Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 15 results - 166 through 180 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ 70 አዳዲስ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት ክፍሎችን ሊከፍት ነው

    ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በአዲሱ የትምህርት ዘመን በሁለተኛ እና ሦስተኛ ድግሪ 70 አዳዲስ ትምህርት ዓይነቶችን ለመክፈት መዘጋጀቱን አስታወቀ። ይህም ዩኒቨርሲቲው በሁለተኛ እና ሦስተኛ ዲግሪ የሚሰጣቸውን የትምህርት ዓይነቶች 101 እንደሚያደርሰው ተጠቁሟል።

    የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታምሩ አኖሌ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንዳሉት በ2013 የትምህርት ዘመን በዩኒቨርሲቲው አዲስ ከሚከፈቱት 19 የሦስተኛ ዲግሪ መርሀግብሮች ውስጥ የገዳ እና የአስተዳደር ጥናት አንዱ ነው።

    ቀሪዎቹ የተለያዩ የሁለተኛ ዲግሪ መርሀግብሮች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ይህም ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በሦስተኛ ዲግሪ ይሰጥ የነበረውን አንድ መርሀግብር ወደ 20 ከፍ ሲያደርገው የሁለተኛ ዲግሪውን ደግሞ ከ30 ወደ 81 የትምህርት ክፍሎች እንደሚያሳድገው ዶ/ር ታምሩ አመላክተዋል። የትምህርት ክፍሎችን ፍላጎት ከመለየት አንስቶ የየሥርዓተ ትምህርት (curriculum) ቀረጻና ትችት እንዲሁም የሰው ኃይልና ግብዓት የማሟላት ሥራዎች በጥንቃቄ መከናወናቸውንም በማከል አስረድተዋል።

    የመማር ማስተማር ሂደቱን ውጤታማ ለማድረግ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የእውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ስምምነት ሰነድ መፈራረሙንም ዶ/ር ታምሩ ገልጸዋል። የመምህራን እጥረት እንዳይከሰት ረዳት ፕሮፈሰርና ከዚያ በላይ የትምህርት ደረጃ ያላቸው 73 የውጭና 43 የሀገር ውስጥ መምህራን ቅጥር መፈጸሙንም አስታውቀዋል።

    ለመማር ማስተማር ሂደት አጋዥ የሆኑ በተለይ ለኢንጅነሪግና ለተፈጥሮ ሳይንስ ቤተ-ሙከራና ቤተ-መጽሐፍት ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ በማድረግ መደራጀቱን ገልጸዋል። ይህም ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት ለማድረስ እገዛ ከማድረግ ባለፈ ከዚህ ቀደም ዩኒቨርሲቲው ለተለያዩ የተግባር ትምህርቶች ወደ ሌሎች አካባቢዎች ተማሪዎችን በመውሰድ የሚያወጣውን ውጭ እንደሚያስቀር አስረድተዋል።

    ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የልህቀት ማዕከል (Center of Excellence) አቋቁሞ ከኢትዮጵያ ምርጥ አምስት እንዲሁም ከአፍሪካ ምርጥ 10 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ አንዱ ለመሆን እየሠራ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጫላ ዋታ ናቸው።

    በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ የገዳ ሥርዓት እንዲካተት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ግንባር ቀደሚ ሚናውን ከመወጣት ባለፈ በዩኒቨርሲቲው ከኮመን ኮርስ (common course) እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ድረስ የገዳ ሥርዓት ትምህርት እየተሰጠ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

    “ዩኒቨርሲቲው በስሩ ባሉት ስምንት ኮሌጆችና በአንድ ኢንስትቲዩት ከ17 ሺህ በላይ ተማሪዎችን እያስተማረ ይገኛል” ብለዋል ዶ/ር ጫላ።

    ምንም እንኳን በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭት ምክንያት መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደቱ ለጊዜው ቢቆምም በቀጣይ ዓመታት የተማሪዎችን ቁጥር በእጥፍ ለማሳደግ እየተሠራ እንደሚገኝ ከፕሬዝዳንቱ ገለፃ ለማወቅ ተችሏል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን

    ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ

    Anonymous
    Inactive

    በብሔራዊ መግባባት ዙሪያ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ጥናታዊ ጽሁፍ አቀረበ

    አዲስ አበባ (ነእፓ) – በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስተባባሪነት በሀገራችን ብሔራዊ መግባባት በመፍጠር ሰላምና መረጋጋት እንዲሁም ዴሞክራሲያዊ ሽግግር እውን ለማድረግ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የመጀመሪያ ዙር ውይይት ነሐሴ 16 ቀን 2012 ዓ.ም መካሄዱ ይታወሳል። የዚሁ መድረክ ሁለተኛ ዙር ውይይት ነሐሴ 30 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ECA) ተካሂዷል።

    በውይይቱ ላይ በከፍተኛ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች አራት የተለያዩ ጽሁፎች የቀረቡ ሲሆን፥ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ሊቀመንበር ዶ/ር አብዱልቃድ አደም “ብሔራዊ መግባባት በኢትዮጵያ፡ ዘላቂ ሰላም፣ ሀገራዊ አንድነት እና ዴሞክራሲያዊ ሽግግር” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል።

    ዶ/ር አብዱልቃድር የብሔራዊ መግባባት ምንነት፣ አጠቃላይ ማዕቀፍ፣ አደረጃጀት፣ ዓለም አቀፍ ተሞክሮ እና ሌሎች ከብሔራዊ መግባባት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን ብሔራዊ መግባባትን አስመልክቶ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ግልጽ እና ተቀራራቢ አቋም እንዲኖራቸው ለማድረግ እንዲሁም ብሔራዊ መግባባትን አስመልክቱ የተሳሳቱ ግንዛቤዎችን ለማስተካካል ጥናታዊ ጽሁፉ ከፍተኛ ፋይዳ እንደነበረው በውይይቱ የተሳተፉ የፖለተካ ፓርቲዎች ገልጸዋል።

    የቀረበው ወረቀት (ጥናታዊ ጽሑፍ) በሀገራችን በቅርቡ ይጀመራል ተብሎ በሚጠበቀው ሁሉን አቀፍ የብሔራዊ መግባባት ሂደት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽዖ እንደሚኖረው ይታመናል።

    ነእፓ ቀደም ሲል በሀገራችን በብሔራዊ መግባባት ዙሪያ የመነሻ ጽሁፍ  በማዘጋጀት ሀሳቡን ለመንግስት፣ ለፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ለሲቪክ ማኅበራትና በኢትዮጵያ ለሚገኙ የውጪ ሀገር የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ማሰራጨቱ ይታወሳል።

    ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሀገራችን ሰላም፣ መረጋጋትና አንድነት እንዲሰፍን፣ ቀጣዩ ምርጫ ነጻ ፍትሀዊ እና ቅቡል እንዲሆን ሁሉን አቀፍ የብሔራዊ መግባባት ሂደት በአፋጣኝ መካሄድ እንዳለበት በጽኑ ያምናል። ይህንኑ እውን ለማድረግ ፓርቲው የጀመረውን ጥረት ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን አጠናክሮ ይቀጥላል።

    በመድረኩ የቀረበውን ጽሁፍ እዚህ ሊንክ ላይ በመጫን ማግኘት ይቻላል።

    ምንጭ፦ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ)

    ተመሳሳይ ዜናዎች

    ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ

    Anonymous
    Inactive

    በኢትዮጵያ አዲስ የ200 ብር ኖት ይፋ ተደረገ፤ ነባሮቹ የ10፣ የ50 እና የ100 ብር የገንዘብ ኖቶችም ተቀይረዋል

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ኢትዮጵያ ነባሮቹን የ10፣ የ50 እና የ100 ብር የገንዘብ ዓይነቶች (የገንዘብ ኖቶች) ሙሉ ለሙሉ መለውጧን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አስታወቁ። በተጨማሪም አዲስ የ200 ብር ኖት መቅረቡንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል። እንዲሁም የ5 ብር ገንዘብ ኖት ባለበት ቀጥሎ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ወደ ሣንቲም እንደሚቀየርም ተገልጿል።

    እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ፥ ነባሮቹን የገንዘብ ኖቶች በመተካት ለግብይት የሚሆን አዲስ የገንዘብ ኖት መጠቀም እንደምትጀምር መስከረም ሦስት ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ ተደርጓል።

    እነዚህ አዲስ የገንዘብ ኖቶች ለሕገ ወጥ እንቅስቃሴዎች የሚደረግ የገንዘብ ድጋፍን፣ ሙስናን እና የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴዎችን ለመቆጣጠርና ለመቀልበስ ይረዳሉ ብለዋል።

    በአዲሶቹ የገንዘብ ኖቶች ላይ የተካተቱት ምስጢራዊ ምልክቶችና መለያዎች የገንዘብ ኖቶቹን አመሳስሎ ለማተም የሚደረጉ ሕገ ወጥ ጥረቶችንም ለማስቀረት እንደሚያግዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አክለው ገልጸዋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ያሰፈሩት መልዕክት (እንግሊዝኛ) እንዲህ ይነበባል፦

    Ethiopia today unveils new Birr notes for 10, 50 & 100 denominations, with introduction of a new Birr 200 note. The new notes will curb financing of illegal activities; corruption & contraband. Enhanced security features on the new notes will also cease counterfeit production.

    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ ማምሻውን በሰጡት መግለጫ የገንዘብ (የብር) ኖቶች ለውጡን ተከትሎ ሕገ-ወጥ ተግባራትን ለመቆጣጠር ዝግጅት ተደርጓል። በተለያዩ ጎረቤት ሀገራት የኢትዮጵያ የብር ኖቶች ክምችት መኖሩን የጠቀሱት ዶ/ር ይናገር፥ ለብር ለውጡ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ቁጥጥር ይደረጋል ብለዋል። ለዚህም ከጸጥታና የደህንነት አካላት ጋር በመነጋገር የመቆጣጠርና የማምከን ተግባራት እንደሚከናወኑ ገልጸዋል። በተለይ በድንበር አካባቢ የሚገኙ ባንኮችም በብር ኖቶች ለውጡ ሕገ-ወጥ ድርጊቶች እንዳይጋለጡ ጥብቅ ክትትል ይደረጋል ብለዋል።

    ዶ/ር ይናገር የብር ኖቶች ቅያሬውን ለማከናወን ማንኛውም ግለሰብ የብር ኖቶቹን ራሱ በባንክ መቀየር ሲገባው፥ በሌላ ግለሰብ (በውክልና) የገንዘብ ኖት ለውጥ ማከናወን የማይችል መሆኑንም ተናግረዋል።

    በ3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ወጪ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን የብር ኖት መታተሙንና የመጠባበቂያ ክምችት እንዲኖር ተጨማሪ የብር ኖቶች እየታተሙ መሆኑን ዶ/ር ይናገር አመልክተዋል። ባለፉት ጥቂት ወራት አዳዲሶቹን የብር ኖቶች ወደ ኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የማጓጓዝ ሥራ መሠራቱንና አሮጌውን ገንዘብ መቀየር የሚያስችል በቂ ክምችት እንዳለ ገልጸዋል።

    ካፒታል ኢትዮጵያ ሳምንታዊ ጋዜጣ በግንቦት ወር 2012 ዓም እንደዘገበው፥ የኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበር (EBA) በነበሩት የብር ኖቶች ላይ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቁን ገልጾ ነበር። ማኅበሩ በአሁኑ ጊዜ በብር ኖቶች መበላሸት ምክንያት ከ113 ቢሊዮን ብር በላይ ከባንክ አገልግሎት ውጪ እንደሆነ በመጥቀስ፥ የሚታየውን የብር ኖቶች ከገበያ/ ከአገልግሎት ውጪ መሆን ችግር ለመቅረፍ የብር ኖቶችን መቀየር አስፈላጊነት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ (NBE) አስገንዝቦ ነበር።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ሌሎች ዜናዎች፦

    የ200 ብር ኖት

    Anonymous
    Inactive

    የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) መግለጫ
    መስከረም 13፥ 2020

    የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ለኢትዮጵያ ውስብስብ የፖለቲካ ችግሮች አስተማማኝና ዘላቂ መፍትሄ ሊገኝ የሚችለው ሁሉን በሚያካትት ዴሞክራሲና በሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ተሳትፎ ብቻ ነው የሚል ቅን እምነት አለው። ይህንንም ለማድረግ ኦነግ ሀገሪቱን የማስተዳደር ስልጣን ያላቸውን እና የተቃዋሚ ቡድኖችን ጨምሮ ከተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎች ጋር በመሆን በኢትዮጵያ የፖለቲካ ቀውሶችን ለመፍታት የጋር ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ሲሠራ ቆይቷል። ኦነግ ከፍተኛ አመራሩን ወደ ሀገር ካዛወረ እ.ኤ.አ. ከመስከረም 15 ቀን 2018 ወዲህ ወደ ሁሉን አቀፍ እውነተኛ ዴሞክራሲ የሚያመራውን የሰላም ሂደት ስኬታማ ለማድረግ በሐቀኝነትና በታማኝነት ለመሥራት ወሰነ።

    ምንም እንኳን ከመጀመሪያው ጀምሮ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ሽግግር አያያዝ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መንግሥት እንዴት እንደተከናወነ አስመልክቶ ኦነግ ደስተኛ ባይሆንም፣ ይሻሻላል ብለን ተስፋ በማድረግ ሁኔታዎችን በትዕግስት ተቋቁመናል፤ ያለ ዋጋ ግን አይደለም።

    ሆኖም እ.ኤ.አ. በ2018 የተጀመረው የፖለቲካ ለውጥ ከውስጥ ከገዢው ፓርቲ እንዲሁም ከውጭ ከተቃዋሚ ቡድኖች ግዙፍ ተግዳሮቶች አጋጠመው። ሁኔታዎቹ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሱ በመሄድ በአሁኑ ወቅት ሁሉም ነገር ከቁጥጥር ውጭ ወደሆነበት ደረጃ በመድረስ መንግሥትን ወደ ውድቀት እያመራው ይገኛል። አሁን በሀገሪቱ ውስጥ በጣም እጅግ አሳሳቢ አለመረጋጋትና የተሰበረ ፖለቲካ ተስፋ ይስተዋላል፤ ሕዝቡ ከገዢው ፓርቲ ተስፋና እምነት አጥቷል። በሀገሪቱ ውስጥ ግልጽ “የሕገ-መንግሥታዊ ቀውስ” የተመለከትን ሲሆን፥ በስልጣን ላይ ያለው ፓርቲ መጀመሪያ ከገባቸው ቃላት ማሽቆለቆሉና ሕገ-መንግሥቱን የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለባቸውን የመንግሥት አካላት ለራሱ የፖለቲካ ጥቅም ሲገለገልባቸው ቆይቷል።

    የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮችንና አባላትን ማሰርና ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች የዕለት ተዕለት ሥራ ናቸው። ምንም እንኳን የጭካኔ ድርጊቶች ቢኖሩም፤ ኦነግ እና ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለውጡን በተናጥል እንዲሁም በጋራ ለመደገፍ ያላቸውን ፍላጎት መግለፃቸውን ቀጥለዋል።

    በተናጠል ካለው የመፍትሄ ሀሳብ በተጨማሪ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ዴሞክራሲያዊ ሽግግሩን ለመደገፍ በተለያዩ የተቃዋሚ ፓርቲዎች መድረክ ላይ ተሳትፏል። ከመድረኮቹ መካከል ለሽግግሩ እና ለዴሞክራሲያዊ ሂደቱ የጋራ ድጋፍ ለመስጠት ያለመው ትብብር ለሕብረ-ብሔር ዴሞክራሲያዊ ፌዴራሊዝም (ትብብር) አንዱ ነበር። እ.ኤ.አ. በሚያዝያ 2020 ይህ ትብብር በሽግግር ሂደት ላይ ለመንግሥት ሁሉን አቀፍ የመፍትሔ ምክረ-ሀሳቦችን አቅርቧል። የመፍትሄ ምክረ-ሀሳቦቹ በመግባባት ላይ ለተመርኮዘ የፖለቲካ እልባት በለውጡ እንዴት መቀጠል እንደሚቻልና የተረጋጋ ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር እንዴት በደረጃ-በደረጃ ሂደት ሊመሠረት እንደሚችል በግልጽ አስቀምጧል።

    የመፍትሄ ሀሳቦቹ በኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት ማዕቀፍ ውስጥ የተቀረፁ ሲሆን የለውጡ ሂደት ስህተቶችና የገዢው ፓርቲ ባህሪይ፣ አሁን ያሉ የአለመረጋጋትና የፀጥታ ጉዳዮች፣ እና የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ግምት ውስጥ ያስገባ ነው። በአጠቃላይ የለውጥ ሥርዓቱን ተግዳሮቶች በሁለቱም አቅጣጫዎች (ገዢው ፓርቲ እና ተቃዋሚዎች) በመተንተን በገዢው ፓርቲና በተቃዋሚ ቡድኖች በጋራ የሚተገበር ተግባራዊ የመፍትሔ ምክረ-ሀሳብ አቅርበናል።

    የቀረቡት ሀሳቦች ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሳተፉ የሚያስችላቸው አስገዳጅ የፖለቲካ ኮንቬንሽን እንዲኖርና እውነተኛ ዴሞክራሲን ለመገንባትና በሀገሪቱ ውስጥ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ የለውጡ ሂደት ትክክለኛ ቁጥጥርን ለማረጋገጥና ትብብሩና አባል ድርጅቶች እንዲሁም ሌሎች ኃይሎች ሁሉ የበኩላቸውን ሚና የሚጫወቱበትን የዜጎች ኑሮ መሻሻልን ያረጋግጣል።

    የታሰበው አስገዳጅ የፖለቲካ ኮንቬንሽን የሚከተሉትን ያካትታል፦

    1. የውጭ ግንኙነት ምክር ቤት፦ የሀገር ውስጥ አመኔታን ለማነሳሳት እና ዓለምአቀፍ ተቀባይነት እንዲያገኝ ለማድረግ
    2. የተቀናጀ ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት፦ በክልሎች ውስጥ የፀጥታ አደረጃጀቶችን ትግበራ ለመከታተል
    3. የዴሞክራሲ ግንባታ ተቋም፦ አስፈፃሚዎችን ተጠያቂ ሊያደርጉ የሚችሉ ገለልተኛ የፍትህ አካላት፣ የምርጫ ቦርድና ነጻ ሚዲያ ራስን ማስተዳደርና ስልጣንን ለመጠበቅ
    4. ከፍተኛ የፖለቲካ ችግሮችን ለመፍታት ብሔራዊ የጋራ መግባባት እንዲፈጠር መንግሥት ግንባታና በሀገር ግንባታ መካከል ያሉ አለመግባባቶችንና ልዩነቶችን የሚፈታ አካል
    5. ማንኛውንም ለምርጫው የሚደረግ ሌላ የጊዜ ማራዘሚያ ጥያቄን ለመገደብና አመቺውን የምርጫ ቀን ለማስቀመጥ የኮንቬንሽኑን አፈፃፀም የሚከታተል አካል

    በተጨማሪም እነዚህ አካላት የሚሠሩበትን የኃላፊነት፣ የሥርዓትና የአሠራር ዘዴ ዝርዝርን ጨምሮ የመፍትሔ ምክረ-ሀሳቦቹን ተግባራዊነት አመልክተናል። እነዚህን የመፍትሔ ሀሳቦች ተግባራዊ ማድረጉ ዴሞክራሲን ለመገንባትና በሀገሪቱ ውስጥ ዘላቂ ሰላም ለመፍጠር ይረዳል ብለን እናምናለን። ከዚህም ሌላ በክልላዊ መንግሥታት መካከል ያለውን የፀጥታ ጉዳዮች እንዲሁም በመንግሥትና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል እና በተቃዋሚዎች እርስ በርሳቸው መካከል ያሉ ልዩነቶችን እንዲሁም “በመንግሥት ግንባታ” እና “በሀገር ግንባታ” ላይ ተቃራኒ አቋም ላላቸው ጉዳዮችም መፍትሄ ያቀርባል።

    ስለሆነም በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የተስፋፉ ቀውሶችን ይፈታል ብለን ስለምናምን የኢትዮጵያ መንግሥት እነዚህን የመፍትሄ ምክረ-ሀሳቦች እንደገና እንዲያጤን በጥብቅ እናሳስባለን። እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን የሚወጡ ከሆነ በእውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሂደት ውስጥ የበኩላችንን ለመወጣት ፈቃደኛ መሆናችንን በድጋሚ ለመግለጽ እንወዳለን።

    በዚህ አጋጣሚ ዓለምአቀፍ ማኅበረሰብ ኢትዮጵያን ከሕገ-መንግሥታዊ ቀውሶች እና ከጠቅላላው ትርምስ ለመታደግ ጠንካራ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ እናቀርባለን።

    በተለይም የአፍሪካ ሕብረትየተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አካላት፣ የአውሮፓ ሕብረት እና ሌሎችም ዓለምአቀፍ ማኅበረሰብ የኢትዮጵያ መንግሥት ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ድርድር እንዲያደርግ እና ነፃና ፍትሃዊ ምርጫን የሚያዘጋጅና ተግባራዊ የሚያደርግ በሥልጣን መጋሪያ የሽግግር መንግሥት አማካይነት ሁሉን አካታች የዴሞክራሲ ፍኖተ-ካርታ በጋራ እንዲያስቀምጥ እንዲያሳስቡ አጥብቀን እንጠይቃለን።

    የአፍሪካን ሰላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ በብዙ የአፍሪካ አገራት ግጭትን ለመከላከል እና መፍትሄ ለማምጣት ውይይትን ማዕከል ያደረገ አቀራረብን በመምራት እና በማስተዋወቅ የአፍሪካ ሕብረት እየተጫወተ ያለውን ሚና እናደንቃለን። አሁን በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ቀውስ ከማንኛውም አካል የበለጠ የአፍሪካ ሕብረትን የላቀ ትኩረት ይጠይቃል ብለን እናምናለን። በአፍሪካ ሕብረት አዋጅ አንቀጽ 4 (ሸ) መሠረት ህብረቱ ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመከላከል በአባል ሀገር ውስጥ ጣልቃ የመግባት መብት አለው።

    ብሔራዊ እና ዓለምአቀፉ ማስረጃዎች የኢትዮጵያ ሥርዓት ቀጣይነት ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ላለፉት 27 ዓመታት በሀገሪቱ ዜጎች ላይ መፈጸሙንና ባለፉት ሁለት ዓመታትም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ እንደተፈፀመ በግልጽ ያሳያሉ። በተጨማሪም በአብዛኛዎቹ የክልል መንግሥታት አጠቃላይ አስተዳደርን አደጋ ላይ የሚጥሉና በመላ ሀገሪቱ የፀጥታ ቀውስ የሚያመጡ የተደራጁ እና ጠንካራ የታጠቁ ኃይሎች አሉ። አሁን ካሉት ቀውሶች እና በፍጥነት ከሚጓዙ እምቅ ግጭቶች እና ስጋቶች አንጻር የአፍሪካ ሕብረት በአፋጣኝ ጣልቃ ገብቶ ኃላፊነቱን መወጣት አለበት።

    አሁን በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ በአፍሪካ ሁለተኛዋን ትልቅ ሀገር መበታተን ብቻ ሳይሆን “ሰላማዊና የተረጋጋች አፍሪካን” የሚመኝ አጀንዳ 2063 የተባለውን የአፍሪካ ሕብረት ምኞት 4 (Aspiration 4) ለማሳካት ካሉ ዋና እንቅፋቶች መካከል አንዱ መሆኑን ማሳሰብ እንወዳለን። በተጨማሪም ፊንፊኔ (አዲስ አበባ) የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መቀመጫ፣ የኦሮሚያ ዋና ከተማና የአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤት በመሆኗ የአፍሪካ ሕብረት ጽሕፈት ቤትና እዚያ የሚሠሩ ከ2000 በላይ ሠራተኞች ደህንነት አሁን በኢትዮጵያ በተለይም በኦሮሚያ ካለው የሰላም የአለመረጋጋት ጉዳዮች ጋር ከግምት ውስጥ መግባት አለበት።

    የተባበሩት መንግሥታት በዓለም ላይ የሚከሰቱ ቀውሶችን በማስወገድ ረገድ የተጫወተውን ሚና የምንገነዘብ ሲሆን፥ የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት (UNSC)፣ የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (UNHRC) እና ሌሎችም በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የሚከሰቱ ቀውሶችን ለማስወገድ የድርሻቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን። በተለይም በዓለምአቀፍ ደረጃ ሰላምንና ፀጥታን ለማስጠበቅ በተባበሩት መንግሥታት ቻርተር መሠረት ቀዳሚ ኃላፊነት ያለው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በአፍሪካ ካሉ ትልልቅ ሀገሮች ሁለተኛ የሆነችዋ ኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊ፣ ሰብዓዊ መብቶች እና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች ሲያጋጥሟትና ወደ ውድቀት ስታመራ ጆሮ ዳባ ብሎ ማለፍ የለበትም።

    የአውሮፓ ሕብረት ብሔራዊ የለውጥ አጀንዳውን ለመደገፍና ከኢትዮጵያ ጋር ልዩ ልዩ የልማት ትብብሮችን በመፍጠር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ውህደት፣ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን እየተጫወተ ያለውን የመሪነት ሚና እናደንቃለን። ሆኖም እ.ኤ.አ. በ2018 የተጀመረው የፖለቲካ ለውጥ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በአግባቡ ባለመመራቱ ግዙፍ ፈተናዎች ገጥሞት ወድቋል። ይህም የአውሮፓ ሕብረት ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነትና ሕብረት ለኢትዮጵያ ያለውን ሁሉንም ምኞት ይገታል። ስለዚህ የአውሮፓ ሕብረት በቀጠናው ያሉ ቁልፍ አጋሮቹ ያጋጠማቸውን የፖለቲካ ቀውሶችን ለማስቀረት ባለው አቅም ጣልቃ እንደሚገባ እናምናለን።

    ስለሆነም፦

    1. በአፍሪካ ሕብረት በአንቀጽ 4 (ሸ) /Article 4(h)/ እና በሌሎች የሕብረቱ ደጋፊ አንቀጾች ላይ በተቀመጠው መብቱ ላይ በመመሥረት በኢትዮጵያ ቀውሶች ውስጥ ጣልቃ እንዲገባ ጥሪ እናቀርባለን።
    2. በኢትዮጵያ የሰላምና ደህንነት አደጋዎች በግልጽ የሚታዩ በመሆናቸው የጸጥታው ምክር ቤት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አንቀፅ 39 እና 41 ላይ በተመለከቱት ግዴታዎች መሠረት ተገቢ እርምጃዎችን እንዲወስድ ጥሪ እናስተላልፋለን። የመንግሥታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔም (UNHRC) በኢትዮጵያ የተፈጸሙ ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ለመቅረፍ በዚሁ መሠረት እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን።
    3. ይህ የመቶ ዓ መት ግዙፍ ግጭትና በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት ላይ የጎላ ጉዳት ስለሚያስከትልና የአውሮፓ ሀገራትና የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ እና የልማት አጋርነት የሚነካ በመሆኑ የአውሮፓ ሕብረት በኢትዮጵያ በተለይም በኦሮሚያ ለተፈጠረው አለመረጋጋት ከፍተኛ ትኩረት እንዲሰጥ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
    4. በኢትዮጵያ ያሉ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ያቀረብነውን የመፍትሄ ሀሳብ በቁም ነገር በመመልከት እየተቃረበ ያለውን አስከፊ ቀውስ ለማስቀረት ከእኛ ጋር እንዲሠሩ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

    ገለልተኛ የኦሮሞ የፖለቲካ ኃይሎችና መላው ኦሮሞ ሕዝብ ማንኛውንም ዓይነት የፖለቲካና የፀጥታ ችግር ለማስወገድ ለኦሮሚያ የሽግግር መንግሥት እንዲዘጋጁ ጥሪ እያቀረበ፥ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በዚህ አቋም ላይ ባለድርሻ አካላትን በሁለቱም የመንግሥት ደረጃዎች ማማከሩ እንደሚቀጥል ያሳውቃል።

    ድል ለሰፊው ሕዝብ!
    የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)
    ፊንፊኔ
    መስከረም 13፥ 2020

    የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)

    Semonegna
    Keymaster

    ሸገር ፓርክ በትልቅ ሥነ-ሥርዓት ተመርቋል

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የአዲስ አበባን ከተማ የቀይራል ተብሎ የሚጠበቀው ሸገር ፓርክ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በአዲስ ዓመት ዋዜማ ጳጉሜን 5 ቀን 2012 ዓ.ም. ባለስልጣናት እና ጥሪ የተደረገላቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር እንግዶች በተገኙበት ተካሂዷል።

    በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች እና የተለያዩ የሃይማኖት አባቶችና ሌሎችም በተገኙበት ተካሂዷል።

    ሸገር ፓርክ የኢትዮጵያን ሕብረ ብሔራዊነት በሚያሳይ መልኩ የተገነባ ሲሆን፥ በውስጡ የተፈጥሮ እጽዋትንም ያካተተ ነው። ፓርኩ የኢትዮጵያን ቀደምት ታሪክ በማሳየት የወደፊት ብሩህ ተስፋን የሚያሳይ የወዳጅነት ፓርክ እንደሆነ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዘግቧል።

    ግንባታው ከአንድ ዓመት በፊት የተጀመረው ሸገር ፓርክ በቻይና ግዙፉ የግንባታ ሥራ ተቋራጭ ኩባንያ “China Communications Construction Company (CCCC)” የተገነባ ነው።

    በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በፓርኩ ግንባታ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቻይና የተለያዩ ኩባንያዎች ትልቁን የወዳጅነት ሽልማት አበርክተዋል። በግንባታው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረጉ ኢትዮጵያዊያንም እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

    ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በሸገር ፓርክ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰዱ ነጥቦች፡-

    • አዲስ አበባ ይህን ፓርክ ማግኘቷ ስሟንና ደረጃዋን ከፍ ያደርገዋል፤
    • ይህ እና ሌሎች ፓርኮች የከተማይቱንና የሀገራችንን ገፅታ ያስውቡታል፤
    • ፓርኩ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል፤
    • ፓርኩ ተባብሮ መሥራት የሚያስገኘውን ውጤት ማሳያ ነው፤
    • ሸገር ፓርክ ከመሃል ሀገር ሳንወጣ ሩቅ ቦታ የተጓዝን የሚያስመስለን ፓርክ ነው፤
    • ከተለምዶው የተለየ ነገር ማየት አድማሳችንን ያሰፋዋል፤
    • [በግሌ] ይህ ፓርክ በዚህ ፍጥነት ለምረቃ ይበቃል ብዬ አላሰብኩም ነበር፤
    • በፓርኩ በሚገኘው የአበባ ማፍያ ስፍራ ከዓይናችን ጠፍተው የቆዩ አበቦችን ሳይቀር ማስተዋል ችያለሁ፤
    • ውበትን መሻት ካለንበት ሀኔታ ጋር አይፃረርም፤
    • አገራችንን የማስዋብ ጥረታችንን ከሌሎች የልማት ጥረቶቻችን ጋር ጎን ለጎን ካስኬድነው በአጭር ጊዜ የአገራችንን ገፅታ መቀየር እንችላለን፤
    • በፕሮጀክቱ የተሳተፉ ሁሉም አካላት የላቀ ምስጋና ይገባቸዋል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ሸገር ፓርክ

    Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የበረራ ትኬትን በኤሌክትሮኒክ ክፍያ ዘዴ አማካኝነት አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን ስምምነት አደረገ
    ደንበኞች የ‘ጉዞጎ’ (GuzoGo) መተግበሪያን በመጠቀም የሀገር ውስጥ እና ዓለምአቀፍ የበረራ ትኬቶችን መግዛት የሚችሉበት አሠራር ተዘርግቷል

    አዲስ አበባ – የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ሶልጌት ትራቭል (Solgate Travel) የበረራ ትኬት ሽያጭ በኤሌክትሮኒክ ክፍያ ሥርዓት ለማከናወን የሚያስችላቸውን ስምምነት ነሐሴ 29 ቀን 2012 ዓ.ም በተካሄደ ይፋዊ ሥነ-ሥርዓት ፈጽመዋል።

    በስምምነቱ መሠረት ደንበኞች የሲቢኢ ብር (CBE Birr) እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሁሉም ቅርንጫፎች አማካኝነት ክፍያቸውን መፈፀም የሚያስችል የ‘ጉዞጎ’ (GuzoGo) መተግበሪያን በመጠቀም የሀገር ውስጥ እና ዓለምአቀፍ የበረራ ትኬቶችን መግዛት የሚችሉበት አሠራር መዘርጋቱን ነው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ ምክትል ፕሬዚዳንት የሆኑት አቶ ዮሐንስ ሚሊዮን የገለፁት።

    ደንበኞች በረራቸውን ለማስመዝገብና የትኬት ሽያጭ ለማከናወን የሚያስችለው የ‘ጉዞጎ’ (GuzoGo) የሞባይል መተግበሪያን ከድረ-ገጽ በማውረድና የሞባይል ስልካቸው ላይ በመጫን አገልግሎቱን ማግኘት ያስችላልም ነው የተባለው።

    በስልካቸው ላይ የጉዞጎ መተግበሪያን ያልጫኑ፣ ለቸኮሉ ወይም በሌሎች የተለያዩ ምክንያቶች መጠቀም ላልቻሉ ተጓዦች ወደ 7473 የጥሪ ማዕከል በመደወል የጉዞ ቦታ ማስያዝና ትኬት መቁረጥ የሚቻልበት አሠራር መዘርጋቱም ነው የሶልጌት ትራቭል ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ ሽፈራው የገለጹት። ወደ 7473 የስልክ ጥሪ ማእከል በመደወል የሚፈልጉትን በረራ በማስመዝብ ክፍያቸውን በሲቢኢ ብር ወይም በባንኩ ቅርንጫፎች በማከናወን የትኬት ግዥ መፈጸም እንደሚችሉ አቶ ቴዎድሮስ ጠቁመዋል።

    በቀጣይ ደንበኞች አገልግሎቱን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሞባይል እና የኢንተርኔት ባንክ አገልግሎቶች አማካኝነት ማግኘት የሚችሉበት አሠራር በቅርቡ የሚተገበር መሆኑን ለማወቅ የተቻለ ሲሆን ተጓዥ ደንበኞች ‘የጉዞጎ’ (GuzoGo) መተግበሪያን በመጠቀም የሀገር ውስጥ የሆቴል ክፍል ማስያዝ (reservation) የሚችሉበት አገልግሎቱን ለመጀመር መዘጋጀታቸውን  ነው የጉዞጎ ሥራ አስኪያጅ አቶ በእርሱፈቃድ ጌታቸው በስምምነት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የገለጹት።

    ሶልጌት ትራቭል የኤሌክትሮኒክ የክፍያ ዘዴን በመተግበር የአየር ትኬት ሽያጭ አገልግሎት ለመስጠት ኢትዮጵያ ውስጥ በረራ ካላቸው 10 አየር መንገዶች የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኤመሬትስ (Emirate)፣ ሉፍታንዛ (Lufthansa)፣ ኳታር ኤርዌይስ (Qatar Airways)፣ ተርኪሽ ኤርላይንስ (Turkish Airlines)፣ ኬንያን ኤርዌይስ (Kenyan Airways)፣ ፍላይ ዱባይ (Fly Dubai)፣ ገልፍ ኤር (Gulf Air)፣ ኢጅፕትኤር (EgyptAir) እና ሳኡዲያ (Saudia) አየር መንገዶች ጋር እየሠራ በመሆኑ አገልግሎቱን የበለጠ ውጤታማ እንደሚያደርገው ኃላፊዎቹ ገልጸዋል።

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሶልጌት ትራቭል ጋር የፈጸመው ስምምነት የባንኩን ደንበኞች የዘመናዊ የክፍያ ሥርዓት ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያደርገው ጥረት አካል ሲሆን፥ ባንኩ ከውሃና ፍሳሽ አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከኢትዮ ቴሌኮም፣ ከሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽሕፈት ቤት፣ ከአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ፣ ከመልቲቾይስ ኢትዮጵያ፣ ከክፍለ ከተሞች፣ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከሌሎች የመንግሥትና የግል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋር በመተባበር በተለያዩ የኤሌክትሮኒክ ክፍያ ዘዴዎች አገልግሎቱን እያቀረበ እንደሚገኝ ይታወቃል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

    GuzoGo

    Anonymous
    Inactive

    አዲስ አበባ በራሷ ግዛተ-መሬት ላይ የፌዴራል አድያምነት /ክልልነት/ መብት ሊረጋገጥላት ይገባል!
    ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ

    የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አወቃቀር በመመዘኛዎቹ ላይ በኢትዮጵያ ተፃራሪ አቋም ባላቸው ልሂቃን ዘንድ ስምምነት ላይ ሊደርስ ቢችል፣ ፌዴራላዊ የመንግሥት አደረጃጀት የፖለቲካ አለመግባባት መንስ ዔ ሊሆን የሚችል አልነበረም። ይህ ጥያቄ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ችግር ዋነኛ መገለጫ ሊሆን የበቃው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ልሂቃን በዚህ ጥያቄ ዙሪያ ላለፉት ሃምሳ ዓመታት ሊግባቡ ባለመቻላቸው ነው። ሊግባቡ ያልቻሉበትም ምክንያት በኢትዮጵያ ሀገረ-መንግሥት የግንባታ ታሪክ ላይ ልዩነታቸውን ማጥበብ ባለመቻላቸው ነው። ይህ ትውልድ ደግሞ በአጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት በ1940ዎቹ ዓመታት ተወልዶ በ1950ዎቹ መጨረሻና በ1960ዎቹ መጀመሪያ ላይ ለዩኒቨርሲቲ ደረጃ የደረሰው ትውልድ ነበር። እንደ አጋጣሚ ሆኖ በ1960ዎቹ ሁኔታ ደግሞ ዓለም በሁለት ተፃራሪ የካፒታሊዝምና የሶሻሊዝም ጎራዎች ፉክክር ተቀስፋ ተይዛ የነበረችበት ወቅት ነበር። በ1960ዎቹ ለጉልምስና ከደረሰው ትውልድ ውስጥ አብዛኛው ነው ባይባልም ተራማጅ የሆነ አስተሳሰብ አለኝ ብሎ ያቀነቅን የነበረው የትውልዱን የአመራር ሚና የተጫወተው የማርክሲዝም ሌኒኒዝም (Marxism–Leninism) አስተምህሮ የተቀበለው ነበር።

    ይሁንና የዚህ የ1960ዎቹ የተማሪ አብዮተኞች እና የ እ ነሱ ከፊል ውጤት ሆነው ያቆጠቆጡት የነገድ ድርጅት መሪዎች የኢትዮጵያን ታሪክ በተፃረረና ባልተገናዘበ ሁኔታ የሶቭየት ሕብረትን የኮሚኒስት ፓርቲ መሪ የስታሊንን “የብሔርና የቅኝ ግዛት ጥያቄ” መጽሐፍ ቃል በቃል በመገልበጥ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ዋነኛ ችግር “የጨቋኝና የተጨቋኝ ብሔረሰቦች መስተጋብር ነው” የሚል የሀሰት የታሪክ ትርክት ይዘው ተነሱ። እነዚህ ከተማሪ አብዮተኝነት ወደ ነገድ ድርጅትነት የተሸጋገሩት ከደርግ መንግሥት ጋር ለ17 ዓመታት ጦርነት አድርገው በታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ያላሰለሰ ድጋፍ በ1983 ዓ.ም በኢትዮጵያ ጦር ላይ ድል ሊቀዳጁ በቁ። አነዚህ ኃይሎች በተጠናወታቸው “የጨቋኝና የተጨቋኝ ብሔረሰቦች” የሀሰት ትርክት ውጤት የሆነውን የመገንጠል መብት ሕገ-መንግሥታዊ መብት ያደረገ፣ ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ ያለመ ቋንቋን መሠረት ያደረገ መንግሥታዊ የፌዴራል አወቃቀር በኢትዮጵያ ላይ አነበሩ።

    በሀገራችን ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ የጐሳና የዘረኝነት ፖለቲካዊ አደረጃጀት የመንግሥት የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ አደረጃጀት ዓይነተኛ መገለጫ ከመሆን አልፎ ይኸው ዓይነት አደረጃጀት  ወደ እምነት ተቋማት ሳይቀር ዘልቆ እንዲገባ ተደረገ። በሀገሪቱ ታሪክ በማይታወቅ ሁኔታ በተረኝነት መንፈስ የተቃኘ ተቋማዊ/መንግሥታዊ ሙስና እና የፍትህ መዛባት የሥርዓት መገለጫ ሊሆን በቃ። ከሕዝቡ ታሪካዊ አሠራር ጋር ባልተገናዘቡ የክልል አደረጃጀቶች ምክንያት በሀገራችን እንግዳ በሆነ መልኩ ማንነትን እና እምነትን መሠረት ያደረጉ ግጭቶች እንዲበራከቱ፣ ሕዝብ የተረጋጋ ሕይወት እንዳይኖረው በፌዴራል መንግሥቱና በክልል መንግሥታት መካከል የኃላፊነትና የተጠያቂነት ጉዳይ አሻሚ በማድረግ፣ የሀገሪቱ ብሔራዊ ስሜት እንዲላሽቅ በምትኩ ጠባብና ክልላዊ አስተሳሰብ እንዲሰፍን ተደረገ። በኢትዮጵያ የዘውግ ፌዴራሊዝም ሥርዓት ችግር ብሔረሰብን ዋነኛው የፌዴራል ሥርዓቱና የሀገር መንግሥት ግንባታ መሠረት ማድረጉ ነው።

    እዚያው ተወልዶ ያደገውና ከአራቱም የኢትዮጵያ ማዕዘናት የመጣውን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ አንድ ብሔረሰብን እና አንድ ቋንቋ ተናጋሪነትን መሠረት አድርጎ በተዋቀረ ክልል ውስጥ አስገብቶ እንዲተዳደር ማድረግ  ፍትሃዊነት የለውም። የአዲስ አበባ ሕዝብ ጥያቄ ከራሴ ውጭ በእኔ ዕጣ ሌላ ሊወስንብኝ አይገባም የሚል ነው። አዲስ አባባ በኦሮሚያ ምድረ ፅፋዊ (geographic) ክልል ውስጥ በመገኘቷ ብቻ ለአዲስ አበባ ባለቤትነት የመብት መብለጫ፣ ለተፈጠረ ውጥንቅጥ ደግሞ የአዲስ አበባ ሕዝብን መብት ማሳነሻ ማድረግ በምንም መመዘኛ ተገቢነትም ሆነ ተቀባይነት የለውም።

    የኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት በአንቀጽ 69 “የፌዴራሉ መንግሥት ርዕሰ ከተማ አዲስ አበባ ነው። የከተማው አስተዳደር ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ሥልጣን ይኖረዋል። ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል” ይላል። የአዲስ አበባ ከተማ ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ሥልጣን እንዳለው ቢታወቅም የህወሓት እና የኦነግ በሆነው ሕገ-መንግሥት ውስጥ “በአዲስ አበባ ከተማ የኦሮሚያ ክልል ልዩ ጥቅም ይኖረዋል” በሚል መካተቱ ችግሩን ሆን ተብሎ እንዲወሳሰብ አድርጎታል።

    በ1989 ዓ.ም የወጣው የአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር ማቋቋሚያ ቻርተር መሠረት አዲስ አበባ ራሷን በራሷ እንድታስተዳድር ሲደነገግ፣ በሕገ-መንግሥቱም ሆነ በአዲስ አበባ ከተማ ቻርተር መሠረት የከተማዋ ስምና ስያሜ አዲስ አበባ እንደሆነ ተደንግጓል። ይሁንና ቻርተሩን መሠረት በማድረግ ተዘጋጅቶ የቀረበው ረቂቂ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ የመጽደቅ ሂደቱ በደባ እንዲቀር ተደርጓል። አዲስ አበባ እንደ ዋሽንግተን ዲሲ እና እንደ ካንቤራ (Washington, DC and Canberra) የፌዴራል መንግሥት ግዛት ናት የሚል የሕግ አንቀጽ የለም። ይህ አይደለም እንዳይባል በወንጀልም ሆነ በፍትሀ-ብሔር ጉዳይ በአዲስ አበባ የግዛት ክልል ውስጥ የተፈፀመ ወይም የተከናወነ የሕግ ጥሰት ግን ልክ የፌዴራል መንግሥት ይዞታ አንደሆነችው ዋሽንግተን የመዳኘት ሥልጣንን ለፌዴራል መንግሥቱ ይሆን ዘንድ በሕግ ተለይቶ ተሰጥቷል። ማለትም በተግባር የፌዴራል መንግሥቱ አዲስ አበባን እና ድሬደዋን የራሱ ግዛት አድርጓቸዋል።

    ሕገ-መንግሥቱ አዲስ አበባ እራሱን የማስተዳደር ሙሉ ሥልጣን የሰጠው መሆኑ ከላይ የተጠቀሰው የወንጀልና የፍትሀ-ብሔር ጉዳዮችን ለመዳኘት ከተሰጠው ሥልጣን ጋር ሲዳመር አዲስ አበባ ልክ እንደ ዋሽንግተን የፌዴራል ግዛት እንደሆነች ለመረዳት ይቻላል። በተጨባጭ ግን አዲስ አበባ ከተማ የተተወላት የከተማ-ነክ አስተደደርና ከማዘጋጃ ቤት አገልግሎት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን የመዳኘት ሥልጣን ነው። ማለትም ስለ ዳኘነት ሲሆን መሬቱ የፌዴራል መንግሥት፣ ስለ ሌሎች አስተዳደራዊ ጉዳዮች ሲሆን የከተማ መስተዳድሩ ሆኗል።

    አዲስ አበባ ራሷን የማስተዳደር መብት በሕገ-መንግሥቱ የታወቀ ቢሆንም፤ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ጭምር ኢ-ፍትሀዊ በሆነ መንገድ ውክልና የላትም። ሕገ-መንግሥቱ ከሚደነገገው ውጭ ስትደዳደር የቆየችው በህወሓት/ኢህአዴግ፣ አሁን ደግሞ በኦህዴድ/ብልጽግና ነው። በሌሎች ክልሎች ክልሎችን የሚያስተዳድሩ የክልል ፓርቲዎች አሉ /ትግራይ፣ ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ደቡብ ወዘተ…/ አዲስ አበባ ላይ ግን የሚወክላት የፖለቲካ ፓርቲ የለም። ገዥ ፓርቲዎች ፍላጎታቸውን የሚጭኑባት ከተማ ናት። ቀደም ሲል ህወሓት/ኢህአዴግ አሁን ደግሞ ኦህዴድ/ብልጽግና ፓርቲ አዲስ አበባን ማስተዳደሩን ቀጥሎበታል። ይህ ሁኔታ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በሕገ-መንግሥቱ የተሰጣቸውን ራሳቸውን የማስተዳደር መብት ፍፁም የሚጥስ ነው።

    አዲስ አበባን እንዲመራ የሚመደበው በገዢው ፓርቲ ውስጥ ከነበሩ ወይም ካሉ የክልል ገዢ ፓርቲዎች እንጂ በከተማው ሕዝብ ነፃ ምርጫ አልነበረም፤ አሁንም አይደለም። አዲስ አበባ ቀደም ሲል ከሁለቱ ክልሎች /ትግራይኦሮሚያ/ አሁን ከ “ለውጡ” ወዲህ ደግሞ ከኦሮሚያ ክልል በሚመጡ ተሹዋሚዎች እንድትደዳደር መደረጉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ጥቅምና ፍላጎት እንዳይከበር ያደረገ የፖለቲካ ደባ ነው። ከዚህም ባሻገር ከ7 ሚሊዮን የሚልቀውን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴው በግብር መልክ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለመንግሥት ካዝና የሚያስገባውን ነዋሪ የፖለቲካ ባይተዋር ያደረገ እና በዕጣ ፈንታው ላይ  እንዳይወስን ያደረገ ኢ-ፍትሀዊ የሆነ የፖለቲካ አካሄድ ነው። የአሜሪካን አብዮት እንደቀሰቀሰው /Taxation without Political Representation/ እንደሚለው መፈክር ሠርቶ ግብሩን እየገበረ የፖለቲካ ባይተዋር በማድረግ በዕጣ ፈንታው ላይ እንዳይወስን አድርጎታል። ይህ ፍትሀዊ ያልሆነ የፖለቲካ አካሄድ ከመሆኑም በተጨማሪ በግልጽ የሕገ-መንግሥቱን አንቀጽ 49 እና አንቀጽ 89 ይጥሳል።

    የኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት ትልቁ ወለፈንዲ የአዲስ አበባ ጉዳይ ነው። በአንቀጽ 69 መሠረት የአዲስ አበባ ከተማ የፌዴራሉ ርዕሰ ከተማ እና የከተማው ነዋሪ ሕዝብ እራሱን በራሱ የማስተዳደር መብት ይኖረዋል ሲል ደንግጓል። ማለትም፥ አዲስ አበባ የተወላጆቿና እና የሁሉም ከ80 በላይ የሆኑት የኢትዮጵያ ብሔረሰቦች በባለቤትነት የሚኖሩባት ከተማ ናት። የአዲስ አበባን አስተዳደር ስንት አማራ፣ ስንት ኦሮሞ፣ ስንት ትግሬ፣ ስንት ጉራጌ፣ ስንት ወላይታ፣ ስንት ሱማሌ፣ ስንት አደሬ፣ ስንት ጋምቤላ፣ ስንት ቤንሻንጉል፣ ስንት ማኦ ወዘተ… እንደሚኖሩባት በተጨባጭ የተረጋገጠ አሃዛዊ መረጃ (statistics) ስለሌለ የአዲስ አበባ ባለቤትነት ሊሰጥ የሚችለው ከሕገ-መንግሥቱ መንፈስ ውጭ ለመላ ቋሚ ነዋሪዎቿ ነው ሊሆን የሚችለው። ይሁንና የአዲስ አበባን ከተማ ባለቤትነት በተመለከተ እንደ ሌሎች የፌዴራል መንግሥት ዋና ከተማዎች እንደሆኑት እንደ ሞስኮ፣ በርሊን፣ ቪየና እና ብራስልስ ለፌዴራል መንግሥት ተጠሪ ያልሆኑ፣ በኢትዮጵያም ከ1983 ዓ.ም ሰኔ ወር ጀምሮ ሕገ-መንግሥቱ ተግባራዊ እስከ ተደረገበት 1987 ዓ.ም ነሐሴ ወር ድረስ ክልል 14 ተብላ የክልልነት ደረጃ የተሰጠበትን ሁኔታ መልሶ ተግባራዊ ማድረግ  ፍትሃዊ እና የነዋሪዎቿን ሕጋዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው።

    አዲስ አበባ እንደ ፌዴራል መንግሥት ርዕሰ ከተማነቷ የግዛተ-መሬቷ ባለቤትነትን ለፌዴራል መንግሥቱ ሳይሆን በሽግግር ወቅት እንደነበረው በፌዴራል አድያምነት /በክልልነት/ ደረጃ እንደገና እንድትዋቀር ባልደራስ እውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) ለከተማዋ ሕዝብ ጥሪውን ያቀርባል።

    ከሀገራችን ዘመናዊ የታሪክ ጅማሮ ጋር የተሰናሰለ እድሜ ያላት አዲስ አበባ ከተማ፥ በመልክ-ዕምድር አቀማመጧ የሀገሪቱ እምብርት ላይ መገኘቷ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታዋን የጎላ አድርጓታል። ይህ ሁኔታዋ ለሀገራችን ዜጎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ለመስጥ የሚያስችል አቅም ያላት ከተማ እንድትሆን ሰፊ ዕድል ሰጥቷታል። ነገር ግን ከተማዋ ያላትን ሰብዓዊና ቁሳዊ አቅም አሟጣ በመጠቀም ለነዋሪዎቿ ተስፋ መሆን እንዳትችል በሀገራቸን የነበሩ እና ያሉት ገዢዎች አተያይ እና የአመራር ፈሊጥ ትልቅ ተግዳሮት ሆኗል። “በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” እንዲሉ ጎሳን መሠረት ያደረገው የባለፉት 30 ዓመታት የሀገራችን ፖለቲካን ያነበረው ሥርዓት የአዲስ አበባ ከተማን ህልውና የበለጠ ተፈታትኖታል፤ ከባድ አደጋንም የፈጠረ ሆኗል።

    አዲስ አበባ የሀገራችን ርዕሰ መዲና ከመሆኗ ባሻገር፣ የአፍሪካ ሕብረት እና የጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ተምሳሌትና መናኸሪያ፣ የትላልቅ ዓለም አቀፍ ተቋማት መታደሚያ ናት። የሀገራችን 65% ምጣኔ-ሀብት በአንበሳ ድርሻነት ይዛለች፤ በሀገሪቱ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ቤተ-እምነቶች እና የእምነቱ ተከታዮች ተቻችለው የሚኖሩባት የአብሮነት መገለጫ ከተማ ስትሆን፥ የታሪካችን መገለጫ የሆኑ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርስ እና ትውፊት የተመዘገበባት፣ እንዲሁም የተለያዩ ቋንቋዎችና ባህሎች ሕብር ፈጥረው በነፃነት የሚንጸባረቁባት የኢትዮጵያ ብዝሃነት ማሳያ ፈርጥ ናት።

    ከተማችን አዲስ አበባ ባለፉት 3 አስርት ዓመታት ሲመሯት የነበሩት ሁሉ ምን ልጠቀምባት እንጂ ምን ላድርግላት የሚል ኃላፊነት የሚሰማቸው ባለመሆኑ ችግሮቿን የተወሳሰቡ አደርጎታል። እንደ ፓርቲያችን እምነት፥ ለዚህ ችግር በዋነኝነት ያጋለጣት በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ አስተዳድር ተሰይሞ ሊያስተዳድራት አለመቻሉ ጉልህ ስፍራ ይይዛል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን በከንቲባነት ሲመሩ የቆዩት ግለሰቦች በአብዛኛው የከተማውን ነዋሪ ሥነ-ልቦና በቅጡ ያልተረዱ፣ ራዕይ-አልባ የሆኑ እና ከፍተኛ የብቃት ጉድለት የሚስተዋልባቸው ናቸው።

    አዲስ አበባ ከተማ ራስ ገዝ (በአሁኑ አጠራር ክልል) እንድትሆን መሆኑ እውነተኛ ፌዴራላዊ አስተዳደር በኢትዮጵያ ውስጥ ለማንበር በሚደረገው ጥረት ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ያምናል፤ በመሆኑም አዲስ አበባ ራስ ገዝ አስተዳደር እንዲኖረው በላቀ መንገድ መታገል አስፈላጊ ሆኗል።

    የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ላለፉት ዘመናት በተለይም የህወሓት/ኢህአዴግ ሥልጣን ዘመን ጀምሮ በመረጠው የመተዳደር መብቱን ተነፍጎ፣ ከኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ኦህዴድ በውክልና ተቀብሎ አስተዳድራለሁ በሚል የተረኝነት፣ የሙስና፣ የባህል በአጠቃላይ የዘረኝነት ሰለባ ሆኗል። የተረኛነት ስሜት ነቀርሳ የሆነበት ኦህዴድ/ብልጽግና የአዲስ አበባን ሕዝባዊ አውቃቀር (demography) ከመቀየር ጀምሮ ተጠንቶ የከተማው ሕዝብ ባልመከረበት የትምህርት ሥርዓት ውስጥ ረጅም እጁን ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ በመስደድ፣ የከተማውን መሬት በማስወረር እና ነዋሪው ጥሮ ግሮ ቆጥቦ የሠራውን ቤት አንዴ ለኦሮሚያ የመንግሥት ሠራተኞች በሚል ሌላ ጊዜ ደግሞ የተለየ ምክንያት በመስጠት እየዘረፈ  መሆኑ የከተማዋን ነዋሪ በደል ጫፍ አድርሶታል።

    ዛሬ ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞካራሲ ፓርቲ ይህንን የዘመናት የአዲስ አበባ ሕዝብ ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ መብቱን የሚጠይቅበት ጊዜ ላይ መድረሱን ተገንዝቧል። በኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ፍትህ ማግኘት የሚቻለው የከተማው ነዋሪ ራሱ የመረጠው ሥርዓት ሲዘረጋ መሆኑን በቅርቡ ተረድቷል። አሁን እየደረሰበት ያለው ግፍ መነሻው ለሕዝብ ተጠያቂነት ያለው ትክክለኛ አስተዳደር አለመኖሩና ይህንን ተገን በማድረግ ወደ ዝርፊያ የገቡና ለዚሁ ሁኔታ እንዲያመቻቸው ብቻ የሚሠሩ የውክልና መሪዎች በመሆናቸው ከእነዚህ አስተዳደር ውጭ እንዲሆን ለማስቻል ዴሞክራሲን ለማስፈን እንዲረዳ ነው።

    ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ አዲስ አበባ ከተማ ራስ ገዝ እንድትሆን ብዙ ዜጎች ጥያቄ ሲያነሱ እንደነበረ ያምናል። ይህ የከተማው ነዋሪ ጥያቄም፣ ፓርቲው እንዲመሠረት ገፊ ምክንያት እንደሆነ በመገንዘብ፣ ትላንት ዜጎች ሲያነሱት የነበረው ጥያቄ ወደላቀ ምዕራፍ መሸጋገሩን በማብሰር፤ የአዲስ አበባ ሁለንተናዊ ችግር አስጨንቋቸው እና እንቅልፍ ነስቷቸው ለነበሩ ዜጎች ሁላ ይህ የእናንተ የትላንትና የትግል ጥያቄ በመሆኑ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባችኋል። የዜጎች በደልና ጭቆና እንዳንገበገባችህ እናምናለን፤ ይህንንም ለመቅረፍ በጋራ እንድንቀሳቀስ እንጠይቃለን።

    ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ የከተማችንን ነዋሪ የሚመጥን አስተዳደር እንዲዘረጋ የሚያደርገው ጥረት፣ ከአንድ የፖለቲካ ድርጅት ጥያቄ በላይ እንደሆነ ያምናል። በመሆኑም በሀገራችን የምትገኙ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ለከተማው ነዋሪ የራሱን ራስ ገዝ አስተዳደር እንዲመሠረት አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍና ትብብር እንድታደርጉለት፤ ምሁራን እና ታዋቂ ግለሰቦችም የሚመሠረተው አስተዳደር የሚያስፈልገውን ድጋፍና አወቃቀር በአግባቡ እንዲይዝ መልክ ለማስያዝ የሚረዳ ልምዳችሁን፣ እውቀታችሁን እንዲሁም ተፅዕኖ የመፍጠር አቅማችሁን እንድታበረክቱ ጭምር አደራ ይላል።

    በዋነኝነት የአዲስ አበባ ራስ ገዝ አስተዳደር ባለቤት ሁሉም የከተማው ነዋሪ እንደሆነ ባልደራስ በጽኑ ያምናል። ይህንንም ለማድረግ የሚያስችል ሕጋዊና ሰላማዊ ትግል በማድረግ የፌዴራል መንግሥት ጥያቄውን እንዲቀበልና በሀገሪቱ አሁን ባለው ሥርዓት መሠረት ሕዝበ-ውሳኔ ተካሂዶ የራስ ገዝ አስተዳደር (ክልል) እንዲሆን እንጠይቃለን። ይህንንም ጥያቄ እውን ለማድረግ እና በሕጉ አግባብ እንዲስተናገድ ለማድረግ የተከማው ነዋሪ የስምምነት ፊርማ የማሰባሰብ ሂደት ውስጥ ተሳታፊ እንዲሆን ጥሪ እናቀርባለን። ጥሪውም በነዋሪ ሕዝቧ ፍላጎት ላይ የተመሠረተ መሆኑን ለማስረገጥ ድጋፉን በፊርማ የሚያቀርብበት የአሠራር ዘዴ ይቀይሳል።

    በመጨረሻም ይህንን የጳጉሜን ሣምንት በግፍ ለታሰሩ የፓርቲያችን መሪ አቶ እስክንድር ነጋ፣ አቶ ስንታየሁ ቸኮል፣ ወ/ሮ ቀለብ ስዩም እና ሌሎች የፓርቲው አባላትና አመራሮች በግፍ ከታሰሩበት እንዲፈቱ በተለያዩ መንገድ ግፊት ለምታደርጉ ወገኖች ምስጋናችንን እያቀረብን፥ መንግሥት በማን አለብኝነት ያለኃጢያታቸው አስሯቸው የሚገኙ ንፁሃን መሪዎቻችንን እና አባላቶቻችንን በአስቸኳይ እንዲፈቱ በድጋሚ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    መጪው የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት፣ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ተላቀን በሰላም ወጥተን የምንገባበት፣ ለሀገራችን ዜጎች ሰብዓዊ መብት የሚከበርባት፣ ለተበደሉ ፍትህ የሚሰፍንበት፣ ዴሞክራሲ የሚያብብበት እንዲሆን እንመኛለን፤ ለብሔራዊ መግባባት ሁሉም የፖለቲካ ወገኖች አንድ ላይ ተቀምጠው ስምምነት ላይ የሚያደርስ ተጨባጭ ሥራዎች የምናከናውንበት ዘመን እንዲሆን መልካም ምኞቱን ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ይገልጻል።

    ድል ለእውነተኛ ዲሞክራሲ!
    ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ)
    ጳጉሜ 3 ቀን 2012 ዓ.ም

    ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ

    Anonymous
    Inactive

    ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

    የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ድርጅታዊ ህልውና ባገኘባቸው ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ የአማራ ሕዝብ እውነተኛ ድምፅ በመሆን ሕዝባችንን ከህልውና ስጋት ለመታደግ፣ አንድነቱን ለማረጋገጥና ጥቅሞቹን ለማስጠበቅ የተቀጣጠለውን ንቅናቄ ጠንካራና የማይቀለበስ መሠረት በማስያዝ ረገድ የበኩሉን አስተዋጽዖ አድርጓል። የአማራውን ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ምጣኔ ሀብታዊ ጥያቄዎች ከፍ አድርጎ በመያዝና ለነፃነት፣ ለፍትህና ለእኩልነት የሚደረገውን ትግል በመምራት ሕዝባዊ አመኔታን ለማትረፍ ችሏል።

    አብን ጠንካራ ኢትዮጵያዊ ርእይ የሰነቀ ንቅናቄ በመሆኑ በሀገራዊ የሽግግር ሂደት ውስጥ አዎንታዊ ሚና ለመጫወት ከፍተኛ ጥረት አድርጓል። አማራው በታላቅ መስዕዋትነት ያስገኘው ለውጥ መስመሩን እንዳይስት፣ በትግላችን የተንበረከኩ ጠላቶች መልሰው እንዳያንሰራሩ፣ የፈነጠቀው የለውጥ ተስፋ እንዳይጨነግፍና ዳግም የሀገራችንና የሕዝባችን ህልውና አደጋ ላይ እንዳይወድቅ ያላሰለሰ ትግል ሲያደርግ ቆይቷል።

    ይሁን እንጂ ጥረቶቻችን እንደሚጠበቀው ያህል ፍሬ ከማፍራት ይልቅ እየመከኑና የሀገራዊው የፖለቲካ አውድ ከጊዜ ጊዜ ተስፋ አስቆራጭ እየሆነ መምጣቱን የሚጠቁሙ በርካታ ምልክቶችን አስተውለናል። ንቅናቄያችን በዚህ ረገድ በአማራ ሕዝብና በኢትዮጵያ ላይ ያንዣበበውን ጽኑ አደጋ በሚያሳዩ ሦስት አበይት ጉዳዮች ላይ ያለውን አቋም በግልፅ ለማሳወቅ ይሻል።

    1. በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈፀሙ በደሎችና የዘር ጥቃቶችን በተመለከተ፦

    አብን በሀገራችን በየትኛውም ክፍል፣ በማናቸውም ኃይልና በየትኛውም ሕዝብ ላይ የሚፈፀሙ የሽብርና የዘር ጥቃቶችን ያለማመንታት አውግዟል። የጋሞ ተወላጆች በቡራዩ በግፍ ሲጨፈጨፉ፣ የአዲስ አበባ ወጣቶች ታፍሰው ወደ ጦር ካምፕ ሲጋዙ፣ የጌዴዖ ወገኖቻችን ሰብዓዊ እርዳታ ተነፍገው በርሀብ ሲረግፉ፣ ቤተ እምነቶች በእሳት ሲጋዩና አማኞች በጭካኔ ሲታረዱ ድምፃችንን ከፍ አድርገን ለኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ እንዲሁም ለዓለም ማኅበረሰብ በማሰማት ዜጎች ከጥቃት እንዲጠበቁና ሰብዓዊ መብቶቻቸው ተከብረው እንዲኖሩ ጥረት አድርገናል።

    በተለይ በኦሮሚያ ክልል በተደጋጋሚ የተከሰቱትን ማንነትና እምነት ተኮር የዘር ማፅዳት፣ የዘር ፍጅትና ሰብዓዊ ወንጀሎችን ለመከላከልና ለማስቆም ሰፊና ያላሰለሰ ትግል አድርገናል። ዜጎች በአማራነታቸው ተመርጠው ቤታቸው ሲፈርስና ሲፈናቀሉ፣ አማራ ተማሪዎች ከኦሮሚያ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች በዘር ጥቃት ተገደው ሲለቁና እገታ ሲፈፀምባቸው፣ በኦሮሚያና በሌሎች ክልሎች በሚኖረው ሕዝባችን ላይ የዘር ማጽዳትና ሰብዓዊ ወንጀሎች ሲፈጸሙ ከማውገዝና ማዕከላዊና ክልላዊ መንግሥታት ጥቃቶቹን በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ ግፊት ከማድረግ ባለፈ አደጋውን አስቀድሞ መከላከልና ማስቀረት በሚቻልበት መንገድ ላይ ሰፊና የተቀናጁ ጥረቶችን ስናደርግ ቆይተናል።

    በዚህ ረገድ ንቅናቄያችን ካደረጋቸው በርካታ ጥረቶች መካከል ለአብነት ሚያዚያ 29 ቀን 2012 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል የሽብር ኃይሎች ማንነት ተኮርና በተለይም አማራውን ዒላማ ያደረጉ የዘር ጥቃቶች ሊፈፅሙ እንደሚችሉ ከሁኔታዎች ጥናት በመተንበይ ለዚህ ማዕከላዊ መንግሥቱ ልዩ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርግ በአካል ለሀገሪቱ ከፍተኛ መሪዎች ከማስረዳት ባለፈ በመግለጫ ጭምር በአንክሮ ማሳሰቡ ይታወሳል።

    1.1. ከሰኔ 22 ለሊት እስከ ሰኔ 25 ቀን 2012 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል የተደረገው የዘር ማጥፋት፦

    መንግሥት ተቀዳሚ የሆነውን ሰላምና ደኅንነት የማሰከበር ኃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ ባለመቻሉ የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ሽፋን በማድረግ ጽንፈኛ ኃይሎች ጥምረት ፈጥረውና ተዘጋጅተው በኦሮሚያ ክልል በሚኖሩ በዋነኝነት በአማሮች ላይ፣ በተጓዳኝም በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ከሰኔ 22 ሌሊት እስከ ሰኔ 25 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ በሽፋኑም ባስከተለው ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመትም እስከዛሬ ከታየው እጅግ ሰፊና አሰቃቂ የዘር ጥቃት ፈፅመዋል።

    አብን ይህን መረን የለቀቀ የዘር ማጥፋት ድርጊት በወቅቱ ከማውገዝ ባሻገር ጭፍጨፋው በተፈፀመባቸው አካባቢዎች የጥናት ቡድን ልኮ በደረሰው ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት ላይ ዝርዝር መረጃዎችን በማሰባሰብና በማጠናቀር ሰነድ አዘጋጅቷል። ሰነዱ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶ ለሚመለከታቸው የሀገር ውስጥና ዓለማቀፍ አካላት በተለይም ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ ፣ ለሰብአዊ መብት ተቋማትና ለአማራ አደረጃጀቶች እየተሰራጨ ሲሆን ፣ ንቅናቄያችን የዘር ፍጅቱ እውቅናና ትኩረት እንዲያገኝና ፍትህ እንዲረጋገጥ ቀጣይ እርምጃዎችን የሚወስድ ይሆናል።

    ሀ. የጥፋቱ አድማስ፦

    ንቅናቄያችን ያደረገው ጥናት በወቅቱ በኦሮሚያ ክልል ከተፈፀመው ሰፊ የዘር ጥቃት ውስጥ በስድስት ዞኖች በሚገኙ በ26 ከተሞችና አካባቢዎች የደረሰውን ያካትታል። በምሥራቅ ሸዋ ዞን ደብረዘይት፣ ናዝሬት፣ መተሐራ፣ ዝዋይ፣ አዳሚ ቱሉ፣ ቡልቡላ፣ መቂ ከተሞችን፤ በምዕራብ አርሲ ዞን ሻሸመኔ፣ አርሲ ነገሌ፣ አሳሳ፣ ዶዶላ ከተሞችን፤ በምሥራቅ ሃረርጌ ዞን ሃረማያ፣ ባቴ፣ ከምቦልቻ፣ ጉርሱም ከተሞችን፤ በሃረማያ ወረዳ ኦዳ በሊናና መልካ ገመቹ አካባቢዎችን፤ በጃርሶ ወረዳ አሌ ከተማን፣ ሚደጋ ቶላ ወረዳን፤ በባቢሌ ወረዳ የተለያዩ ስፍራዎችን፤ እንዲሁም በሃረሪ ክልል ሃረር ከተማን፤ በምዕራብ ሃረርጌ ዞን ጭሮ ወይም አሰበ ተፈሪ፣ ሚኤሶ፣ አሰቦት ከተሞችና አካባቢዎችን፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን በተለይም ወሊሶ፤ በጅማ ዞን በጅማ ከተማ የደረሱትን የዘር ጥቃቶች ያካትታል።

    በጥቃቱ ከወደመው ሀብትና ንብረት መካከል 378 መኖሪያ ቤቶች፣ 111 ከብቶችና በርካታ የእርሻ ማሳዎች፣ የእህልና የሸቀጣሸቀጥ ክምችቶች፤ ከ300 በላይ ከአነስተኛ እስከ ከፍተኛ የንግድ ድርጅቶችና ህንፃዎች፣ 189 ሆቴሎችና ፔንሲዮኖች፣ 5 ትምህርት ቤቶች፣ 15 መድሃኒት ቤቶችና የህክምና ተቋማት፣ 8 ባንኮችና የኢንሹራንስ ተቋማት፣ 117 የተለያዩ ተሸከርካሪዎች ተዘርፈዋል፤ ተሰባብረዋል፤ በእሳት ተቃጥለዋል። አብያተ ክርስቲያናት፣ የእምነት መገልገያዎችና ታሪካዊ ቅርሶች ሳይቀር የጥቃቱ ሰለባ ሆነዋል። በተፈፀመው እጅግ ከፍተኛ ጥቃት በብዙ ቢሊዮን ብር የሚገመት ሀብትና ንብረት ወድሟል።

    አብን በተጨባጭ መረጃና ማስረጃ ባጠናቀረው ዘገባ ግኝት መሠረት ከሰኔ 22 ለሊት እስከ ሰኔ 25 ቀን 2012 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል የተፈፀመው ጥቃት ዓለምአቀፍ የዘር ማጥፋት መስፈርቶችን የሚያሟላና የማያሻማ የዘር ማጥፋት ድርጊት መሆኑን ያምናል።

    ጥቃቱ በዘርና በእምነት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ‹‹ነፍጠኛ›› እና ‹‹የነፍጠኛ ኃይማኖት›› በሚል የዘር ፍጅት መለያ በዋነኝነት በተጠቀሱት ዞኖች የሚኖሩትን በሚሊዮን የሚቆጠሩ አማሮችን ዒላማ ያደረገ ነው። ሙስሊም አማሮችም የጥቃቱ ሰለባ ሆነዋል። የኦርቶዶክስ ኃይማኖት ተከታይ ኦሮሞዎችና ሌሎችም ኢትዮጵያውያን ለጥቃት ተዳርገዋል።

    በዚህ የዘር ማጥፋት ጥቃት ከ200 በላይ አማሮች በአሰቃቂ ሁኔታ በሜንጫ፣ በዱላና በድንጋይ እየተጨፈጨፉ ሕይወታቸው አልፏል።

    በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የጥቃቱ ሰለባዎች ከቀላል እስከ ፅኑ አካላዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል። በጥቂቱ ከ20 ሺህ የሚበልጡ ወገኖችም አስቸኳይ የእለት እርዳታ ፈላጊ ሆነው ሜዳ ላይ ተጥለዋል።

    የአማሮች ሀብትና ንብረቶች እየተመረጡ በመውደማቸው ጥቃቱ በተፈፀመባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ሆን ተብሎ የህይወት ዋስትና እንዲያጡ ተደርገዋል። ችግሩ በነዚህ አካባቢዎች ብቻ የሚወሰን ሳይሆን በመላው ኦሮሚያ የሚኖሩ ወደ 15 ሚሊዮን የሚጠጉ አማሮችና ኦርቶዶክስ አማኞችን ለከፍተኛ የህልውና ስጋትና ሥነ-ልቡናዊ ጉዳት ዳርጓቸዋል።

    ለ. የጥፋቱ ተዋንያን፦

    በሁሉም አካባቢዎች ጥቃቱን በተቀናጀ ሁኔታ በመምራት፣ በማስተባበርና በመፈፀም በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል። በተለይ በኦሮሞ ፅንፈኛ የፖለቲካ ቡድኖች፣ ድርጅቶችና ታዋቂ ግለሰቦች ሳይቀር ‹‹ቄሮ›› በሚል ስም የተደራጁ ወጣቶች ዋነኛ የጥቃት ኃይሎች ነበሩ።

    እነዚህ ቡድኖች ከአንዱ ከተማ ወደ ሌላው አቅራቢያ ከተማ ወይም ከገጠር ቀበሌዎች ወደ ከተማ እየተሰማሩ የሚያጠቁ ፣ በከተማው የሚገኙ ዒላማ የተደረጉ ሰዎችን ቤቶችና ንብረቶችን ዝርዝር የያዙ ጠቋሚዎች በቅንጅት የሚሰሩበት ነው። ለንብረቶች ማቃጠያ ቤንዚንና መሰል ግብአቶችንም የሚያቀርቡ ነበሩበት።

    በተለያዩ ደረጃ ያሉ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የክልሉ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችና አባላት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በጥቃቱ ከመሳተፋቸውም በላይ ጭፍጨፋውን ለማስቆም ፍላጎት አጥተው ቆመው መመልከታቸውንም ከፍጅቱ የተረፉ እማኞች አስረድተዋል። የፌዴራል መከላከያ ሰራዊት አመራሮችም እንደ ሻሸመኔና አርሲ ነገሌ ባሉ አካባቢዎች ለቀረበላቸው የድረሱልን ጥያቄ ‹‹ከበላይ ትዕዛዝ አልተሰጠንም›› በሚል ለእርዳታ አልተገኙም።

    የዘር ፍጅቱን ተከትሎ የኦሮሚያ ክልልም ሆነ የፌዴራሉ መንግሥት ወንጀሉን በስሙ በመጥራት ወንጀለኞችን ለሕግ ከማቅረብ ይልቅ ድርጊቱን ተራ ግጭት በማስመል ወደ ማስተባበል ገብተዋል። ከዘር ፍጅቱ የተረፉ ተጠቂ ወገኖችንም በተገቢው ሁኔታ በማቋቋም ረገድ ዳተኝነት ይስተዋላል።

    1.2. የአብን አቋም፦

    በአጠቃላይ አብን በጥናቱ ባረጋገጠው መሠረት በኦሮሚያ ክልል የተደረገው የዘር ማጥፋት ተገቢውን ትኩረት ያለማግኘቱና ችግሩን በአጭር ጊዜም ይሁን በዘለቄታ ለመፍታት የሚታየው ዳተኝነት ፓርቲያችንን ክፉኛ ያሳስበዋል። ስለሆነም፦

    ሀ) የተፈፀመው ወንጀል የዘር ማጥፋት መሆኑ ታምኖበት በስሙ እንዲጠራና ለተፈፀመው ወንጀልም ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠየቅ፤

    ለ) መንግሥት የተፈፀመውን የዘር ፍጅት የሚያጣራና የሚመረምር ልዩ የምርመራ ኮሚሽንና አቃቤ ሕግ ጽ/ቤት እንዲያቋቁምና ወንጀለኞች የሚዳኙበት ልዩ ችሎት እንዲሰይም፤

    ሐ) መንግሥት በንፁሃን ዜጎች ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ወንጀል የሚዘክር ቋሚ መታሰቢያ እንዲያቆም፤

    መ) ችግሩን በዘለቄታ ለመፍታት በክልሉ በሚኖሩ የተለያዩ ማህበረሰቦችና ሕዝቦች መካከል የእርቅና የመግባባት ስራዎች እንዲጀመሩ ፤

    ሠ) የኦሮሚያ ክልልም በክልሉ ለሚኖሩ ኦሮሞ ያልሆኑ ማህበረሰቦችና ሕዝቦች ሰብአዊና ህገ መንግሥታዊ መብቶቻቸው የሚከበሩበት ዋስትና እንዲሰጥ ፤

    ረ) መንግሥት የዘር ፍጅቱን በመዘገባቸው ምክንያት ያሰራቸውን የአስራት ሚዲያ ጋዜጠኞች ያለምንም ቅድመሁኔታ በአስቸኳይ እንዲለቅ አብን ይጠይቃል።

    2. በአዲስ አበባ የሚፈፀሙ ወንጀሎችና ብክነቶችን በተመለከተ፦

    ፓርቲያችን አብን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና በፌዴራል መንግሥቱ በከተማዋ ውስጥ የሚፈፅሙትን ወንጀሎች ፣ ሙስናና ብክነቶች የሚመረምር ቡድን በማቋቋም ሰፊ ጥናት እያካሄደ ይገኛል። ከዚህ ጥናት የተገኘ መረጃን መሠረት በማድረግ በከተማዋ ከፍተኛ ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራ፣ ተቋማትን በአንድ ብሔር ተወላጆች የመሙላት፣ ሕገ-ወጥ የመታወቂያ እደላና በርካታ ተያያዥ ወንጀሎች እንደተፈፀሙ አረጋግጧል። ይህም በተለይ ከሰኔ 2011 ወዲህ እጅግ የተባባሰ እንደነበር ተገንዝቧል።

    2.1. ሕገ-ወጥ ወረራ፣ ሰፈራና ማፈናቀል

    የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በአንጡራ ሃብታቸው ያቆሙት ጎጇቸውና ድርጅቶቻቸው ያለርህራሄና ያለሕግ አግባብ የሚፈርሱባትና ዜጎች ሜዳ ላይ የሚወረወሩበት፤ ከፊሎች ደግሞ በዘር፣ በፖለቲካ ወገንተኝነትና በጥቅም ትስስር በገፍ መሬት የሚቸራቸው፤ የከተማዋ ነዋሪ ከእለት ጉርሱ ቀንሶ የገነባው የጋራ መኖሪያ ቤት በልዩ መብት የሚታደላቸው ከተማ ሆናለች።

    አብን በከተማዋ የሚፈፅሙትን ሕገወጥነቶች ከማውገዝና በተለያዩ መድረኮችና መገናኛ ብዙሃን አማካኝነት ከማጋለጥ ባሻገር አቅም በፈቀደ መጠን የሰብአዊ ርዳታዎችን በማቅረብ ኢትዮጵያውያን ወገኖችን ለመታደግ ጥረት አድርጓል። መላው ሕዝባችን በተለይም ለሕዝብና ለሀገር ጥቅሞች ፣ መብቶችና ፍላጎቶች ቆመናል የሚሉ የፖለቲካ ኃይሎች ከንቅናቄያችን ሀገርን የማዳን ታሪካዊ ጥሪ ጎን እንዲቆሙ ወትውተናል።

    ከዚህም ባለፈ ንቅናቄያችን ጉዳዩን ትኩረት ሰጥቶ በማጥናት ለሀገሪቱ ከፍተኛ የመንግሥት አካላት በተደጋጋሚ አቤት ብሏል። ታህሳስ 2 ቀን 2011 ዓ.ም በብሔራዊ ቤተመንግሥት በመገኘት ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ጋር እስከመወያየት ደርሷል። በወቅቱም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ችግሮች መኖራቸውን በማመን አስቸኳይ መፍትሔ እንደሚበጅላቸው ቃል ቢገቡም አንዳችም ሳይደረግ አሁን ካለንበት ሁኔታ ላይ ተደርሷል።

    ሰለዚህም የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ይህ እጅግ አሳሳቢ ጉዳይ በአስቸኳይ መፍትሄ ካላገኘ ፅኑ ብሔራዊ ቀውስ የሚፈጥር በመሆኑ፦

    ሀ) አዲስ አበባ ላይ የተፈፀመውን ሁሉንአቀፍ ወረራ በተመለከተ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ ሌሎች የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት ያካተተ አንድ አጣሪ ኮሚቴ እንዲቋቋም፤

    ለ) ባለፉት ሁለት ዓመታት የነበረውን የመሬት አስተዳደርና ማስተላለፍ፣ የመታወቂያ አወጣጥ፣ የቅጥርና ዝውውር እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን እንዲያጣራ/ኦዲት እንዲደረግ፤

    ሐ) በኦዲት ግኝቱ በሚመጣው መሠረት ጥፋተኛ ሆነው የሚገኙ ሁሉም አካላት ለፍትህ እንዲቀርቡ፤

    መ) በኦዲት ግኝቱ ለተለዩ ጉድለቶች አጣሪ ኮሚቴው በሚያቀርበው ምክረ ሐሳብ መሠረት የማስተካከያ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ፤ እንዲሁም

    ሠ) ምርጫ ተካሂዶ ቅቡልነት ያለው ሕጋዊ የከተማ አስተዳደር ምክርቤትና ካቢኔ እስኪዋቀር ድረስ አሁን ያለው የሽግግር አስተዳደር ዘላቂ ውጤት ሊኖራቸው ከሚችሉ ውሳኔዎች እንዲታቀብ፤ አብን ጥሪውን ያቀርባል።

    2.2. ሜጋ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ፦

    ፓርቲያችን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ በጠቅላይ ሚኒስቴር ፅ/ቤትና በከተማ አስተዳደሩም በኩል የሚሰሩ ዋና ዋና 15 ሜጋ ፕሮጀክቶችን ሁኔታ በንቃት በመከታተል ስለፕሮጀክቶቹ ዝርዝር መረጃዎችን ሲያሰባስብ ቆይቷል።

    በዚህም መሠረት በጀታቸው/ወጪያቸው የታወቁ ፕሮጀክቶች የገንዘብ መጠን በአጠቃላይ 5.737 ቢሊዮን ዶላር (ወቅታዊ ምንዛሪው ከ212 ቢሊዮን ብር በላይ) እና ተጨማሪ 59.2 ቢሊዮን ብር በአንድ ላይ ወደ 271 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ እንደሆነ ተረድቷል። በጀታቸው ካልታወቁ ጋር ሲደመር ከዚህ ከፍተኛ መሆኑ አያጠራጥርም።

    አዲስ አበባ ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ ከተማ እንድትሆን የሚደረገውን መንግሥታዊ እንቅስቃሴ በመርኅ ደረጃ አብን ይደግፋል።

    ይሁንና የሜጋ ፕሮጀክቶቹ እጅግ የተጋነነ ወጭ የሚወጡባቸው በመሆናቸው (White Elephant Projects)፤ ይኸው ከፍተኛ በጀት ሀገራችን በብድርና እርዳታ የምታገኘው በመሆኑ፤ አንዳንዶቹ ፕሮጀክቶች ሀገራችን አሁን ካለችበት ሁኔታ አንፃር የቅደም ተከተል ችግር ያለባቸው መሆናቸው ፤ ከአዋጭነት፣ ባለድርሻዎችን ከማሳተፍ፣ ከዲዛይንና ግንባታ አካሄድ፣ ከብክነትና ሙስናን ከማስቀረት፣ በግልጽ ጨረታ የግንባታ ኮንትራክተሮችን ከመለየት እንዲሁም በየጊዜው ስለፕሮጀክቶቹ ለሕዝብ ግልጽ መረጃ ከመስጠት አንፃር ክፍተቶች ያሉባቸው መሆናቸውን አብን ያምናል።

    መንግሥት ይህን ያህል ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ግልጽነት ባልተሞላበትና የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን አንገብጋቢ ጉዳዮች ባላስቀመጠ መልኩ ማዋሉ ፓርቲያችንን ክፉኛ ያሳስበዋል። ስለሆነም፦

    ሀ) መንግሥት ስለፕሮጀክቶቹ ለሕዝብ ግልፅ ማብራሪያ እንዲሰጥ፤

    ለ) በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት የሀገራችን ኢኮኖሚ ክፉኛ እየተደቆሰ በመሆኑ ቀውሱ ሀገርን ለከፋ አደጋ የሚዳርግ ማኅበራዊ ቀውስ ከማደጉ በፊት አስፈላጊ የኢኮኖሚ ድጋፍ ማእቀፎችን ቀርፆ ወደ ሥራ እንዲገባ፤

    ሐ) የተጋነኑና አንገብጋቢ ያልሆኑ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማጠፍ በጀቱን የነፍስ አድን ርዳታ ለሚፈልጉ ወደ 18 ሚሊዮን ዜጎች ድጋፍ እንዲያውለው፤

    መ) በሀገራችን ያለው የሥራ አጥነት በአስከፊ ሁኔታ ላይ መገኘቱን በማጤን መንግሥት ጊዜውንና አቅሙን ለወጣቶች ሥራ እድል ፈጠራና ለኢኮኖሚ ሽግግር እንዲያውል አብን ጥሪውን ያቀርባል።

    3. ብሔራዊ ውይይትና መግባባትን በተመለከተ፦

    አብን የሀገራችን የፖለቲካ ቀውስ በምርጫ ብቻ እልባት ያገኛል የሚል አቋም የለውም። ስለዚህም ከምርጫ በፊት እንደ ሀገር መደማመጥ፣ መከባበርና መተማመን እንዲቻልና አሁን የተፈጠረው የሽግግር ጊዜም እንዳለፉት ዘመናት እድሎች እንዳይከሽፍ ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ የሰለጠነ ውይይት፣ ምክክርና ድርድር እንዲዘጋጅ፤ ለዚህም ግልጽ ማእቀፍ እንዲኖርና ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያሳተፈ የብሔራዊ ውይይት መድረክ እንዲከፈት ወትውቷል።

    መንግሥት ለእውነተኛ የፖለቲካ ድርድርና ብሄራዊ መግባባት ዳተኝነት በማሳየቱ ምክንያት ፅንፈኛ ኃይሎች ሀገር አፍራሽ ድርጊታቸውን በማናለብኝነት እንዲቀጥሉ እድል ሰጥቷቸዋል። በዚህ ረገድ ትሕነግ የሚዘጋጅበት ሕገ-ወጥ ምርጫ በወረራ በተያዙ የአማራ መሬቶች በወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምትና ራያ የሚኖረው ሕዝባችን ላይ የሚያደርሰውን ፅኑ አፈናና ግፍ መንግሥት እንዲያስቆም በተደጋጋሚ ጥሪ አቅርበናል።

    የፌዴሬሽን ም/ቤት ዘግይቶም ቢሆን የወሰነውን ውሳኔ የፌዴራል መንግሥቱ በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲያደርግና ትህነግ በህገወጥ ምርጫ በወልቃይትና ራያ ሕዝባችን ላይ የሚያደርሰውን ሰብአዊ ቀውስ እንዲያስቆም የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ጥሪ ያቀርባል።

    በተጨማሪም ፡-

    ሀ) ሀገርን ወደ ዴሞክራሲ ለማሻገር ሁሉም ባለድርሻ አካላት የማይተካ ሚና እንዳላቸው በማመን መላው የፖለቲካ ኃይሎች የሀገራችን አደገኛ ወቅታዊ ሁኔታ ባጤነ መልኩ በኃላፊነት እንዲንቀሳቀሱ፤

    ለ) መንግሥት በውል የታወቀና የታቀደ ሁሉንአቀፍ ብሔራዊ ውይይት፣ ምክክርና ድርድር የማስተባበርና የማመቻቸት ኃላፊነቱን እንዲወጣ፤

    ሐ) ሁሉም ዜጎች በተለይም ሲቪክ አደረጃጀቶች፣ የሚዲያ ተቋማት፣ ምኁራን፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ወጣቶችና ሴቶች እንዲሁም ባለሀብቶች ለሚደረገው ብሔራዊ ውይይት፣ ምክክርና ድርድር ውጤታማነት የየድርሻቸውን አስተዋፅኦ እንዲኖራቸው፤

    መ) የዓለምአቀፍ ማኅበረሰቡ የሁሉንአቀፍ ብሔራዊ ውይይት፣ ምክክርና ድርድር ሂደት እንዲደግፍና መንግሥት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲወጣም ጫና እንዲፈጥር የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ታሪካዊ ጥሪውን ያስተላልፋል።

    “አንድ አማራ ለሁሉም አማራ ፤ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ!›”
    የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)
    አዲስ አበባ፣ ሸዋ፤ ኢትዮጵያ!
    ጳጉሜ 2 ቀን 2012 ዓ.ም

    የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)

    Anonymous
    Inactive

    የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር የሚያስችሉ ሁኔታዎችን እያጤነ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ

    አዲአ አበባ (ትምህርት ሚኒስቴር) – የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሚሊዮን ማቴዎስ የ2013 ዓ.ም የትምህርት ሂደትን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ከትምህርት ቤቶች አከፋፈት ጋር ተያይዞ ባሉ ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።

    የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በኢትዮጵያ መከሰቱን ተከትሎ ከ42,000 በላይ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ይማሩ የነበሩ ከ26 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ ሆነዋል።

    የ2013 ዓመት ትምህርትን ለመጀመር የሚስችሉ ሁኔታዎችን ለመቃኘት የጥናት ቡደን ተቋቁሞ ጥናት እያደረገ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል። በጥናቱ መሠረት ትምህርት ቤቶች በአንድ ክፍል ውስጥ ከ20 እስከ 25 ተማሪዎችን ለማስተማር የሚያስችል አቅም ስለመኖርና አለመኖራቸው ልየታ እየተካሄደ መሆኑንም ጠቁመዋል።

    የተማሪዎችን ርቀት ለማስጠበቅ በአንድ ወንበር አንድ ተማሪ እንዲቀመጥ የሚደረግ ሲሆን በፈረቃ ትምህርት መስጠት፣ ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች መገንባት፣ የማኅበረሰብ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን ለማስተማሪያነት መጠቀም እንደ አማራጭ ጥቅም ላይ እንደሚውሉ ተገልጿል። ይህንን ታሳቢ በማድረግ አንዳንድ ክልሎች አስቀድመው ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን የገነቡ ቢሆንም፥ ሁሉም ክልሎች በየትምህርት ቤቱ ተጨማሪ ክፍሎችን እንዲገነቡ እየተደረገ ነው።

    በትምህርት ቤቶች ውስጥ በቂ የንጽህና ወሃ እንዲኖር ማድረግ፣ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘርና ማስክ የማቅረብ ሥራዎችም እንደሚሠሩ በተሰጠው መግለጫ ላይ ተነስቷል።

    የኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭት ያለበት ሁኔታ እየተገመገመ ደረጃ በደረጃ ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት የሚያስችሉ ሁኔታዎች እየተጤኑ ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ሚሊዮን ማቴዎስ ለስኬቱ ወላጆችና ባለድርሻ አካላት ከመንግሥት ጎን እንዲቆሙ ጠይቀዋል።

    ከኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ዜና ሳንወጣ፥ ሚኒስቴሩ በቀጣይ ተማሪዎች በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፁ ሆነው እንዲወጡ በትኩረት እንደሚሠራ በ10 ዓመቱ ዕቅድ ውይይት ላይ አስታውቋል።

    በውይይቱ ወጣቶች አሁን እየታዩ ባሉ አላስፈላጊ ድርጊቶች እና እንቅስቃሴዎች ውስጥ ገብተው መገኘታው በተማሪዎች የሥነ-ምግባር ግንባታ ላይ በትኩረት ያለመሥራት አንዱ ምክንያት መሆኑ ተነስቷል።

    በዕቅዱ ውስጥ ተማሪዎች ከመማር ማስተማር ባሻገር በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፁ ብቁ ዜጋ ሆነው እንዲወጡ ለማድረግ የሚያስችሉ አሠራሮች እንደሚዘረጋ ተጠቁሟል።

    ሀገራቸውን የሚወዱ፣ ብዝሃነትን የሚያስተናግዱ፣ ለወንድማማችነት ትኩረት የሚሰጡ በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፁ ብቁና ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ ለማድረግ የሚያስችሉ አሠራሮች በ10 ዓመቱ ዕቅድ ውስጥ ተካትተዋል።

    ለማኅበረሰቡ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የሚሰጡ፣ የትምህርት ቤቶችን ሕግና ደንብ የሚያከብሩ፣ በበጎ ምግባራቸው ማኅበረሰቡ የሚረከባቸው ተማሪዎችን መፍጠር በ10 ዓመቱ ዕቅድ ውስጥ በትኩረት ይሠራባቸዋል ተብሏል።

    ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ትምህርት ሚኒስቴር

    Anonymous
    Inactive

    ዛሬ በይቅርታ ላይ ስናፌዝ ዋልን!
    በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር)

    የሀገሬ ሰዎች ለይቅርታ (ይቅርታ ለመጠየቅም፣ ይቅርታ ለማድረግም) ንፉግ ናቸው። “ሳላውቅ ያስቀየምኳቸሁ፣…” ብሎ ይቅርታ መጠየቅ። መጀመሪያ እስቲ አውቀን የበደልናቸውን ይቅርታ እንጠይቅ። አውቄ የበደልኩት የለም ለማለት ነው? በየአንዳንዳችን ልብ የበደል ቁልል አለ፤ ያንን ለመናድ መድፈር ነው ይቅርታ። የበደልከውን ሰው፥ “ይህን ስላደረግኩህ ይቅር በለኝ” ብለህ መጋፈጥ። በደለኛነትን ሸሽጎ በይቅርታ መንጻት አይቻልም።

    ይቅርታ በጅምላ አይሆንም። መሪዎች የገደሉትን፣ ያሰሩትን፣ ያፈረሱበትን፣ የወረሱትን፣… ወዘተ በስም እየጠሩ ይቅርታ መጠየቅ አለባቸው – እውን ይቅርታ ከፈለጉ። ጎንደር ላይ ወጣት ሲረሽን የነበረ፣ ተነስቶ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ የሚጠይቅበት ምክንያት የለም፤ የገደለውን ያስገደለውን በስም እየጠራ፣ የሟች ቤተሰቦች ነው ይቅርታ መጠየቅ ያለበት። ደቡብ አፍሪካ ከአፓርታይድ ስትላቀቅ የተደረገው ይኸውም ነው። በሀገር ላይ የተሠራ በደል ካለ (ለምሳሌ ኢትዮጵያን የባህር በር እንደማሳጣት ዓይነት) ሕዝብ ይቅርታ ይጠየቃል። አንድ ተማሪ የበደለ መምህር ክፍል ገብቶ “ያስቀየምኳችሁ ይቅርታ” ሲል፥ ‘ፐ! ይቅርታ ጠየቀ’ ይባልለታል። በፍጹም፤ ይቅርታ አልጠየቀም!! ስሙን ጠርቶ፣ የበደለውን ገልጾ ነው ይቅርታ መጠየቅ ያለበት።

    ይቅርታ መጠየቅ ነው ወይንስ ማግኘት ቁም ነገሩ? እንዴ ይቅርታችንን ተበዳይ መቀበል አለመቀበሉን ማወቅ የለብንም? ካለብን ከበደልነው ጋር መጋፈጥ የግድ ነው። የጎረቤቴ ልጅ በተገደለ፣ በታሰረ እናት አባቱ እንጂ እኔን ማን ይቅርታ አድራጊ አደረገኝ?

    ደግሞ አንዳንዱ ይገርማል፤ እራሱን ከኢየሱስ መስቀል ላይ ሰቅሎ መሀሪ ይቅር ባይ መሆን ያምረዋል፤ ይቅርታ እኮ ዝቅ ማለት ነው። “ሳላውቅ በድያችኋለሁ፥ ይቅርታ አድርጉልኝ፤ እናንተ ግን አውቃችሁ በድላችሁኛል፥ ይሁንና ይቅር ብያችኋለሁ” ሲባል እኔ ንጹህ፣ እናንተ ኃጢአኞች ማለት እኮ ነው። እስቲ የሚከተለውን ይቅርታ እንመልከት።

    “… እስከዛሬዋ ቀን ድረስ ባለማወቅ ለበደልኩት ለማንኛውም በደል ይቅርታን በትህትና እጠይቃለሁ። እኔንም ለበደሉኝ፣ ያለበደሌ ለከሰሱኝ፣ ያለተግባሬ መጥፎን ስም ሰጥተው ላሳጡኝ፤ ሕዝብን ለማገልገል በምተጋበት ወቅት አላስፈላጊ ጦርነትን በመክፈት ሲያደክሙኝና አላሠራ ሲሉኝ ለነበሩት ሁሉ ከልብ የሆነ ይቅርታን አድርጊያለሁ።

    አሁን እዚህ ውስጥ ምን የይቅርታ መንፈስ አለ? ይቅርታ ጠያቂው፣ አውቆ የበደለው አንድም ነገር የለም። እሱ ላይ የተደረገውን በደል ግን ሆን ተብሎ፣ ታቅዶ እንደተደረገ በዝርዝር ተቀምጧል። ምናለ የእነሱንም፥ ‹‹ሳታውቁ ለበደላችሁኝ›› ብሎ ቢያልፈው? ወይ የእሱንም (እሱ የበደለውንም፣ ያጠፋውንም) ቢዘረዝረው?

    እና እባካችን ያልደረስንበትን እንተወው፤ ቢያንስ ጽንሰ-ሀሳቡ ለልጆቻችን ይቀመጥ፤ እነሱ ይደርሱበት ይሆናል፤ የልጅ ልጆቻቸውም ቢሆኑ።

    በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር)*

    * በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር) ደራሲና ገጣሚ ሲሆኑ፥ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የሂዩማኒቲስ፤ የቋንቋዎች ጥናት የጆርናሊዝምና የኮሚኒኬሽን ኮሌጅ ውስጥ ደግሞ መምህር ናቸው። ከዚህ ቀደም ለህትመት ከበቁላቸው ሥራዎች ውስጥ የማይፃፍ ገድል፣ የራስ ምስል፣ ያልተከፈለ ስለት፣ የወይራ ስር ጸሎት፣ የማይጻፍ ገድል፣ የተስፋ ክትባት፣ እና ፍካት ናፋቂዎች የጠቀሳሉ። በተጨማሪም በብሔራዊ ቲያትር ቀርቦ በተመልካች ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነትን ያገኘው “ደብተራው” የተሰኘው የሁለት ገጸባሕርያት ቲያትር (two-handler theater) ደራሲ ናቸው። በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ሊያገኟቸው ይችላሉ።

    ** ሰሞነኛ ኢትዮጵያ፦ በሰሞነኛ ድረገጽ የአማርኛ ፎረም (semonegna.com/forums) ላይ የሚገኝ ማንኛውም ጽሑፍ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንጸባርቅ ሲሆን፥ ጽሑፉ የሰሞነኛ ኢትዮጵያንንም ሆነ የተሳታፊዎችን አመለካከትና ምልከታ ላይወክል ይችላል።

    በድሉ ዋቅጅራ

    Anonymous
    Inactive

    8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት ስምንት ግለሰቦችንና ተቋማትን የዓመቱ በጎ በማለት ሸልሟቸዋል

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በልዩ ሁኔታና መስፈርት ጳጉሜን 1 ቀን 2012 ዓ.ም በኢንተርኮንቲነንታል አዲስ ሆቴል የተከናወነው 8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት ስምንት የተለያዩ ግለሰቦችን፣ ድርጅቶችንና ማኅበራትን በጎ ተሸላሚዎች በማለት ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።

    የዘንድሮውን የስምንተኛውን ዙር የበጎ ሰው ሽልማት እንደቀደሙት ዓመታት ሁሉ በተለመዱት በአስሩ ዘርፎች እና በተለየ ድምቀት እንዳይካሄድ በዓለምአቀፍ ደረጃ የተከሰተው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ (ኮቪድ-19) የሽልማቱ አዘጋጆችን እንደገታቸው ጋዜጠኛና የሥራ አመራ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ወ/ሮ ሕሊና አዘዘ በመግቢያ ንግግሯ ላይ ገልጻለች።

    የዚህን ዓመት ሽልማት ለማከናወን ከየካቲት 1 እስከ መጋቢት 15 ቀን 2012 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ከ200 በላይ የዕጩዎች ጥቆማ ከሕዝብ መቀበላቸውን እና የሽልማት ድርጅቱ የሥራ አመራር ቦርድ የዕጩዎቹን ታሪካቸውንና አብርክቷቸውን በማጥናት ላይ እያለ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በመከሰቱ ምክንያት የተሟላ ዝግጅት ሊያደርጉ አለመቻላቸውን ጋዜጠኛ ሕሊና ጠቅሳለች።

    የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢ.ፌ.ዲ.ሪ) ፕሬዝደንት ክብርት ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ ካርዲናል ብርሃነኢየሱስ፣ እንዲሁም የበጎ ሰው ሽልማት የበጎ አድራጎት ድርጅት መሥራችና የቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የአግዮስ መጻሕፍት ሥራ አስኪያጅ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት ተገኘተዋል።

    የ8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚዎች የሚከተሉት ናቸው፡-

    1. አቶ ካሊድ ናስር

    የመጀመሪያ ልዩ ተሸላሚ ባለፉት አምስት ወራት በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት የገዛ መኖሪያ ግቢያቸውን ሳይቀር በመስጠት፣ መጠለያ የሌላቸውን (የጎዳና ተዳዳሪዎችን) በመደገፍ የበጎ አድራጎት ሥራ የሠሩት አቶ ካሊድ ናስር ናቸው።

    1. አቶ ኪሮስ አስፋው

    አቶ ኪሮስ አስፋው ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ያለማቋረጥ መቶ ጊዜ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቦንድ የገዙ እና በደም መፍሰስ የሚሞቱ እናቶችን ለመታደግ ለ21 ጊዜ ደም የለገሱ ግለሰብ ናቸው።

    1. አቶ ብንያም ከበደ

    የኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቪዥን መሥራች ጋዜጠኛ ብንያም ከበደ የ8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት 3ኛ ልዩ ተሸላሚ ሆኗል። ጋዜጠኛ ብንያም ከበደ በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት ልጆች በየቤታቸው ሲሆኑ የሚመለከቱት የሚመጥናቸውና በተለያየ ቋንቋ መሰናዶዎች የሚቀርብበት የኢትዮጵያ ልጆች ቴሌቭዥንን ከመክፈት ጀምሮ ያደረጉት አስተዋጽዖም የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚ አድርጓቸዋል።

    1. ጋዜጠኛ መሀመድ አል-አሩሲ (محمد العروسي / Mohammed Al-Arousi)

    በአረብኛ ቋንቋ የኢትዮጵያን ሀሳብና እውነት (በተለይም በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ) በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ሲያስረዳና ሲከራከር የቆየው አቶ መሐመድ አል-አሩሲ (محمد العروسي / Mohammed Al-Arousi) የዘንድሮ የበጎ ሰው ልዩ ተሸላሚ ሆኗል። ከኢትዮጵያዊ ቤተሰቦች በሳዑዲ አረቢያ የተወለደው መሐመድ አል አሩሲ፥ የሕዳሴ ግድብን በሚመለከት ስለኢትዮጵያ በተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ሙግት በማድረግ ይታወቃል።

    1. ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ

    በሕዳሴ ግድብ ላይ እንዲሁም በአባይ ወንዝ ላይ ኢትዮጵያ ባላት የልማት ተጠቃሚነት ዙሪያ የተለያዩ ጥናቶችን ያደረጉትና በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ስለሕዳሴ ግድብ ተግተው በመሞገት የሚታወቁት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ የዘንድሮው የበጎ ሰው ተሸላሚ ሆነዋል።

    1. ኢትዮ ቴሌኮም

    ኢትዮ-ቴሌኮም በዓመቱ ውስጥ በተለይ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል መልዕክት በማስተላለፍ፣ ማዕድ በማጋራት፣ እንዲሁም የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል በሠራቸው የበጎ አድራጎት ሥራዎቹ የ2012 ዓ.ም የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚ ሆኗል። ድርጅቱን በመወከል የተገኙት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ወ/ት ፍሬሕይወት ታምሩ ሽልማቱን ተረክበዋል።

    1. የሕክምና ባለሙያዎችና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች

    የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በሀገራችን ከተከሰተ ጀምሮ ራሳቸውን አደጋ ላይ ጥለው የዜጎችን ደኅንነት ለመጠበቅ ከፊት የተሰለፉ የጤና ባለሞያዎችና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች የ2012 ዓ.ም የዓመቱ የበጎ ሰው ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል። የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በመድረኩ የጤና ባለሞያዎችንና የድጋፍ ሰጪ ሠራተኞችን በመወከልም ሽልማቱን ተቀብለዋል።

    1. የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሠራተኞች በሙሉ

    የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጸጥታውን የሚቆጣጠሩ የመከላከያ ሠራዊት እና የፌዴራል ፓሊስ አባላት፣ እንዲሁም የሕዳሴው ግድብ የመሠረት ድንጋይ ከተጣለበት ከመጋቢት 24 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ በጉባ በሥራ ላይ የሚገኙ የግድቡ ሠራተኞች የ2012 ዓ.ም የበጎ ሰው ሽልማት ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል። በጉባ የሚገኙ ሠራተኞችን ወክለው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሥራ አስኪያጅ ኢ/ር ክፍሌ ሆሮ ሽልማቱን ተረክበዋል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    8ኛው የበጎ ሰው ሽልማት

    Semonegna
    Keymaster

    ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ እና አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በአጠቃላይ ከ3 ሺህ በላይ ተማሪዎችን አስመረቁ

    ዲላ/አርባ ምንጭ (ኢዜአ/አ.ም.ዩ) – ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መረሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 1,043 ተማሪዎችን ነሐሴ 30 ቀን 2012 ዓ.ም. አስመረቀ።

    በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጫላ ዋታ እንደገለጹት ከተመራቂዎቹ መካከል 283 በመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው። ቀሪዎቹ በምስክር ወረቀት የተመረቁ መሆኑን አስረድተዋል።

    ተመራቂዎቹ ትምህርታቸውን በበይነ መረብ ቴክኖሎጂ አማካኝነት ሲከታተሉ እንደቆዩ አመልክተው፥ በተለይ የሁለተኛ ዲግሪ ተመራቂዎች የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከመከሰቱ በፊት የክፍል ትምህርታቸውን ማጠናቀቃቸውን አስታውቀዋል።

    ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው በተጓዳኝ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን መከላከልን ጨምሮ በተለያዩ የማኅበረሰብ አገልግሎቶች ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ዶ/ር ጫላ ገልጸዋል።

    የዩኒቨርሲቲው የቦርድ አባል አቶ ኡዴሳ ክዮላ በበኩላቸው፥ ተመራቂዎቹ በቀጣይ በሚሰማሩበተ የሥራ መስክ ሀገርና ሕዝብ የሚጠብቅባቸውን ኃላፊነት በታማኝነትና ታታሪነት እንዲወጡ አሳስበዋል።

    ከተመራቂዎቹ መካከል በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ትምህርቱን የተከታተለው ቅዱስ ይገረሙ በሰጠው አስተያየት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ያሳደረውን ተጽዕኖ ተቋቁሞ ትምህርቱን በማጠናቀቅ ለምረቃ በመብቃቱ መደሰቱን ገልጿል። በሰለጠነበት በ“ሶፍትዌር ዲዛይን” ዘርፍ በመሰማራት እራሱንና ሀገሩን ለመጥቀም እንደሚሠራ ተናግሯል።

    በሁለተኛ ዲግሪ ማኔጅመንት የትምህርት ዘርፍ የተመረቀው ዋቆ ጥላሁን በበኩሉ በትምህርት ቆይታው ያገኘውን እውቀት በመጠቀም ውጤታማ ሥራ ለማከናወን እንደሚጥር ገልጿል።

    የሦስተኛ ትውልድ ዩኒቨርሲቲ የሆነው ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መረሃ ግብሮች የሚያስተምራቸው ከ17 ሺህ በላይ ተማሪዎች እንዳሉት በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ወቅት ተገልጿል።

    ከተማሪዎች ምርቃት ጋር በተያያዘ፥ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ለ33ኛ ጊዜ አስመርቋል።

    ዩኒቨርሲቲው በ2012 ዓ.ም በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር በመደበኛ፣ በክረምት፣ በሳምንት መጨረሻ እና በተከታታይና ርቀት ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 2,326 ተማሪዎች ቅዳሜ ነሐሴ 30/2012 ዓ/ም በተመሳሳይ ዕለት አስመርቋል።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፥ ዩኒቨርሲቲው በስድስት የተለያዩ ካምፓሶች በ76 የመጀመሪያ ዲግሪ፣ በ99 የ2ኛ ዲግሪ እና በ21 የ3ኛ ዲግሪ መርሀግብሮች በአጠቃላይ ከ36 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና መደበኛ ባልሆኑ መርሀግብሮች በማስተማር ላይ ይገኛል። ተቋሙ ባለፉት 33 ዓመታት በልዩ ልዩ የምህንድስና፣ የሕክምናና የጤና፣ የግብርና፣ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ፣ የማኅበራዊ እንዲሁም የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ዘርፎች 56,958 ምሩቃንን በማፍራት ለሀገሪቱ የሰው ሀብት ልማት ጉልህ አስተዋፅዖ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

    አክለውም በ2012 የትምህርት ዘመን በ2ኛው አጋማሽ ላይ በዓለም ላይ በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት በሁሉም ደረጃዎች በመማሪያ ክፍል ሆኖ የመማር ማስተማር ሂደት የተቋረጠ ቢሆንም፥ ዩኒቨርሲቲዎች ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመሆን ባደረጉት ከፍተኛ ጥረት ቴክኖሎጂን በመጠቀም የጥናትና ምርምር ሥራቸውን ሲሠሩ የቆዩ ተማሪዎች አስፈላጊውን የምረቃ መስፈርት በማጠናቀቅ ለምረቃ መብቃታቸውን ተናግረዋል። በቀጣይ ዓመታት በተከፈቱ የ2ኛ እና የ3ኛ ዲግሪ መርሀግብሮች ላይ የማጠናከር ሥራ የሚሠራ ሲሆን፥ ዩኒቨርሲቲው በ2013 የትምህርት ዘመን በዩኒቨርሲቲው ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በ3ኛ ዲግሪ የሚያስመርቅ መሆኑን ባቀረቡት ሪፖርት ጠቁመዋል።

    የዕለቱ የክብር እንግዳ የጋሞ ዞን አስተዳዳሪና የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ እንደተናገሩት፥ የመማር ግቡ ከግለሰብ ህይወት እስከ ሀገር ድረስ ያሉ የተለያዩ ችግሮችን በመፍታት ምቹና ተስማሚ አኗኗርን ለመፍጠር የለውጥና የዕድገት ጎዳናን መከተል ነው። በመሆኑም የዕለቱ ተመራቂዎች ሀገራችን ኢትዮጵያ ወደ ብልፅግና ማማ እንድትደርስ የበኩላችሁን ድርሻ እንድትወጡ ሲሉ አሳስበዋል። በተጨማሪም ወደ ሥራ ዓለም ሲቀላቀሉ በተሰማሩበት መስክ ሁሉ ሀገራቸውንና ሕዝባቸውን በታማኝነት እንዲያገለግሉ ጠይቀዋል። ሀገሪቱ በበርካታ ፈተናዎች ውስጥ እየተሻገረች የምትገኝ እንደመሆኗ መጠን ፈተናዎቹን በብቃት መክተን ወደ መልካም ዕድል መቀየር ይጠበቅብናል ብለዋል።

    በመጨረሻም የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር የቻለ ከበደ እና የሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር በለጠ ይልማ የእጩ ምሩቃን መግለጫ በመስጠት አስመርቀዋል።

    በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ በክብር እንግድነት፣ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እንዲሁም የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እና አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ (አ.ም.ዩ)

    ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ እና አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አስመረቁ

    Semonegna
    Keymaster

    በግማሽ ቢሊዮን ብር የተገነባው ኃይሌ ሪዞርት አዳማ ተመረቀ
    ተቃጥለው የነበሩ የሻሸመኔ እና ዝዋይ የኃይሌ ሪዞርቶችና ሆቴሎች ወደሥራ እንደሚመለሱም ተገለጸ

    አዳማ (አዲስ ዘመን) – በአዳማ ከተማ በ500 ሚሊዮን ብር በሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ “ኃይሌ ሪዞርቶች እና ሆቴሎች” (Haile Resorts & Hotels) ኢንቨስትመንት የተገነባው ዘመናዊው ኃይሌ ሪዞርት አዳማ ተመረቀ።

    ነሐሴ 28 ቀን 2012 ዓ.ም. በተካሄደው የምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ የሆቴሉ ባለቤት ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ እንደገለጸው፥ አዲሱ ኃይሌ ሪዞርት አዳማ በአጠቃላይ 300 ለሚሆኑ ዜጎችና የአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም ባሻገር ከፍተኛ ጥረት ባለው አገልግሎት ሕብረተሰቡን ለማገልገል የቆመ ነው ብሏል።

    ለሀገር ጎብኚዎች በምቹ የቦታ አቀማመጡና ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ መገኘቱ ሆቴሉን ተመራጭ እንደሚያደርገው የጠቆመው ሻለቃ አትሌት ኃይሌ፥ ሪዞርቱ 106 የእንግዳ ማረፊያ ክፍሎች፣ ሁለት ደረጃቸውን የጠበቁ የመመገቢያ አዳራሾች እንዲሁም ባሮችና ሌሎች ደረጃቸውን የጠበቁ የስብሰባ አዳራሾች እንዳሉትም ገልጿል።

    “ኃይሌ ሪዞርቶች እና ሆቴሎች” ድርጅት ፈተናዎች ቢገጥሙትም በምሥራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ ለመሆን ተጨማሪ ሪዞርቶችን ለመክፈት ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን የጠቆመው ሻለቃ ኃይሌ፥ በቅርቡም በአዲስ አበባ፣ በወላይታ ሶዶ፣ በኮንሶ፣ በደብረ ብርሃን፣ በጎርጎራ እና በተቀሩት የኢትዮጵያ ክፍሎች እንዲሁም በምሥራቅ አፍሪካ ሆቴሎችና ሪዞርቶችን ከፍቶ ዓለምአቀፍ ተወዳዳሪ ለመሆን እየሠራ መሆኑንም ተናግሯል።

    በቅርቡ የቃጠሎ ጉዳት የደረሰባቸው የሻሸመኔ እና ዝዋይ የኃይሌ ሪዞርቶችና ሆቴሎች በቅርቡ ወደ ቀደመ ሥራቸው እንደሚመለሱም አትሌት ኃይሌ ተናግሯል። መንግሥት ለሪዞርቶቹ ከለላ ከመስጠት አልፎ ሥራ በማስጀመር ሂደቱ አስፈላጊውን ትብብር እንዲደርግም ጠይቋል።

    ሪዞርቶችና ሆቴሎች ለአንድ ሀገር የቱሪዝም ኢንዱስትሪ የላቀ ድርሻ እንዳላቸው የጠቀሰው ሻለቃ ኃይሌ፥ በእነዚህ መሠረተ ልማቶች ላይ አሉታዊ ክፍተት ሲያጋጥም መንግሥት ኃላፊነት ወስዶ ችግሩን ካልፈታው ኢንቨስትመንቱ ሊጎዳ እንደሚችል ጠቁሟል። ውድመት የደረሰባቸው ሁለቱ ሪዞርቶችና ሆቴሎችም የሕዝብ ገንዘብ በመሆናቸው በአስቸኳይ ወደሥራ እንደሚመለሱ አመላክቷል።

    እንደሻለቃ አትሌት ኃይሌ፥ ገለፃ በተለይ ኃይሌ ሪዞርት ዝዋይ በፍጥነት ወደሥራ እንዲመለስ ጥረት እየተደረገ ሲሆን፤ በእነዚህ ሪዞርቶች እና ሆቴሎች ውስጥ ሲሠሩ የነበሩና በአሁኑ ወቅት ከሥራ ውጪ የሆኑ ሠራተኞችን ወደሥራ ለመመለስ ከመንግሥት እገዛ ይጠበቃልም ብሏል። የሆቴሎቹን መከፈት እውን ለማድረግ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የፌዴራል መንግሥትና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ጋርም እየሠራ መሆኑን ተናግሯል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

    ኃይሌ ሪዞርት አዳማ

    Anonymous
    Inactive

    የገጠር ከተሞችንና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ
    ከ919 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ገለፀ

    የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኤሌክትሪክ ኃይል ባልደረሰባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሀገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት መርሀ ግብርን (National Electrification Program) በመተግበር በስፋት እየሠራ ይገኛል።

    መርሀ ግብሩ እስካሁን ብዛት ያላቸው የገጠር ከተሞችንና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን፤ በቀጣይም ፍትሃዊ ተደራሽነትን ባማከለ መልኩ ሰፊ ሥራዎች እንደሚያከናውን ተገልጷል።

    የሀገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራም ኃላፊ አቶ ሁሴን መሀመድ እንደገለፁት፥ ፅ/ቤቱ ከተመሠረተበት ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ የኤሌክትሪክ ኃይል ባልደረሰባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች ኃይል የማዳረስ ሥራ ሲሠራ መቆየቱንና ከ2010 ዓ.ም እስከ 2012 ዓ.ም መባቻ ድረስ ከ63 ሺህ 900 በላይ አዳዲስ ደንበኞችን ተጠቃሚ ማድረጉን ጠቁመዋል።

    የኤሌክትሪክ ኃይል ባልደረሰባቸው አካባቢዎች ኃይል በማዳረስ የደንበኞች ቁጥር ለመጨመር ቁልፍ ሚና ያለው ይህ መርሀ ግብር፥ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከ6 ሺህ 759 በላይ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ መሆናቸውን ኃላፊው ገልፀዋል። ከ1998 ዓ.ም በፊት ተጠቃሚ የነበሩት የገጠር ከተሞችንና መንደሮችን ብዛት ሲታይ ግን ከ667 የማያላፉ እንደነበሩ አስታውሰዋል።

    ኃላፊው አክለውም፥ ፕሮግራሙ በ2012 ዓ.ም በጀት ዓመት በአዲስና በመልሶ ግንባታ 405 የገጠር ከተሞችና መንደሮች በማገናኘት ከ32 ሺህ በላይ ደንበኞችን ኃይል ለማዳረስ አቅዶ፤ 325 የሚሆኑት የገጠር ከተሞችና መንደሮች በማገናኘት 25 ሺህ 232 አዳዲስ ደንበኞች የኃይል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። ለዚህም ከመንግሥት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ 919 ሚሊዮን 277 ሺህ 349 ብር ወጪ መደረጉን ጠቅሰዋል።

    በተጨማሪም ለዕቃ አቅርቦት ግዥ የሚሆን የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የኃይል ማሠራጫ ዕቃዎች በተለይ የትራንስፎርመር እና የኮንዳክተር እጥረት በዋናነት የመርሀ ግብሩ ተግዳሮቶች መሆናቸውን ተጠቅሷል።

    በመጨረሻም በያዝነው በጀት ዓመት ፕሮግራሙ 450 የገጠር ከተሞችና መንደሮች በማገናኘት 54 ሺህ አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ አቅዶ እየሠራ መሆኑን አቶ ሁሴን አስታውቀዋል።

    የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመላው ሀገሪቱ ፍትሃዊ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማሳደግ በ”ብርሃን ለሁሉ” (Lighting to All) መርሀ ግብር እ.ኤ.አ በ2025 ከዋናው የኃይል ግሪድ 65 በመቶ እና ከግሪድ ውጪ በተለያዩ የኃይል አማራጮች 35 በመቶ የሚሆነውን ሕብረተስብ ተጠቃሚ ለማድረግ ስትራቴጂ ቀይሶ በመንቀሳቀስ መሆኑ ይታወቃል።

    ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዜና ሳንወጣ፥ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ከ2.8 ቢሊዮን ኪሎ ዋትስ በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነት መቀነስ መቻሉን አስታውቋል። ተቋሙ እንዳለው በ2012 በጀት ዓመት ቴክኒካልና ቴክኒካል ያልሆነ የኃይል ብክነትን ለመከላከል ባደረገው የክትትልና ቁጥጥር ሥራ 2,823,055,758.11 ኪሎ ዋትስ የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነት ወይም በገንዘብ 1,113,863,407.24 ብር ከብክነት ማዳን ችሏል።

    ተቋሙ የኃይል ብክነቱን መቀነስ የቻለው የኤሌክትሪክ ስርቆትን በመከላከል፣ በትክክል የማይሠሩ፣ የተቃጠሉ፤ የቆሙ ቆጣሪዎች በወቅቱ እንዲቀየሩ በማድረግ፣ የታሪፍ ለውጥ የሚያስፈልጋቸውን ደንበኞች የታሪፍ ለውጥ በማድረግ፣ ቢል የማይወጣላቸው ደንበኞችን ወደ ሲስተም እንደገቡ በማድረግ፣ ያልተፈቀደ የኃይል ጭነት በመቆጣጠር፣ ከቆጣሪው ልኬት ውጪ የተገጠመ አውቶማቲክ ፊዩዝን (automatic fuse) በመቀየር፣ የዝቅተኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪ ደንበኞች የተገኘ የማባዣ ስህተት በማስተካከል፣ የገቢ ደረሰኝ የሌላቸው እንዲኖራቸው በማድረግ እና የመሳሰሉ ቴክኒካል ያልሆነ የኃይል ብክነትን ለመቀነስ የሚያስችሉ ሥራዎችን በመሥራት ነው።

    ተቋሙ ቴክኒካል የኃይል ብክነትን ለመቀነስም የ2000 Common Meter Reading Instrument (CMRI) በተስተካከለው software design መጫን፣ የደንበኞች ቆጣሪ ቅያሪ ሥራ፣ የ383 የደንበኞችን መረጃ ወደ አዱሱ ሲሰተም (SAP) ማዛወርና የመሳሰሉ ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን በ2013 በጀት ዓመትም ሊከሰቱ የሚችሉ ቴክኒካልና ቴክኒካል ያልሆኑ የኃይል ብክነቶችን ለመቀነስ ሰፊ ዕቅድ ይዞ እየተንቀሰቀሰ በይገኛል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

    የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

    Anonymous
    Inactive

    ግልፅ ደብዳቤ ለኢንጂነር ታከለ ኡማ (ቢደርስም ባይደርስም)
    ወንድማገኘሁ አዲስ

    ሰላምታዬንና አክብሮቴን በማስቀደም የተከበሩ ሚኒስትር ኢንጂነር ታከለ ኡማ፥ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በጥናት ደረስኩበት ብሎ ይፋ ላደረገው ሰነድ በሰጡት መልስ የተገነዘብኩት እንደ አንድ ተራ ዜጋ ላቀርብልዎት እወዳለሁ።

    ሲጀመር የሰጡት ርዕስ ራሱ ችግር እንዳለበት ይሰማኛል። ማስረጃ አጠናቅሬያለሁ ያለ ድርጅት መግለጫ ከማውጣቱ ሰነዱን ለሚመለከታቸው አቅርቦ ይመሩት የነበረው ፅሕፈት ቤት መልስ ስላልሰጠ። ኢዜማ ከዚህ ቢሮ መልስ አግኝቶ ቢሆን ኖሮ አንደኛ መልሱን ሪፖርቱ ላይ ያካትት ነበር፤ አሳማኝ የሆኑ ጉዳዮች ከቀረቡም ፓርቲው ከሪፖርቱ ላይ የተወሰኑትን እንዲያርም ወይም እንዲያሻሽል ዕድሉ ክፍት ይሆን ነበር ብዬ አምናለሁ።

    በመቀጠልም ምላሽ ለመስጠት ተገቢው ቦታ ባልገኝም ሲሉ ተገቢው ቦታ ለመሆኑ የቱ ነው? ሰነዱ በቀጥታ ከሚመለከታቸው ግለሰቦች አካላት እርስዎና እርስዎ ይመሩት የነበረው ተቋም በመሆናቸው መልስ እንዳይሰጡ ቦታ ምክንያት ይሆናል ብዬ አላስብም ።

    በመቀጠልም የመሬት ወረራን በተመለከተ ስልጣን ላይ ከወጣንበት የመጀመሪያ ቀን ጀምሮ እስከ መጨረሻዋ ቀን ድረስ ጠንካራ እርምጃዎች ስንወስድበት የነበረ ጉዳይ ነው ብለዋል።  ለእርስዎ አድልተን ያሉትን ብንቀበል እንኳን “የመሬት ወረራውን አስቆሙት ወይ? የኮንዶሚኒየሙን አድሎአዊ እደላ አስወገዱት ወይ ነው?” ጥያቄው በራስዎ አንደበት የሀይማኖት ተቋማት ሳይቀሩ በኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ሲወረሩና በመንግሥት አካላት ሲፈርሱ በተነሳብዎት ተቃውሞ ምክንያት እርስዎ ራስዎ ይቅርታ አልጠየቁም ወይ? ከፍተኛ የሆነ የመሬት ወረራ እንዳለ በይፋ አልተናገሩም ወይ? ባለፉበት ባገደሙበት ሁሉ የከተማዋን መሬት ለግለሰቦችና ለተቋማት ሲያድሉ አልነበር ወይ?

    ሌላው ክቡር ኢንጂነር ታከለ ኡማ፥ የተፈናቀሉትን አርሶ አደሮች በመታከክ እንደ ህወሀቶቹ የቀን ጅቦች ብሄርዎን ዋሻ ለማድረግ የሄዱበት መንገድ በጣም ከእርስዎ በጭራሽ ያልጠኩት ነበር። ለመሆኑ የትኛው የኢዜማ የመግለጫው ክፍል ላይ ነው “የተፈናቀሉት ገበሬዎች የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ አይሆኑ” የሚለው። ማነው በቃለ መጠይቁስ ላይ “ለተፈናቀሉት ቤት አይሰጥ” ያለው? በእርስዎ የስልጣን ዘመን በገፍ ቤት የታደላቸው በሺዎች የሚቆጠሩት የኦሮሚያ ባለስልጣናት የተፈናቀሉ አርሶ አደሮች ነበሩ ወይ? እስከ ልጅ ልጅ የሚሰጠው መሬት ፍትሀዊ ነበር ወይ? ለስፖርት ክለቦች የታደለውስ? ይህ ሁሉ እየሆነ ያለው እኮ “በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ድሆች ከዛሬ ነገ አንገታችንን ማስገቢያ፣ ልጆቻችንን ማሳረፊያ ቤት ልናገኝ ነው” በማለት ቤትን የህልውናቸውና የተስፋቸው ጥግ አርገው እየጠበቁ ሳለ ነው።

    “እኛ ሕጋዊ እርምጃ ስንወስድ የዛሬ ተችዎቻችን የሰብዓዊ መብት ተነካ፤ ዜጎች ተፈናቀሉ ብለው ዘመቻ የከፈቱብን አካላት ናቸው” ብለዋል። በመጀመሪያ ደረጃ እርምጃ ሲወሰድ የሰብዓዊ መብት መከበር አለበት የሚለው ዓለም-አቀፋዊ መርህ እንደተጠበቀ ሆኖ ‘ዘመቻ’ ላሉት ቃል ግን ይቅርታ ያድርጉልኝና ማፈር ይኖርብዎታል። ለእርስዎም ሆነ ለመንግሥትዎ የኢዜማን ያክል ዕድል የሰጠ አንድም ድርጅት የለም። መወቀስ ካለበትም በሰጣችሁ ሰፊ ዕድልና በታገሳችሁ ልክ መሆን አለበት፤ ምንም እንኳን ሁለቱም ምክንያታዊ ናቸው ብዬ ባምንም።

    ሌላው እጅግ አስገራሚ የሆነው ደሞ “አንድም ቀን ለተናቀሉት የመቆርቆር ስሜት አሳይቶ የማያውቅ ድርጅት” ሲሉ የጠቀሱት ለመሆኑ ኢዜማ የጠቀሷቸው ዜጎች ሲፈናቀሉ ህልው ፓርቲ ነበር ወይ? ያፈናቀላቸው እኮ የራስዎ ድርጅት የዛሬው የኦሮሚያ ብልጽግና የትናንቱ ኦህዴድ ነበር! ተረሳ ክቡር ሚኒስትር? አርበኞች ግንቦት 7 (አግ7) እንዲሁም ከስመው ኢዜማን የመሠረቱት እኔ የማቃቸው ፓርቲዎች እና ግለሰቦች ሁሉ እናንተ ስታፈናቅሉ እነሱ ከተፈናቃዮች ጎን ሆነው ድምፃቸውን ሲያሰሙ የነበሩ መሆናቸውን አስረግጬ መናገር እችላለሁ። እንደ አንድ ለወገኑ እንደሚቆረቆር ኢትዮጲያዊ እኔም ከእነሱ ባለሁበት ያቅሜን ስጮህ ነበር። ለምን ይዋሻል ኢንጂነር?!

    “የአርሶ አደሮችን ጉዳይ ለተቀባይነት ማግኛ” በማለት የፃፉት እና “መጀመሪያ ላይ በሀሰተኛ መረጃ ሀገር ማፍረስ እንጂ አይገነባም” ላሉት ደሞ ትንሽ ማለት አለብኝ። ለመሆኑ ኢዜማ እርስዎ ባሉት መልኩ ተቀባይነት ማግኘት እንደሚቻል ጠፍቶት ነው በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ደጋፊዎቹን ያጣው? ሌላው ቢቀር በእናት ድርጅትዎ መዋቅር በአብዛኛው ኦሮሚያና እርስዎ ሲያስተዳድሯት በነበረችው በአዲስ አበባ ከተማ በፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ላይ ሲደርሱ የነበሩት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በማስጮህ ብቻ ተከታይን ማፍራት አይቻልም ብለው ያስባሉ? ይልቅስ ከላይ እንደጠቀስኩት የተፈናቃዮችን ልብ በፀረ-ኢዜማ ትርክት ለማነፅና ጭፍን ተከታይ ለማፍራት የኳተኑት እርስዎ ራስዎ ነዎት። በነገራችን ላይ፥ ለሀገር ሰላምና መረጋጋት ዕድል መስጠት ከመንግሥታዊ ኢ-ሕገመንግሥታዊ ተግባራት ጋር ማበር አይደለም።

    ክቡር ኢንጂነር፥ አሁን ላይ በደንብ የገባኝ ከስልጣን ሲወርዱ፣ በሀሳብ መሟገት ሲያቅታቸውና ፖለቲካ ፊት ስትነሳቸው “ብሔርን መደበቂያ ዋሻ” ማድረግ በስፋት እየተዛመተ ያለ አስፈሪ ፖለቲካዊ ባህል መሆኑን ነው። እርስዎም ይሄን መንገድ በመከተል የእነ ሀይለመስቀል ሸኚን ፣ የእነ አቦይ ስብሀትን የእነ ልደቱ አያሌውን ዱካ እንደተከተሉ ተረድቻለሁ።

    የአሿሿምዎ ሂደት አጠያያቂነት እንደተጠበቀ ሆኖ ክቡር ሚኒስትር፥ እርስዎ የታላቋ አዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ነበሩ። ሲያስተዳድሯት የነበረችው አዲስ አበባ ማለት የ AU፣ የ ECA እና የመሳሰሉት ታላላቅ ዓለም-አቀፋዊ ድርጅቶች መቀመጫና በዓለም ላይ 3ኛዋ ወይም 4ኛዋ የዲሎማሲና የፖለቲካ ከተማ እንደሆነች ዓለም የሚያውቀው ሀቅ ነው። አሁንም ቢሆን ሚኒስትር እንጂ እንደኔ አክቲቪስት አይደሉም። ቢሆን ደስ የሚለኝ ‘ቀረበ’ የተባለውን ሰነድ በሚገባ ፈትሸው ተመጣጣኝ በሆነ አግባብ መልስ ቢሰጡ ነበር። ሰነዱን በሙሉም ሆነ በከፊል ወይም በተወሰነ ደረጃ ተቀብለው፥ ያም ካልሆነ ተቃውመው የነበሩበትንና ያሉበትን ወንበር የሚመጥን አጸፋ ይሰጣሉ ብዬ ጠብቄ ነበር። በእኔ በኩል ያደረጓቸውን በጎ ተግባራት በዜሮ የማጣፋ ሰው አይደለሁም። የዛሬው መልስዎ ስሜቴን በእጅጉ ቢበርዘውም ለበጎ ለበጎዎቹ ሥራዎችዎ ዛሬም ክብር እሰጣለሁ። ይሁን እንጂ በቀረበብዎ ክስ እና በሰጡት መልስ ምክንያት የተደበቀውን “ኢንጂነር ታከለ ኡማን” ማየቴን ደሞ አልሸሽግዎትም። አሁን ለደረስኩበት ግንዛቤ ትልቁ ግብአቴ ደግሞ እርስዎ ራስዎ የነገሩንን ጭምር በመካድዎ ነው። ይሄ ሁሉ ሆኖም የነበሩበትንና ያሉበትን ደረጃ የሚመጥን መልስ ካለ ለመስማት አሁንም ፍቃደኛ ነኝ።

    ክቡር ሚኒስትር፥ ስንብቴን አስቀድሜ እያቀረብኩ ደብዳቤዬን ከማጠናቀቄ በፊት እርስዎ ወይም ይመሩት የነበረው አስተዳደር ስለተሞገታችሁ ብቻ ሀገር እንደማትፈርስ በርግጠኝነት ልነግርዎ እወዳለሁ። ይልቅስ ሀገር የሚያፈርሰው የዜጎችን ድምፅ ለማፈን ይመሩት የነበረው ተቋም እየወሰደ ያለው ኢ-ሕገመንግሳታዊና ኢ-ዴሞክራሲያዊ እርምጃ ነው። የኢዜማ መግለጫዎች መታገድ የከንቲባ አዳነች አቤቤ ሳይሆን የእስዎ የሁለት ዓመታት የከንቲባነት ዘመን ውጤት ነው። የክብርት ከንቲባዋን ውጤት ደሞ ሰነባብተን እናየዋለን።

    አክባሪዎ ወንድማገኘሁ አዲስ

    ተያያዥ ጉዳዮች፦

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ፦ በሰሞነኛ ድረገጽ የአማርኛ ፎረም (semonegna.com/forums) ላይ የሚገኝ ማንኛውም ጽሑፍ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንጸባርቅ ሲሆን፥ ጽሑፉ የሰሞነኛ ኢትዮጵያንንም ሆነ የተሳታፊዎችን አመለካከትና ምልከታ ላይወክል ይችላል።

    ግልፅ ደብዳቤ ለኢንጂነር ታከለ ኡማ

Viewing 15 results - 166 through 180 (of 730 total)