Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 10 results - 721 through 730 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያን ሰብዓዊ መብት አያያዝ ሁኔታ የሚገመግም ሰነድ በተለያዩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ተጠናቅሮ ቀረበ። በየአራት ዓመቱ በሚካሄደው የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት መድረክ ላይ ኢትዮጵያ ለሦስተኛ ጊዜ ተሳታፊ ሆና ትቀርባለች።

    አቅራቢ፦ ጽዮን ግርማ (ቪኦኤ አማርኛ)

    ዋሽንግተን ዲሲ፦ በየአራት ዓመቱ ለሚካሄደው የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት የአገራት የሰብዓዊ መብት መገማገሚያ መድረክ ላይ የኢትዮጵያን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሁኔታ ለመገምገም የሚያስችል ሰነድ ቀረበ። ሰነዱን ካቀረቡት የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዋቂ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ውስጥ፤ ሲቪከስ (CIVICUS)፣ ሲፒጄ (CPJ)፣ ዲፌንድ ዲፌንደርስ (Defend Defenders)፣ አርቲክል 19 (Article 19)፣ አክሰስ ናው (Access Now)፣ ፔን ኢንተርናሽናል (PEN International) እና የኢትዮጵያ የመብት ድርጅቶች ኅብረት (ኢመድህ) ይገኙበታል።

    በየአራት ዓመቱ በሚካሄደው የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት (United Nations Human Rights Council/UNHRC) መድረክ ላይ ኢትዮጵያ ለሦስተኛ ጊዜ ተሳታፊ ሆና ትቀርባለች። በዚህ ጉባዔ ላይ ውይይት የሚደረገው ከ197 በላይ የዓለም ሀገሮች መካከል ሲሆን ሀገራቱ የሰብዓዊ መብት አያያዛቸውን በሚመለከት ሪፖርት የሚያቀርቡበት እንዲሁም የሚቀርብባቸውን ወቀሳና ትችት አዳምጠው የሚያሳሽሉትን “አሻሽላለሁ” የሚሉበት ያልተስማሙበትን ደግሞ ያልተስማሙበትን ምክንያት የሚያስረዱበት ስብሰባ ነው።

    ሀገራቱ እንዲያሻሽሉ የሚነገራቸውና ምክረ ሀሳብ የሚቀርበው በሰብዓዊ መብት ዙሪያ የሚሠሩ ድርጅቶች አጠናቅረው በሚያቀርቡት ሪፖርት መሠረት ነው። ከዚያም ከአራት ዓመት በኋላ ሲመለሱ አሻሽለው እንደሆነ ወይም ደግሞ የባሰ ሁኔታ ተፈጥሮ እንደሆነ ይጠየቃሉ።

    ከአራት ዓመት በኋላ ዘንድሮ ለሚደረገው ሰብዓዊ መብት አያያዝ ሁኔታ ሪፖርትም ዘጠኝ የሚሆኑ ድርጅቶች ኢትዮጵያን የተመለከተ ሰነድ አደራጅተው አቅርበዋል። በዚህ ሰነድ ውስጥ ኢትዮጵያ መሻሻል አሳይታበታለች የተባለው ተጠቅሷል። በቀጣይ ልታሻሽል ይገባታል የተባለውም በምክረ ሀሳብ ሰፍሯል።

    ከእነዚህ ድርጅቶች ስብስብ ለሰብዓዊ መብቶች በኢትዮጵያን የሚመሩት (የኢመድህ ዳይሬክተር) አቶ ያሬድ ኃይለማርያም ስለሰነዱ ተጠይቀዋል።

    በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሁኔታ ሪፖርት ሙሉውን እዚህ ጋር ማንበብ ይችላሉ

    ቃለምልልሱን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ

    ምንጭ፦ ቪኦኤ አማርኛ

    About the Association for Human Rights in Ethiopia (AHRE)

    Association for Human Rights in Ethiopia (AHRE) is a non-governmental, non-partisan, and not-for-profit organization dedicated to the advancement of human rights protection in Ethiopia by providing support to the work of Ethiopian Human Rights Defenders and performing advocacy and other related tasks that cannot be carried out effectively by human rights organizations based in Ethiopia because of administrative and legal restrictions, security risks and resource constraints.

    ሰብዓዊ መብት

    Semonegna
    Keymaster

    በፌዴራል ፖሊስ አባላት መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የሶስት ፖሊሶች ሕይወት ጠፋ ― የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – ዛሬ [መስከረም 24 ቀን 2011 ዓም] ማለዳ በአዲስ አበባ ቦሌ ወሎ ሰፈር አካባቢ በፖሊስ አባላት መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የሶስት ፖሊሶች ሕይወት መጥፋቱን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ።

    ምክትል ጀኔራል ኮሚሽነር መላኩ ፋንታ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደገለጹት በፌዴራል ፖሊስ አባላቱ መካከል በተፈጠረው አለመግባባት አንድ አባል በያዘው መሳሪያ በከፈተው ተኩስ ሁለት ፖሊሶችን ገድሏል።

    ድርጊቱን የፈጸመውን አባል በቁጥጥር ስር ለማዋል ጥረት ተደርጎ ባለመሳካቱ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ለመከላከል ሲባልም እርምጃ ተወስዶበታል።

    ወንጀሉን ከፈጸመ በኋላ ወደፎቁ የላይኛው ክፍል በመውጣት ላይ ሳለ በቁጥጥር ስር ሊያውሉት ሲከታተሉት የነበሩትን ስድስት የስራ ባልደረቦቹን በመተኮስ አቁስሏቸዋል።

    ለጥበቃ በታጠቀው ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ተኩሱን እንደከፈተ የተረጋገጠው ይህ የፖሊስ አባል አለቆቹን ከገደለ በኋላ ተጨማሪ መሳሪያ ከባልደረቦቹ በመቀማት ሊይዙት በመጡት የጸጥታ ሃይሎች ላይ እስከ ማለዳ ደረስ ሲተኩስ ቆይቷል።

    አለመግባባቱ የተከሰተበት ስፍራ በርካታ ነዋሪዎች የሚገኙበት የመኖሪያ አፓርተማ በመሆኑ ፖሊስ በሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ማድረጉን ምክትል ጀኔራል ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።

    ”አባሉ በሥራ ቦታ ላይ መጥቶ ምድብ ቦታው ላይ ከነበሩ አባላት ጋር የሥራ ርክክብ ሲያደርጉ ግጭት ተፈጥሮ የከፋ ችግር እንዳያደርስ ምክር ቢሰጠውም መቀበል አልቻለም፤ በያዘው መሳሪያ የሥራ ጓዶቹ በሆኑ ሁለት ፖሊሶች ላይ የሞት አደጋ አድርሷል” ብለዋል።

    በተደረገው መከላከል የከፋ አደጋ ሳይደርስ አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድ መደረጉንና ፖሊስ በሲቪል ሰዎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ የመከላከል ሥራ መሥራቱንም አክለዋል።

    አባሉ ተደጋጋሚ የስነ-ምግባር ችግር ባይመዘገብበትም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሚደረግ የሥራ ግምገማ ሊያርማቸው የሚገቡ ጉዳዮችን እንዲያስተካክል ቢነገረውም ያልተቀበለው በመሆኑ የዛሬውን ችግር ሊፈጥር እንደቻለ ምክትል ጀኔራል ኮሚሽነር መላኩ ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና ARTS TV

    የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር)– ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ የ20ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን እያከበረ ሲሆን ይህን ተከትሎም ኦርቢስ በራሪው የአይን ሆስፒታል በቦሌ ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ የስልጠና አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

    የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ከበደ ወርቁ በመክፈቻ ስነ ሥርዓቱ ላይ በመገኘት እንደተናገሩት ሀገሪቱ በአይን ህክምና ዙሪያ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች። ለነዚህ ሥራዎች መሳካትም በርካታ በአይን ህክምና ዙሪያ የሚሠሩ አጋር አካላት ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በትብብር እየሠሩ መሆናቸውን የተናገሩት ዶ/ር ከበደ ወርቁ በተለይም ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ሊታከም የሚችል አይነ-ስውርነትን አስቀድሞ በመከላከል ረገድ፣ የዘርፉን ባለሞያዎች በዕዉቀት እና በክህሎት በማብቃት፣ በአይን ህክምና ዙሪያ የሚሠሩ የትምህርት ተቋማትን አቅም በመገንባት፣ ለአይን የሚደረጉ ጥንቃቄዎችን አስመልክቶ ግንዛቤ በመፍጠር እንዲሁም በዘርፉ የሚደረጉ ጥናትና ምርምሮች ላይ በመሥራት እና የተለያዩ ግብአቶችን በማቀረብ ላለፉት ሀያ አመታት ከፍተኛ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው አመስግነዋል።

    በቀጣይም ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በአይን ህክምና ዙሪያ ለሚያከናውናቸው ስራዎች በትብብር እንደሚሰራ እና ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። በዕለቱም ዶ/ር ከበደ ወርቁ በቦሌ ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ በመገኘት ኦርቢት በራሪውን የአይን ሆስፒታል ወይም የአውሮፕላን ውስጥ የአይን ሆስፒታል ጎብኝተዋል።

    ኦርቢስ ኢንተርናሽናል

    በኢትዮጵያ የኦርቢስ ዳይሬክተር ዶ/ር አለማየሁ ሲሳይ በበኩላቸው ስለበራሪው የአይን ሆስፒታል እንደተናገሩት ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህክምና ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር ለአምስተኛ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ የመጣ ሲሆን አውሮፕላኑ በረቂቅ ቴክኖሎጂ የበለጸገ የማስተማሪያ ተቋም በመሆን ያገለግላል።

    በዚህም ለዶክተሮች፣ ለነርሶች እና ለህክምና ቴክኒሺያኖች ስልጠና ከመስጠት በተጨማሪ ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በመተባበር የአይን ህክምና ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲደርስ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። በራሪው የአይን ሆስፒታል በውስጡ እጅግ ዘመናዊ የቀዶ ጥገና፣ የመማሪያና የማገገሚያ ክፍሎች ያሉት እንደሆነ የተናገሩት ዳይሬክተሩ፥ የበጎ ፈቃደኛ ሀኪሞች ስልጠናን በአውሮፕላን ወስጥ እና በአካባቢው ከሚገኙ ሆስፒታሎች ጋር በመተባበር ይሰጣልም ብለዋል።

    በራሪው የአይን ሆስፒታል ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ ከከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህክምና ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር ለአምስተኛ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣም ገልጸዋል። ለሚቀጥሉት 15 ቀናትም በራሪው ሆስፒታል በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚቆይ ለማወቅ ተችሏል።

    ኦርቢስ ኢንተርናሽናል መንግስታዊ ያልሆነና የበጎ አድራጊ ዓለማቀፋዊ ድርጅት ሲሆን ዋነኛ ተግባሩም ዓይነ ስውርነትን መከላከልና የዓይን ህክምናን መስጠት ነው። ኦርቢስ ኢንተርናሽናል እ.ኤ.አ በ1960ዎቹ አሜሪካዊ የዓይን ህክምና ባለሙያ ዶ/ር ዴቪድ ፓተን (Dr. David Paton) ጽንሰ ሀሳቡን ጀምሮት በድርጅት ደረጃ የተቋቋመው  ደግሞ እ.ኤ.አ በ1982 ዓ.ም ሲሆን ዋና መቀመጫውን ኒው ዮርክ ከተማ (ኒው ዮርክ፣ አሜሪካ) አድርጎ ከ90 በላይ ሀገራት ይሠራል።

    ምንጭ፦ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኢ.ም.ባ.ኮ)– የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን በአፍሪካ (ኢ.ም.ባ.ኮ) ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የባቡር አካዳሚ በቢሾፍቱ ከተማ ለመገንባት በርካታ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን የኮርፖሬሽኑ ባቡር አካዳሚ ዘርፍ ም/ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አብይ ጌታቸው ገለፁ።

    ለባቡር አካዳሚው ግንባታ የቻይና መንግስት ሳውዝዌስት ጂአኦቶንግ ዩኒቨርሲቲ (Southwest Jiaotong University) ባካሄደው አማካሪ የአዋጭነት ጥናት መነሻነት የገንዘብ ድጋፍ የፈቀደ መሆኑን የገለፁት አቶ አብይ በተጠናው የአዋጭነት ጥናትና በኮርፖሬሽኑ ፍላጎት መሠረት የትግበራ ስምምነት (Implementation Agreement) እ.ኤ.አ ታህሳስ 19 ቀን 2017 ከቻይና ኤምባሲ የንግድና ኢኮኖሚክ ካውንስለር ቢሮ፤ እንዲሁም የግንባታ ዲዛይን መነሻ ሃሳብ (Scheme design) ጥር 6 ቀን 2018 እ.ኤ.አ ከአማካሪ ድርጅቱ ጋር መፈራረማቸውን ተናግረዋል።

    በግንባታው የዲዛይን መነሻ ሃሳብ መሰረትም የግንባታው የመጀመሪያ ዲዛይን (Preliminary Design) ተዘጋጅቶ በአሁኑ ወቅት በቻይና መንግስት በኩል ግንባታውን የሚያከናውን የኮንትራክተር መረጣ ሂደት ላይ መሆኑንና እስከ ቀጣይ ህዳር ወር ድረስ ኮንትራክተሩ ተለይቶ ግንባታው ከታህሳስ አጋማሽ እስከ ጥር ወር መጀመሪያ ባለው ጊዜ ሊጀመር እንደሚችልም አቶ ዓቢይ ገልፀዋል።

    ግንባታውን ተቆጣጥሮ በጥራት ከመረከብ በተጨማሪ ግንባታው የሚከናወንበትን ቦታ ማዘጋጀት ከኮርፖሬሽኑ ሃላፊነቶች አንዱ ሲሆን ለአካዳሚው ግንባታ ማስፋፊያውን ጨምሮ ከሚያስፈልገው 157.7 ሄክታር መሬት ውስጥ የ62 ሄክታር መሬት ከኦሮሚያ ክልል የከተማ ልማትና ቤቶች ቢሮ እና ከከተማ መሬት ማኔጅመንት ኤጀንሲ ጋር በመነጋገር ከክልሉ መንግስት ህጋዊ ፈቃድ ለማግኘት በሂደት ላይ መሆኑን የገለፁት አቶ ዓቢይ የመሬት ፈቃዱ እንደተገኘ ዲዛይኑ ቀርቦ ግንባታው እንደሚጀመር፤ በተጨማሪም የግንባታ ግብዓቶችን ማምረቻ ሳይቶች ለኮንትራክተሩ ማቅረብ፣ የተለያዩ መሠረተ ልማቶችን (ውሃ፣ መብራት…) ወደ ሳይቱ ማቅረብ የኮርፖሬሽኑ ኃላፊነት መሆኑንና ይህን ተግባር የሚያከናውን ፕሮጀክት ጽ/ቤት ተቋቁሞ በእንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን

    ከግንባታው ጋር ተያይዞ ከሥራ ቦታቸው ለሚፈናቀሉ የአካባቢው ማህበረሰበም በካሳ ክፍያ ብቻ የሚተው ሳይሆን በጋራ የሚሠሩ ሥራዎችን በማቅረብ፣ ቴክኒካል ድጋፍ በመስጠትና የበለጠ ተጠቃሚ መሆን የሚችሉበት ፕሮፖዛል በማቅረብ ከክልሉ ከተማ ልማትና ቤቶች ቢሮ ጋር በመሆን ህብረተሰቡን ያማከለ የተቀናጀ ልማት ፕሮፖዛል ቀርቧል ያሉት አቶ አቢይ የመሬት ፈቃዱ እንደተገኘ ወደ ሥራ እንገባለን ብለዋል።

    ኮርፖሬሽኑ በአካዳሚ ዘርፍ የባቡር አካዳሚ ከማስገንባት ባለፈም የባቡር ዘርፉ የሚፈልገውን የሰው ኃይል ለማብቃት የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት ባለሙያዎችን በተለያዩ የትምህርት መስኮች በሃገር ውስጥና በውጭ እያሰለጠ ይገኛል።

    በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመሆን ከ1ኛ እስከ 4ኛ ዙር ከ400 በላይ የሚሆኑ ባለሙያዎችን በማስተርስ ፕሮግራም ያስተማረ ሲሆን የ1ኛ ዙር ተመራቂዎች ሁሉም በኮርፖሬሽኑ በስራ ላይ እንደሚገኙ የገለፁት አቶ አብይ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ዙር የተማሩት ደግሞ ኮርፖሬሽኑ በቀጣይ የሀገራዊ ሴክተሩን አቅም በመገንባት ለሚያከናውነው የራስ ኃይል ሥራዎች በመደራጀት ላይ በሚገኙ ቢዝነስ ዩኒቶች ስር ለስድስት ወር በሥራ ላይ ስልጠና በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ ስልጠናቸውን እንዳጠናቀቁ ወደ ሥራ የሚገቡ መሆናቸውን ገልፀዋል።

    ምንጭ፦ ኢ.ም.ባ.ኮ

    Semonegna
    Keymaster

    ኢህአዴግ 11ኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን በሀዋሳ ከተማ ጀመረ

    ሀዋሳ ከተማ፣ ደቡብ (ኢዜአ) – የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ለሶስት ቀናት የሚዘልቀውን ጉባዔውን የደቡብ ክልል ዋና ከተማ በሆነችው ሀዋሳ ማካሄድ ጀምሯል።

    በጉባዔው ቀደም ብለው ድርጅታዊ ጉባዔያቸውን ያጠናቀቁት የኢህአዴግ አራቱ እህት ድርጅቶች (የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ እና የሕዝበ ወያኔ ሀርነት ትግራይ) እና አጋር ፓርቲዎችም ተሳታፊዎች ናቸው፡፡

    በዚህ ጉባዔ ላይ 2 ሺህ የሚጠጉ ተሳፊዎች ታዳሚ ሆነዋል። ከነዚህም 1 ሺህ ያህሉ ተሳፊዎች በድምፅ የሚሳተፉ ናቸው።

    ———————————————-

    ———————————————-

    የውጭ አገራት ወዳጅ ፓርቲዎችን ጨምሮ፣ በአገር ውስጥ ያሉ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማኅበራትና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶችም ከዛሬ ጅምሮ በሚካሔደው ጉባዔ ላይ የሚካፈሉ ይሆናል።

    የኢህአዴግ ሊቀመንበርና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) 11ኛውን ድርጅታዊ ጉባዔ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በዋናነት በ10ኛው ጉባኤ መግባባት የተደረሰባቸውን አቅጣጫዎች አፈጻጸምን በተመለከተ የበላይ አመራሩ ግምገማ ለጉባኤ ተሳታፊ አባላት የሚቀርብበትና ከዚያም በመነሳት በቀጣይ ሁለት አመታት ተግባራዊ ሊደረጉ የሚገባቸውን ጉዳዮች አቅጣጫ የሚያስቀምጥበት ይሆናል ብለዋል።

    ጉባዔተኛው ከበላይ አመራሩ የሚቅርብለትን መነሻ በመያዝ ባለፉት 27 ዓመታት እንደ ድርጅት ያካሄደውን ጉዞ በመገምገም አገራችን የምትገኝበትን የትግል መድረክ ከግምት ውስጥ በማስገባት ኢትዮጵያ ወደ አዲስ የሰላም፣ የዴሞክራሲና የልማት አቅጣጫ ሊያሸጋግር እንደሚችል በታመነበት አቅጣጫ ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃልም ብለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵይ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    ኢህአዴግ

    ቪድዮ፦ The Oromo Democratic Party (ODP) is the new OPDO, with Abiy Ahmed and Lemma Megersa as its leaders

    Semonegna
    Keymaster

    በ2010 ዓ.ም ወደ ከፍትኛ ትምህርት ተቋማት የሚገቡ 280 ኤርትራውያን ስደተኞች የመግቢያ ፈተና እንዲወስዱ መደረጉንና በአሁኑ ወቅት ፈተናውን ያለፉ 150 ተማሪዎች መለየታቸውን አስረድተዋል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ/UNHCR)፦ በኢትዮጵያ በስደት ላይ ከሚኖሩ ኤርትራውያን መካከል 150 ተማሪዎች በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ገብተው የመማር ዕድል እንደሚያገኙ በኢትዮጵያ የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር አስታወቀ።

    በተያዘው ዓመት ሌሎች ቁጥራቸው ከ11ሺህ በላይ የሆኑ ህጻናት (የስደተኛ ኤርትራውያን ልጆች የሆኑ) የቅድመ መደበኛ ትምህርት ዕድል ማግኘታቸውም ተመልክቷል።

    በኢትዮጵያ የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር (Ethiopia Administration for Refugee and Returnee Affairs/ ARRA) የሰሜን ጽህፈት ቤት የትምህርት ኦፊሰር አቶ ኤፍሬም ሀጎስ ለኢዜአ እንደገለጹት ከ180 ሺህ የሚበልጡ ኤርትራውያን ስደተኞች በተለያዩ መጠለያ ጣቢያዎች ይገኛሉ፡፡

    የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ ኤርትራውያን ስደተኞች መካከል 150 ተማሪዎች ዘንድሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በነጻ ለመማር እድል እንደሚሰጣቸውም ተናግረዋል።

    ወደ ከፍትኛ ትምህርት ተቋማት የሚገቡ 280 ስደተኞች የመግቢያ ፈተና እንዲወስዱ መደረጉንና በአሁኑ ወቅት ፈተናውን ያለፉ 150 ተማሪዎች መለየታቸውን አስረድተዋል።

    ፈተናውን ያለፉ 150 ስደተኞችም በተለያዩ የኢትዮጵያ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እንደሚከታተሉም ነው አቶ ኤፍሬም የገለጹት።

    ኤርትራውያን ስደተኛ ተማሪዎች በኢትዮጵያ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ መደረጉ በሁለቱ አገራት መካከል አሁን የተጀመረውን ሰላማዊ ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክረውም ተናግረዋል።

    ◌ ቪድዮ፦ ኢትዮጵያ የቀይ ባህር እና የምጽዋ ወደቦችን ለመጠቀም ቅድመ ዝግጅቶችን እያጠናቀቀች ነው

    የኢትዮጵያ መንግስት ለኤርትራውያን ስደተኞች የትምህርት ዕድል ሲሰጥ የአሁኑ ለሰባተኛ ጊዜ ሲሆን በየዓመቱ ከ100 ያላነሱ ተማሪዎችም የዕድሉ ተጠቃሚ ሆነዋል።

    በተመሳሳይ በትግራይ ክልል በሚገኙ አራት የኤርትራውያን ስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ 11ሺህ 87 ኤርትራውያን በቅድመና በመደባኛ ትምህርት እንዲሁም በሙያ ክህሎት ማበልጸጊያ እንዲማሩ መደረጉን አቶ ኤፍሬም አክለው ተናግረዋል።

    በተለያዩ ምክንያቶች ከአገራቸው ተሰደው ወደኢትዮጵያ ቢመጡም ልጆቻው እዚህ የትምህርት ዕድል በማግኘታቸው መደበኛ ትምህርታቸውን መቀጠላቸውን የተናገሩት ደግሞ በማይዓይኒ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙት አቶ ተስፋልደት ይህደጎ የተባሉ ስደተኛ ናቸው።

    በአዲ ሓሩሽ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ሌላው ስደተኛዋ ወይዘሮ ለምለም ዘካሪያስ እንደተናገሩት በአካባቢያችን የሚገኙ ትምህርትቤቶች ለኤርትራውያን ተማሪዎች በራቸው ክፍት መሆኑ ትልቅ እድል መሆኑን ገልጸዋል።

    “ልጆቻቸው ከኢትዮጵያውያን ወንደሞቻቸው ጋር በአንድ ክፍል ውስጥ እንዲማሩ መደረጉ በሁለቱ አገራት ህዝቦች መካከል ጠንካራ ግንኙነት ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት የላቀ አስተዋፅኦ አለው” ብለዋል።

    የኢትዮጵያ መንግስት ለኤርትራውያን ስደተኞች እየሰጠ ያለው የከፍተኛ የትምህርት እድል ለሌሎች አገራት በመልካም አርአያነት የሚጠቀስ መሆኑን የገለጸው ደግሞ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለማግባት የመግቢያ ፈተና የወሰደው ተማሪ ዓንዶም ፍሳሃየ ነው።

    እስከ ግንቦት ወር 2010 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በአጠቃላይ 71,833 ኤርትራውያን ስደተኞች ትግራይ ክልል ውስጥ በሚገኙ አራት መጠለያ ጣብያዎችና አፋር ክልል ውስጥ በሚገኙ ሁለት መጠለያ ጣብያዎች ውስጥ እንደሚገኙ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች መርጃ ድርጅት (UNHCR) ዘግቧል።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እና የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች መርጃ ድርጅት (UNHCR)

    ኤርትራውያን

    Semonegna
    Keymaster

    በኢትዮጵያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የጤናውን ዘርፍ ለማገዝ የተሰራችው ሰው አልባ አውሮፕላን (drone) ከቢሾፍቱ አየር ኃይል ወደ አዳማ ከተማ የተሳካ በረራ አድርጋለች።

    የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሰው አልባ አውሮፕላንን በመጠቀም የህክምና መሣርያዎችን እና መድኃኒቶችን ለማጓጓዝ የሚያስችል ስምምነትም ተፈራርመዋል።

    ስምምነቱ በ6 ጣቢያዎች 24 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በመጠቀም እስከ 5ኪ.ግ. የህክምና ቁሳቁሶችንና መድኃኒቶችን ለማድረስ የሚያስችል ነው።
    ስምምነቱን የተፈራረሙት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስተር ጌታሁን መኩርያ (ዶ/ር ኢንጂ.) እና የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን ናቸው።

    የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌታሁን መኩርያ (ዶ/ር ኢንጂ.) ሰው አልባ አውሮፕላንኗ በሳይንስና ቴክኖሎጂ የቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዞች መሠራቷን ጠቅሰው ለሳይንስና ቴክኖሎጂ መዳበር የበለጠ አስተዋጽዖ ሊያደርጉ የሚችሉ የሙያ ማኅበራትንና ወጣት የፈጠራ ባለሙያዎችን በመደገፍ በቀጣይ መሰል ቴክኖሎጂዎች ሽግግር ዙርያ ከቴክኖሎጂ ኢንተርፕራይዞች ጋር በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    የጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ መርክል ባደረጉላቸው ግብዣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር አብይ አህመድ በጥቅምት ወር ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ጀርመን የሚያቀኑ ሲሆን፥ በአውሮፓ የሚገኙ ኢትዮጵያዊንን አግኝተው ያነጋግራሉ ተብሏል።

    አዲስ አበባ (የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር አብይ አህመድ በጥቅምት ወር ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ጀርማን የሚያቀኑ ሲሆን፥ በዚሁ ጉብኝታቸውም ከጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ መርክል (Angela Merkel) እና ሌሎች የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በጀርመን ዋና ከተማ በርሊን እንደሚገናኙም ነው የተገለጸው።

    የጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ መርክል በፈረንጆቹ ነሃሴ ወር በኢትዮጵያ እየመጣ ያለውን ለውጥ በመደገፍ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ጎን መሆናቸውን በስልክ በገለጹበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጀርመን ይፋዊ ጉብኝት እንዲያደረጉ መጋበዛቸውም ታውቋል።

    በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር አብይ አህመድ በጥቅምት ወር መጨረሻ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ጀርመን የሚያቀኑ ሲሆን፥ በአውሮፓ የሚገኙ ኢትዮጵያዊንን አግኝተው ያነጋግራሉ ተብሏል።

    በፈረንሳይ ፓሪስ፣ ጀርመን ፍራንክፈርት ከተሞችም በሚዘገጁ መድረኮችም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር አብይ ከኢትዮጵያዊያኑ ጋር እንደሚገናኙ የተገለጸው።

    ሀገራዊ ዜና፦ አብይ አህመድ (ዶ/ር) እና ደመቀ መኮንን በድጋሚ የኢህአዴግ ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ

    በፈረንጆቹ ጥቅምት 31 ቀን 2011 (ጥቅምት 21 ቀን 2011 ዓም) ዓም በጀርመን ሁለተኘዋ ከተማ ፍራንክፈርት ላይ መድርክ እንደሚዘጋጅ እና ጠቅላይ ሚኒትሩ በአውሮፓ የሚገኙ ኢትዮጵያዊንን አግኝተው እንደሚያነጋግሩም ታውቋል።

    ለዚሁ ፕሮግራምና የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አቀባበልን እስመልክቶ ከ80 ማህበራት የተውጣጡ አበላት ያሉት ኮሚቴ አየሰራ መሆኑንም ነው የተገለጸው።

    በጀርመን የኢትዮጵያ ቆንሰላ ጄኔራል ምህረት አብ ሙሉጌታ እንደገለጹት አሁን ላይ በኢትዮጵያ እየታየ ያለውን ለውጥ በመደገፍ 25 ሺህ ያህል ኢትዮጵያን ፍርንክፈረት ኮመርዝባክ አረና ስታዲየም (Commerzbank-Arena) በሚዘጃጀው ፕሮግራም ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

    ምንጭ፦ የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት

    ጀርመን

    Semonegna
    Keymaster

    በሺዎች የሚቆጠሩ ግለሰቦች አዲስ አበባ ላይ መታሰራቸው በተለይም ከሺሻ ቤቶችና ጫት ቤቶች መወሰዳቸው ጋር ተያይዞ ሺሻ ህገ-ወጥ ነው? ከሆነስ ግለሰቦቹ ወደ ፍርድ ቤት ለምን አልቀረቡም? ወደ ተሐድሶ ካምፕ ለምንድን ነው? የሚላኩት የሚሉ ክርክሮች መነሳት ጀምረዋል።

    አዲስ አበባ (ቢቢሲ አማርኛ)– ሰሞኑን በአዲስ አበባ በተከሰተው ቀውስ የሟቾች ቁጥር 28 መድረሱን ፖሊስ ገልጿል። ቀውሱንም ተከትሎ በአዲስ አበባ የተለያዩ መጠጥ ቤቶችን ጨምሮ የመዝናኛ ቦታዎች ወደ ሦስት ሺ ሁለት መቶ የሚሆኑ ሰዎች በጅምላ እንደታሰሩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት አምነስቲ አስታውቋል።

    ፖሊስ በበኩሉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልፆው መቶ ሰባ አራት ለፍርድ እንደሚቀርቡ እንዲሁም አንድ ሺ ሁለት መቶ አራት ሰዎችን ለማነፅና ለማስተማር በሚል ወደ ጦላይ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፕ ለተሐድሶ ስልጠና ተልከዋል።

    የአዲስ አበባ ፖሊስ ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር የሞከሩትን እንዳሰረ ቢገልፅም አምነስቲ (Amnesty International) በበኩሉ እስሩን አውግዞ በአሁኑ ሰዓት እየታዩ ያሉ ለውጦችን ወደ ኋላ የሚጎትት ነው ብሏል።

    በሺዎች የሚቆጠሩ ግለሰቦች አዲስ አበባ ላይ መታሰራቸው በተለይም ከሺሻ ቤቶችና ጫት ቤቶች መወሰዳቸው ጋር ተያይዞ ሺሻ ህገ-ወጥ ነው? ከሆነስ ግለሰቦቹ ወደ ፍርድ ቤት ለምን አልቀረቡም? ወደ ተሐድሶ ካምፕ ለምንድን ነው? የሚላኩት የሚሉ ክርክሮች መነሳት ጀምረዋል።

    ደኅንነታቸውና ያልተረጋገጠ የስፈተ ወሲብና ጸጉርን ለማሳድግ የሚረዱ እና የከንሰር መድኃኒቶች በህገወጥ መንገድ ሊገቡ ሲሉ ተያዙ

    የኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድሃኒት እና የጤና ክብካቤ አስተዳደር ባለስልጣን የትምባሆ ቁጥጥር መመሪያ መጋቢት ወር 2007 ዓ.ም ያወጣ ሲሆን፤ በመመሪያውም መሰረት የትምባሆ ምርቶች በማለት የሚዘረዝራቸው በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ከትምባሆ ቅጠል የተዘጋጁ በማጨስ፣ በመሳብ፣ በማኘክ፣ በማሽተት ወይም በሌላ መንገድ የሚወሰድ ማንኛውም ንጥረ ነገር ሆኖ የጋያ ወይም የሺሻ ትምባሆን፣ የኤሌክትሮኒክ ኒኮቲን ይጨምራል።

    የመመሪያው ዓላማም በዝርዝር የተቀመጠ ሲሆን ትምባሆን በመጠቀምና ለትምባሆ ጢስ በመጋለጥ በማህበረሰቡ ላይ የሚደርሰውን የጤና፣ የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና አካባቢያዊ ጉዳቶችን ለመከላከልና ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የፈረመማቻቸውን የትምባሆ ቁጥጥር ኮንቬንሽንም ለማስፈፀም ነው።

    መመሪያው ከባለስልጣኑ ፈቃድ ሳያገኝ የትምባሆ ምርትን ለንግድ ተግባር ወደ ሃገር ውስጥ ማስገባት፣ ማከፋፈል ወይም በጅምላ መሸጥ እንደማይቻል ያስቀመጠ ሲሆን፤ የትምባሆ ምርትን ማስተዋወቅና ስፖንሰር ማድረግ በፍፁም የተከለከለ እንደሆነ በግልፅ አስቀምጧል።

    በዚህም መሰረት ማጨስ የተከለከለባቸው ቦታዎች ተብለው የተቀመጡት፤ በህዝብ መጓጓዣዎች፣ በጤናና በትምህርት ተቋማት፣ በምግብ ቤቶች፣ በመዝናኛ ቦታዎች፣ በአውሮፕላን ማረፊያ፣ በፋብሪካዎችና በህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሾች ናቸው።

    ምንም እንኳን በነዚህ ቦታዎች ቢከለከልም ከትምህርት ተቋማት፣ ከመንግሥት መስሪያ ቤትና ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት አገልግሎት ከሚሰጡ ተቋማት ውጭ ለማጨስ የተከለለ ወይም የተሰየመ ክፍል ለብቻው የአየር ማናፈሻ (ventilation) የተገጠመለት ከሆነ በሌሎቹ ቦታዎች ማጨስ እንደሚቻል ተቀምጧል።

    በዩኒቨርስቲ፣ በኮሌጅና በሌሎች ተቋማት የተከለለ ክፍል ካለ ትምባሆንም ሆነ የትምባሆን ምርት መገልገል እንደሚቻልም መመሪያው ያትታል።

    ማንበብዎን ይቀጥሉ፦ በኢትዮጵያ ህግ ሺሻ ማጨስ ህገ- ወጥ ነውን?

    ሺሻ


    Semonegna
    Keymaster

    ለሶማሌ ክልል በድጎማ ከተመደበ በጀት ላይ ከ130 ሚሊዮን ብር በላይ በቀድሞ የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሐመድና በሌሎች ግለሰቦች መወሰዱን ጠቅሶ፣ ገንዘቡ እንዳይንቀሳቀስ ፖሊስ አሳገደ፡፡

    የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን በተለያዩ የምርመራ መዝገቦች ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት ባቀረበው ማመልከቻ፣ የክልሉ ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ አብዲ መሐመድ (አብዲ ኢሌ) እና የክልሉ ልዩ ኃይል ፖሊስ አዛዥ የነበሩት አቶ አብዱራህማን አብዱላሂን ጨምሮ፣ በ11 ሰዎች ለግል ጥቅም ተወስዷል ያለውን በአጠቃላይ 132.2 ሚሊዮን ብር እንዲታገድ ጠይቋል፡፡

    የተሻሻለውን የፀረ ሙስና ልዩ የሥነ ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 882/2007 አንቀጽ (8) በመተላለፍ የተፈጸመና የተጠቀሰውን ያህል የብር መጠን ያለው ጉዳት፣ በመንግሥት ላይ የደረሰ መሆኑን በማስረዳት ገንዘቡ እንዲታገድ ጠይቋል፡፡ ፍርድ ቤቱም የተጠቀሰው ገንዘብ ተለዋጭ ትዕዛዝ እስከሚሰጥ ድረስ እንዳይንቀሳቀስና ተጠብቆ እንዲቆይ፣ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክና ሌሎች ባንኮችም ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

    ማንበብዎን ይቀጥሉ፦ በቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንትና በሌሎች ግለሰቦች ተወስዷል የተባለ 130 ሚሊዮን ብር ታገደ

Viewing 10 results - 721 through 730 (of 730 total)