ከአንድ ደርጅት እንዲሁም በውጭ ሀገር ከሚኖር አንድ የአካባቢው ተወላጅ ጋር በመተባበር ለእያንዳንዳቸው ሃያ አምስት፣ ሃያ አምስት ኮምቲዩተሮችን ለትምህርት ቤቶቹ የሰጠ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕ/ር ገብሬ ይንቲሶ ገልጸዋል።

    ፕሬዚዳንቱ አክለውም እነዚህ ኮምፒዩተሮች ተማሪዎቹ ከቴክኖሎጂ ጋር እንዲተዋወቁ ከማድረጋቸውም በተጨማሪ በሁሉም ኮምፒዩተሮች ላይ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር የሚያዘጋጃቸው የመማሪያ መጽሐፍት እና ሌሎች አጋዥ ሊሆኑ የሚችሉ ሶፍትዌሮች የተጫኑባቸው በመሆኑ ተማሪዎቹ በቀላሉ የሚፈልጉትን ለማግኘት እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ለICT (information, communication and technology) እና ሂሳብ መምህራን በICT አጠቃቀም ዙሪያ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል ብለዋል ፕሬዚዳንቱ ።

    ድጋፍ የተደረገላቸው ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው አዲስ የተከፈተ ቢሆንም ለየትምህርት ቤቶቹ የተደረገው ድጋፍ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከማሳለጥ አንፃር ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ነው ያሉ ሲሆን፥ በቀጣይ ትምህርት ቤቶችን በመደገፍ የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ ዩኒቨርሲቲው የራሱን አስተዋጽኦ አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

    ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለትምህርት ቤቶች ከሚያደርገው ድጋፍ በተጨማሪም በሌሎች የማኅበረሰብ-አቀፍ አገልግሎቶች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ዩኒቨርሲቲው አቅዶ እየሠራ መሆኑን የገለፁት የዩኒቨርሲቲው ቢዝነስ ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ ነፃነት ይርጉ ሲሆኑ ከብት በማደለብ፣ በከብቶች ህክምና፣ በዶሮ እርባታበንብ እርባታ፣ በአሳ እርባታ በመሳሰሉት ውጤታማ ሥራዎችን ለመሥራት አቅዶ በተግባር እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አስረድተዋል።

    ምንጭ፦ የትምህርት ሚኒስቴር
    ——
    See also:

    ትምህርት ቤቶች


    Semonegna
    Keymaster

    የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በንሳ ዳዬ ካምፓስ ካለው ርቀትና የመሬት አቀማማጥ አኳያ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ራሱን ወደቻለ ዩኒቨርሲቲ ሊያድግ የሚችል በመሆኑ ግንባታዎቹ ይህንኑን ታሳቢ አድርጎ የተካሄዱ እንደሆነ ታውቋል።

    ሀዋሳ (ሰሞነኛ)– ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ያቋቋመውና ላለፉት 4 ዓመታት በግንባታ ሂዳት ላይ የነበረው የበንሳ ዳዬ ካምፓስ ጥቅምት 30 ቀን 2011ዓ.ም. ወደ ካምፓሱ ለተመደቡ 340 አዲስ ገቢ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል በማድረግ በይፋ ሥራውን ጀምሯል።

    በበንሳ ወረዳ ዳዬ ከተማ ውስጥ ወደተገነባው ካምፓስ ተማሪዎቹ በመጡበት ጊዜ በአከባቢው ማኀበረሰብ ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አቶ አያኖ በራሶ በቦታው በመገኘትለተማሪዎቹ የዩኒቨርሲቲው አባልነታቸውን አረጋግጠውላቸዋል።

    አቶ አያኖ ለተማሪዎች፣ ለአካባቢው ህብረተሰብ እና ለእንግዶች ባስተላለፉት መልዕክት መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በያዘው የትኩረት አቅጣጫ ካምፓሱ የተገነባ ሲሆን ሙሉ በሙሉ ባይጠናቀቅም የሰው ሃይልና አስፈላጊ ቁሳቁሶች በመሟላታቸው ወደ ሥራ መገባቱን አስረድተዋል።

    በንሳ ዳዬ ካምፓስ ካለው ርቀትና የመሬት አቀማማጥ አኳያ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ራሱን ወደቻለ ዩኒቨርሲቲ ሊያድግ የሚችል በመሆኑ ግንባታዎቹ ይህንኑን ታሳቢ አድርጎ የተካሄዱ እንደሆነ ያስታወቁት ፕሬዝዳንቱ፥ ተማሪዎች፣ ሠራተኞችና የአከባቢው ማኀበረሰብ እንደግል ንብረታቸው መንከባከብና ለመጭው ትውልድ የማስተላፍ ግዴታ እንዲወጡ አሳስበዋል።

    አዲስ የተመደቡ ተማሪዎችም ከቤተሰብ ተለይተው የመጡበትን ዓላማ በማንገብ ጊዜያዊ ተግዳሮቶችን በመቋቋም፣ ከአልባሌ ሱሶች (እና ድርጊቶች) በመራቅና በርትቶ በማጥናት ከቤተሰብና ሀገር የተጣለባቸውን አደራ ለመወጣት ራሳቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸው አቶ አያኖ በራሶ አስገንዝበዋል።

    የካምፓሱ ማኔጅንግ ዳይሬክቴር አቶ ገነነ ካቢሶ በበኩላቸው ካምፓሱ በእርሻ ሜካናይዜሼንና በመምህራን ስልጠና የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን ተቀብሎ የሚያሰለጥን ሲሆን፥ በተማሪዎቹ በሚካሄዱ አሳታፊና ችግር ፌች ምርምሮች የአከባቢውን ማሀበረሰብ ያሳተፈ እንዲሆን ህብረተሰቡ እንዲተባበር ተከታታይ ስልጠናዎች የሚሰጡ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

    በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንቶች፣ የበንሳ ዳዬ ከተማ፣ የአከባቢው ቀበሌ ገበሬ ማኀበራት አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና ከአከባቢው ማኀበረሰብ የወጣቶችና ሴቶች ተወካዮች መገኘታቸው ታውቋል።

    ምንጭ፦ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    በንሳ ዳዬ ካምፓስ

    Semonegna
    Keymaster

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ ባስገነባው የህክምና ማዕከል ምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ ለዓመታት ያስተማራቸውን 331 የህክምና ዕጩ ምሩቃን እና በተለያዩ መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 2ሺህ የድህረ ምረቃ መርሀ ግብር ተማሪዎችን ያስመርቃል።

    ጅማ (ሰሞነኛ)– ጅማ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የፌድራልና የክልል መንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የህክምና ማዕከሉን ኅዳር 29 ቀን 2011 ዓም እንደሚያስመርቅ ተዘግቧል።

    የህክምና ማዕከሉ 800 (ስምንት መቶ) አልጋዎች ያሉት ሲሆን፥ በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍል ከ20 ሚሊየን በላይ ሰዎች የህክምና አገልግፍሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው ተብሏል። ማዕከሉ እንደ ደቡብ ሱዳን ላሉ ጎረቤት ሀገራትም አገልግሎት ለመስጠት ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ መሆኑን ተነግሯል።

    ዩንቨርሲቲው ያስገነባው ይህ የህክምና ማዕከል በህክምና እና ጤናው ዘርፍ የምርምር፣ የማስተማሪያ፣ እንዲሁም የማኅበረሰብ አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚያስችል መሆኑም ነው የተገለጸው። በዚህም ጅማ ዩኒቨርሲቲ በሀገሪቱ ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ሲነጻጸር ልቆ የሚታይበትን የማኅበረሰብ ተኮር (community-based) ትምህርትና ምርምር ይበልጥ ያገለብትለታል ተብሎ ይታመናል።

    Ethio-American Doctors Group (EADG): Building a regional healthcare system & medical tourism

    ዩንቨርሲቲው በህክምና ማዕከሉ የምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ ለዓመታት ያስተማራቸውን 331 የህክምና ዕጩ ምሩቃን እና በተለያዩ መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 2ሺህ የድህረ ምረቃ መርሀ ግብር ተማሪዎችን እንደሚያስመርቅም ታውቋል።

    በተመሳሳይ መልኩ ዩንቨርሲቲው ያስገነባው 40 ሺህ ያህል ተመልካቾችን ማስተናገድ የሚችለው ስታዲየም፣ ሲቭክ አዳራሽ፣ መንገዶችና ሌሎች የመሠረተ ልማት ሥራዎች ይመረቃሉ ተብሏል። የሲቪክ አደራሹ በርካታ ተሰብሳቢዎችን በአንዴ የሚያስተናግድና የተለያዩ ኮንፈረንሶችን በተመሳሳይ ጊዜ ለማካሄድ የሚያስችሉ የተለያዩ ክፍሎች እንዳሉትም ተነግሯል። ከዚህ ጋር ተያይዞ እንደተዘገበው ይህ የሲቭክ አዳራሽ ከተማዋን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ ስለመሆኑም ነው የተገለጸው።

    ምንጭ፦ ኢቢሲ / ኤፍ.ቢ.ሲ. / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ማዕከል


    Semonegna
    Keymaster

    ዶ/ር ሂሩት ወልደማርያም በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በአማራ እና በኦሮሞ ብሄር ተማሪዎች መካከል በተነሳው ግጭት የሶስት ተማሪዎች ህይወት ማለፉን ገልፀው፥ የተለየ ፍላጎት ያላቸው ኃይሎች በተማሪዎች መካከል የብሄር ግጭት እንዲነሳ በማድረግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከማስተጓጎል በላይ ለስው ህይወት መጥፋት ምክንያት መሆናቸውን ተናግረዋል።

    አዲስ አበባ (የትምህርት ሚኒስቴር) – በዩኒቨርሲቲዎች ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር አጠቃላይ ማህበረሰቡ ከአካባቢው አስተዳደር ጋር በጋራ እንዲሠራ ተጠየቀ።

    በአሁኑ ወቅት በመላ ሃገሪቱ እየተካሄደ የሚገኘውን ለውጥ ለመቀልበስ የሚፈልጉ ኃይሎች ፊታቸውን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም በማዞር ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደቱን በማወክና ግጭቶች እንዲፈጠሩ በማድረግ ግጭቶቹም የብሄር ግጭት መልክ እንዲይዙ በማድርግ ከፍተኛ ሁከት እና አለመረጋጋት በዩኒቨርሲቲዎች እንዲቀሰቀስ እያደረጉ መሆኑ ተደርሶበታል።

    ይህንኑ ሰሞኑን በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች የተከሰተውን አለመረጋጋትና ሁከት አስመልክቶ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሯ ዶ/ር ሂሩት ወልደማርያም ኅዳር 12 ቀን 2011 ዓ.ም በፅህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ “ዩኒቨርሲቲዎች ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ የተለያየ አስተሳሰብና ክህሎት ያላቸው ወጣቶች የተሰባሰቡበት ቦታ መሆኑን ገልፀው፥ እነዚህን ወጣቶች ለተለያየ የፖለቲካ አጀንዳ ማስፈፀሚያ ለማድረግና እርስ በእርሳቸው ያለመተማመንና በመካከላቸውም የብሄር ግጭት በማስነሳት የመማር ማስተማር ሥራውን ከማስተጓጎላቸውም በላይ በግጭቱ ውድ የሆነውን የሰው ህይወት እንዲጠፋ ምክንያት ሆነዋል“ ብለዋል።

    ዶ/ር ሂሩት አያይዘውም ሰሞኑን በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በአማራ እና በኦሮሞ ብሄር ተማሪዎች መካከል በተነሳው ግጭት የሶስት ተማሪዎች ህይወት ማለፉን ገልፀው፥ በግጭቱ ህይወታቸውን ላጡ ውድ ተማሪዎቻችን የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገልፀው ለተማሪ ቤተሰቦችና ለማህበረሰቡ መፅናናትንም ተመኝተዋል።

    አሁን የሚስተዋለውን ችግር ለመፍታትም ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፤ የዩኒቨርሲቲ ቦርድ አባላት፤ የሁለቱም ብሄር ተወካዮችና ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ጋር በመሆን የዕርቅና ሰላም የማስፈን ሥራ ለመሥራት ወደ ዩኒቨርሲቲው እንደሚሄድ ሚኒስትሯ ጨምረው ገልፀዋል።

    ዩኒቨርሲቲዎች የዕውቀት የክህሎትና የአዳዲስ ሃሳቦች ማፍለቂያ ተቋሞች መሆናቸውን የገለፁት ሚኒስትሯ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ሙሉ ጊዜያቸውን ለትምህርትና ለምርምር በማዋል የመጡበትን ዓላማ ማሳካትና በቆይታቸውም ነገሮችን በደንብ የሚያስቡና አንዳንድ ወደ ጥፋት የሚሄዱ ተማሪዎችንም ወደ በጎነት የሚመልሱ ሊሆኑ እንደሚገባቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

    በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምቹና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር የአካባቢው ማህበረሰብ የአስተዳደር አካላትና የፀጥታ አካላትም በጋራ ሊሠሩ እንደሚገባ በመግለጫው ተካቷል።

    ምንጭ፦ የትምህርት ሚኒስቴር

    ተጨማሪ ትምህርት ተኮር ዜናዎች

    የመማር ማስተማር ሂደት

    Semonegna
    Keymaster

    ግንባታው ስድስት ዓመታትን የፈጀው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቀን 2000 የሚሆኑ ታካሚዎችን ሊያስተናግድ የሚችል፣ 11 የቀዶ ሕክምና ክፍሎች እና 500 አልጋዎች አንዳሉት ተገልጿል።

    ባሕር ዳር (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ207 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነገ በሦስት አገሮች መሪዎች ይመረቃል።

    የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ እና የሕክምና ኮሌጅ የሥራ አፈጻጸም ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር የሺጌታ ገላው በጋራ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ዩኒቨርሲቲው የግንባታ ወጪው 207 ሚሊዮን ብር የፈጀውና ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነውን ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት በተገኙበት ህዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም. በድምቀት እንደሚያስመርቅ ገልጸዋል።

    በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ ከሦስቱ መሪዎች በተጨማሪ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውና ሌሎችም ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ባለስልጣናትና ጥር የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ፕሮፌሰር የሺጌታ ተናግረዋል።

    ከዚሁ መግለጫ ጋር አብሮ እንደተጠቀሰው በዩኒቨርሲቲው የሕክምና ኮሌጅ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ 148 የህክምና ተማሪዎችም ከኮሌጁ ለስድስተኛ ጊዜ ይመረቃሉ።

    በእነዚህ የሆስፒታሉ እና የተማሪዎቹ ምረቃ መርሀ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢፌዴሪ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)፣ የኤርትራ ሀገረ ግዛት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና የሱማልያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት መሐመድ አብዱላሂ መሐመድ በተገኙበት ይከናወናሉ።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንቱ ዶክተር ፍሬው ተገኘ እንደገለጹት በመሪዎቹ የሚመረቀው ሆስፒታሉ የቀዶ ህክምና የሚጠይቁና ወደ ክፍተኛ ሕክምና መስጫ ቦታ የተላኩ (referral) በሽታዎችን የሚያክምና በተለያዩ የትምህርት ክፍሎች (ዲፓርትመንቶች) ውስጥ በሕክምና እና በጤና ባለሙያነት ተማሪዎችን የሚያሰለጥን ነው።

    Ethiopia: Are Ethiopian hospitals constructed in environment-suitable and climate-friendly way?

    ግንባታው ስድስት ዓመታትን የፈጀው ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቀን 2000 የሚሆኑ ታካሚዎችን ሊያስተናግድ የሚችል፣ 11 የቀዶ ሕክምና ክፍሎች ያሉት፣ 500 አልጋዎችን መያዝ የሚችል መሆኑን ፕሮፌሰር የሺጌታ አብራርተዋል። በክልሉ ካሉት ስፔሻላይዝድ ሆስፒታሎች በጥራትም ሆነ በአገልግሎት የተሻለ ሆኖ ለመገኘት መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።

    ሀምሌ 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ከተመረቀው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል በመቀጠል በክልሉ ስድስተኛ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እንደሚሆን አስታውቀዋል። አያይዘውም ሆስፒታሉ ለምርቃቱ ቀን ይብቃ እንጅ እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የህክምና ቁሳቁሶችና ሌሎች መሟላት ያለባቸው ነገሮች ስላሉ ከመንግስት በተጨማሪ ለጋሽ አካላትና በዚህ ዙሪያ የሚሠሩ ወገኖችን ትብብር የሚጠይቅ መሆኑን ገልጸዋል።

    ሚያዝያ 28 ቀን 1992 ዓ.ም በኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር ስር በሙሉ ዩኒቨርሲቲነት የተመረቀው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሀገሪቱ ውስጥ ካሉት ግዙፍ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ሲሆን፥ በ2010 ዓ.ም  52,830 ተማሪችዎችን፣  219 የትምህርት  ዘርፎች (69 በመጀመሪያ/ባችለር ዲግሪ፣ 118  በሁለተኛ/ማስተር  እና 32 በሶስተኛ/ዶክትሬት ዲግሪዎች) ተቀብሎ ያስተምራል። ዩኒቨርሲቲው ስምንት ካምፓሶች ሲኖሩት፥ በውስጣቸውም አምስት ኮሌጆች፣ አራት ተቋማት (institutes)፣  ሁለት ፋኩልቲዎችና አንድ የሕግ ትምህርት ቤት (School of Law)  አሉት።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

    Semonegna
    Keymaster

    ከህመሜ እስከ ስደቴ አብሮኝ ለታመመውና በመንፈስ አብሮኝ ለተሰደደው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ለመገናኘት አበቃን –  የባህል ሙዚቃ አቀንቃኙ አርቲስት ፋሲል ደመወዝ በባሕር ዳር ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አቀባበል ላደረጉለት ወዳጆቹ እና አድናቂዎቹ

    ባሕር ዳር (አብመድ)– ላለፉት ስድስት ዓመታት ኑሮውን በአሜሪካ ያደረገውና የባህል ሙዚቃ አቀንቃኙ አርቲስት ፋሲል ደመወዝ ባሕር ዳር ገብቷል። በባሕር ዳር ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስም አድናቂዎቹ አቀባበል አድርገውለታል።

    የሀገር ፍቅር ስሜቱ ከፍተኛ እና ያመነበትን የሚያቀነቅን እንደሆነ የሚነገርለት አርቲስት ፋሲል ደመወዝ በህዝቡ ዘንድ ተወዳጅ ነው። “ነፃነት በተነፈገው ህዝብ መካከል በኖርኩባቸው ዓመታት ከህመሜ እስከ ስደቴ አብሮኝ ለታመመውና በመንፈስ አብሮኝ ለተሰደደው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ለመገናኘት አበቃን” ያለው አርቲስት ፋሲል ከዚህ ጋር አያይዞም “መድረክ ላይ እንዳልዘፍን የተከለከልኳቸውን የሙዚቃ ስራዎቸን በዚህ ህዝብ ፊት ለማቅረብ በመታደሌ ደስተኛ ነኝ” ብሏል።

    በቀጣይ በተለያዩ ቦታዎች ተንቀሳቅሰህ ህዝብን የማግኘት ዕድል እንደሚኖረው በአቀባበሉ ላይ የተገኙ ጋዜጠኞች ላቀረቡለት ጥያቄ ምላሽ ሲሰጥ አርቲስቱ ከአሜሪካን ሀገር ወደ አገር ቤት ያመጡኝ አስተዋዋቂዎች (ፕሮሞተሮች) የሚያውቁት ሆኖ እስካሁን ባለኝ መረጃ በባሕር ዳር ከተማ አንድ የሙዚቃ ድግስ መኖሩን ነው በማለት ምላሽ ሰጥቷል።

    “ድግስ ጠርቻችኋለሁ” ያለው አርቲስት ፋሲል ደመወዝ ስለታገላችሁለት ነፃነት በነፃነት እንጫዎታለን ነው ያለው። በአርቲስቱ የአቀባበል ሥነ ስርዓት ላያ የተገኙት እማሆይ ፀሃይ ዓለሙ “ፋሲልን በስራዎቹ እና በሀገር ፍቅሩ እወደዋለሁ” መጣ ሲባል ስለሰማሁ እንኳን ለሀገርህ አበቃህ ለማለት ነው የመጣሁት በማለት ለየአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ጋዜጠኞች መልስ ሰጥቷዋል።

    በተመሳሳይ የቀድሞ ጓደኛው እና የሥራ ባልደረባው አርቲስት ቹቹ ምስጋናው ለፋሲል ያለው ፍቅር እና አክብሮት የተለየ መሆኑን ገልፆ “ለኢትዮጵያ ገና በርካታ ሥራዎችን የሚሠራ እና አሉ ከሚባሉ የባህል ሙዚቀኞች አንዱ በመሆኑ እንኳን ወደ ሀገሩ በሰላም ገባ” ሲል በአርቲስቱ መምጣት የተሰማውን ደስታ ገልጻል።

    የአርቲስት ፋሲል ደመወዝ እህት እስከዳር ደመወዝ በወንድሟ ወደ ሀገር መመለስ የተሰማት ደስታ ከፍተኛ መሆኑን ገልጻ በህመሙ እና በስደቱ ወቅት ከጎኑ ለነበረው ህዝብ ምስጋናዋን አቅርባለች።

    አርቲስት ፋሲል ደመወዝ በባሕር ዳር ስታዲየም ህዳር 1 ቀን 2011 ዓ.ም “ሀገሬ ኮንሰርት” በሚል መሪ ሃሳብ የሙዚቃ ሥራዎቹን ለህዝብ ያቀርባል ተብሎም ይጠበቃል ሲል የዘገበው አብመድ ነው።

    አርቲስት ፋሲል ደመወዝ ወደ አሜሪኣ ከተሰደደ በኋላም የሙዚቃ ሥራውን አድናቂዎቹ ያቀርብ የነበረ ሲሆን የተለያዩ ነጠላ ሙዚቃዎችን፣ እንዲሁም አማርኛ ሙዚቃ አድማጭ ዘንድ እጅግ ተቀባይነት ያገኘለትን “እንቆቅልሽ” የተሰኘ አልበም ሠርቷል። በአሜሪካ እና በካናዳ የተለያዩ ግዛቶችም እየተዘዋወረ የሙዚቃ ዝግጅቶች (ኮንሰርቶች) ላይ ከአድናቂዎቹ ጋር ተገናኝቷል። አሜሪካ ውስጥ ፍሎሪዳ ግዛት ካቀረበው ኮንሰርት ላይ የተቀነጨበውን እዚህ ጋር ይመልከቱ

    ምንጭ፦ የአማራ መገናኛ ብዙሀን ድርጅት (አብመድ)

    አርቲስት ፋሲል ደመወዝ

    Semonegna
    Keymaster

    “ለኢንቨስትመንት በሚል ሰበብ አርሶ አደሩን በማደህየት ኢንቨስትመንቱን ማሳደግ አይቻልም፤ መሬታቸው የሚወሰድባቸው አርሶ አደሮች ተመጣጣኝ ካሳ ማግኘት አለባቸው።” ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው

    ዘጋቢ፡-ደጀኔ በቀለ (አብመድ)

    ባሕር ዳር – የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ በ2011 ዓ.ም በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ፣ በሕግ ማዕቀፎች እና አሠራሮች ላይ ሲሰጥ የነበረውን ክልላዊ የምክክር መድረክ ዛሬ አጠናቅቋል።

    የአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ለኢንቨስትመንት በሚል ሰበብ ብዙ አርሶ አደሮች መብታቸው ተጥሶ እንደነበር በመጥቀስ አርሶ አደሩን በማደህየት ኢንቨስትመንቱን ማሳደግ አይቻልም፤ መሬት የሚወሰድባቸው አርሶ አደሮች ተመጣጣኝ ካሳ ማግኘት አለባቸው ሲሉ አስገንዝበዋል። ቀደም ሲል ካሳ የማያገኙበት ሕግ የነበረ ቢሆንም ሕጉን የማስተካከል እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል።

    አርሶ አደሮች እና የነባር ይዞታ ባለቤቶች መሬታቸውን ሕጋዊ በሆነ መንገድ እንዲጠቀሙ መደረጉ ጥያቄ በሚያነሱበት ጊዜ በመረጃ ላይ የተመሠረተ ምላሽ ለመስጠት ከማገዙም በላይ ህብረተሰቡ ተረጋግቶ እንዲሠራ ያደርገዋል። በመሆኑም አርሶ አደሩን ከአላስፈላጊ እንግልት የምናድንበት በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

    አርሶ አደሮች በጉልበተኛ ጥቅማቸውን የሚያጡበት ፍትሃዊ ያልሆነ አሠራር ካለ የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ቢሮ ህዝባዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ጠንክሮ መሥራት እና የፍትህ ስርዓቱን ማስከበር ይጠበቅበታልም ነው ያሉት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው።

    ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራን በተመለከተ ትኩረት ተሰጥቶት እንዲሠራ ርዕሰ መስተዳድሩ በጥብቅ አሳስበዋል። በተለይ የወል መሬቶች በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ግለሰቦች ይዞታ ስር እየገቡ በመሆኑ በፍጥነት መግታት ካልተቻለ ስር እየሰደደ ሄዶ ግለሰቦች ላይ ጫና ማሳደሩ እንደማይቀር አስገንዝበዋል።

    በመድረኩ የተሳተፉ አካላት በባለቤትነት ይዞ በመንቀሳቀስ ከሚመለከተው ባለድርሻ አካላት ጋር ትኩረት ሰጥተው ሊሠሩ እንደሚገባም አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።

    ለተከታታይ አምስት ቀናት የቆየውን የምክክር መድረክ የተካፈሉ አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው በሚችሉት አቅም ሁሉ ህብረተሰቡን ለማገልገል ፍቃደኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

    ተጨማሪ ዜና፦ ኢትዮጵያዊው ባለሃብት አቶ በላይነህ ክንዴ እያስገነቡ ያሉት የምግብ ዘይት ፋብሪካ በቅርቡ ሥራ ይጀምራል

    አቶ ወዳጅ ምስክር ከሰሜን ወሎ ዞን፣ ወይዘሮ በላይነሽ አሻግሬ ደግሞ ከደቡብ ጎንደር ፋርጣ ወረዳ በምክክር መድረኩ የተገኙ ተሳታፊዎች ናቸው። ከውይይቱ በቂ ግብዓት እንዳገኙ ነግረውናል። ተሳታፊዎቹ እንደተናገሩት ወቅቱን መሰረት ያደረገ የገጠር መሬት አጠቃቀም ስልጠና መውሰዳቸው ለቀጣይ የተጣለባቸውን የሕዝብ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ዝግጁ እንደሚያደርጋቸው ለአብመድ ጋዜጠኞች አረጋግጠዋል።

    በመዝጊያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር ገዱ አንዳርጋቸው የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ቢሮ ከወረዳ እስከ ክልል ድረስ ተቋማዊ በሆነ መንገድ ሥራውን በአግባቡ ለመወጣት ጥረት እያደረገ ያለ ተቋም መሆኑን አውስተው፥ መሬት ሀብት እና የማንነት መገለጫ መሆኑን በመረዳት የኃላፊነት ስሜት በተሞላበት መንገድ ሲንቀሳቀስ ለቆየው ለተቋሙ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ ሥራው አድካሚ መሆኑን በመጥቀስ ወደ ዘመናዊ የመረጃ ቋት ለማስገባት ተቋሙ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል።

    ከገጠር መሬት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ ማንኛውም ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት የሚችለው በመድረኩ ላይ የተሳተፈው ባለሙያ ነው፤ በተለይ በምዕራብ ቆላማው የክልሉ አካባቢዎች ለበርካታ ዘመናት ጥሩ አሠራር ያልነበረባቸውን ቦታዎች በዚሁ ተቋም ውስጥ በተሰማሩ ሙያተኞች እና አመራሮች አማካኝነት ውጤታማ በሆነ መንገድ ማስተካከል ተችሏል ብለዋል።

    በከተሞች ዙሪያ የሚኖሩና ትኩረት የማያገኙ አርሶ አደሮች ጥቅማቸው እና መብታቸው እንዲከበር በማድረግ በኩል ትልቅ ሥራ ተሰርቷል፤ ተገፍተው ለነበሩ አርሶ አደሮች በተገቢው መንገድ ካሳ እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የአማራ መገናኛ ብዙሀን ድርጅት (አብመድ)

    ገዱ አንዳርጋቸው

Viewing 15 results - 16 through 30 (of 31 total)