Search Results for 'ጎንደር ዩንቨርሲቲ'

Home Forums Search Search Results for 'ጎንደር ዩንቨርሲቲ'

Viewing 4 results - 1 through 4 (of 4 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    የጋሞ ሽማግሌዎች (የጋሞ አባቶች) መንግሥት ኖረም አልኖረ በአካባቢያቸው ላይ፤ በተለይም በገዛ ልጆቻቸው የማንም ሌላ ኢትዮጵያውን ሕይወትም ሆነ ንብረት እንደማይወድም ተንበርክከው፤ ግን ደግሞ በመንፈስ ልዕልና ከፍ ብለው አሳይተውናል።

    ታላቅ ክብር ለጋሞ ሽማግሌዎች ይሁን!
    (ያሬድ ኃይለማርያም)

    ለእውነት የቆሙ ሽማግሌዎች እጦት፣ በካድሬ እና በመንጋ ፖለቲከኛ ክፉኛ ለተመታችው አገሬ የጋሞ ሽማግሌዎች (የጋሞ አባቶች) ፍቱን መድኃኒት ናቸው። እንደ ጋሞ ሽማግሌዎች ዓይነት ቅን አሳቢ፣ የፍቅር መምህር፣ የተግባር ሰው፣ ደፋር እና ዝቅ ብለው የከፍታን ውሃ ልክ የሚያሳዩ ሽማግሌዎች ከየማህበረሰቡ ቢገኙ ከገባንበት ቅርቃር በቀላሉ ለመውጣት ዕድል ይኖረን ነበረ። በሽማግሌ እና በካድሬ መካከል ያለውን ልዩነት መለየት ያልቻሉ ቀሳውስት፣ ሼኾች፣ አባገዳዎች፣ ፓስተሮች፣ መንፈሳዊ አባቶች ኮሽ ባለ ቁጥር አበል እየተከፈላቸው በየሆቴሉ ሲማማሉ እና በሕዝብ ስም እነሱ ሲታረቁ ቢውሉም መሬት ላይ ጠብ ያለ ነገር የለም።

    የአገራችን ችግር ቅን አሳቢ እና ለእውነት የወገነ፣ ያመነበትን በትክክል የሚናገር፣ ክፉን የሚያወግዝን እና ጥሩውን የሚያበረታታ እውነተኛ ሽማግሌ፣ ደፋር ምሁር፣ ሃቀኛ ፖለቲከኛ፣ ሚዛናዊ ጋዜጠኛ እና መሰሪ ያልሆነ የአገር መሪ ይፈልጋል። ለጋሞ ሽማግሌዎች እና ሽማግሌዎቹንም ለሚያከብሩት የጋሞ ወጣቶች ትልቅ ክብር አለኝ። ጥሩ ምሳሌም ሊሆኑ ይችላሉ።

    የአማራ ሽማግሌዎች ከወዴት አላችሁ? የትግራይ ሽማግሌዎች ከወዴት አላችሁ? የኦሮሞ ሽማግሌዎች እና አባገዳዎች ከወዴት አላችሁ? እነዚህን ክልሎች በተለየ ሁኔታ የምጠራው ሦስቱም ክልል ውስጥ ያለው እሳት አገሪቱን ወደ ከፋ ሁኔታ እየገፋት ያለ ስለመሰለኝ ነው። በማኅበረሰብ ውስጥ ግጭት ሲፈጠር፣ ዜጎች በጠራራ ፀሀይ ሲታረዱ፣ እናት ከነልጆቿ ከቅዮዋ ተፈናቅላ ዱር ስታድር፣ ሕጻናት በነፍሰ በላዎች ታፍነው ገሚሱ ሲገደሉ፣ የዩንቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች በወሮበላ ታጣቂዎች ታፍነው ሲወሰዱ የመንግስት ክርን ቢዝል እናንተ የአገር ሽማግሌዎች የት ገባችሁ?

    የጋሞ ሽማግሌዎች (የጋሞ አባቶች) መንግሥት ኖረም አልኖረ በአካባቢያቸው ላይ፤ በተለይም በገዛ ልጆቻቸው የማንም ሌላ ኢትዮጵያውን ሕይወትም ሆነ ንብረት እንደማይወድም ተንበርክከው፤ ግን ደግሞ በመንፈስ ልዕልና ከፍ ብለው አሳይተውናል። ከዛም አልፈው ይህን ትልቅ የሽምግልና እና የፍቅር መንፈስ ይዘው ከአንድ አገሪቱ ጫፍ ወድ ሌላው ጫፍ ተጉዘዋል። መንፈሳችሁ በሌሎች ሽማግሌዎች ይደር!!

    ክብር ለጋሞ ሽማግሌዎች ይሁን!
    (ያሬድ ኃይለማርያም)

    ከጋሞ ኢትዮጵያውያን ጋር በተያያዘ የጋሞ አባቶች እና ወጣቶች ጥር 14 ቀን 2012 ዓ.ም. “የሰላም ጉዞ” በሚል መርህ ከአርባ ምንጭ በመነሳት የተለያዩ ከተሞችን በማቋረጥ መዳረሻቸውን ጎንደር ከታማ እና የጥምቀት በዓልን አድርገው መጓዛቸውንበዚህ ሳምንት ተዘግቧል።

    በጉዞው የጋሞ አባቶች የአካባቢያቸውን ሰላም እንዴት እንዳስጠበቁ ተሞክሮዎቻቸውን ለሌሎች እንዳካፈሉ እና የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሰላም ተምሳሌትነትም ለሌሎች የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተሞክሮነት አሳይተዋል። አባቶች በጉዞው የተለያዩ ከተሞችን ያቋረጡ ሲሆን፥ በጉዟቸው መሃል ባረፉባቸው ከተሞችም ስለ ሰላም እና አንድነት ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ምክክር አድርገዋል። እንዲሁም ተማሪዎችን ስለአቃፊነት፣ ስለ ሰላምና አንድነት እንደመከሩም የጋሞ ዞን ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ መረጃ ሰጥቶ ነበር።

    የሰላም ዦቹ የጋሞ አባቶች እና ወጣቶች በአዲስ አበባ በብሔራዊ ቤተ መንግሥት ተገኝተው የአንድነት ፓርክን የጎበኙ ሲሆን፥ የጉዞው መዳረሻ በሆነችው ታሪካዊቷ የጎንደር ከተማም ከከተራ በዓል ጀምረው እስከ ጥር 14 ቀን 2012 ዓ.ም. ለአራት ቀናት እንደሚቆዩ ተዘግቧል።

    የአብሮነትና የሰላም ጉዞውን ኅብረ መንጎል ሚዲያና ኦሞቲክ ጀኔራል ጠቅላላ ንግድ ድርጅት በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን፥ የጉዞውን አላማ በመደገፍ የሰላም ሚኒስቴር፣ የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ እንዲሁም የደቡብ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮዎች ለአዘጋጆች የድጋፍ ደብዳቤ ሰጥተዋቸዋል።

    ምንጮች፦ ያሬድ ኃይለማርያም እና ፋና ብሮድካስቲንግ

    የጋሞ አባቶች

    Semonegna
    Keymaster

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን የፈረንሳይኛ ቋንቋ አስተምሮ በዲፕሎማ ፕሮግራም ተቀብሎ ለማሰልጠን ተቀማጭነቱ አዲስ አበባ ውስጥ ከሆነው የፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር ስምምነት ላይ መድረሱን ዩኒቨርስቲው አስታወቋል።
    —–

    ጎንደር (ኢዜአ) – ጎንደር ዩንቨርሲቲ የፈረንሳይኛ ቋንቋ የስልጠና ማእከል ለመክፈት ከፈረንሳይ ኤምባሲ በኢትዮጵያ ጋር ስምምነት መድረሱን አስታወቀ።

    ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በፈረንሳይኛ ቋንቋ ተማሪዎችን በዲፕሎማ ፕሮግራም ተቀብሎ ለማሰልጠን ተቀማጭነቱ አዲስ አበባ ውስጥ ከሆነው የፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር ስምምነት ላይ መድረሱን ዩኒቨርስቲው አስታወቋል።

    የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ጽሕፈት ቤት በበኩሉ የስልጠና ማዕከሉ መከፈት ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ቱሪስቶችን በቋንቋቸው ለማስጎብኘትም ሆነ በሆቴሎችና በመዝናኛ ስፍራዎች ቀልጣፋ የቱሪስት መስተንግዶ ለመስጠት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብሏል።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስራት አጸደወይን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንዳስታወቁት፥ የትምህርት ስልጠናው የሚሰጠው ከኢምባሲው ጋር በመተባበር ነው። ስልጠናውን በተቀናጅ አግባብ ለመስራት ማዕከል ይቋቋማል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፥ ማዕከሉን ለመክፈት የሚያስችለው ስምምነት ከኤምባሲው ጋር ጥቅምት 11 ቀን 2012 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ይፈራረማል።

    በሚደረገው ስምምነቱም የፈረንሳይኛ ቋንቋ አስተማሪዎችን ከመመደብ ጀምሮ የማስተማሪያ ግብአቶችን በራሱ ወጪ ለዩኒቨርሲቲው እንደሚያሟላ ገልፀዋል። የማዕከሉ መከፈት ዋና ዓላማ በፈረንሳይኛ ቋንቋ የሰለጠኑ አስጎብኚዎችና የሆቴል አስተናጋጆችን እጥረት ለመቅረፍ እንዲያስችል የታሰበ መሆኑን ተናግረዋል።

    ዩኒቨርሲቲው ከቱሪዝም ትምህርት ክፍሉ ጋር በመቀናጀት ከዚህ ዓመት አጋማሽ ጀምሮ ቋንቋውን በሰርተፊኬትና በዲፕሎማ ደረጃ ለመስጠት ታቅዶ እየተሠራ መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያና ፈረንሳይ ከ100 ዓመታት በላይ የዘለቀ ዲፖሎማሲያዊ ግንኙነት አላቸው ያሉት ፕሬዘዳንቱ፥ በአፍሪካም ከ20 በላይ ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ሀገሮች መኖራቸውን አመልክተዋል።

    የጎንደር ከተማ በዓለም ቅርስነት የተመዘገቡ የአጼ ፋሲል ቤተ-መንግስትና የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ በመሆኑ በርካታ ቁጥር ያላቸው የፈረንሳይ ቱሪሰቶች ለጉብኝት እንደሚመጡ ተናግረዋል።

    የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ጽህፈት ቤት የህብረተሰብና ቱሪዝም ሃላፊ አቶ ታደሰ ይግዛው እንዳሉት ከሆነ በአካባቢው ካሉት 80 አስጎብኚዎች መካከል የፈረንሳይኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ከ2 አይበልጡም።

    በርካታ ፈረንሳይኛ ተናጋሪዎች ፓርኩን ለመጎብኘት እንደሚመጡ የተናገሩት ኃላፊው፥ ዩኒቨርሲቲው ለመክፈት ያሰበው የፈረንሳይኛ ቋንቋ ማሰልጠኛ የፓርኩን የፈረንሳይኛ ቋንቋ ተናጋሪ አስጎብኚ እጥረት እንደሚያቃልል ተናግረዋል።

    የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከፈረንሳይኛ ቋንቋ በተጨማሪ የመጥፋት አደጋ የተጋረጠበትን የግእዝ ቋንቋ ለመታደግ በዚህ ዓመት የግእዝ ቋንቋ ትምህርት ቤት ለመክፈት መዘጋጀቱ በቅርቡ መገለጹ የሚታወስ ነው።

    ምንጭ፦ ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    Semonegna
    Keymaster

    በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሥር ከሚገኙት ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የጎንደር ዩንቨርሲቲ በርካታ ቁሳዊና መንፈሳዊ እሴት የያዙ መጻህፍት ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገሩ ለማድረግ ሥርዓተ ትምህርት (curriculum) ተቀርጾና መምህራን ተቀጥረው የግእዝ ቋንቋን ለማስተማር መዘጋጀቱን አስታውቋል።

    ጎንደር ዩንቨርሲቲ የግእዝ ቋንቋ በመጀመሪያ ዲግሪ መስጠት ሊጀምር ነው

    ጎንደር (ኢዜአ) – ጎንደር ዩንቨርሲቲ የመጥፋት አደጋ የተጋረጠበትን የግእዝ ቋንቋ ለመታደግ በአዲሱ የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ ዲግሪ የቋንቋ ትምህርት ለመስጠት መዘጋጀቱን አስታወቀ።

    የጎንደር ዩንቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኘ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደተናገሩት ኢትዮጵያ የግእዝ ቋንቋ ባለቤት ብትሆንም ለቋንቋው ማደግና መስፋፋት የተሰጠው ትኩረት አነስተኛ ነው። “በዚህም ሳቢያ ቋንቋው የመጥፋት አደጋ የተጋረጠበት ከመሆኑም በላይ በግእዝ ቋንቋ የተጻፉ በርካታ የብራና መጻፍትን ለጥናትና ምርምር ስራ ለማዋል አልተቻለም “ብለዋል።

    ዘመናት የተሻገሩና በቋንቋው የተጻፉ ለዘመናዊ ሕክምና ሙያ የሚያግዙ፣ ምጣኔ ሀብታዊ፣ ባህላዊና ታሪካዊ ፋይዳ ያላቸው በርካታ መጻሕፍት በኃይማኖት ተቋማትና ገዳማት ተወስነው መኖራቸውን አመልክተዋል።

    ዩንቨርሲቲው እነዚህን ቁሳዊና መንፈሳዊ እሴት የያዙ መጻህፍት ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገሩ ለማድረግ ሥርዓተ ትምህርት (curriculum) ተቀርጾና መምህራን ተቀጥረው የግእዝ ቋንቋን ለማስተማር መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።

    በትምህርት ዘመኑ 50 ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅት መደረጉን ያመለከቱት ዶክተር ካሳሁን፥ ትምህርቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠውም በኤክስቴንሽንና በክረምት መርሃ ግብሮች መሆኑን አስረድተዋል። ትምህርቱ ሰፊ ተቀባይነት እያገኘ ሲሄድ መደበኛ ተማሪዎችን ጭምር በቀጣይ በግእዝ ቋንቋ አሰልጥኖ ለማስመረቅ መታቀዱን አመልክተዋል።

    በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሥር ከሚገኙት ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የጎንደር ዩንቨርሲቲ፥ በአጠቃላይ 87 የመጀመሪያ ዲግሪ፤ 158 ሁለተኛ ዲግሪና 29 የሦስተኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች እንዳሉት ተገልጿል። በመደበኛ፣ በተከታታይና በክረምት መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የሚከታታሉ ከ45ሺ በላይ ተማሪዎች በዩንቨርሲቲው ይገኛሉ።

    ምንጭ፦ ኢዜአ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    —–
    ተመሳሳይ ዜናዎች

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኢትዮጵያ ― ዜናዎችና ጠቃሚ መረጃዎች


    Semonegna
    Keymaster

    የአቶ ገዱ አንዳርጋቸውን የስልጣን መልቀቅ ጥያቄ ተከትሎ የአዴፓ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እና የጠቅላይ ሚኒስትር የመሠረተ ልማት እና የከተማ ልማት አማካሪ ሚኒስትር የሆኑት ዶ/ር አምባቸው መኮንን ርዕስ መስተዳደር ሆነው ተሹመዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው መልቀቂያ ጥያቄ አቀረቡ። ርዕሰ መስተዳድሩ እየተካሄደ ባለው የክልሉ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ነው ጥያቄውን ያቀረቡ ሲሆን፥ ምክር ቤቱም ጥያቄያቸውን ተቀብሏል። የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ)በበኩሉም የርዕሰ መስተዳድሩን ጥያቄ መቀበሉን የ አማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት እና ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ዘግበዋል።

    አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ባለፈው ዓመት የካቲት ወር ለሦስተኛ ዙር በርዕሰ መስተዳድርነት ተመርጠው ሲያገለግሉ እንደነበር ይታወሳል። በአጠቃላይም ከታህሳስ ወር 2006 ዓ.ም. ጀምሮ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በመሆን አገልግለዋል።

    አቶ ገዱ አንዳርጋቸው “ታላቁን የአማራ ሕዝብ ለመምራት ዕድል የሰጠኝን ፓርቲዬን አመሠግናለሁ፤ በስልጣን ዘመኔ በሰጠኋቸው ውሳኔዎች ያስከፋኋችሁ ካላችሁ ከልብ ይቅርታ እጠይቃለሁ። ወኔና ጉልበት ሆኖኝ የኖረውን የአማራ ሕዝብ አመሠግናለሁ፤ ለአዲሱ ርዕሰ መስተዳድርም መልካም የሥራ ዘመን እመኛለሁ” ብለዋል በመሰናበቻ ንግግራቸው።

    የአቶ ገዱ አንዳርጋቸውን የስልጣን መልቀቅ ጥያቄ ተከትሎ ምክር ቤቱ የአዴፓ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑትን ዶ/ር አምባቸው መኮንንን ርዕስ መስተዳደር አደርጎ ሾሟል። ዶ/ር አምባቸው ከአዴፓ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው በተጨማሪ የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮን የመሠረተ ልማት እና የከተማ ልማት አማካሪ ሚኒስትር በመሆን እያገለገሉ ነበር።

    እድገታቸው ጋይንት፣ ጎንደር ውስጥ የሆነው ዶ/ር አምባቸው መኮንን የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ሆነው ከመሾማቸው በፊት በተለያዩ የመንግስት ቦታዎች ለ28 ዓመታት ሠርተዋል።

    ዶ/ር አምባቸው ከኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ፣ ቀጥሎም ደቡብ ኮርያ ከሚገኘው ከኮርያ የልማት ኢንስቲትዩት (Korea Development Institute) በፐብሊክ ፖሊሲ የማስተርስ ዲግሪ፣ ከዚያም እንግሊዝ ሀገር ካንተርበሪ ከተማ ከሚገኘው ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኬንት (University of Kent) ሌላ ማስተርስ ዲግሪ እና የዶክትሬት ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ዶ/ር አምባቸው መኮንን


Viewing 4 results - 1 through 4 (of 4 total)