Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 15 results - 256 through 270 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    2ተኛው አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ ተጀመረ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ሁለተኛው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ኡመር ሁሴን፣ የደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው፣ ሌሎች ሚኒስትሮች፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የፌደራልና የክልል አመራሮች፣ የአካባቢው ማኅበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት የ2012 ዓ.ም የ5 ቢሊዮን የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አርብ ግንቦት 28 ቀን 2012 ዓ.ም. በሀዋሳ ከተማ በታቦር ተራራ በይፋ ተጀምሯል።

    የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ባስጀመሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ካለፈው ዓመት ጀምሮ ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት 20 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል አቅዳ እየሠራች እንደሆነ ገልፀዋል።

    ባለፈው ዓመት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር 84 በመቶ መፅደቁን አስታውሰው፥ ዘንድሮ የታቀደውን 5 ቢሊዮን ችግኝ ተከላ ግቡን ለማሳካት ለኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ (ኮቪድ-19) አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ ግቡን ማሳካት ከእያንዳንዱ ዜጋ እንደሚጠበቅ አሳስበዋል።

    በዘንድሮ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በደቡብ ክልል በ227 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ 1.5 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን፥ ወይራ፣ ዋንዛ፣ ዝግባ እና የአበሻ ፅድ የመሳሰሉት ሃገር በቀል ችግኞች የሚተከሉ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

    በዓለም ለ47ተኛ ጊዜ በሀገራችን ለ27ተኛ ጊዜ የሚከበረው የአለም የአካባቢ ቀንም (World Environment Day) “አካባቢን መጠበቅ የብዝሃ-ህይወትን በመጠበቅ ነው” በሚል መሪ-ቃል ከ2012 ዓ.ም አገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ጋር እየተከበረ ይገኛል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የዘንድሮው መሪ ቃል “ለተፈጥሮ ጊዜ እንስጥ” (‘Time for Nature’) የሚል ነው።

    ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት “40 ዛፍ በነፍስ ወከፍ” በሚል መሪ ቃል ሀምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም 200 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀምበር ለመትከል አቅዳ 353 ሚሊዮን 633 ሺህ 660 ችግኞች ተተክሎ የዓለም ክብረ ወሰን መያዟ የሚታወስ ነው።

    አምና 4 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ በአጠቃላይ 4.7 ቢሊዮን በላይ ችግኞች መትከል የተቻለ ሲሆን 23 ሚሊዮን ሕዝብ መሳተፉም ይታወሳል። በቀጣም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ በየዓመቱ የሚካሄድ ይሆናል ተብሏል።

    ምንጭ፦ የግብርና ሚኒስቴር/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አረንጓዴ አሻራ

    Semonegna
    Keymaster

    ሕብረት ባንክ አዲሱን መለያ እና አርማውን ይፋ አደረገ

    ሕብረት ባንክ የተገነባበትን የሕብረትና የአካታችነት መርሁን የሚያጐላለትን አዲስ መለያ እና አርማ ይፋ አደረገ። ባንኩ አዲሱን መለያ ቀርጾ ያጠናቀቀው ዓለም-አቀፍ ደረጃ ያለውን የባንኩን የጨረታ መስፈርቶች በሟሟላት ከተመረጠው ስቱዲዩኔት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ከተሰኘ ሀገር በቀል አማካሪ ድርጅት ጋር በመሆን ነው። እንደ ምንጊዜውም ባንኩ እንዲህ ዓለም-አቀፋዊ ብቃት ካላቸው ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች ጋር በመሥራት ይህንን የመሰሉ ትልልቅ ፕሮጀክት ሊያሳካ ችሏል። በተመሳሳይ ሕብረት ባንክ በቅርቡ የኮርባንኪንግ እና የኦንላይን ፕላትፎርም በራሱ የየመረጃ ቴክኖሎጂ (information technology) ቡድን ማዘመኑ የሚታወስ ነው።

    አዲሱ የባንኩ መለያ ሕብረት ባንክ ከደንበኞቹ፣ ከአጋሮቹና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ትስስር እንዲያንፀባርቅ ሆኖ የተቀረፀ ሲሆን፤ በሕብረት እና በጋራ እድገት ላይ የተመሠረተ መስተጋብር ወይም “eco-system” ለመፍጠር ባንኩ የወሰደውን ቁርጠኝነትም ጭምር የሚያረጋግጥ ነው። ባንኩ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፥ “በእርግጥም የስኬታችን ምንጭ ደንበኞቻችን እና አጋሮቻችን ናቸው። ‘በሕብረት እንደግ’ የሚለው የባንካችን መሪ ቃልም ለዚህ እውነት እማኝ ነውና በጐላ እና በደመቀ መልኩ መገለጥ እና መታየት ይገባዋል” ብሏል።

    መግለጫው ሲቀጥል እንደሚከተለው ይነበባል፦

    ይህንን ታሳቢ ባደረገ መልኩ አዲሱ የባንካችን መለያ በዕለት ተዕለት ሕይወታችን ከቴክኖሎጂ ጋር ያለንን ቁርኝት ከግንዛቤ ውስጥ የከተተና፣ ከዚህ በስተጀርባ ውስብስብ የሚመስሉ አያሌ ጉዳዮች በመላ የሚቃለሉበትን መንገድ የሚጠቁም ብሎም ወደፊት ለመገስገስ የምንገባውን ቃልኪዳን የሚያረጋግጥ ነው።

    ሕብረት ባንክ ያካበተውን የቴክኖሎጂ ብቃት፣ የደንበኞቹንና የአጋሮቹን አብሮነት እንዲሁም በፋይናንሱ ዘርፍ ያዳበረውን ልምድ በመሰነቁ የተሻለ ነገን በሕብረት ለመገንባት የሚያስችል ጠንካራ ጉልበት እንዳለው እሙን ነው።

    አዲሱ የሕብረት ባንክ መለያ የተለያዩ ሕብረ ቀለማትን ያካተተ ሲሆን ይህም የሕብረትን ምንነት የሚያንጸባርቅ ነው። ቀለማቱ ዘመናዊነትን፣ ሙያዊ ጨዋነትንና፣ መስህብን በማመላከት ዕይታን የሚስቡና በቀላሉ ተለይተው የሚታወቁ ናቸው ።

    የአዲሱ የባንካችን መለያ እና አርማ ፍሬ ሀሳብ ‹‹ሕብረት›› ከሚለው ስማችን የተወሰደ ሲሆን መልዕክቱም ትብብርን፣ ሕብርን፣ አብሮነትን፣ አጋርነትን፣ ቅንጅትንና መተጋገዝን የሚገልጽነው።

    ይኽንን ምከግምት ውስጥ በማስገባት እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ባንክ ስማችን በዓለም-አቀፍ ደረጃ “ሕብረት ባንክ” በሚለው ስያሜ ብቻ የሚወከል ስለሆነ እንደከዚህ ቀደሙ “ዩናይትድ ባንክ” የሚለውን የእንግሊዝኛ ትርጓሜ እንደአማራጭ ስያሜ በቀጣይ የማንጠቀም መሆኑን እናሳውቃለን። የአዲሱ መለያ ቃል-ኪዳንም (brand promise) “በሕብረት የተሻለ ነገን እንገነባለን” የሚል ነው። ይህም ቃልኪዳን ውስጣችንን የሚያነቃቃና ከጅምሩ የተመሰረትንለትንና አሁንም የምንጠቀምበትን መሪ ቃል (tag line) “በሕብረት እንደግ” የሚለውን በሕብረት የማደግ ዓላማ የሚያጸና ነው።

    ምንጭ፦ ሕብረት ባንክ

    ሕብረት ባንክ

    Semonegna
    Keymaster

    የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን ምላሽ ለመስጠት ከ220 በላይ የሕክምና መስጫ እና ለይቶ ማቆያ ማዕከላት ዝግጁ ተደርገዋል ― የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

    አዲስ አበባ (የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት) – በሀገራችን የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን ምላሽ ለመስጠት ከአንድ መቶ ሺህ በላይ ሰዎችን ሊይዙ የሚችሉ ከ220 በላይ የሕክምናና የለይቶ ማቆያ ማዕከላት ተዘጋጅተዋል።

    በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከል የኮቪድ-19 የተቋማት ዝግጁነት ክፍል አስተባባሪ አቶ ኢሳያስ መሠለ እንደገለጹት፥ የኮሮና ቫይረስ በቻይና ዉሃን ከተማ (Wuhan) ከተከሰተ ጀምሮ በሀገራችንም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተሠርተዋል። ከዚህም ውስጥ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸውን ሰዎች የሕክምና መስጫ ማዕከል (treatment centers)፣ የበሽታውን ምልክት የሚያሳዩ ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎላቸው ውጤታቸው እስኪታወቅ ተለይተው የሚቆዩበት (isolation centers) እንዲሁም ከመጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ማንኛውም ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ግለሰብ ለ14 ቀናት ለይቶ ማቆያ መግባት እንዳለበት በተላለፈው ውሳኔ መሠረት የለይቶ ማቆያ ቦታዎችን (quarantine centers) መለየትና ዝግጁ ማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ናቸው።

    በዚህም መሠረት ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በአዲስ አበባና በክልሎች ሙሉ በሙሉ ለኮሮና ቫይረስ ህሙማን አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘውን የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ጨምሮ ከ10,000 በላይ ሰዎች የሕክምና አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ከ40 በላይ ማዕከሎች (treatment centers) ዝግጁ የሆኑ ሲሆን ከ15,000 በላይ ሰዎችን አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ከ100 የሚበልጡ የለይቶ ማቆያዎች (isolation centers) እንዲሁም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ ከ80 በላይ የለይቶ ማቆያዎች (quarantine center) ተዘጋጅተዋል።

    ከዚህ ጋር በተያያዘም የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ብሔራዊ የድንገተኛ ማዕከል የኢንፌክሽን መከላከልና መቆጣጠር የውሀ፣ ሳኒቴሽንና ሀይጅን (WASH) ክፍል አስተባባሪ ወ/ሮ ኢክረም ሬድዋን እንደተናገሩት፥ ለኮሮና ቫይረስ (የኮቪድ-19) በሽታ በተዘጋጁ የለይቶ ማቆያ እና ሕክምና ማዕከላት ያሉ የውሀ፣ ሳኒቴሽንና ሀይጅን (WASH) እንዲሁም ኢንፌክሽንን ከመከላከልንና መቆጣጠር አንፃር ያሉ ክፍተቶችን በመለየት ለመሙላት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከውሀ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ ከውሀ ልማት ኮሚሽን እና ከአጋር ድርጅቶች በተደረጉ ድጋፎች ሲሆን የውሀ መቆራረጥና እጥረት ያለባቸውን ተቋማት ክፍተት መሙላት፤ የውሀ አቅርቦት መቆራረጥን ለመቀነስ የውሀ ታንከሮችና ፓምፖችን መግጠም፣ ውሀን በትራክ ማቅረብ እንዲሁም የእጅ መታጠቢያ እጥረት ባለባቸው የለይቶ ማቆያ እና ሕክምና ማዕከላት ከእጅ ንክኪ የጸዱ በእግር መከፈት የሚችሉ ተንቀሳቃሽ የእጅ መታጠቢያዎች እንዲተከሉ ተደርጓል።

    በተጨማሪም ለሁሉም ለይቶ ማቆያ እና ሕክምና ማዕከላት የኢንፌክሽን መከላከልና መቆጣጠር ባለሙያ እና በአዲስ አበባ ለሚገኙ የለይቶ ማቆያ እና ሕክምና ማዕከላት የፀረ ተህዋሲያን ኬሚካል ርጭት ባለሙያዎች ተመድበዋል። ለነዚህ ባለሙያዎችም የኮቪድ-19 የኢንፌክሽን መከላከልና መቆጣጠር ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ባለሙያዎቹም በአጠቃላይ የሚከናወኑ ተግባራት ኢንፌክሽንን ከመከላከልና መቆጣጠር አንጻር በአግባቡ እየተካሄዱ መሆናቸውን በየዕለቱ ይከታላሉ ብለዋል።

    በአጠቃላይ በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከሚሰሩ ሥራዎች ባሻገር ህብረተሰቡ የሚያደርጋቸው ጥንቃቄዎች ለበሽታው ያለመስፋፋት ወሳኝ በመሆናቸው ህብረተሰቡ ሳይዘናጋ የሚተላለፉ መልዕክቶችን እና መከላከያ መንገዶችን ተግባራዊ በማድረግ የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል።

    ለተጨማሪ መረጃ በስልክ መስመር 8335 ወይም በ952 በመደወል ወይም በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኢሜል አድራሻ ephieoc@gmail.com በመጠቀም ወይም ባሉበት ክልል በተዘጋጁ ነፃ የስልክ መስመሮች በመደወል ሪፖርት እንዲያደርጉ ወይም በአካባቢው ለሚገኙ ጤና ተቋማት በስልክ እንዲያሳውቁ እንጠይቀለን።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

    የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ

    Anonymous
    Inactive

    የዜጎች ሰብዓዊ መብት መከበር በምንም ምክንያት እና በማንኛውም ጊዜ ለድርድር የማይቀርብ ነው!
    ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

    አምነስቲ ኢንተርናሽናል (Amnesty International) «ሕግን ከማስከበር ባሻገር» በሚል ርዕስ ባወጣው ዘገባ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች ሁለት አካባቢዎች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ተፈጽመዋል ያላቸውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ዘርዝሯል። በዘገባው ውስጥ በፀጥታ አስከባሪዎች እርምጃ በአሰቃቂ እና ከሕግ ውጪ በሆነ ሁኔታ የዜጎች ሕይወት መጥፋቱን፣ ሴቶች መደፈራቸውን፣ በማቆያ ካምፖች ውስጥ ሰቆቃ መፈፀሙን፣ ከሕግ አግባብ ውጪ እስር መፈጸሙን፣ ዜጎች ከሚኖሩበት እንደተፈናቀሉ እና ንብረታቸው እንደወደመ ተዘርዝሯል። በተጨማሪም በተለያዩ ማኅበረሰቦች መካከል የእርስበርስ ግጭት ሲከሰት የአካባቢ አስተዳዳሪዎች እና ፀጥታ ኃይሎች የዜጎችን ደኅንነት ከማስጠበቅ ይልቅ በግጭቱ ውስጥ እንደተሳተፉ እንዲሁም ኃላፊነታቸውንም በአግባቡ እንዳልተወጡ ተጠቅሷል። እነዚህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ጉባዔ በአካባቢው ይፈፀማሉ ብሎ ካወጣው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ዘገባ ጋር ተመሳሳይነት አላቸው።

    በዘገባው ውስጥ የተጠቀሱት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተመለከተ ዘገባውን በሠራው ተቋም ምላሽ ወይንም ማብራሪያ ከተጠየቁ የፌደራል እና የክልል ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቶች መካከል የአማራ ክልል የሰላም እና ደህንነት ግንባታ ቢሮ ብቻ መልስ እንደሰጠ ዘገባው ጠቅሷል። በሁሉም ደረጃ ያሉ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በተሰማሩበት የኃላፊነት ዘርፍ የተከሰቱ ችግሮችን በተመለከተ የሚቀርብላቸውን የማብራሪያ ጥያቄዎች በቀናነት መቀበል እና ምላሽ መስጠት ግዴታቸው እንደሆነ እናምናለን። የሚቀርቡ ጥያቄዎችን በርን ክፍት አድርጎ መቀበል እና ግልጽነት የተሞላው ምላሽ መስጠት፣ እንዲሁም የተሠሩ ስህተቶችን ለማረም ዝግጁ መሆን በሂደት ለምንገነባው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት አስፈላጊ እሴቶች ናቸው። በዚህ ረገድ የአማራ ክልል ሰላም እና ደህንነት ግንባታ ቢሮ ላሳየው አርኣያ የሚሆን ተግባር ያለንን አክብሮት መግለጽ እንወዳለን። የፌደራል መንግሥቱን ጨምሮ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የመንግሥት አካላት በተለይ ከሰብዓዊ መብት ጋር በተያያዘ ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች እና ጥቆማዎች ከዳተኝነት እና ተጠያቂነትን ለመሸሽ ከሚደረግ ማንኛውም ሙከራ በመታቀብ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው ምላሽ መስጠት ይጠበቅባቸዋል።

    የአምነስቲ ዘገባ በሁለት የተወሰኑ ቦታዎች እና ውስን ክስተቶች ላይ ያጠነጠነ መሆኑ ተከሰቱ የተባሉትን ጥሰቶችም ሆነ ሌላ በሀገራችን የተከሰቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ሙሉ በሙሉ ለመረዳትም ሆነ የእርምት እርምጃ ለመውሰድ በቂ መረጃ የያዘ ነው ተብሎ ባይወሰድም በውስጡ የያዛቸው የከፍተኛ ሰብዓዊ መብት ጥሰት ሰለባ የሆኑ ዜጎች ስም፣ የተፈጸመበት ቦታ እና ጥሰቱን እንደፈጸሙ የተጠቀሱት ተቋማት በግልጽ መቀመጥ ግን የመረጃውን ትክክለኛነት ለማጣራት ቀላል ከማድረጉም በላይ ተጨማሪ ምርመራ ተደርጎ የተጠቀሱት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መፈጸማቸው ከተረጋገጠ የእርምት እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ከበቂ በላይ አመላካች ናቸው። በአምነስቲ ዘገባ ያልተካተቱ በየጊዜው ለዜጎች ሕይወት መጥፋት፣ የአካል መጉደል፣ ከመኖሪያቸው መፈናቀል፣ የተማሪዎች መታፈን፣ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት መታሰር እና መንገላታትን ጨምሮ በተለያየ መንገድ ይፋ የተደረጉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንዳሉም ይታወቃል።

    በመሆኑም የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በአምነስቲ ኢንተርናሽናል ዘገባ ውስጥ የተካተቱትን ጨምሮ የለውጡ አስተዳደር ሥልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ አንስቶ በፌደራል እና የክልል መንግሥት የጸጥታ ኃይሎች፣ የፖለቲካ ዓላማ ባነገቡ ታጣቂዎች እንዲሁም በየአካባቢው በተደራጁ ኢ-መደበኛ ቡድኖች ዜጎች ላይ የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የሚመረምር ልዩ ቡድን በአስቸኳይ እንዲያቋቁም እና ምርመራ አድርጎ ውጤቱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ለክልሎቹ ምክር ቤቶች እና ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ እንጠይቃለን። በዘገባው በተጠቀሱ እና ከዛም ውጪ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደተፈጸመባቸው በሚታወቁ (በሚጠረጠሩ) ቦታዎች የተከሰቱት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በቦታው ድረስ በመገኘት ከተጎጂዎች እና ከተጎጂ ቤተሰቦች፣ በጊዜው በአካባቢው ግዳጅ ላይ ከነበሩ የፀጥታ አስከባሪዎች፣ የአካባቢው አስተዳዳሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻዎችን በማግኘት ሰፊ ምርመራ እንዲደረግ እንጠይቃለን።

    የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ይህንን ኃላፊነት እንዲወስድ ማድረግ እና አስፈላጊውን ድጋፍ መስጠት የሀገራችንን ችግሮች አውድ በበለጠ የሚገነዘብ እና በዜጎች ዘንድ ያለው ተዓማኒነት በሂደት እያደገ የሚሄድ ሀገር በቀል የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ተቋም እንዲሆን እንዲሁም የተቋሙን አቅም በሂደት በመገንባት ለምናደርገው የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ በጎ አስተዋፅዎ እንደሚያደርግ እናምናለን።

    የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በዜጎች ዘንድ ያላቸው አመኔታ እና የሕዝብ ወገንተኝነት ስሜት መገንባት ለምንፈልገው ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት በሚደረግው ምርመራ ውስጥ ኃላፊነታቸውን የሚመጥን ትብብር እንዲያደርጉ እና የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ተፈጽመው በሚገኙበት ጊዜ ሁሉ ጥፋቱን በቀጥታ የፈፀሙ፣ እንዲፈፀም ትዕዛዝ የሰጡ እና ዜጎችን ከአደጋ የመጠበቅ ኃላፊነታቸውን በማንኛውም መንገድ ያልተወጡ አባሎቻቸው ላይ አስተማሪ የሆነ እርምጃ ወስደው ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ እና ለሕዝብ ወገተኝነታቸውን እንዲያረጋግጡ አንጠይቃለን።

    በዚህ አጋጣሚ በተለይ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የሀገራችንን ድንበር እና ሉዓላዊነት ለማስከበር እና በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች የሚነሱ ችግሮችን ለመቆጣጠር እና መፍትሄ ለመስጠት እየከፈለ ላለው መስዕዋትነት ከፍተኛ አድናቆት እና ክብር እንዳለን ለመግለጽ እንወዳለን። ሠራዊቱ በመደበኛነት ሥልጠና ከወሰደበት የግዳጅ ዓይነት የተለየ እና ሰላማዊ ዜጎች በሚኖሩበት ቦታዎች የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ እና የሕግ የበላይነትን ለማስፈን የሚወስዳቸው ግዳጆች የሚፈልጉትን ተጨማሪ ሥልጠናዎች በአግባቡ ማግኘት እንዳለበት ለማሳሰብ እንወዳለን። ነገር ግን የሠራዊቱን መስዕዋትነት እና ያለበትን ኃላፊነት በፍፁም በማይመጥን መልኩ የዜጎች ሰብዓዊ መብት ላይ ጥቃት እንዳደረሱ የተረጋገጡ እና በምንም መልኩ እጃቸው ያለበትን አባላቱ ላይ አስተማሪ እርምጃ በመውሰድ የሕዝብ አለኝታነቱን እንዲያረጋግጥ አጥብቀን እንጠይቃለን።

    ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ግልጽ እንዳደረግነው፣ ምንም ሕገ መንግሥታዊ መሰረት የሌለው የክልል ልዩ ኃይል አደረጃጀት የዜጎችን ደህንነት ከማስጠበቅ ይልቅ እራሱን የአንድ ወገን ጠባቂ እና ተከላካይ አድርጎ በመቁጠር ለዜጎች ደህንነት ስጋት ሆኖ መቀጠሉን የሚያሳዩ ተደጋጋሚ ማስረጃዎች እያየን ነው። ስለዚህም መንግሥት ይህን በየክልሉ የተደራጀ ልዩ ኃይል ወደክልሎቹ መደበኛ የፖሊስ ኃይል አልያም የፌደራል ፖሊስ እና የሀገር መከላከያ ሠራዊት እንዲቀላቅል አሁንም ደግመን እናሳስባለን።

    የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎች ሰብዓዊ መብት መከበር በምንም ምክንያት እና በማንኛውም ጊዜ ለድርድር የማይቀርብ መሆኑን እና ዜጎች ላይ ጥፋት የሚያደርሱ አካላትን ተጠያቂ ማድረግ መገንባት ለምንፈልገው ሥርዓት ያለውን ከፍተኛ ዋጋ በመረዳት ለዜጎች ደህንነት እና ሰብዓዊ መብቶች መጠበቅ እና ተጠያቂነት እንዲሰፍን ያለውን ቁርጠኝነት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ለሚያደርገው ልዩ ምርመራ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ በማድረግ እና በምርመራው ውጤት ላይ በመመስረትም አስፈላጊውን የእርምት እርምጃ በመውሰድ ቁርጠኝነቱን በድጋሚ እንዲያረጋግጥ እናሳስባለን።

    የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችም የሰብዓዊ መብት ጥሰትን እና በየጊዜው የሚከሰቱ ጉዳዮችን ሰበብ በማድረግ የሀገር መረጋጋትን እና ሰላምን እንዲሁም የዜጎችን ደህንነት አደጋ ውስጥ ሊጥል ከሚችል የፖለቲካ ትርፍን ዓላማ ካደረገ ማንኛውም እንቅስቃሴ እንዲታቀቡ አጥብቀን እንጠይቃለን።

    የኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት
    ግንቦት 25 ቀን 2012 ዓ.ም

    የዜጎች ሰብዓዊ መብት መከበር

    Anonymous
    Inactive

    የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ የሰጠውን መግለጫ በተመለከተ የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

    ሕዝባዊነት እና ዲሞክራሲያዊነት ከማያውቀው የህወሓት ገዢ መደብ፣ የተጎሰመው የሁከትና ብጥብጥ አቋቁሙኝ ነጋሪት መግለጫ ሰምና ወርቅ።

    የህወሓት ጥገኛ ገዢ መደብ የሰሞኑ መግለጫ ሰሙ በሕዝባዊነት፣ ሕጋዊነት፣ ሰላማዊነት፣ የዲሞክራሲያዊነትና የሀገራዊ አንድነት የተለበጠ አዛኝ ቅቤ አንጋችነት ባዶ ጩኸት ነው፤ ወርቁ ደግሞ በሴረኝነት፣ በቡድነኝነት፣ በሀገር ጠልነት እና በኢ-ዲሞክራሲያዊነት ሁሉን ፍጥረት በሚያስማማ ሕዝባዊ ቅቡልነት እጦት የተንሳፈፈን ኃይል በማንኛውም ኢ-ሰላማዊ መንገድ በመጠቀም የመተንፈሻ ድጋፍ በመስጠት ለመመለስ ያለመ የስሌት ችግር የሚስተዋልበት ኢ-ሞራላዊ የሁከት አታሞ ነው።

    የህወሓት የጥገኛ ገዢ መደብና ከተለያዩ የመንግሥት መዋቅሮች የተሰባሰቡ የኩርፍያ አድመኞች በቀድሞ የኢህአዴግ አወቃቀር በተለያዩ ግዜያት በተደረጉ ግምገማዎች የሥርዓትና የሀገር አደጋዎችን በመለየት ለማስወገድ በተዘጋጁ መድረኮች ሲናዘዙ ቆይተዋል።

    እንደ ኮሮና ቫይረስ ባሉ በማያከራክሩ ህልው ዓለማዊ፣ ሀገራዊና ክልላዊ ሁኔታዎች ውስጥም ሆነን ጭምር ግላዊ ፍላጎቶቻቸው ሕዝብ ላይ ለመጫን እየሄዱበት ያለው አቅጣጫና ርቀት አሁንም አነጋጋሪና ዳግም የስህተት ታሪክ ሀወልትና ማፈርያ እንደሚሆን ከወዲሁ መገመት ይቻላል።

    ይህ ለእኔ ስለኔ እና የእኔ ብቻ የሆነ የገዢ መደብ በሕዝባዊነት በዲሞክራሲያዊነትና በቀናኢ የኢትዮጵያዊ አንድነትም የማያምን መሆኑን አንዳንድ አባላቱ በድፍረት ባለፉት ሁለት ዓመታት በቀረቡበት ሚድያዎች ሁሉ ለሕዝብና ሕዝባዊነት ያላቸውን ቅጥ ያጣ ንቀት በገዛ አፋቸው ያለህፍረት መስክረዋል።

    አስተዋይና አርቆ አሳቢ የሆንከው መላው የሀገራችን ሕዝብ ሆይ፤ በዲሞክራሲ ስም እየማለ እና እየተገዘተ፣ ዲሞክራሲ ማዕከላዊነት በሚል ማሞኛ ፈሊጥ ለዓመታት እራስን በራስ ለማስተዳደርና ለሀቀኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ማበብና መበልፀግ እንቅፋት ሆኖ፣ በምስለኔዎች የሞግዚትነት አሠራር የሀገራችን የፖለቲካ እድገት አቀጭጮ፣ በመጠላለፍ ሴራና በመከፋፈል ላይ የመሠረተውን ይህን የገዢ መደብ የጥፋት ሃሳብ በጥብቅ በማውገዝ ሰላምና አንድነትህን በንቃት በመጠበቅ እንድትታገለው ታሪካዊ ጥሪ ይድረስህ።

    በተለይም መላው የትግራይ ሕዝብ፥ አርሶ አደሩ፣ የመንግሥትና የግል ሠራተኞች፣ ምሁራን፣ ነጋዴዎች፣ ነባር ታጋዮችና ለፍትህና ለነፃነት አካላችሁን ያጎደላቹ ሀቀኛ የሕዝብ ልጆች፣ ወጣቶች፥

    • በሀገረ ኢትዮጵያ ሕብረ-ብሔራዊ አንድነት ምሥረታ የትግራይ ሕዝብ ያለውን ጉልህ ታሪክና ጅግንነት ከካዱና ካሳነሱ፤
    • ላለፉት 29 ዓመታት የትግራይ ሕዝብ የታገለለትን አላማ ረስተው ለግልና ቡድናዊ ጥቅማቸው ካደሩ፤
    • ሕዝባዊ የልማት ተጠቃሚነትን በቡድናዊ ጥቅም ለውጠው በገዛ መሬትህና ሀገርህ ለዘመናዊ ባርነት የሽጥሁን፤
    • በኢትዮጵያዊ አንድነትህ የማትደራደረውንና ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖችህ ጋር በሰላምና በመተሳሰብ ለዘመናት መኖርህ እንቅልፍ ነስቷቸው ሌት ተቀን የሚያሴሩብህን፤
    • “በምድር ላይ ያለ የፖለቲካ ኃይል እኔ ነኝ” በሚል ያነሰ አስተሳሰብ፣ በሺዎች ዓመታት የሚቆጠረውን ጅግንነትህን እና ታሪክህን ወደ አርባዎች አውርደው “ከኛ በላይ ለአሳር” የሚመስለውን ትምክህታዊና ሸውራራ የታሪክ ትርክታቸውን ‘በንቀት ለመጋት ከሚሞክሩ የዘመኑ አዋቂ ነን ባይ አላዋቂዎች፤
    • ለዓመታት በስልጣን ዘመናቸው በከተማ ሲንደላቀቁ፣ በመላው የትግራይ ገጠሮችና ከተሞች የንፁህ ውሃ እጦት እሮሮህ ለመስማትና ለመመለስ ጀሮ ዳባ ልበስ ካሉ፤
    • ከምንም በላይ የጥይት ባሩድ ለሰለቸህ፣ የጦርነት ኪሳራውን በተግባር በማወቅህ አጥብቀህ ሰላም ናፋቂና ፈላጊ መሆንህ የጎረበጣቸው፤

    እነዚህ የገዢ መደብ አለቆች ጠንቀኝነታቸውንና ተዘርዝሮ የማያልቀውን ጥፋታቸውን በጊዜው በመገንዘብ፥ ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ሆነህ በድጋሚ እንቢተኝነትህን እንድታሳይና በሰላማዊ መንገድ ታግለህ ታሪክህን በድምቀት እንድታድስ ልዩ ጥሪ እናቀርብልሀለን።

    ለሕጋዊ፣ ሰላማዊ እና አስተዋይ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ኃይሎች፥ በፖለቲካዊ አመለካክታችሁና አቋማቹ የቱንም ያህል ብትቃረኑ፣ ሕዝባዊነት፣ ሕጋዊነት እና ሰላማዊነትን ተላብሳችሁ የሚጠብቅባችሁን ታሪካዊ ድርሻ እንድታዋጡ አደራችንን ለማስተላለፍ እንወዳለን።

    እንግዲህ “ከክፉ ዛፍ መልካም ፍሬ አይጠበቅምና” መልዕክትና መልዕክተኛው የተቃረኑበትን ሰሞነኛ መግለጫው፣ ብሩህና አስተዋይ ለሆነው ሕዝባችን ሰምና ወርቁን እንደሚገነዘበው የሚያምነው የብልፅግና ፓርቲ፣ በየትኛውም ደረጃ ሕዝባዊ ተሳትፎን በመተማመን ከፊቱ የተጋረጠበትን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከላከልን ቀዳሚ ትኩረቱ በማድረግ፣ ሕዝቡ ራሱንና ወገኑን እንዲጠብቅ በአፅንኦት ይገለፅፃል።

    ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
    የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ

    የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ

    Anonymous
    Inactive

    የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ

    የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ማዕከላዊ ኮሚቴ ከግንቦት 15 እስከ 22 ቀን 2012 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባው በፍጥነት እየተለዋወጠ ያለው የዓለም፣ የአካባቢያችንና የሀገራችን ሁኔታ ጨምሮ የክልላችን ሰላምና ደኅንነት፣ የኮረና ቫይረስ በሽታ ስጋትና የመከላከል ሥራ፣ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደት፣ የድርጅትና የመንግሥት ሥራ አፈፃፀም እንዲሁም በአስተዳደር በኩል እየመጡ ያሉት ለውጦች አስመልክቶ ሰፊ ውይይት አካሂዷል።

    ኮሮና ቫይረስን ወይም ኮቪድ-19ን ተከተሎ እየመጣ ያለውን አዲስ ዓለማዊ ሁኔታ የልማታዊና ዴሞክራሲያዊ መስመር አስፈላጊነትንና ትክክለኛነትን የሚያረጋግጥ ነው። ቀድመውንም ቢሆን የመንግሥት ስልጣን ሽግግርን ለብቻ ተቆጣጥረህ ጠባብ ጥቅምህን ለማርካት፣ የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለአፍታ እንኳን ግድ የሌለው ጥገኛ የብልፅግና ቡድን በተፈጠረው አዲስ ዓለማዊ ሁኔታዎችና ፈተናዎች ራሱን አስተካክሎ በሕዝባዊ ትግልና በሕዝብ ልጆች መስዋእትነት በግንቦት 20 የተመዘገቡ አስደናቂ የዴሞክራሲና የልማት ድሎች አጠናክሮ ከማስቀጠል ይልቅ የጥፋት መንገድ አጠናክሮ ቀጥሎበታል።

    በጊዜያዊ ጥቅም ወይም በጥላቻ የዚህ ሥርዓት መጠቀሚያ በመሆን ሙያቸውንና ስብዕናቸውን አሳልፈው የሰጡ አካላት ከፊት በማሰለፍ በግላጭ ሕገ-መንግሥቱን በመጣስ ስልጣን ላይ እንደሚቆይ ይፋ ያደረገው የብልፅግና ቡድን ለማስመስል እንኳን ውሳኔ ይሰጣሉ የተባሉትን ተቋሞች የሚሉትን እስከምንሰማ ድረስ እንኳን ሊታገስ አልቻለም። በእንደነዚህ ዓይነት ወደ ጥፋት የሚምዘገዘገው የብልፅግና ቡድን የሚያስተዳድረው መንግሥት ባላት ሀገር ሆነን መሠረታዊ ዓላማችንንና ልማታችንን ለማሳካትም ሆነ የገጠመንን የኮሮና ቫይረስ ፈተና ለመመከት ምን ያህል ከባድ እንደሆነ ሁሉም ሊገምተው የሚችል ነው።

    የ‘ብልፅግና’ ቡድን ሉዓላዊነትና መሠረታዊ የሚባሉ የሀገር ጥቅሞች ለሽያጭ በማቅረብ፣ ሕገ መንግሥትንና ሥርዓትን እንዲሁም ሁሉም ዓይነት ከፊቱ ላይ የቆሙትን ሕጎችንንና ተገቢ የመንግሥት አሠራሮችን በመጣስ ስልጣን ላይ ለመቆየት ከመወሰን አልፎ ሥርዓትንና ሕግን አክብረው በሄዱት አካላት ላይ ይፋዊ ጦርነት ወደ ማወጅ ተሸጋግሮ ይገኛል። የዚህ ቡድን ፉከራዎችና ሴራዎች በአካሄዳችን ላይ ይሁን በሕዝባዊ ትግላችን ተጨማሪ ቁጭትና ወኔ ከመፍጠር አልፈው ሌላ ፋይዳ ያላቸው እንዳልሆኑ ግልፅ ቢሆንም ለጠባብ ፍላጎት ሲባል የሀገርና የመላ ሕዝቦች ጥቅም ወደ ገደል ገፍትሮ ለመጣል ‘ብልፅግና’ ምን ያህል ዝግጁ እንደሆነ ለሁሉም ግልፅ ሆኗል።

    ይሁን እንጂ ወትሮም ቢሆን ህልውናውንና ጥቅሙን በጠንካራ ክንዱና በትክክለኛ አስተሳሰቡ የተመሠረተ መሆኑን፤ ታሪኩንና ትግሉን በተጨባጭ አሳምሮ የሚያውቅ ሕዝባችን፤ የጥገኞች ቀጣይ በርካታ ጥቃቶችን ተቋቁሞና የመመከት ተግባሩን አጠናክሮ መቀጠሉን አረጋግጠናል። ድርጅታችን ህወሓት ሕዝባችን እያካሄደ ላለውን ፍንክች የማይል ቀጣይነት ያለው ትግል ከፍተኛ ክብርና አድናቆቱን ይገልፃል። ወደፊትም ሁኔታዎች በጥብቅ እየገመገምን የምናሳልፋቸው ውሳኔዎች በንቃት እንደሚከታተልና እንደሚፈፅም የትናንትም የዛሬም ታሪካችን ምስክር ነው። እያካሄድን ያለነው የተፋፋመ ትግል በሁሉም የሰላም፣ ልማትና ዲሞክራሲ አውዶች ተስፋ የሚያሰንቁና ለቀጣይ ድሎችም አመቺ ቦታ የሚፈጥሩ ውጤቶች እየተመዘገቡ ናቸው። ይህ በእንዲህ እንዳለ አሁንም ሕዝባችንን ያላረካንባቸው በርካታ ጉዳዮች እንዳሉ አሳምረን የምንረዳው እውነታ ነው።

    ከሕዝባችንና ከመሪ ድርጅታችን ፊት ለፊት መግጠም ከብረት ጋር መጋጨት የሆነባቸው ጥገኛ ቡድንና ተከታዮቹ በዋነኛነት በተቀናጀ የሚዲያ ዘመቻ የታገዘ ግልፅ ውሸት በመመሥረትና ባንዳዎችን በማዝመት ውስጣዊ ሰላማቻንን በማደፍረስና ልማታችንን በማደናቀፍ ወደ ድቅድቅ ጭለማ ሊያስገቡን እየሠሩ መሆናቸውን ሁሉም በተለይ ደግሞ ሕዝባችን የሚገነዘበው ጉዳይ ነው።

    በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ሆነን በአንድ እጃችን ሁለገብ የመመከት ሥራዎቻችን እያጎለበትን በሌላም በኩል ፈጣን የልማትና የመልካም አስተዳደር ማስፈን፣ ሕዝባችንንና መላ መዋቅራችንን እንዲሁም የሰላምና የልማት ወዳጅ የሆነ ኃይል ሁሉ ሊረባረብላቸው የሚገቡ ጉዳዮች መሆናቸው በማረጋገጥ የህወሓት ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ከሚያዝያ 23 እስከ 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባው ያሳለፋቸው ውሳኔዎችንና አቅጣጫዎችን በማጽደቅና መሠረት በማድረግ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ የሚከተሉትን ውሳኔዎችን አሳልፏል።

    1. የኮሮና ቫይረስ መከላከል ሥራ ከዚህ በፊት ሲደረግ እንደቆየው አዲስ ለውጦች፣ ተጨባጭ የክልላችን ሁኔታ እንዲሁም ሳይንሳዊ ማስረጃዎችን መሠረት በማድረግ ሕዝባችንን ለማዳን እየተከላከልን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት በሚቀንስ መልኩ እየተገመገመ በጥብቅ እንዲመራ ተወስኗል።
    2. የ‘ብልፅግና’ ቡድን ከድሃ ጉሮሮ እና ልማት ቀምቶ ያልተቆጠበ ሃብት በማፍሰስ ሀገር ከጫፍ እስከ ጫፍ ለማበጣበጥ፣ በዶክሜንተሪ ፊልሞች የታገዘ ዘር የማጥፋት ጥሪ እንዲካሄድና ሁሉም መብቶች እንዲረጋገጡ እያደረገ ያለው ጭፍን ፀረ-ሕዝብና ስልጣንን በገንዘብ የመግዛት ተግባር እንዲቆም ብቻም ሳይሆን ከጥፋት መንገድ ወጥቶ በሕገ-መንግሥት መሠረት የሚመለከተው ወገን ሁሉ ተሳትፎ ባረጋገጠ መልኩ እና ወደ ምክንያታዊ ውይይት እንዲገባ እንዲሁም ጨርሶ ሳይረፍድ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ከማፍረስ እንዲቆጠብ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ያሳስባል።
    3. ሙሉ ዝግጅትና የሕብረተሰቡን ጤና የመጠበቅ ሥራ በመሥራት በሕገ መንግሥት በተዘረጋው ሥርዓት መሠረት ሁሉንም እኩል ማየት የሚችል ኃይል የሚመራው ሀገራዊ ምርጫ እንዲካሄድ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ዳግም ያሳስባል።
    4. ምርጫ በሀገር-አቀፍ ይሁን በክልል ደረጃ በሺዎች መስዋዕትነትና ከፍተኛ ዋጋ የተከፈለበት ሕገ-መንግሥታዊ ዋስትና ያገኘ መብት እንጂ ገደብ የለሽ የስልጣን ጥማት ያለው ግልገል አምባገነን የሚሰጠው ወይም የሚከለክለው ችሮታ አይደለም። የትግራይ ሕዝብ ከድሮም ቢሆን ራሱን በራሱ የማስተዳደር መብቱን በመስዋዕትነቱ ያረጋገጠ፣ በማንኛውንም ሁኔታ በራሱ ላይ ይሁን በሌሎች ሕዝቦች ላይ ባርነት እንዲነግስ የማይፈቅድ ሕዝብ ነው።

    የትግራይ ሕዝብ በመስዋዕትነቱ ያረጋገጠው መብት በማንኛውንም ጊዜ እና ሁኔታ ወደ ድርድር እንደማይቀርብና የዚህን መብት ተግባራዊነት ወደ ኋላ መመለስ የሚችል ማንኛውም ምድራዊ ፖለቲካዊ ኃይል እንደሌለ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አስምሮበታል። ስለዚህም የፌደራል ስልጣን በአምባገነናዊ አኳኋን ተቆጣጥሮ ያለው ኃይል በተለመደው አካሄዱ የሕዝቦችን መብት እየደፈጠጠ መቀጠሉን አጠናክሮ እየገፋበት በመሆኑ ሕዝባችን በመስዋዕትነቱ ያረጋገጠው እና የማንም ፈቃድ የማይጠይቅበት፣ ራስን በራስ የማስተዳደር መብት በተግባር ለመተርጎም በክልላችን ምርጫ እንድደረግ እና ይህንን ለማድረግ የተጀመሩ ዝግጅቶች ለማድረግ የተጀመሩ ዝግጅቶች በሕግ አገባብ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ወስኗል።

    የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ በትግራይ ምርጫ እንዲካሄድ ሲወስን በ‘ብልጽግና’ ጥገኛ ባህርይ ምክንያት የተጀመረው ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት የማፍረስና ሀገር የመበተን ሂደት ወደ መጨረሻ ምዕራፍ እየደረሰ መሆኑን ይገነዘባል። አሁንም ቢሆን ሁሉም የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና እና ሕዝቦች የሀገራችንን ሕገ-መንግሥት ያጎናፀፋቸው ራስን በራስ የማስተዳደር መብት እንዳያጡ ትግላቸው ማጠናከር እንደሚገባቸው ህወሓት ያምናል። ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም ይህንን ተገንዝቦ አዎንታዊ ሚና እንዲጫወት ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    1. የ‘ብልፅግና’ ቡድን ምርጫ ላለማካሄድና የስልጣን ዕድሜውን ለማራዘም እየወሰዳቸው ካሉ ሕገ-ወጥ እርምጃዎችና ሴራዎች በተጨማሪ የድርጅታችን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በትግራይ ክልል ሕግና ሥርዓት እንደሚቀጥልና ‘ብልፅግና’ ምርጫ ለማስቀረት እየሠራ በመሆኑ በትግራይ ደረጃ በሕግ መሠረት ምርጫ ለማካሄድ ውሳኔ ባሳለፈበት ወቅት የብልጽግና መሪ አሁንም መሠረታዊ የሕዝቦች ራስን በራስ የመወሰን መብት ክብር እንደሌለው በሚያሳይ መልኩ የጦርነት አዋጅ ይፋ አድርጓል። የትግራይ ሕዝብ በፉከራና የጦርነት ነጋሪት መጉሰም እንደማይደነግጥና መብቱን አሳልፎ እንደማይሰጥ የሚታወቅ ሃቅ ነው። ኃላፊነት በጎደለው አካሄድ እንዲሁም የ‘ብልፅግና’ ቡድን እና መሪው የሚመጣ ማንኛውንም ጥፋት ብቸኛው ተጠያቂዎች ራሳቸው መሆናቸው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብና ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ መገንዘብ ይገባቸዋል።
    2. በልማት ሥራዎች፣ የዴሞክራሲ ባህል እና አስተዳደር የተጀመሩ ለውጦች በጊዜ የለንም መንፈስ በበለጠ ፍጥነት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በየደረጃው ያለው አመራር በከፍተኛ የኃላፊነት መንፈስ እንዲሠራው ተወስኗል። ይህ በእንዲህ እንዳለ መላው ሕዝባችንና ሁሉም የመንግሥትና የድርጅት መዋቅሮች ለርካሽ ዓላማቸው ሲሉ ከልማትና የዴሞራሲ ግንባታ ሃዲድ አውጥተው ወደ ብጥብጥና ጥፋት ሊያስገቡን የሚረባረቡ ብልጽግና ኃይሎች፣ አይዞህ ባዮችና እና ተላላኪዎቹ ለመመከት የተጀመረውን ትግል እንዲጠናከር ተወስኗል።
    3. የራስን ዕድል በራስ የመወሰንና ራስን በራስ የማስተዳደር መብት፣ የሕዝባችን ደኅንነትና ሰላምን የማረጋገጥ ጉዳዮች ላይ አብሮው ሊሠሩ ዝግጅ ከሆኑ የሀገራችንና የክልላችን የፖለቲካ ኃይሎች የተጀመረውን ዝምድና በፍጥነት ወደ ከፍተኛ ደረጃ እንዲሸጋገርና ትርጉም ያለው ለውጥ ሊያመጣ ወደሚችልበት የሕዝባችን ደኅንነትና የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ሥራዎች እንዲገባ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ወስኗል። የሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓትንና መንግሥትን አስፈላጊነትና ቀጣይነት በአግባቡ ተረድታችሁ፣ ይህን ለማረጋገጥ የድርሻችሁ ሀገራዊ ግዴታ እንደምትወጡ እና ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንቅስቃሰያችሁን አጠናክራችሁ እንደምትቀጥሉ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ያምናል።

    የትግል ጥሪ፤

    የተከበርክ የትግራይ ሕዝብ፥ የራስን ዕድል በራስ የመወሰንና ራስን በራስ የማስተዳደር መብቶች ለመናድ ሕገወጡ የ’ብልፅግና’ ቡድን እየተከተለው ያለው የተቻኮለ አካሄድ እና የጦርነት አባዜ ሰላማዊና ሕጋዊ ትግል በማካሄድ ለመመከት የትግራይ ሕዝብ በተለይ ደግሞ የትግራይ ወጣቶች የትግል ዝግጁነታቸውና አደረጃጀታቸውንእንዲያጠናክሩ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ጥሪውን ያቀርባል።

    ኮሮና ቫይረስ በህልውናችን ላይ እና በጀመርነው የመመከት እንቅስቃሰያችን ለያደርስ የሚችለውን ተፅዕኖ በመረዳት፣ የባለሞያዎች ምክርና የመንግሥት መመሪያዎች በጥብቅ በመተግበር፣ ሕዝባችን ተገቢ ትኩረት በመስጠት እንዲመክተው ከከፍተኛ አደራ ጭምር ጥሪውን ያቀርባል። ህልውናችን፣ ሰላማችንና ልማታችን ለማረጋገጥ ደግሞ መላ ሕዝባችን የሚያጋጥሙትን ችግሮች ተሸክሞ፣ ምርቱና ምርታማነቱ ይበልጥ እንዲጠናክር በድጋሜ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    የተከበራችሁ የድርጅታችን ህወሓት አባላት፣ በየደረጃው ያላችሁ አመራሮች፥ አሁን ያለንበት መድረክ የሚጠይቀውን ፅናትና መስዋዕትነት በውል ተገንዝባችሁ፣ ሕዝባችን ለማዳን በሚደረገው ሁለንተናዊ ትግል ግንባር ቀደም ድርሻችሁ እንዲትወጡና አርአያነታችሁ አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ የህወሓት ማዕከላይ ኮሚቴ ጥሪውን ያቀርባል።

    የተከበራችሁ የክልላችን የሕዝብ ማኅበራትና ሲቪክ ተቋሞች፥ ዛሬም እንደትላንቱ ለሰላማችሁ፣ ለልማታችሁና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ከእናንተ በላይ ሊቆረቆር የሚችል ኃይል እንደሌለ ተገንዝባችሁ በመመከት እንቅስቃሴ በጠቃላይ፣ በተለይ ደግሞ ምርጫውን በድል እንዲጠናቀቅ በከፍተኛ ፍጥነት እንድቀጥሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    የተከበራችሁ የሀገራችን ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች፥ የአፈና፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ ጭቆናና የተለያዩ በደሎች እንዲሁም ሁለንተናዊ ችግሮች የጀመራችሁት ትግል አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ለመሠረታዊ መብቶች፣ ፍትህና እኩልነት በምታደርጉት ትግል ህወሓት ዛሬም እንደትላንቱ ከጎናችሁ እንደሚቆም ያረጋግጣል።

    የተከበራችሁ የሀገራችን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት፥ ሕገ-መንግሥቱን ለመናድ የተጀመረውን እንቅስቃሴ ሊያስከትለው የሚችል ሀገር የማፍረስና እልቂት በውል ተገንዝባችሁ፣ ይህ ተግባር እንዲቆም ታሪካዊ ኃላፊነታችሁ እንድትወጡ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    በሕገ-መንግሥት መሠረት የተዋቀራችሁ የሀገራችን የክልሎችና ተቋማት፥ ሕዝብ የሚያስቀድምና ሕገ-መንግሥቱን የሚያከብር መንገድ እንድትከተሉ እና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት በመናድ ላይ ከመሳተፍ እንድትቆጠቡ ጥሪያችን እናቀርባለን።

    የተከበራችሁ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለይ ደግሞ በትግራይ ሕግ አክብራችሁ የምትንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና አስተዋፅኦ ያላችሁ ኃይሎች፥ አሁን ያለው ተጨባጭ ሁኔታ በጥሞናና በዕውቀት በመመርመር የብልፅግና ቡድን የያዘው የጥፋት መንገድ እንዲቆም ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ፣ ከሕግና ከታሪክ ተጠያቂነት ራሳችሁን እንድታድኑ ጥሪ እናቀርባለን።

    የተከበራችሁ የትግላችን አጋር፣ የጎረቤት ሀገሮች ሕዝቦች በተለይ የኤርትራ ሕዝብ፥ አሁንም እንደ ትላንቱ የጋራ ችግሮቻችን ለመፍታት ትግላችንና ትብብራችን እንድናስቀጥልና ይበልጥ እንድናጎለብት ጥሪ እናቀርባለን።

    የተከበራችሁ የዓለማቀፍ ተቋሞች በተለይ ደግሞ ኢጋድ (IGD)አፍሪካ ሕብረት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታችሁ አካላት፥ በኢትዮጵያ በለውጥ ስም እየተካሄደ ያለው ዘግናኝ የሰብዓዊ መብት ጥሰት፤ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን የመናድና ሀገሪቱን የማፍረስ እንቅስቃሴ በጠራ መረጃ እና ዕውቀት እንዲሁም በከፍተኛ የኃላፊነት መንፈስ አወንታዊ ሚናችሁ እንድትወጡ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    ዘለዓለማዊ ክብርና ሞገስ ለጀግኖች ሰማዕታት!
    ድልና ድምቀት ለ29ኛው የግንቦት 20 ድል በዓል!
    አሁንም መስመራችን አጥብቀን እንመክት!
    ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ማዕከላይ ኮሚቴ
    ግንቦት 23 ቀን 2012 ዓ.ም.
    መቐለ

    የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ

    Anonymous
    Inactive

    የሠራተኞቻቸውን ደመወዝ የቀነሱ እና ከሥራ ያሰናበቱ 14 ሆቴሎች ተለይተው ታወቁ – የኢትዮጵያ የሆቴል ባለሙያዎች ማኅበር

    አዲስ አበባ (ኢፕድ) – የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ያስከተለውን የሥራ መቀዛቀዝ ምክንያት በማድረግ የሠራተኞቻቸውን ደመወዝ ያልከፈሉ፣ የቀነሱ እና ሠራተኞቻቸውን ከሥራ ያሰናበቱ 14 ሆቴሎች መለየታቸውን የኢትዮጵያ የሆቴል ባለሙያዎች ማኅበር አስታወቀ።

    የኢትዮጵያ የሆቴል ባለሙያዎች ማኅበር የኮምኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ እጅጉ እንደሻው ግንቦት 21 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደገለጹት፥ መንግሥት የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፉን ለመደገፍ ድጎማ ቢያደርግም አንዳንድ ሆቴሎች ሠራተኞቻቸውን እያሰናበቱ፣ እንዲሁም ደመወዛቸውን እያስቀሩና እየቀነሱ ነው።

    ሆቴሎችን መለየት የተቻለው ማኅበሩ በመሠረተው የቴሌግራም የመገናኛ ዘዴ መሆኑን ጠቁመው፥ ሠራተኞች የደረሰባቸውን ችግርና ሥራ የለቀቁበትን ደብዳቤ ይዘው መጥተዋል። ማኅበሩ የተገኙ የደብዳቤ ማስረጃዎችን በመያዝ ለኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበር ኮንፌዴሬሽን ማሳወቁን አቶ እጅጉ አመልክተዋል።

    “ተበድረን ለሠራተኛ አንከፍልም፤ መንግሥት እንደሚያደርግ ያድርጋችሁ” ያሉ ሆቴሎች መኖራቸውን የገለጹት አቶ እጅጉ፥ መንግሥት ያወረደውን መመሪያና ድጎማ ተፈፃሚ የሚያደርጉ አሠራሮችን እንዲያመቻች አሳስበዋል።

    እንደ አቶ እጅጉ ገለጻ፥ የሆቴል ሠራተኞች የትራንስፖርት አገልግሎት አያገኙም፤ የሚከፈላቸው ደመወዝ በፊትም አነስተኛ ነበር። በዚህ ወቅት የደንበኛ ጉርሻም አያገኙም። የትራንስፖርት ዋጋ በእጥፍ ጨምሯል:: ከአነስተኛ ደመወዛቸው ላይ ግብር ይቆረጥለታል:: በመሆኑም መንግሥት ለእንዲህ አይነት ሠራተኞች የግብር ቅናሽ ወይም ምኅረት እንዲያደርግላቸውና ሙሉ ደመወዛቸውን እንዲያገኙ አሳስበዋል።

    የኢትዮጵያ የሆቴል ባለሙያዎች ማኅበር ፀሐፊ አቶ ክፍሉ ገብረእግዚአብሔር በበኩላቸው፥ ሆቴል ያለሠራተኛ ባዶ ህንፃ ማለት እንደሆነ ገልፀው፥ “የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጊዜያዊ ነው፤ ነገ ያልፋል። ልምድ ያላቸውን የሆቴል ሠራተኞች ማሰናበት ለባለሀብቱም ለአገርም ክስረት ነው” ብለዋል።

    የሆቴል ሠራተኛ ዲፕሎማት እንደመሆናቸው በአግባቡ ካልተያዙ የሠራተኞች ዕጣ ለባለሀብቱም እንደሚተርፍ አመልክተው፥ “በዚህ ወቅት የተባረረ ሠራተኛ ነገ ቀን ሲወጣ ‘ና!’ ቢባል የሚመጣበት ሞራል አይኖረውም። የሆቴል ሠራተኛ ደንበኛን የሚያረካው በደስታ ሲሠራ ነው” ሲሉም አቶ ክፍሉ ተናግረዋል።

    በኢትዮጵያ የሆቴል ባለሙያዎች ማኅበር የሥልጠና እና ምርምር ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ ሥዩም እንደገለጹት፥ በሌሎች ሀገራት እንኳን ያልተደረገውን የኢትዮጵያ መንግሥት ለሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ ድጋፍ አድርጓል። ይህ ዓይነት ድጋፍ በሌሎች ዘርፍ አልተደረገም። መንግሥት ያደረገው ድጋፍ ግን ከታች ባለው የአፈፃፀም ችግር ክፍተት ታይቶበታል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 

    የኢትዮጵያ የሆቴል ባለሙያዎች ማኅበር የኮምኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ እጅጉ እንደሻው

    Anonymous
    Inactive

    በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሞታ በተገኘችው ተማሪ (ሃይማኖት በዳዳ) የተጠረጠረው ግለሰብ በቁጥጥር መዋሉን ፖሊስ አስታወቀ

    አዲስ አበባ (ኢፕድ) – ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ውስጥ የተገደለችው የወጣት ሃይማኖት በዳዳ ተጠርጣሪ ገዳይ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ስር ያዋለው የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪ የሆነውና በ20ዎቹ እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ ደግነት ወርቁ የተባለ ወጣት ሲሆን፥ ወጣት ደግነት ወርቁን ፖሊስ የ27 ዓመቷን ሃይማኖት በዳዳ ሕይወት በማጥፋት ጠርጥሮት በቁጥጥር ስር አውሎታል።

    ግንቦት 20 ቀን 2012 ዓ.ም. ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት ባካሄደው ክትትል ነው ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር የዋለው። ቀን ከሌሊት በተካሄደው በዚህ ክትትል የተያዘው ወጣቱ ደግነት ወርቁ ከሟች ጋር ምንም ዓይነት ትውውቅ እንዳልነበራቸው በቁጥጥር ስር በኋላ ለሰዓታት በተደረገ ምርመራ የወንጀሉን ዝርዝር ለፖሊስ አስርድቷል።

    ግለሰቡ የ12ኛ ክፍል ተማሪ እንደነበርና የኤች አይ ቪ ኤድስ መድኃኒት ለማግኘት ምርምር ላይ ስለሆንኩ የጥቁር አንበሳ ሐኪሞች ይርዱኝ በማለት ወደ ግቢው በተለያዩ ጊዜያት ይመላለስ እንደነበር ዘርዝሯል። ከዚያም በግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደልማዱ ለዚሁ ጉዳይ እንደመጣ ገንዘብ እንደተቸገረና ቢላዋ ይዞ በግቢው ውስጥ ከሚገኙ ቢሮዎች በአንዱ ላፕቶፕ ወይም ሞባይል ካገኘ ሰርቆ ሽጦ ለመጠቀም ሲዟዟር የሟች ክፍል ክፍት በመሆኑ መግባቱን አስረድቷል። ሟች ሃይማኖት በዳዳ ሞባይሏን እንድትሰጠው ጠይቋት እምቢ ስትለው መታገላቸውንና ከዚያም በያዘው ስለት ወግቷት ንብረቱን ይዞ መውጣቱን ተናግሯል።

    ፖሊስ ከሟች ጋር የቅርብ ግንኙነት የነበራቸው 12 ተጠርጣሪዎችን ይዞ ተጨማሪ ምርመራ ማድረጉን የግድያ ወንጀሎች ምርመራ ዳይሬክቶሬት ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ኢቲቪ) ገልጿል። ለፖሊስ ምርመራ ትልቅ አቅም የሆነው የሟች ወላጅ አባት ከሳምንት በፊት ለልጃቸው የሰጧት የ5 ሺ ብር ቼክ ነው።

    ገዳዩ በወቅቱ የሟችን ላፕቶፕና ሞባይል ፓስፖርት መታወቂያና ይህንን ቼክ ወስዶ ስለነበር ቼኩን የካ አካባቢ በአንድ ባጃጅ ተሳፍሮ አሽከርካሪውን መታወቂያ ስላልያዝኩ በአንተ መታወቂያ ይህንን ብር አውጣልኝ ብሎት የባጃጁ ሹፌርም (አቶ እንዳለማው ታረቀኝ) መልኩን አስተውሎ ስለነበር ምርመራው ከዚህ እንደጀመረ ፖሊስ ገልጿል፡

    ኮሚሽኑ በወቅቱ የሆስፒታሉ የደኅንነት (security) ካሜራ ከአገልግሎት ውጪ መሆኑን (‘update’ እንዳልተደረገ) እና የጥበቃ ሠራተኞችም ቢላዋ ተይዞ እስከሚገባ ፍተሻቸው አጋላጭ መሆኑንም ጠቁሟል ሲል የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ዘግቧል።

    ሃይማኖት በዳዳ ማነች?

    ወጣት ሃይማኖት በዳዳ ተወልዳ ያደገችው መተሃራ ከተማ ሲሆን፥ ወላጆች በአሁኑ ወቅት በአዳማ ከተማ ጎሮ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ይኖራሉ። በ2009 ዓ.ም. ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በ’ክሊኒካል ፋርማሲ’ የመጀመሪያ ዲግሪዋን በማዕረግ ያገኘች ሲሆን፥ በዚያው በተማረችበት ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት ስታገለግል ነበር። ከዚያም በ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሁለተኛ ዲግሪዋን በመከታተል ላይ እንደነበረች አባቷ አቶ በዳዳ ፈይሳ ተናግረዋል።

    የሃይማኖት አባት አቶ በዳዳ ፈይሳ ልጃቸው 2009 ዓ.ም ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ በ’ክሊኒካል ፋርማሲስት’ በማዕረግ ተመርቃ በዩኒቨርስቲው በመምህርነት ስታገለግል መቆየቷን ያስታውሳሉ። ከዚያም ሁለተኛ ዲግሪዋን ለመማር ወደ ጥቁር አንበሳ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተልካ ትምህርቷን በመከታተል ላይ እንደነበረች ይናገራሉ።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) እና ቢቢሲ አማርኛ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 

    ሃይማኖት በዳዳ

    Anonymous
    Inactive

    ኢትዮጵያ ውስጥ ማንኛውም ሰው ከቤት ውጪ ሲሆን የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ (ጭንብል) እንዲያደርግ የግዴታ መመሪያ ተሰጠ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ ኢትዮጵያ) – በኢትዮጵያ ማንኛውም ሰው ከቤት ውጪ በሚሆንበት ጊዜ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ (ጭንብል) ማድረግ ግዴታ ሆነ። የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በትላንትናው ዕለት (ግንቦት 19 ቀን 2012 ዓ.ም.) ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ፥ መግለጫው ከተሰጠበት ዕለት ጀምሮ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ (ጭንብል) ከቤት ውጪ በሁሉም ቦታዎች ማድረግ ግዴታ እንደሆነ ያትታል። ሙሉ ጋዜጣዊ መግለጫው እንደሚከተለው ይነበባል።

    ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

    በሀገራችን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከተከሰተበት እለት ጀምሮ በመንግሥትና በባለድርሻ አካላት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ሲሆን ትዕዛዞች፣ ክልከላዎችና መልዕክቶች እየተላለፉ ነዉ። እነዚህን መልዕክቶችና ትእዛዞች ሰምቶ ለራስ በመፈጸምና ሌሎችን እንዲፈፅሙት በማድረግ በኩል በአንዳንድ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተሻሉ ሁኔታዎች ቢኖሩም ነገር ግን በርካታ በሚባለዉ ሕብረተሰቡ ዘንድ የመዘናጋት፣ የቸልተኝነትና በሽታዉን አስመልክቶ የሚሰጡ ትእዛዛቶች ወደ ጎን በመተዉ የሚሰጡ መግለጫዎችን የመላመድና ትኩረት ያለመስጠት ሁኔታዎች እየተስተዋለ ይገኛል።

    በቅርቡ በመንግሥት ተቋማት፣ በልማት ድርጅቶችና በግል ተቋማት ወሰጥ ያደረግነዉ ምልከታ ከቅደመ ጥንቃቄ ጋር በተያያዘ የመዘናጋት፣ ትኩረት ያለመሰጠት ሁኔታ አሳሳቢ እንደሆነ ለማረጋገጥ ችለናል። ማኅበረሰባችን በተለያዩ ቦታዎች ላይ በተለይም በግብይት ቦታዎችና በትራንስፖርት አገልግሎት መሰጫ አካባቢ እያሳየ ያለዉ መዘናጋትና ሕጎቹን ያለማክበር ጉዳይ አሳሳቢ ነዉ።

    ይህ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በሀገራችን በተገኘበት እና የአሰቸኳይ ጊዜ አዋጅ በታወጀበት ሰሞን የነበሩ ጥንቃቄዎች ጋር ሲነጻጸር እየቀነሰ መዘናጋት እየጨመረ ሲሆን፥ በተቃራኒዉ አሁንም በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱ እጅጉን አሳሳቢና ዋጋ የሚያስከፍል ጉዳይ እየሆነ ይገኛል።

    መንግሥት በሽታዉን ለመከላከልና ስርጭቱን ለመቀነስ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አዉጆደንብና መመሪያዎችን በማዉጣት ተግባራዊ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ከዚህ ቀደም የወጡ መመሪያ ቁጥር 1/2012 እና መመሪያ ቁጥር 2/2012 ማሻሻያዎችን የያዘ መመሪያ ቁጥር 4/2012ን አፅድቆ ሥራ ላይ እንዲዉል አቅጣጫ ሰጥቷል። በዚሁ መሠረትም በመመሪያ ቁጥር 4 በኮድ 2 የቤት ተሸከርካሪዎች ተጥሎ የነበረዉ ከፊል የእንቅስቃሴ ክልከላ፣ የማሰክ አጠቃቀም፣ በአገር አቋራጭ የሕዝብ ተሸከርካሪዎች ላይ እንዲሆም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ሠራተኞች መግቢያና መዉጫ ስዓት ላይ ማሻሻያ አድርጓል።

    የኮድ ሁለት የቤት ተሸከርካሪዎች ላይ መጣል ሚገባው የትራንስፖርት ሚኒስቴር በኩል የተደረገውን ጥናት መነሻ በማድረግ በከፊል በመገደብ ግለሰቦች ቤታቸዉ እንዲዉሉ በማድረግ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ታሳቢ ተድርጎ በሙሉና በጎዶሎ መለያ ቁጥር ከፊል እገዳ ተጥሎ መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን ሆኖም የኮድ 2 ተሸከርካሪ ባለቤቶች በታሰበዉ መልኩ ቤታቸዉ ከመዋል ይልቅ የሕዝብ ትራንስፖርት በመጠቀም እና ታርጋዎችን እየቀያየሩ የመጠቀም ሁኔታ መታየቱ እንዲሁም ተራቸዉ ባልሆነ ቀን ቤታቸዉ ከመዋል ይልቅ በሰፊዉ የመንቀሳቀስ ሁኔታ የተስተዋለ መሆኑ ክልከላዉን መልክ መቀየር አሰፈላጊ ሆኗል። በመሆኑም በአጠቃላይ በኮድ ሁለት የቤት ተሸከርካሪዎች ተጥሎ የነበረዉ ክልከላ ተነሰቶ አጠቃላይ የትራንስፖርት እንቅስቃሴውን ለመገደብ የሚያስችል አማራጭ ክልከላ እንድተገበር የሚኒስትሮች ኮሚቴ ወስኗል። የእንቅስቃሴ ገደብ መቀነሻ አሠራሮች አንዱ የሆነዉ በሀገር አቋራጭ ተሸከሪካሪዎች የሚንቀሳቀሱ ሰዎችን ቁጥር መቀነስ ነው።

    የዋጋ ጭማሪ ማድረግ ሰዎች ከቦታ ቦታ እንዳይንቀሳቀሱ ለመገደብ አሰተዋጽኦ እንደሚያደረግ በትራንስፖርት ሚኒስቴር የተደረገው ጥናት ያመላክታል። በዚሁ መሠረት አገር አቋራጭ የሕዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪዎች መደበኛ የወንበር አቅማቸዉ ከ45 (አርባ አምስት) ሰዉ በላይ የሆነ ተሸከርካሪዎች የሚያስከፍሉት የታሪፍ ጭማሪ ከመደበኛ ዋጋዉ 75% እንዲሆን የተወሰነ ሲሆን መደበኛ የወንበር ቁጥራቸዉ እስከ (45) አርባ አምስት ሰዉ የሆኑ የሕዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪዎች የሚያስከፍሉት የታሪፍ ጭማሪ ደግሞ 100% መሆኑ ተወሰኗል።

    በተያያዘ የሚኒስትሮች ኮሚቴ በተሻሻለዉ መመሪያ መሠረት የማስክ አጠቃቀምን አስመልክቶ ከቤት ዉጭ በማንኛዉም ቦታ የአፍ እና አፈንጫ መሸፈኛ ማስክ ማድረግን ግዴታ እንዲሆን ወስኗል። የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ በፋብሪካዎች የተሠራ ወይም ባህላዊ ጨርቅ ሊሆን ይችላል። ይህን ግዴታ በማሰፈጸም ረገድ የጸጥታ መዋቅሩ ኃላፊነት እንዳለበት ተወሰኗል።

    በሌላ በኩል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ መግቢያ ስዓት 1፡30 እንዲሆን የተቀመጠ ሲሆን መዉጫ ስዓቱም 9፡30 እንዲሆን ተደርጎ ተሸጋሽጓል። ይህም የትራንስፖርት መጨናነቅ ለመቀነስ ነው።

    በአጠቃላይ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሁሉም ሕብረተሰብ ኃላፊነትና ግዴታ ያለበት በመሆኑ የሚታዩ መዘናጋቶችን እና ችላ ባይነትን በመቅረፍ ሁላችንም ህግና ሥርዓቱን ማክበር ግዴታ እንደሆነ በመገንዘብ መላዉ የሀገራችን ሕዝብ እራሱ፣ ቤተሰቡንና ሀገሩን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከሚያስከትለው ጉዳት ለአፍታም ሳይዘናጋ ለመጠበቅ ርብርብ እንዲያደረግ ጥሪያችንን እናቀረባለን።

    የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ
    ግንቦት 19 ቀን 2012 ዓ.ም.
    አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

    የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ (ጭንብል)

    Anonymous
    Inactive

    “የትግራይ ሕዝብ ህወሓትን በቃህ ሊለው ይገባል” አቶ ደረጀ በቀለ – የኢትዮጵያ ፌዴራሊስት ኃይሎች ጥምረት ሊቀመንበር

    አዲስ አበባ (አዲስ ዘመን) – የትግራይ ሕዝብ ህወሓትን (ህዝበ ወያኔ ሃርነት ትግራይ) በቃህ ሊለው እንደሚገባ የኢትዮጵያ ፌዴራሊስት ኃይሎች ጥምረት ሊቀመንበር አስታወቁ። 45 ዓመታት የዘለቀው የህወሓት ትግል የጉዞ ምዕራፉ ወደመጠቃለሉ መቃረቡንም አመልክተዋል።

    ሊቀመንበሩ አቶ ደረጀ በቀለ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳመለከቱት፥ ህወሓት የትግራይን ሕዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመነጠል የሚያደርገውን አካሄድ ተገንዝቧል፤ በቃህ ሊለው ይገባል። የትግራይ ወጣቶች፣ የትግራይ ምሁራን፣ በትግራይ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ፖለቲካ ፓርቲዎች ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው አመልክተው፣ ላለፉት 45 ዓመታት ያደረጋቸውን በማሰብ፤ የህወሓትን አመራሮች በቃችሁ ሊሏቸው እንደሚገባ አስታውቀዋል።

    የትግራይ ወጣት የህወሓትን ወቅታዊ አካሄድ እንደማይቀበለው መገንዘባቸውን የጠቆሙት አቶ ደረጀ፥ ሕዝቡ ከድህነት መውጣትን የሚፈልግ መሆኑን አመልክተዋል። ህወሓት የዘረፈውን ወደአውሮፓና መሰል አገሮች ከማሸሽ የዘለለ ለሕዝቡ የሰራለት ነገር እንደሌለም መታዘባቸውን ተናግረዋል። በተለይ በትግራይ ያለው የገጠር ሕዝብ ስለህወሓት መሰሪነትና ተንኮል በደንብ ይገነዘባል ያሉት ሊቀመንበሩ፥ የትግራይን ሕዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመነጠል የሚያደርገውንም አካሄድ ሕዝቡ መገንዘቡን አመልክተዋል። የትግራይ ተወላጆችና የትግራይ ሕዝብ ህወሓትን በቃህ ሊሉት እንደሚገባም ጠቁመዋል።

    እንደእርሳቸው ማብራሪያ፤ የህወሓት አመራሮች በመቐለ ብቻ ሳይሆን በአዲስ አበባና በሌሎች ክልሎች ጭምር ከህንጻ እስከተሽከርካሪ የሚገለጽ ሀብት አከማችተዋል። በአንጻሩ በክልሉ የዕለት ጉርሱን፣ ጫማና ልብስ ማሟላት እንኳን ያቃተው ሕዝብ (በተለይ በገጠሩ) ተፈጥሯል። የህወሓት አመራሮች ለዚህ ሕዝብ ታግለንለታል ካሉ ሕዝቡ ነጻ መውጣት ነበረበት፤ ቢያንስ ትንሽ መሻሻልም ሊያሳይ ይገባ ነበር። ስለሆነም የትግራይ ሕዝብ፣ ልሂቃንና ሌላውም የሕብረተሰብ ክፍል የሚያደርጉትን ድጋፍ ማቆም አለባቸው ሲሉ መክረዋል።

    በየክልሉ ተበትነው ያሉና በውጭ አገራት የሚገኙ የትግራይ ተወላጆችም ለህወሓት የሚያደርጉትን ድጋፍ ቆም ብለው እንዲያስቡ ጥሪ አቅርበዋል። በሚያደርጉት ድጋፍ በአገራቸው ለውጥ ስለመኖሩ መመልከት እንዳለባቸው፣ ህወሓት 27 ዓመታት ኢትዮጵያን ሲገዛና ሀብቱን እንደፈለገው ሲያሽከረክር ለትግራይ ሕዝብ ምን አደረገ? ብለው ሊያስተውሉ ይገባል ሲሉ አመልክተዋል።

    ችግር ሲመጣባቸው መቐለ ተሰበሰቡ እንጂ አካባቢውን እንኳን አይተው የማያውቁ ብዙዎች ናቸው ያሉት ሊቀመንበሩ፥ ክልሉን ባስጎበኟቸው ጊዜ አምባሳደር ስዩም መስፍን በተገኙበት የጉብኝት መርሐ ግብር የአምባሳደር ስዩም የትውልድ አካባቢ መመልከታቸውን አስታውሰው፤ የአካባቢው ነዋሪዎች አምባሳደር ስዩምን ከዛን ዕለት በስተቀር እንደማንኛውም ሰው በቴሌቪዥን ከመመልከት ውጪ በአካል አይተዋቸው እንደማያውቁ እንደነገሯቸውም ነው የገለጹት።

    በክልሉ፣ በሌሎች ክልሎችና በውጭ አገራት የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች ሕወሓት ለሕዝቡ ምን አደረገለት ወይም ምን አደረገበት ብለው ሊመረምሩ እና እነዚህን ግለኛ አመራሮች በቃ ሊሏቸው እንደሚገባ በመጠቆም፥ የትግራይ ሕዝብ እንደሌሎች ኢትዮጵያውያን ወንድሞቹ የሚፈልገውን ፓርቲ ደግፎ የነጻነት አየር መተንፈስ እንዲችል ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

    የትግራይ ሕዝብ ትክክለኛ አካሄድ የሚሄድ ኢትዮጵያዊ መሆኑን በመጠቆምም፤ የትግራይን ሕዝብ እገነጥላለሁ ብሎ የሚፎክረው ህወሓትም የግል ስሜትና ፍላጎቱን እንጂ የሕዝቡ ፍላጎትና ድጋፍ እንዳልሆነም ተናግረዋል። ሕዝቡ ለህወሓት ባዶ ፉከራ ሳይሆን ለኢትዮጵያዊነቱ ቅድሚያ የሚሰጥ፣ ኢትዮጵያዊነቱን እንደሚያከብር መገንዘባቸውንም አቶ ደረጀ ተናግረዋል። ህወሓት ለራሱ ጥቅምና ስልጣን ማስቀጠያ በሚያመች መልኩ እንጂ ለክልሉ ሕዝብም ሆነ ለክልሉ የተሻለ እድገት ሲል ያከናወነው ነገር አይታይም ብለዋል። በትግራይ ክልል እየሆነ ያለው የማግለል ተግባር ግን የህወሓት ሥራ ውጤት እንጂ የሕዝቡ ፍላጎትም ተግባር እንዳልሆነም አስታውቀዋል።

    የትግራይ ሕዝብ በድህነት ውስጥ የሚገኝ፣ በአፈና ውስጥ ያለ፤ ከስጋት ያልተላቀቀ መሆኑን ገልጧል። እንደሌሎች ኢትዮጵያዊ ወገኖቹ የፈለገውን የመደገፍ የሚፈልግ፣ ከተወሰኑ የህወሓት ቡድኖች አፈና መውጣትን የሚናፍቅ መሆኑንም ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ ሕዝብም ለህወሓት ባዶ ፉከራ ሳይሆን ለዚህ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ የትግራይ ሕዝብ ጆሮ ሰጥቶ የሕዝቡን እውነት ማድመጥ እንደሚኖርበት ደረጀ በቀለ አመልክተዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አቶ ደረጀ በቀለ

    Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለጭነት አገልግሎት ተግባር በ22 የመንገደኛ አውሮፕላኖቹ ላይ የምህንድስና ማስተካከያ /conversion/ አደረገ

    አዲስ አበባ (የኢትዮጵያ አየር መንገድ) – እንደሚታወቀው የዓለማችንን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ደረጃ ያስቆመው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ (COVID-19) ከሌሎች ዘርፎች በተለየ ሁኔታ የአየር መንገድ ኢንዱስትሪውን ከ90 በመቶ በላይ እንዲቆም አድርጓል። በዚህም የተነሳ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የመንገደኛ በረራዎቹን በተመሳሳይ ሁኔታ ከ90 በመቶ በላይ እንዲቆሙ በመደረጋቸው የተነሳ የአየር መንገዱን ህልውና የሚፈታተንና በታሪኩ የመጀመሪያ ከሆነው ዓለምአቀፋዊ ቀውስ ለመውጣት ሙሉ በሙሉ የሥራቴጂክ እቅድ ለውጥ በማድረግ የትኩረት አቅጣጫውን ወደ እቃ ጭነት ቢዝነስ በማዞር እየሠራ ነው። ከዚህም ጋር በተያያዘ በመላው ዓለም እየጨመረ ለመጣው የጭነት አገልግሎት (cargo service) ፍላጎት በነበሩት የጭነት ማመላለሻ አውሮፕላኖች አጠናክሮ አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል። ይህንን አዲስ ስትራቴጂ በመጠቀም የጭነት ማጓጓዝ አቅሙን ለማሳደግ ተጨማሪ 22 የመንገደኛ አውሮፕላኖችን (passenger planes) የጭነት አገልግሎት እንዲሰጡ በውስጥ አቅም የምህንድስና ማስተካኪያ (conversion) ተደርጎባቸው በጭነት አገልግሎት ሥራ ላይ ይገኛሉ።

    አየር መንገዱ በመንገደኛ አውሮፕላኖቹ ውስጥ የሚገኙ መቀመጫዎችን ከቦታቸው በማንሳት ስፍራው ለጭነት አገልግሎት እንዲውል ያደረገው ዓለምአቀፍ የአቪየሽንና የቴክኒክ ተቆጣጣሪ አካላት ያስቀመጧቸውን መስፈርቶች በመከተልና በማሟላት ነው። አየር መንገዱ የኮሮናን ቫይረስ ወረርሽኝን ለመዋጋት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ሕይወት አድን የሆኑ የሕክምና ቁሳቁሶችን በመላው አፍሪካ በማጓጓዝ ላይ ይገኛል። የአገልግሎት ተልዕኮውን በብቃት ለመወጣትም በመንገደኛ አውሮፕላን የእቃ ማስቀመጫ ቦታ፣ እንዲሁም የአውሮፕላኖቹ ወንበሮች ሳይነሱ ጭነት በመጫን አገልግሎቱን በማቀላጠፍ ላይ ይገኛል።

    አቶ ተወልደ ገብረማርያም፥ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የጭነት አገልግሎት ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን አስመልክተው፥ “የመንገደኛ አውሮፕላኖቻችንን ለጭነት አገልግሎት እንዲውሉ በማጥናትና በማስተካከል የምህንድስና ሥራ ላይ የተሳተፉትን የአየር መንገዳችን የአውሮፕላን ጥገና ክፍል /MRO/ ብቁ ባለሙያዎችን ከልብ አደንቃለሁ፤ አመሰግናለሁ። ይህ ተግባር በዚህ አስቸጋሪ ወቅት የበርካታ ደንበኞቻችንን ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችለንን የተሻለ አቅም ለመፍጠር ያስችለናል። በዓለማችን የሚገኙ ሕዝቦች የተከሰተውን ወረርሽኝ ለመመከት የሚያስችላቸውን የሕክምና ቁሳቁስም ሆነ ሌሎች የመሠረታዊ ፍሎጎት ቁሶች በእጅጉ የሚፈልጉበት ጊዜ ላይ እንገኛለን። በዚህ ታሪካዊና አስቸጋሪ ወቅት ይህንን ዓለምአቀፍ ወረርሽኝ ለመዋጋት ዋነኛ ተዋንያን በመሆናችን ደስተኞች ነን። ከዚህም ጋር በተያያዘ አገልግሎታችንን አሁን ካለበት በላቀ ደረጃ ለማሳደግ የተለያዩ አማራጮችን በማጤን ላይ እንገኛለን።” ብለዋል።

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ ፈታኝ በሆነው በዚህ ወቅት የዓለምን ማኅበረሰብ ለማገልገል ባደረገው ጥረት ሕይወት አድን የሆኑ የሕክምና መሣሪያዎችን በበርካታ መጠንና ፍጥነት ያጓጓዘ ሲሆን፣ በዚህም አጠቃላይ የአገልግሎት ብቃቱን በማስመስከሩ ምስጋናና አድናቆት እየተቸረው ይገኛል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኢትዮጵያ አየር መንገድ

    Anonymous
    Inactive

    በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ የሰጠው መግለጫ

    ከሁሉ አስቀድመን በመቐለ ከተማ በጠራራ ፀሀይ ክልሉን እየገዛ ባለው ፓርቲ በታጠቁ ሀይሎች በጥይት ተደብድቦ በተገደለው ትግራዋይ ወጣት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን፤ ለቤተሰቦቹ ለወዳጆቹና ለአብሮ አደግ ጓደኞቹ እንዲሁም ለሰላም ወዳድ የትግራይ ሕዝብ መፅናናትን እንመኛለን።

    በአሁኑ ሰዓት አገራችን ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተዉ ገዳይና አሰከፊ የሆነዉን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከሕዝብ ጋር በመሆን የመከላከል እና ሕዝብን የማዳን ሥራ እተሠራ ይገኛል።

    በዚሁ ሁኔታ መንግሥትና ፓርቲያችን ዘርፈ-ብዙ የሆኑ የሪፎርም ሥራዎችን በማከናወንና በመተግበር ላይ ይገኛል። ከእነዚህ ጉልህ ዘርፈ ብዙ አወንታዊ ዉጤቶች ባሻገር የተለያዩ ችግሮችና ተግዳሮቶች አብይ ፈተና ሆነዋል። በተለይም በግጭት አትራፊዎች በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሚፈጥሩትና በሚቀሰቅሱት ግጭቶችና ሁከቶች ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ሲቀጥፍ መመልከት እየተለመደ መጥቷል። ይህም ድርጊት ለሕዝቦች ሆነ ለሀገራዊ አንድነት የማይበጅ እንዲሁም አሳዛኝ ድርጊት ነዉ።

    ሕዝባችን በዚህ ፈታኝ ወቅት ያጋጠመውን ድርብ ፈተናና ችግር በማለፍ ወደሚፈልገውና ወደሚገባው የሰላም፣ የብልጽግና የመረጋጋት፣ የዲሞክራሲና የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በመንግሥት ሆነ በፓርቲ በተለያዩ ደረጃዎች የሚገኙ የመንግሥት አመራሮችና ሠራተኞች ሕዝባዊነታቸው፣ የአመራር እሴቶቻቸውና ጥበባቸው የሚፈተንበት ታሪካዊ ጊዜ ላይ እንደምንገኝም ማስተዋልና መበርታት ይገባል።

    ሆኖም መንግሥት ከሕዝብ ጋር በመሆን ችግሮችንና ተግዳሮቶችን በመለየትና ቅድሚያ በመስጠት እንዲሁም የስጋት ደረጃና መጠኖችን በመመርመርና በመፈተሽ ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ያላሰለሰ ጥረት እየተደረገ ባለበት ሁኔታ ፀረ ለውጥና ጸረ-ኢትዮጵያዊያን ኃይሎች ሆን ብለዉና አቅደዉ በተሳሳተ መንገድ ሕዝቡን በማደናገርና ወደ ጥፋት ጎዳና ለመምራት እየሠሩ ይገኛሉ።

    በተጨማሪም ይህንን አስቸጋሪ የታሪክ አጋጣሚ ለግላዊ ጥቅማቸዉና ፍላጎታቸው ለማሟላት ሕዝብንም ሆነ ሀገርን የሚጎዱ አስነዋሪና አጸያፊ ተግባሮችን በመፈፀም ላይ እንደሚገኙ የአደባባይ ምስጢር ከሆነ ሰነባብቷል።

    የትግራይ ሕዝብ የቅርብ ሆነ የሩቅ ታሪኩ እንደሚያሳየው፣ ጭቆናንም ሆነ አፈናን የሚፀየፍ ለኢትዮጵያ አንድነት መስዋዕት የከፈለ ሕዝብ ነው። በትግሉና በመስዋዕትነቱም ለመላው የሀገራችን ሕዝቦች ጉልህ ሕዝባዊ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ የበኩሉን ድርሻ የተወጣና በመወጣትም ላይ ያለ ሕዝብ ነዉ። የትግራይ ሕዝብ ከሌሎች ሕዝቦች ጋር በአንድነት በመሆን ባካሄደው እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ በከፈለው መስዋዕትነት የሰላምና ዲሞክራሲ ብልጭታ የማየት ፍላጎቱ በቀረበው ቁጥር የሚሸሽበት ምናባዊ ዓለም ብቻ እየሆነበት መጥቷል። ከሁለት ቀናት በፊት በመቐለ ከተማ የተከሰተው ለአንድ ወጣት ክቡር ሕይወት ህልፈትና ለሁለት ወጣቶች የመቁሰል አደጋ በክልሉ ዉስጥ የሰላምና ዲሞክራሲ እጦት ማሳያ ነዉ።

    በሰላም ወዳዱና እንግዳ አክባሪ በሆነዉ የመቐለ ከተማ ነዋሪ መሪር የሀዘንና ውጥረት ድባብ ዉስጥ ይገኛል። ይህ ክቡር የሰው ሕይወት የጠፋበትና ከባድ የመቁሰል አደጋ ያጋጠመበት ክስተትም ሰላምንና ፀጥታን በሕግ አግባብ ለማስጠበቅ ኃላፊነት በተሰጠው የፀጥታ አካል የተፈፀመ መሆኑ እጅጉን በጣም አሳዛኝ ያደርገዋል። ይህም ድርጊት ብዙ መስዋዕት ለከፈለ የማይገባዉ ነዉ። በመሆኑም የወጣቱ ግብረመልስም በክልሉ ሰላምና ዲሞክራሲ ጉዳይ ላይ የኔ ጉዳይ ነዉ የሚል ከፍተኛ የሰላም፣ የልማትና የለውጥ ፍላጐቶችና ቁርጠኝነት እንዲሁም ዝግጁነት መኖሩን በግልፅ አሳይቷል።

    እንደሚታወቀዉ በአስቸኴይ ጊዜ አዋጅ የማስተዳደርና የማሰፈፀም አግባቦች ውስጥ የሰው ልጅን ዲሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብቶችን ማክበርና በሕግ የማስከበር ተግባር ላይም የፀጥታ አካላት የላቀ ሰብአዊነት፣ ታጋሽነትና፣ ፍፁም ሕዝባዊነትን የተላበሱ መሆን ይገባቸዋል። የዲሞክራሲና የተሻለ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ልምድ ጉዳይ ከአስተምህሮት ስርፀትና ግልፅ ተጠያቂነትን ከማስፈን አሠራር ጋር በቀጥታ የሚገናኝ ጉዳይ ሲሆን፤ ዜጎች በመንግሥታቸው የደኅንነት ስሜት እንዲሰማቸው የሚያደርግ ቢሆንም እንደ አለመታደል ሆኖ በትግራይ ክልል በወቅቱ የሚስተዋሉ ሕገ-ወጥ ክስተቶች አፈናና ግልፅ የሰብዓዊ መብት ረገጣ እንዳለ ማስተዋል ተችሏል። በተለይም እራሳቸውን ለመከላከል በማይችሉ ወጣቶች ላይ መተኪያ የሌለውን ክቡር ሕይወታቸዉን እስከመቅጠፍ የደረሰ የኃይል እርምጃ በየትኛውም መለኪያ መወገዝ ያለበትና ፈፅሞ ተቀባይነት የሌለው እኩይ ተግባር ነው። ድርጊቱም በፍጥነት ተጣርቶ የተወሰደው እርምት እርምጃ ለሕዝብ ይፋ እንዲደረግ አጥብቀን እንጠይቃለን።

    ይህ እኩይ ተግባር በተለይ በክልሉ ወጣቶች ላይ ያነጣጠረ በመሆኑ፣ ይህን መሰል የአፈና ተግባር የክልሉ ወጣት ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መልኩ አጥብቆ እንዲታገለው የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ጥሪውን እያቀረበ፤ በአጠቃላይ ሀገራዊ የለውጥ እንቅስቃሴዎች ላይ የነቃ ፖለቲካዊ ተሳትፎ በማድረግ በክልሉና በሀገር ደረጃ የተደቀኑ ችግሮችን ለመቅረፍ በምታደርጉት እንቅስቃሴ ፓርቲያችን ድጋፉ እንደማይለያችሁ ለመግለፅ እንወዳለን።

    “ወደ ሕዝብ የተኮሰ ውድቀቱን አፋጠነ” እንደሚባለው፣ የገዢዎች የውድቀት ምልክት የሚጀምረዉ ወደ ሕዝብ መተኮስ የጀመሩ ዕለት ነው። ስለሆንም በትግራይ ክልል በተለይ ደግሞ በመቐለ ከተማ ባጋጠመው ክስተት፣ በክልሉ የዲሞክራሲና የሰብዓዊ መብት አያያዝ ጉዳይ የክልሉ ገዢ ፓርቲና መንግሥት አካሄዱን ቆም ብሎ እንዲመረምር አስገዳጅ ማንቂያ ደወል ነው። የትግራይ ብልፅግና ፓርቲም ጉዳዩን በአፅንኦት እንደሚከታተለውና ለሚመለከታችሁ ሁሉ በጥብቅ ያሳስባል።

    በዚህ አጋጣሚ ለሁሉም የትግራይ ወጣት እና ለውጥ ፈላጊ ኃይል ከትግራይ ብልፅግና ፓርቲ ጋር በመሆን የለውጥ ሂደቱን እንዲያፋጥኑ ከፓርቲያችን ጋር እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ፓርቲያችን የትግራይ ሕዝብ እንደማንኛዉም ኢትዮጵያዊ የሚገባዉን ጥቅም እንዲረጋገጥ እና ሃገራዊ አንድነቱ እንዲጠናከር ይሠራል። በጥቂት ገዥ የህወሓት ቡድን በተለይ በዝምድና እና ጥቅም ትስስር እንዲሁም በሥልጣን ጥማት ምክንያት ትግራይን ከሌሎች የሀገሪቱ ሕዝቦች ለመነጠል የሚደረግ ሥራም ሆነ ሴራ በጥብቅ የምንታገለዉና የምናወግዘዉ መሆኑን በጥብቅ እናሳዉቃለን።

    በመጨረሻም ለሟች የዘለዓለም እረፍት፣ ለቤተሰብና ወዳጅ ዘመዶች መጽናናትን ከልብ እንመኛለን።

    የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ
    ግንቦት 11ቀን 2012 ዓ.ም.

    የትግራይ ብልፅግና ፓርቲ

    Anonymous
    Inactive

    ከአብሮነት ለኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት (አብሮነት) የተሰጠ መግለጫ

    አብሮነት ለኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት (አብሮነት) ከግንቦት ወር 2010 ዓ.ም. ጀምሮ በሀገራችን የተከሰተው “የለውጥ ሂደት” መሠረታዊ የሀገሪቱን የፖለቲካ ችግሮች ለመፍታት በሚያስችል አግባብ ያልተካሄደና የከሸፈ መሆኑን በመገንዘብ ሀገሪቱን ወደ አንድ አዲስና ጤናማ የሽግግር ሂደት የሚያስገባ አማራጭ ሃሳብ በረቂቅ ደረጃ አዘጋጅቶ ለሕዝብ ውይይት ማቅረቡ ይታወቃል።

    ከኮሮና ቫይረስ ወደ ሀገራችን መግባት ጋር በተያያዘ በረቂቅ ሰነዱ ላይ በአሰብነው መጠን ሕዝባዊ ውይይቶችን ማካሄድ ባንችልም በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ቀላል የማይባል የሕብረተሰብ ክፍል በረቂቅ ሰነዱ ላይ አስተያየት እንዲሰጥበት ማድረግ ተችሏል። በአብሮነት አባል ፓርቲዎች ውስጥ ያሉ መዋቅሮች በረቂቁ ላይ በስፋት እንዲወያዩበት የተደረገ ሲሆን፥ ከተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ከተገኙ ግብአቶች በተጨማሪ ከ700 በላይ የሆኑ አስተያየቶች በኢሜል (email) አማካኝነት መሰብሰብ ተችሏል። የተለያዩ ምሁራንና የፖለቲካ መሪዎችም ሰነዱ እንዲደርሳቸውና ሃሳብ እንዲሰጡበት ማድረግ ተችሏል።

    እነዚህን ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተገኙ አስተያየቶች ባገናዘበ ሁኔታ የአብሮነት አባል የሆኑት ሦስቱ ፓርቲዎች በረቂቅ ሰነዱ ላይ ሰፊ ውይይትና ክርክር ካካሄዱበት በኋላ ገንቢ የሆኑ ማሻሻያዎችን በረቂቅ ሰነዱ ላይ በማድረግ ይህንን የእርቅና የአንድነት የሽግግር መንግሥት እንዲቋቋም የሚጠይቅ ሰነድ የጋራ ሰነዳቸው እንዲሆን ተቀብለውታል። በይዘት ደረጃ ማሻሻያ የተደረገባቸው ጉዳዮችም ሁለት ናቸው።

    አንደኛ- ሀገር አቀፍ የሕዝብና የቤት ቆጠራ ጉዳይ አወዛጋቢ የፖለቲካ አጀንዳ እየሆነ በመምጣቱ የሽግግር መንግሥቱ አንዱ ኃላፊነት የሕዝብና ቤት ቆጠራ ማካሄድ እንዲሆን፤ ሁለተኛ- የሽግግር መንግሥቱ የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ረቂቅ የማቅረብ ብቻ ሳይሆን በሕዝበ-ውሳኔ ሕገ-መንግሥት የማሻሻል ኃላፊነት እንዲኖረው የሚያደርግ ነው። እነዚህንና ሌሎች መለስተኛ ማሻሻያዎችን በማድረግ ሰነዱ ከዛሬ ግንቦት 10 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ የሦስቱ አባል ድርጅቶችና የአብሮነት ኦፊሴላዊ ሰነድ እንዲሆን የተወሰነ ሲሆን፥ የሀገራችን የፖለቲካ ኃይሎችና ሕዝቡ ጥያቄውን እስከሚቀበሉት ድረስ ሰነዱ አንድ ቁልፍ የፖለቲካ የመታገያ አጀንዳችን ሆኖ እንዲቀጥል ተወስኗል።

    አብሮነት በወቅታዊው የሀገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ላይ የረጅም ጊዜ ግምገማ አካሂዶ የደረሰበት አቋም “ሀገራችን ኢትዮጵያ ከእንግዲህ መዋቅራዊ ችግሮቿን በአስተማማኝ ሁኔታ ሊፈታ በሚችል ውጤታማ የሽግግር ሂደት ውስጥ ማለፍ እስካልቻለች ድረስ እንደተለመደው በየአምስት ዓመቱ የይስሙላ ምርጫ በማካሄድ ወደ መዋቅራዊና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ልትሸጋገር አትችልም” የሚል ነው።

    በአሁኑ ወቅት በስልጣን ላይ የሚገኘውና ከሁለት ዓመት በፊት ስልጣን ለመያዝ የበቃው ብልፅግና ፓርቲ በሀገሪቱ ውጤታማ ሽግግር ለማካሄድና ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ቃል ገብቶ የነበረ ቢሆንም ቃሉን ጠብቆ የኢትዮጵያን ሕዝብ ወደ መዋቅራዊ ዲሞክራሲ ማሸጋገር አልቻለም። ፓርቲው ለሕዝብ የገባውን ቃል ወደ ተግባር ለመለወጥ የሚያስችል እውቀትና ልምድ ብቻ ሳይሆን ቅንነትና ፍላጎት የሌለው ኃይል በመሆኑ ምክንያት ሀገሪቱን ወደ በጎ አቅጣጫ ከመምራት ይልቅ የራሱን የፖለቲካ ስልጣን በማጠናከር ወደ ለየለት አምባገነናዊ ኃይልነት መቀየርን የመረጠ ይመስላል።

    ይህ ኃይል እራሱንም ሆነ ሀገሪቱን ወደ ከፍተኛና ውስብስብ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ከማስገባቱ በፊት፥ በሀገሪቱ የምንገኝ የፖለቲካ ኃይሎችና የሀገሪቱ ዋና ባለቤት የሆነው ሕዝብ ተባብረን በሕጋዊና ሰላማዊ ትግል ወደ ትክክለኛው መስመር እንዲገባ ካላስገደድነው በስተቀር በአጭር ጊዜ ውስጥ በታሪካችን አይተነው ወደማናውቅ አምባገነናዊ ኃይል እራሱን ሊቀይርና ሀገሪቱንም ከባድ እና ውስብስብ ወደ ሆነ አደጋ ሊያስገባት ይችላል።

    አብሮነት ሀገራችንን ከእንዲህ ዓይነት አስፈሪ ጥፋት መታደግ የሚቻለው በቂ የሥነ-ልቦናና የመዋቅር ዝግጅት ያልተደረገበት ሀገራዊ ምርጫ በማካሄድ ሳይሆን፥ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ሁሉን አቀፍ የሆነ የእርቅና የአንድነት የሽግግር መንግሥት በማቋቋም ነው ብሎ በፅኑ ያምናል።
    መዋቅራዊ የሆኑ የፖለቲካ ችግሮቻችንን በአግባቡ ለመፍታት በሚያስችል የሽግግር ሂደት ውስጥ እስካላለፍን ድረስ ግን ላለፉት 29 ዓመታት በስልጣን ላይ በቆየው ገዢ ፓርቲ፣ በሥራ ላይ ባለው ሕገ-መንግሥት እየተመራንና ከአለፉት አምስት ምርጫዎች ያልተለየ ስድስተኛ ዙር ምርጫ በማካሄድ የሀገራችንን ችግሮች በዘላቂነት መፍታት አንችልም። እንዲያውም ስድስተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ካለፉት ምርጫዎች የተለየና የተሻለ ማድረግ እስካልቻልን ድረስ ሀገራችን ህልውናዋን ወደሚፈታተን የእርስ በእርስ ጦርነት ወይም መንግሥት-የለሽ ሁኔታ ልትገባ ትችላለች የሚል ከፍተኛ ስጋት አለን። ይህንን የሽግግር መንግሥት ሰነድ ብዙ ተጨንቀንና ተጠበን እንድናዘጋጅ ያስገደደንም ይኸው ስለ ሀገራችን ህልውና መቀጠል የሚሰማን ስጋት ነው።

    ይህ ለሀገራችን ህልውና መቀጠል መድኅን የሚሆን የሽግግር መንግሥት መቼና እንዴት ሊቋቋም ይችላል? በማንና ለምን ሊቋቋም ይገባዋል? ሂደቱና የመጨረሻ ግቡስ ምን ሊሆን ይችላል? የሚሉትን ጥያቄዎች በዝርዝር ለመመለስ በሚያስችል መጠን ተዘጋጅቶ ቀርቧል።

    ስለሆነም፦

    ገዢውን ፓርቲ ጨምሮ በሀገሪቱ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች “ሀገራችን ሰላማዊ፣ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ አካሂዳ በዘላቂነት ወደ መዋቅራዊ ዲሞክራሲ ለመሸጋገር በምን ዓይነት የሽግግር ሂደት ውስጥ ማለፍ ይገባታል?” በሚለው ጥያቄ ዙሪያ የየራሳቸውን ዝርዝር አማራጭ ለውይይት እንዲያቀርቡ፤

    የኮሮና ቫይረስን ስርጭት በአግባቡ ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት በማያስተጓጉል ሁኔታ መንግሥት የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚያቀርቧቸው አማራጭ ሃሳቦች ዙሪያ ውይይትና ድርድር አካሂደው የጋራ መፍትሄ የሚያመነጩበት ሀገራዊ የምክክር ሂደት /national dialogue/ በፍጥነት እንዲያመቻች፤

    የኢትየጵያ ሕዝብም በአንድ ውጤታማ የሽግግር ሂደት ማለፍ ለሀገሪቱ ችግሮች በዘላቂነት መፈታት አስፈላጊና የማይተካ ሚና ያለው ቅድመ-ሁኔታ መሆኑን በመገንዘብ ሀገራዊ የምክክር ሂደት እንዲጠራ የራሱን ግፊትና ትግል እንዲያደርግ

    አብሮነት በአፅንኦት ይጠይቃል።

    ከዚህ ውጭ ገዢው ፓርቲ ላለፉት 29 ዓመታት እንዳደረገው ሁሉ አሁንም “የሀገሪቱንዕጣ-ፈንታ መወሰን የሚገባኝ እኔ ብቻ ነኝ” በሚል መታበይ ወይም “እኔ አሻግራችኋለው” በሚል ያልተገባ ፍልስፍና በስልጣን ላይ የሚቀጥል ከሆነ ግን ሀገሪቱ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ አደገኛ የብጥብጥ አዙሪት ልትገባ የምትችልበት ዕድል ሰፊ ነው። ሀገራችን ከዚህ ዓይነቱ አሳሳቢ ስጋት ወጥታ ወደ ዘላቂ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እንድትሸጋገር ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል በየበኩሉ የሚጠበቅበትን ድርሻ እንዲወጣ አብሮነት ጥሪውን ያቀርባል።

    አብሮነት ለኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት (አብሮነት)
    ግንቦት 10 ቀን 2012 ዓ.ም.
    አዲስ አበባ

    ምርጫ በኢትዮጵያ ― የኢትዮጵያ ብሔራዊ እና ክልላዊ ምርጫዎች ― ሰሞነኛ ዜናዎችና መረጃዎች

    አብሮነት ለኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት (አብሮነት)

    Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 27 ፓርቲዎችን ሰረዘ

    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እስከ መጋቢት 3 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ በቀድሞ ሕግ የምስክር ወረቀት (ሰርተፍኬት) የነበራቸው እና በቀድሞው ሕግ ምዝገባ ጀምረው ለነበሩ 106 ፓርቲዎች በአዲሱ ሕግ ላይ የተቀመጡ መስፈርቶችን እንዲያሟሉ በደብዳቤ ማሳወቁ ይታወሳል። ከቦርዱ ደብዳቤ ከደረሳቸው 106 የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል 76 የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰነዶችን ያቀረቡ ሲሆን በሕጉ መሠረት ተሟልቶ የቀረበ ስለመሆኑ እየተመረመረ ይገኛል።

    ምርመራውም፦

    • ፓርቲዎቹ በደብዳቤ የተገለጸላቸውን ነጥቦች ሁሉንም ማሟላታቸውን ማረጋገጥ (የሕገ–ደንብ ለውጥ ጠቅላላ ጉባዔ ሰነዶች አቀራረብ፣ የመስራቶች ፊርማ… የመሳሰሉት)፣
    • የፖለቲካፓርቲዎችበሕጉመሠረትማሟላትየሚገባቸውንየመሥራችአባላትብዛትትክክለኛነትንለመፈተሽካቀረቡትየመሥራችአባላትዝርዝርናሙናየማውጣት፣
    • ናሙናዎቹበትክክልግለሰቦቹየተፈረሙመሆናቸውንወደተፈረሙበትቦታበመላክማረጋገጥ፣
    • የሕገ–ደንብለውጦችና፣የጠቅላላጉባዔሰነዶችበትክክልመያያዛቸውንማረጋገጥንያጠቃልላል።

    ይህ እንደተጠናቀቀም ሰነዶቻቸው ካስገቡት 76 ፓርቲዎች መካከል ምን ያህሎቹ መስፈርት እንዳሟሉ በቦርዱ ይፋ የሚደረግ ይሆናል። ነገር ግን የሚጠበቅባቸውን ሰነድ ማስገባት ያልቻሉ እና ጊዜ እንዲራዘምላቸው የጠየቁ 15 የፓለቲካ ፓርቲዎች ሲኖሩ ከነዚህ ፓርቲዎች መካከል ከስር የተጠቀሱት የ13ቱ አጥጋቢ ምክንያት ባለማቅረባቸው እንዲሰረዙ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ወስኗል።

    የተጨማሪ ጊዜ ጥያቄ አቅርበው ተቀባይነት ሳያገኙ የተሰረዙ ፓርቲዎች ዝርዝር የሚከተለው ነው፦

    1. የኢትዮጵያውን ዴሞክራሲያዊ አንድነት ንቅናቄ (ኢዴአን) – የመሥራች አባላት ዝርዝር ያላቀረበ፣ ጉባዔ ያላካሄደ
    2. የገዳ ሥርዓት አራማጅ ፓርቲ (ገሥአፓ) – የመሥራች አባላት ዝርዝር ያላቀረበ
    3. የየም ብሔረሰብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (የብዴን) – የመሥራች አባላት ዝርዝር ያላቀረበ፣ ጉባዔ ያላካሄደ
    4. የደንጣ ዱባሞ ክችንችላ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት – የመሥራች አባላት ዝርዝርም ያላቀረበ፣ ጉባዔ ያላካሄደ
    5. የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ኮንግረስ (ኮንግረስ) – የመሥራች አባላት ዝርዝር ያላቀረበ
    6. የትግሪ ወርጂ ብሔረሰብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ትወብዴድ) – ጠቅላላ ጉባዔ ያላካሄደ
    7. የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት (መአሕድ) – የመሥራች አባላት ዝርዝር ያላቀረበ፣ ጉባዔ ያላካሄደ
    8. የኢትዮጵያን አንድነት ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኢአዴድ) – ጠቅላላ ጉባዔ ያላካሄደ
    9. የመላው አማራ ሕዝብ ፓርቲ (መዐሕፓ) – የመሥራች አባላት ዝርዝር ያላቀረበ
    10. የኢትዮጵያውያን አገር አቀፍ ንቅናቄ (ኢሃን) – የመሥራች አባላት ዝርዝር ያላቀረበ
    11. የደቡብ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኮንግረስ (ደቡብ ኮንግረስ) – የመሥራች አባላት ዝርዝር ያላቀረበ
    12. የሸኮና አካባቢው ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ሸአሕዲድ) –ጠቅላላ ጉባዔ ያላካሄደ
    13. ነጻነትና ሰላም ለኢትዮጵያ ሕብረት ፓርቲ ( ነጻነትናሰላም) – የመሥራች አባላት ዝርዝር ያላቀረበ

    በሌላ በኩል ሌሎች 14 ፓርቲዎች ደግሞ ከቦርዱ በተደረገው ጥሪ መሠረት ሰነዶቻቸውን ከነአካቴው ያላቀረቡ ሲሆን አንዳንዶቹ ደግሞ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር መዋሃዳቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም የእነዚህ 14 ፓርቲዎች እንዲሰረዙ ቦርዱ ወስኗል። በመሆኑም ሰነድ ባለማምጣታቸው እንዲሰረዙ የተሰወኑት ፓርቲዎች የሚከተሉት ናቸው።

    1. የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ
    2. መላው ኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
    3. የከምባታ ሕዝቦች ኮንግረስ
    4. የሐድያ ብሔር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት
    5. የኦሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረት
    6. የዲል ወቢ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ
    7. የቤንች ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት
    8. የስልጤ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
    9. የአፋር ሕዝብ ነፃነት ፓርቲ
    10. የሱማሌ አንድነት ፓርቲ
    11. ነፃነት ለአንድነትና ለፍትሕ ፓርቲ
    12. ብሔራዊ ተሀድሶ ለሰላም ልማት
    13. የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝብ ሕብረት
    14. የጋምቤላ ክልላዊ ንቅናቄ

    ሁለት ፓርቲዎች ሰነዶችን ማቅረብ አለመቻላቸው በፓርቲው የውስጥ ችግር የተነሳ መሆኑ ስለታመነበት ጠቅላላ ጉባዔያቸውን የኮቪድ ወረርሽን (COVID-19) በሚያበቃበት ወቅት አንዲያከናውኑ ቦርዱ ሲወስን ሌሎች ሰነዶቻቸው ግን ከላይ በተጠቀሰው መንገድ እየተገመገሙ ይገኛል። በልዩ ሁኔታ የሰነድ ካስገቡ ፓርቲዎች ጋር ሰነዶች እንዲታይላቸው የተደረጉ ፓርቲዎች፦

    1. ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ)
    2. ወለኔ ሕዝቦች ፓርቲ

    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE)

    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

    Anonymous
    Inactive

    እናት ባንክ እና ዳሸን ባንክ የብድር ወለድ ስረዛ/እፎይታ እና የአገልግሎት ማሻሻያ አደረጉ

    አዲስ አበባ (ፋና/ዋልታ) – እናት ባንክ ለተለያዩ የብድር ዘርፎች የብድር ወለድ ስረዛና የአገልግሎት ማሻሻያ ማድረጉን አስታወቀ። ባንኩ በሰጠው መግለጫ ኮሮና ቫይረስ በወረርሽኝነት በዓለምአቀፍ ደረጃ መሰራጨት ከጀመረበት ወቅት አንስቶ በዓለም ማኅበረሰብ ላይ ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ቀውሶችን በማድረስ ላይ እንደሚገኝ ጠቅሷል።

    ይህ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ በኢትዮጵያ በተለይም በኢኮኖሚው ዘርፍ  የንግድ እንቅስቃሴና በንግዱ ማኅበረሰብ ላይ ቀላል የማይባል ጉዳት በማድረስ ላይ መሆኑን ነው የገለጸው። በመሆኑም እናት ባንክ ይህንን ጉዳይ በከፋተኛ ሁኔታ ከግንዛቤ በማስገባት በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ላይ ለተሰማሩ ተበዳሪዎቹ የብድር ወለድ ስረዛና የተለያዩ የአገልግሎት ማሻሻያዎችን ማድረጉን ነው ያሳወቀው።

    የማሻሻያው ዋና ዓላማም እየተከሰተ ያለውን ችግር በጋራ ለመወጣት፣ በደንበኞች የንግድ እንቅሳቃሴ ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ለመቀነስ፣ የብድር አመላለስን የተሻለ ለማድረግና የሀገራችን ኢኮኖሚ ሚዛናዊነቱን ጠብቆ ማስኬድ በሚቻልበት አካሄድ ባንኩ የራሱን ድርሻ ለመወጣት ታሳቢ ያደረገ ነው ብሏል ።

    በዚህም መሠረት የብድር ወለድና አገልግሎት ክፍያን አስመልክቶ በሆቴልና ቱሪዝም የሥራ ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ደንበኞች ከግንቦት እስከ ሀምሌ የብድር ወለድ እንዳይከፍሉ መሰረዙን ገልጿል።

    ከዚያም ባለፈ የብደር ማራዘሚያ ላይ የሚከፈለዉ የአገልግሎት ዋጋ፣ የኦቨር ድራፍት እድሳት ላይ የሚከፈለዉ የአገልግሎት ዋጋ፣ ብድራቸውን ከሚጠበቅባቸው የመክፈያ ጊዜ ቀድመው ለሚከፋሉ ደንበኞች ይጣል የነበረው ቅጣት እንዲሁም ውዝፍ የብድር ዕዳን አዘግይቶ ሲከፈል የሚጣል ቅጣት ሙሉ ለሙሉ መነሳቱንም ነው ያብራራው።

    በዓለምአቀፍ ባንኪንግ ዙሪያም እናት ባንክ የተለያዩ ማሻሻያዎች ማድረጉን ገልጾ፥ በዚህም አስመጪዎች እቃ ወደ ሀገር ለማስገባት ለከፈቱት ሌተር ኦፍ ክሬዲት (LC) አሁን በዓለም ላይ ከተፈጠረዉ ችግር አኳያ አስቀድመዉ ለማራዘሚያ የሚጠየቁት የአገልግሎት ክፍያ ሙሉ ለሙሉ እንዲነሳ መደረጉን አንስቷል።

    በተያያዘም ከኮቪድ-19 ጋር ተዛማጅነት ያላቸውን ዕቃዎች ለሚያሰመጡ አስመጪዎች ባንኩ ሃምሳ በመቶ (50%) የአገልግሎትና የኮሚሽን ክፍያ መቀነሱን ነው የገለጸው።

    እናት ባንክ ማኅብራዊ ኃላፊነትን ለመወጣትና ኮረና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ ለብሔራዊ የኮቪድ-19 ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ የብር 2 ሚሊዮን ብርድጋፍ ከማበርከቱም ባለፈ የባንኩ ሠራተኞችና የደንበኞች ደኅንነት ከወረርሽኙ ለመጠበቅ የተለያዩ የጥንቃቄ እርምጃዎች በመውሰድ ላይ መሆኑን ከባንኩ የተገኘ መረጃ ያመላክታል።

    በተመሳሳይ ዜና፥ ዳሸን ባንክ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እንደሚያሳድርባቸዉ በጥናት በተለዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ለተሰማሩ ደንበኞቹ የወለድ ቅናሽ፣ የብድር እፎይታና ማራዘሚያ ጊዜ ለመስጠት ወስኗል።

    የኮቪድ-19 ስርጭት በተለይ በአንዳንድ ዘርፎች ላይ እያስከተለ ያለው ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን በመገንዘብ ቀደም ሲል በሌሎች ተጎጂ መስኮች ላይ እንዳደረገው ሁሉ በእነዚህ ዘርፎች የተሰማሩ ደንበኞቹ እየደረሰባቸዉ ያለዉን ኢኮኖሚያዊ ጫና ለመጋራት መወሰኑን ለዋልታ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን (ዋልታ) በላከው መግለጫ አስታውቋል።

    በዚህም መሠረት በአበባና አትክልት፣ በሆቴልና ማስጎብኘት (ቱሪዝም)፣ በኤክስፖርት ዘርፍ ላይ የተሰማሩ አምራቾች፣ በፋብሪካ ምርት (manufacturing)፣ በሕዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት እና ትምህርት ተቋማት ዘርፎች ለተሰማሩና በሥራ ላይ ላሉ ደንበኞች እንደ አውሮፓዊያኑ የዘመን ቀመር (እ.አ.አ.) ከሰኔ 1 ቀን 2020 ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የወለድ ቅናሽ፣ የብድር እፎይታና ማራዘሚያ ጊዜ ሰጥቷል።

    ባንኩ በአበባና አትክልት ዘርፍ ለተሰማሩ ተበዳሪዎች ቀደም ሲል በዝቅተኛ ወለድ እያበደረ የነበረ ቢሆንም፥ ዘርፉ ከቫይረሱ ስርጭት ጋር ተያይዞ የደረሰበትን የኢኮኖሚ ጉዳት ከግምት ዉስጥ በማስገባት ከ 1 በመቶ እስከ 2 በመቶ ተጨማሪ ቅናሽ አድርጓል።

    ከፈረንጆቹ ሰኔ 1 ጀምሮ በዘርፉ የተሰማሩ ደንበኞች 7 በመቶ የወለድ ምጣኔ ብቻ እንዲከፍሉ ወስኗል። በተጨማሪም ተበዳሪዎች በሚያቀርቡት ጥያቄ መሠረት የ6 ወር የብድር እፎይታና እስከ 5 ዓመት የሚቆይ የብድር ማራዘሚያ ያለምንም የማራዘሚያ አገልግሎት ክፍያ ፈቅዷል።

    በሆቴልና ማስጎብኘት ዘርፍ የተሰማሩ ተበዳሪዎች እ.አ.አ. ከሰኔ 1 ቀን 2020 ጀምሮ  የሚከፍሉት የወለድ ምጣኔ ወደ 7 በመቶ እንዲቀንስና ተበዳሪዎቹ በሚያቀርቡት ጥያቄ መሠረት የስድስት ወር የብድር እፎይታ ጊዜና እስከ 5 ዓመት ድረስ የሚቆይ የብድር ማራዘሚያ ያለምንም የማራዘሚያ አገልግሎት ክፍያ እንያገኙ ለማድረግ ወስኗል።

    በኤክስፖርት ዘርፍ ላይ የተሰማሩ አምራቾችም እንዲሁ እ.አ.አ. ከሰኔ 1 ቀን 2020 ጀምሮ  የወለድ ምጣኔ ቅናሹ ተጠቃሚ ሆነው ለሶስት ወራት 7 በመቶ ብቻ ወለድ እንዲከፍሉ ተደርጓል። ከዚህም ሌላ በሚያቀርቡት ጥያቄ መሠረትም የሦስት ወር የብድር መክፈያ ዕፎይታ ጊዜና እስከ ሦስት ዓመት ያለምንም የብድር ማራዘሚያ ክፍያ እንዲስተናገዱ መደረጉን ባንኩ በመግለጫው አትቷል ።

    በፋብሪካ ምርት (manufacturing)፣ በሕዝብ ማመላለሻ አዉቶብስና በትምህርት ዘርፎች የተሰማሩ ተበዳሪዎችም ጭምር በሚያቀርቡት ጥያቄ መሠረት ከሰኔ 1 ጀምሮ ለ 6 ወር የብድር መክፈያ እፎይታ ጊዜና እስከ 3 ዓመት ድረስ የብድር ማራዘሚያ ያለምንም የማራዘሚያ አገልግሎት ክፍያ ለመስጠት ወስኗል።

    በተጨማሪ ዳሸን ባንክ ከላይ ለተጠቀሱትና በቫይረሱ ስርጭት ይበልጥ ለኢኮኖሚያዊ ጉዳት እንሚዳረጉ በጥናት ለተለዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ተጨማሪ የወለድ ምጣኔ ማስተካከያ እንዲደረግላቸዉም ወስኗል። ከ17.5 በመቶ እስከ 18 በመቶ ወለድ ይከፍሉ የነበሩና በእነዚህ ዘርፎች የተሰማሩ ደንበኞች የ1.5 በመቶ ወለድ ቅናሽ ተደርጎላቸዉ 16 በመቶና 16.5 በመቶ ወለድ እንዲከፍሉ ተደርጓል ብሏል። ከ14 በመቶ እስከ 17 በመቶ ወለድ ይከፍሉ የነበሩ ደግሞ የ1 በመቶ ቅናሽ ተደርጎላቸዉ ከ13 በመቶ እስከ 16 በመቶ ወለድ እንዲከፍሉ ተወስኗል ።

    ነገር ግን ከላይ የተጠቀሱት ሁሉም የብድር አገልግሎት ማሻሻያ ዉሳኔዎች የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከታወጀበት ጊዜ በፊት በተበላሸ ብድር ዝርዝር ዉስጥ ይገኙ የነበሩ ብድሮችን እንደማይጨምርም ዳሸን ባንክ አስታውቋል።

    ምኝጮች፦ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት/ ዋልታ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ኮርፖሬት

    እናት ባንክ እና ዳሸን ባንክ የብድር ወለድ ስረዛ/እፎይታና የአገልግሎት ማሻሻያ አደረጉ

Viewing 15 results - 256 through 270 (of 730 total)