Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 15 results - 61 through 75 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    የአማራ ብልፅግና ፓርቲ መግለጫ

    አሸባሪው ህወሓት (ትህነግ) የአማራና የአፋር ክልል መሬቶች መውረሩንና በሀገር ላይ እያደረሰ ያለውን ሁለንተናዊ ጥፋትና ሽብር ተከትሎ፥ የአማራ ብልፅግና ፓርቲ የሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ይህንን ይመስላል።

    እምቢ ለባርነት፤ ክተት ለነጻነት!!
    የአማራ ብልፅግና ፓርቲ መግለጫ

    በሁሉም የክልላችን ዞኖች፣ በበርካታ ከተሞች እና ወረዳዎች የህልውና ዘመቻውን ተከትሎ እየተካሄዱ ያሉ መሠረታዊ የውትድርና ስልጠናዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። ሕዝባችን ህልውናውንና ኢትዮጵያን በደምና በአጥንቱ እንደሚጠብቅ የአባቶቹን ቃል-ኪዳን በማደስ ላይ ይገኛል። በዚህም የወገን ጦር ከፍተኛ መነቃቃት ሲያሳይ በአንጻሩ በቅርብም ሆነ በርቀት ያለው ጠላት በፍርሃት እየተናጠ ይገኛል። አሁን መላ የኢትዮጵያ ብሔር ብሄረሰቦች ለህልውናቸውና ለሉአላዊነታቸው ሲሉ ወታደር መሆን መርጠዋል። የዘመቻው ድጋፍ ይህን ሀቅ ያስረግጣል። በታሪክ ስናየው የኖረው እውነታ ኢትዮጵያ ሊቀብሯት የተነሱትን የውጭና የሀገር ውስጥ ፋሽስቶች ሁሉ በመቅበር ስታሳፍራቸው ኑሯለች።

    አሸባሪው ትህነግ፣ ከታሪክ የመማር አንዳች ፍላጎት የለውም። በለመደ የባንዳ ታሪኩ ከጀርባው የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶችን ተማምኖ ወክየዋለሁ የሚለውን ሕዝብ ጥይት ማብረጃ ማድረጉን ተያይዞታል። ለባዕድ ሥርዓት የመታመን ልማድ ያለውና የኢትዮጵያ ካንሰር የሆነው ትህነግ አማራን ሊያጠፋ፤ ኢትዮጵያን ሊበትን ቆርጦ መነሳቱን ተከትሎ በአጸፋው የኢትዮጵያ ብሔር ብሄረሰቦችን በቁጭት ስሜት ከዳር እስከ ዳር አነቃንቋል።

    በክልላችን የታወጀውን የክተት ጥሪ ተከትሎ የታየው አስደማሚ ሕዝባዊ ንቅናቄም ጥሪውን ተቀብሎ የመፋለም ጉዳይ “አማራን እና ኢትዮጵያን የመታደግ ጉዳይ ነው” በሚል እምነት ስለመሆኑ በተግባር እየተረጋገጠ ነው። በሁሉም የንቃናቄ መድረኮች የተሰማው ሕዝባዊ ድምጽ አንድና አንድ ነው። “ጦርነቱ የህልውናና ሀገር ማዳን ዘመቻ ነው” ፤ “በአሸባሪው ትህነግ መቃብር ላይ በጠንካራ ወንድማማችንት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እንገነባለን!” የሚል ነው።

    ምንም እንኳ አሸባሪው ትህነግ ዕድሜው ከ12 ዓመት ህፃን እስከ 70 ዓመት አዛውንት ሴት፣ ወንድ ሳይለይ ኢትዮጵያን ለመውጋት ያሰለፈና የተነሳ ቢሆንም፥ የዚህ ጦርነት ተደማሪ ግብ የትህነግ አስተሳሰብ ቁራኛ የሆነውን የትግራይ ሕዝብን ነጻ ማውጣትን ይጨምራል። በተለይም ኑሮውን በደሳሳ ጎጆ እየኖረ በድንጋይ ስር አፈር እየገፋ የሚኖረው ጭቁኑ የትግራይ አርሶ አደር፥ አሸባሪውን ትህነግ “ልጆቻችንን የት ጣላችኋቸው ?” ብሎ መጠየቅ የሚጀምርበት ጊዜ ሩቅ አይደለም።

    ጦርነት በባህሪው ከሚፈጥረው የኢኮኖሚ ድቀት በላይ ማኅበዊ ቀውሱ ተሻጋሪ ዕዳ እንደሚያመጣ ከትግራይ አርሶ አደሮች በላይ እውነታውን የሚረዳ የለም። ይህ ጦርነት በግብ የኢትዮጵያ ካንሰር የሆነውን ትህነግ ወደመቃብር ማውረድ ቢሆንም በውጤቱ የወላድ መካን የሆነችው የትግራይ እናትም ነጻ ትወጣበታለች። የኢትዮጵያ የግዛት አንድነት በመንደር ወንበዴዎችና ግልገል ሽብርተኞች አደጋ ላይ እንዲወድቅ የኢትዮጵያ ብሔር ብሄረሰቦች እንደማይፈቅዱ በተግባር እያሳዩ ይገኛል።

    የዚሁ ተግባራዊ ዐቢይ ምዕራፍ አካል የሆነው የክልላችን የህልውና ዘመቻ ዝግጅትና አፈጻጸም በስኬት መጓዙን ቀጥሏል። የክተት ጥሪውና የንቅናቄ መድረኩ ወደመሬት ስራ ወርዷል። የወቅቱ ተልዕኳችንም ከአደባባይ ንቅናቄ ወደግንባር መሰለፍ ሁኗል። የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ የልዩ ኃይል ምልመላዎች በመካሄድ ላይ ናቸው። አሁንም የነገ ባለአራት ኮከብ ጀኔራሎች የሚገኙት ዛሬ መከላከያ ሠራዊቱን በመቀላቀል ላይ ከሚገኙት ወጣቶች ነውና ምዝገባው ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል። በተመሳሳይ የአማራ ልዩ ኃይል በሰው ኃይል፣ በአደረጃጃት እና በወታደራዊ ዲሲፕሊን የማጠናከሩ እና የማዘመኑ ተልዕኮ የክተት ጥሪውን በተቀበሉ ጀኔራል መኮንኖቻችን በመካሄድ ላይ ነው። ከወታደራዊ መረጃ አኳያ ቁጥሩን በይፋ ለመግለጽ ባይቻልም የልዩ ኃይላችን፣ የሚሊሻችን በጥቅሉ የአማራ ሕዝባዊ ሠራዊታችን አቅም በፍጠነት እያደገ ነው። በተመሳሳይ ተልዕኮ በሁሉም ማዕከላት ተጠባባቂ ኃይል የማፍራት ስራው የህልውና አጀንዳው አካል ሁኗል።

    ይህም ሁኖ ሰብዓዊነቱን ክዶ ለመጣው ጠላት ከዚህም በላይ ዝግጅት ሊካሄድ ይገባል። ከአንድ ወር ወዲህ ያለውን የጠላት ዝግጅት ብንመለከት፡- በትግራይ በሁሉም ወረዳወች በብዙ ሽህዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ (conscription) ኮታ ተጥሎበታል። ይህ የፌዴራል መንግሥቱ የተናጠል የተኩስ አቁም ካወጀ በኋላ ትህነግ በአማራና አፋር ክልሎች ላይ የከፈተውን ወረራ ተከትሎ የተጣለ ግዳጅ ነው። ከዚህ ግዳጅ በፊት የነበረው ሰልጥኖ የታጠቀው ኃይል አብዛኛው ወደመቃብር የወረደ ሲሆን፤ ይህንኑ የሰው ኃይል ክፍተቱን ለመሙላት በዚህ ወር ብቻ በብዙ ሺህዎች የሚገመት የሳምንታት ስልጠና የወሰዱ ታዳጊዎችን ለወረራ አሰልፏል። ይህ ኃይል ከኢትዮጵያዊነት እሴት የራቀ በመሆኑ እንደአንበጣ በየደረሰበት ያገኘውን የሚወር፣ የሚዘርፍ፣ ሴቶችንና እናቶችን የሚደፍር፣ መሠረተ ልማቶችንም የሚያወድም በጥቅሉ ሰብዓዊነቱን የካደ፤ በአማራና በኢትዮጵያ ጥላቻ ያበደ በመሆኑ በፍጥነት ሊደመመስ ይገባል። እረፍትም ጊዜም ሊሰጠው አይገባም።

    ስለሆነም የህልውና ዘመቻው በጊዜ የለንም መንፈስ ተጠናክሮ ይቀጥላል። መሽቶ በነጋ ቁጥር አሸባሪው ኃይል ወደመቀመቅ የሚወርድበት ጉድጓድ ጥልቀት ይጨምራል። ጠላት በተግባርም ሆነ በአስተሳሰብ ሊቀበር ይገባል።

    ይህ የሽብር ቡድን በተመሳሳይ ሰዓት ከአማራም፣ ከአፋርም እንዲሁም ከጎረቤት ኤርትራ ጋር በአንድ ጊዜ ወደግጭት መግባት ያስፈለገው ግጭት ብቸኛ የዕድሜ ማስቀጠያው እንደሆነ በማመኑ ነው። ባለፉት ሠላሳ ዓመታት በተግባሩም ሆነ በአስተሳሰቡ ለኢትዮጵያ ካንሰር ስለመሆኑ በበቂ ሀገራዊ ኪሳራ ተገምግሟልና አሁን ላይ ለወረራ የተሰለፈባቸው የአማራና የአፋር መሬቶች የአሸባሪው ትሕነግ መቀበሪያ መሆናቸው ይቀጥላል።

    እምቢ ለባርነት፤ ክተት ለነጻነት!!
    የአማራ ብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት
    ሐምሌ 30 ቀን፥ 2013 ዓ.ም.
    ባህር ዳር፥ ኢትዮጵያ

    የአማራ ብልፅግና ፓርቲ መግለጫ

    Anonymous
    Inactive

    ወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከ6 ሺህ 8 መቶ በላይ ተማሪዎችን አስመረቁ
    “የግብርናውን ዘርፍ መዘመን ለምርታማነት መጎልበት የድርሻውን እያበረከተ ነው” – ወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ

    የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን እየተደረገ ያለው ጥረት ለምርታማነቱ መጎልበት የድርሻውን እያበረከተ እንደሚገኝ ወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ አስታወቀ። ኮሌጁ ከ3,200 በላይ ሰልጣኞችን ለ18ኛ ጊዜ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በደረጃ አራት ዲፕሎማ እሁድ ነሐሴ 2 ቀን፥ 2013 ዓ.ም. አስመርቋል። ምሩቃኑ በሰብል፣ በእንስሳት፣ በመስኖ እና በተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃ የሰለጠኑ ናቸው።

    በምርቃት መርሀ-ግብሩ ላይ የኮሌጁ ዲን ረዳት ፕሮፈሰር መርኪኔ መሰኔ ወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ ባለፉት 17 ዙሮች ከ19,700 በላይ ሰልጣኞችን ማስመረቁን አውስተው፥ ዘንድሮ ለምረቃ ከበቁት 3,226 ሰልጣኞች መካከል 1,327ቱ ሴቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።

    ኮሌጁ የእርሻ ሥራ አመራር በሳይንሳዊ ዘዴ በዘላቂነት እንዲቀጥል የሚያግዝ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር ሥራዎችን በ32 ሄክታር ማሳ ላይ እያከናወነ እንደሚገኝ ፕሮፈሰር መርኪኔ ጠቁመዋል። አክለውም ኮሌጁ በ43 ሚሊየን ብር 60 መምህራንን ማስተናገድ የሚችል የመኖሪያ ህንጻ ግንባታ እያካሄደ እንደሚገኝ የተናገሩት ዲኑ፥ ከ30 ሚሊየን ብር በሚበልጥ ገንዘብ የተለያዩ የካፒታል ፕሮጀክቶች ግንባታ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አመላክተዋል። ከ1.3 ሚሊየን ብር በሚበልጥ ገንዘብ የአካባቢውን ማኅበረሰብ ችግር የሚፈቱና የሥራ ዕድል ፈጠራን ማዕከል ያደረጉ የምርምር ሥራዎች መከናወናቸውንም ገልጸዋል።

    የኮሌጁ የአስተዳዳር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ዳምጠው ዳንኤል በበኩላቸው፥ በሀገራችን በግብርናው ዘርፍ እየተመዘገበ ካለው እድገት በስተጀርባ የግብርና ኮሌጅ ምሩቃን ሚና ጉልህ እንደነበር ተናግረው፥ እንቅስቃሴው ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

    ግብርና ከ80 በመቶ ለሚበልጠው የሀገራችን ሕዝብ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩ በተጓዳኝ ለኢንዱስትሪ መስፋፋት መሠረት መሆኑን የተናገሩት አቶ ዳንኤል፥ ኮሌጁ ለዘርፉ መዘመን እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ አርአያነት እንዳለው ጠቁመው፥ በዘርፉ ለላቀ ስኬት የላቀ ጥረት እንዲደረግ አስገንዝበዋል።

    ከተመራቂዎች መካከል በትምህርታቸው የላቀ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷቸዋል። ከምሩቃኑ መካከል አንዳንዶቹ በሰጡት አስተያየት በኮሌጁ ቆይታቸው ተገቢውን ዕውቀትና ክህሎት መጨበጣቸውን ተናግረው በቀጣይ ህብረተሰቡን በቅንነት ለማገልገል መዘጋጀታቸውን መጠቆማቸውን የወላይታ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ዘግቧል።

    በተያያዘ ዜና፥ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በዋናዉ ግቢ እና ዱራሜ ካምፓስ በመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ መረሃ ግብር ያስተማራቸውን ከ3,600 የሚበልጡ ተማሪዎችን ነሐሴ 1 እና 2 ቀን፥ 2013 ዓ.ም. አስመርቋል።

    ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ባስመረቀበት ወቅት በክብር እንግድነት የተገኙት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሙሉ ነጋ ባደረጉት ንግግር፥ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከድህነትና ኋላ ቀርነት ለመላቀቅ የሚደረገውን ሀገራዊ ጥረት ለማገዝ የጎላ ሚና አላቸው ብለዋል።

    ሀገሪቱ የምትገኝበትን ነባሪያዊ ሁኔታ የሚለውጥ ዕውቀትና ቴክኖሎጂ ከማስረጽ ባለፈ የዴሞክራሲ ማጎልበቻ፣ የአብሮነትና የመቻቻል እሴት የሚዳብርበት ተቋማት መሆናቸውን ጠቁመዋል። ሰላም ለሰው ልጆች መሠረታዊና አስፈላጊ መሆኑን ያመለከቱት ዶ/ር ሙሉ፥ ሀገርን ለማፍረስ የሚጥሩ አካላትን በመቆጣጠር ሕግ ለማስከበር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የበኩላቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አመልክተዋል።

    ምሩቃን ወደ ማኅበረሰባቸው በሚቀላቀሉበት ወቅት የሰላም፣ የአንድነት፣ የአብሮነትና የልማት ተምሳሌት በመሆን የቀሰሙትን ዕውቀት ሥራ ላይ አውለው ሕብረተሰቡን በታማኝነት እንዲያገለግሉ ጥሪ አቅርበዋል። እንደ ሀገር ላጋጠሙ ችግሮች የመፍተሄ አካል መሆን እንዳለባቸውም ዶ/ር ሙሉ አመልክተዋል።

    የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሀብታሙ አበበ በበኩላቸው፥ ተመራቂዎች የመረዳዳትና መተሳሳብ እሴቶችን በማስቀጠል ለሀገር ሰላምና እድገት መረጋገጥ የበኩላቸውን እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

    በዩኒቨርሲቲው የአካባቢ ሳይንስ (environmental science) ትምህርት ክፍል ከፍተኛ ነጥብ በማምጣት የዋንጫ ተሸላሚ የሆነው ተማሪ አበበ ታዘበ በሰጠው አስተያየት፥ ከተቋሙ ያገኘውን ዕውቀትና የአብሮነት እሴት አዳብሮ ለሚያገለግለው ማኅበረሰብ ለማዳረስ እንደሚጥር ተናግሯል።

    በተማረችበት የትምህርት መስክ ያገኘችውን ዕውቀትና ክህሎት በመጠቀም ማኅበረሰቡን በታማኝነትና በቅንነት ለማገልገል መዘጋጀቷን የገለጸችው ደግሞ ከሜዲካል ላብራቶሪ (medical laboratory) ትምህርት ክፍል በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀችው ሀውልተ መሐመድ ናት። በተቋሙ ቆይታዋ ያገኘችውን የተለያዩ የባህል እሴቶችን ሌሎች በማካፈል ለሀገራዊ ሰላምና እድገት የበኩሏን አስተዋጽኦ እንደምታደርግ ተናግራለች።

    ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ነሐሴ 1 ቀን ያስመረቃቸው ለዘጠነኛ ጊዜ በተለያየ የትምህርት ዘርፎ ያሰለጠናቸው ከ3,200 የሚበልጡ ተማሪዎችን ነው። የዩኒቨርሲቲው ዱራሜ ካምፓስ ደግሞ በተለያዩ መስኮች ያሰለጠናቸውን 434 የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን በነጋታው፥ ማለትም ነሐሴ 2 ቀን፥ 2013 ዓ.ም. አስመርቋል።

    የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ዱራሜ ካምፓስ በምክትል ማዕረግ የካምፓሱ አስተባባሪ የሆኑት ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶ/ር ዳዊት ለገሰ በምርቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክትና የካምፓሱን ዋና ዋና የተልኮ የሥራ አፈፃፀም ለምረቃ ታዳሚዎች በማቅረብ፥ ምሩቃን ወደ ሥራ ዓለም በሚገቡበት ወቅት ፀብና ጥላቻን የሚያባብሱ የሀይማኖት፣ የዘርና የቀለም ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተዉ ለሀገር አንድነትና ፍቅር ጠንክረዉ ዘብ እንዲቆሙና እንዲሠሩ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።

    ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ወቅት ከ30 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና ተከታታይ መርሀ-ግብሮች እያስተማረ እንደሚገኝ በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ተገልጿል።

    ሰሞነኛ በተለያዩ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች የተማሪዎች ምርቃት

    ወላይታ ሶዶ ግብርና ኮሌጅ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አስመረቁ

    Anonymous
    Inactive

    ለ2013 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ተመራቂዎች
    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ ያስተላለፉት መልዕክት

    የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ምሩቃንና ሥልጠና አጠናቃቂዎች፦

    ወቅቱ በሀገራችን የዘመን አቆጣጠር መሠረት የከፍተኛ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ምሩቃንንና ሰልጣኝ አጠናቃቂዎችን መርቀዉ ወደ ቀጣይ የሕይወት ምዕራፍ ሽግግር መልካም ምኞታቸዉን የሚገልጹበት ነዉ።

    ከተለያዩ የሀገራችን ከፍተኛ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት የዘመኑ ተመራቂዎችና የስልጠና አጠናቃቂዎች እንዲሁም ወላጆችና ቤተ-ዘመዶች፤ ደማቅ በሆነዉ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ወቅት ላይ ያላችሁ በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ እላለሁ።

    በተለይም የመጀመሪያ ዙር ለሆነላችሁ ምሩቃንና ሰልጣኞች፥ ይህ ወቅት የድካማችሁን ፍሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ያያችሁበት ወቅትና የላቀ ደስታ የሚሰማችሁ በመሆኑ፤ በድጋሚ ለዚህ ታላቅ ደስታና የሕይወት ምዕራፍ እንኳን አደረሳችሁ።

    በ2013 የትምህርትና ሥልጠና ዘመን በርካታ ፈታኝ ሁኔታዎችን በመቋቋም ምሩቃንንና ሥልጠና አጠናቃቂዎችን ለወቅቱ ደማቅ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት እያበቃችሁ ያላችሁ የሀገራችን የግልና የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት መምህራንና አሰልጣኞች፣ የትምህርትና ሥልጠና የሥራ መሪዎችና ባለሙያዎች፣ የተማሪዎች የምግብ ቤት፣ የክሊኒክና የግቢ ደህንነት ጥበቃ ሠራተኞች፣ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲዎችና ተቋማት አካባቢ ማኅበረሰብ የሰላምና የልማት አማካሪ ምክር ቤት አባላት በሙሉ፥ እናንተ በትብብር፣ በትስስርና በቅንጅት በመሥራት በኢትየዮጵያ ሰብዓዊ ካፒታል ዕድገትና ልማት ጉዞ የምታበረክቱት አስተዋጽኦ ዘመን ተሻጋሪ በመሆኑ ምስጋናችን እጅግ የላቀ መሆኑን ለመግለጽ እፈልጋለሁ።

    የሰዉን ልጅ በተለይም ወጣቱን በዕዉቀት፣ በክህሎትና በስብዕና በመቅረጽ ሂደት የምታኖሩት አሻራ የነገዋን ዕዉቀት-መር የኢትዮጵያን ማኅበረሰብ የመገንባት ጉዳይ ነዉ።

    ወድ ምሩቃንና ሰልጣኝ አጠናቃቂዎች፥ ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ በርካታ ፈተናዎችን እየተሻገረች ትገኛለች።

    ኢትዮጵያን ከጀግኖች አባቶቻችን እንዴት እንደተረከብን የታሪክ ምሁራንና አባቶቻችን አስተምረዉናል። በእዉነቱ ለማንም ያልተንበረከከች ሉዓላዊት ሀገር ነበረች፤ አሁንም ነች፤ እንደዚሁም ስለመቀጠሏ የምንወስነዉ እኛዉ የዘመኑ ባለቤቶችና ባለአደራዎች ነን። ዛሬ ላይ፥ ሉዓላዊነቷን ለመንጠቅ ከዉስጥና ከዉጭ በርካታ ኃይሎች እየተፈታተኗት ይገኛሉ፤ ድንበራችንን ከማለፍ ባሻገር እስከ ደጃፋችን ደርሰዉ ሊያጠቁን ይፈልጋሉ።

    ኢትዮጵያ በርካታ ተደጋጋሚ ፈተናዎችን የመሻገር ልምድ ያላት ሀገር መሆኗ ይታወቃል። ነገር ግን ፈተናዎቹ በሀገር ሉዓላዊነት ጉዳይ ሲደጋገም ተገቢነት የለዉም፤ ምክንያቱም የሁሉም ዜጋ የህልዉና ጉዳይ አደጋ ላይ በመሆኑና አባቶቻችን ያስረከቡንን ሉዓላዊነቷን ያረጋገጠችና በጽኑ መሠረት ላይ ያደረገች ሀገር ከትዉልድ ወደ ትዉልድ የማሻሻገር ኃላፊነት በአግባቡ የመወጣት ጉዳይ በመሆኑ ነዉ።

    ጀግናዉ መከላከያ ሠራዊታችንና አጠቃላይ መዋቅር ደጀን ከሆነዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በመተባበርና በመቀናጀት ሉዓላዊነቷን የሚፈታተነዉን ኃይል አደብ እንዲገዛ ማድረጉ ሩቅ አይሆንም። ሆኖም ግን የኢትዮጵያን ዘላቂ ሉዓላዊነት መገንባት ቀጣይ የቤት ሥራችን በመሆኑ፥ እናንተ ምሩቃንና ስለጠና አጠናቃቂዎች ሚናችሁን ልትወጡ ይገባል።

    ምሁራን፣ ምሩቃን፣ እና ሰልጣኞች፡-

    ዕዉቀት-መር ማኅበረሰብና ፖሊቲካል-ኢኮኖሚ መገንባት ለሀገራችን ኢትዮጵያ የሉዓላዊነት ግንባታና ዘላቂነት ቀዳሚ መሣሪያ ነዉ ብለን እናምናለን። በዕዉቀት፣ በክህሎትና በጥበብ የበቃ ማኅበረሰብና የበለጸገ ኢኮኖሚ መገንባት ተነጣጥሎ ሊታዩ አይገባም እንላለን። ይህ እዉነት ሊሆን የሚችለዉ ደግሞ ከመማርና ከመሰልጠን ባሻገር፥ ዕዉቀታችንን፤ ክህሎታችንና ጥበባችንን በተገቢዉ ለሀገራችን ዕድገትና ልማት ግብዓት አድርገን በመጠቀም ምጣኔ ይወሰናል።

    ጀግናዉ ሠራዊታችን የሀገራችንን ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ በተለያዩ ግንባሮች እየተዋደቀ ይገኛል።

    እናንተ የዕዉቀት መሣሪያ የያዛችሁ ደግሞ በሰለጠናችሁበት ሙያ በቅንነትና በታታሪነት ሀገራችንና ሕዝባችንን ያለቅድመ-ሁኔታ በታማኝነት ካገለገላችሁ፤ በኢኮኖሚዉ ግንባር ድጋፋችሁ የጎላ ይሆናል።

    ምሩቃን እና ሰልጣኞች፡-

    በሀገራችን አዲስ ምሩቅና ሰልጣኝ የመንግሥት ሥራ መያዝ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ መባልን ከስምና ዝና ጋር ያዛመደ ይመስላል። ሆኖም ግን እዉነቱ ከትምህርትና ሥልጠና በኋላ የተፈጠረዉን አቅም፣ ብቃትና ስብዕና እንደአንድ ካፒታል አካል በመቁጠር፥ ከሌሎች ተጓዳኝ የሀብት ምንጮች ጋር በማዳመር የተሻለ ሥራና ገቢ በሚያስገኙ መስኮች ያለብክነት መሰማራትን የሚያካትት መሆኑን መዘንጋት አያስፈልግም።

    አዳዲስ ምሩቃንና ሰልጣኞች፥ እስካሁን ያገኛችሁትን የዕዉቀትና የክህሎት አቅምና ብቃት በመጠቀም፥ የሥራ ዕድል ለመፍጠር፣ ሀብት ለማመንጨትና ባለጸጋ ለመሆን በርካታ አማራጮችን ኢትዮጵያ እየዘረጋች ነዉ። ይህን ለማየትና ለመገንዘብ የሚቻለዉ ከዚህ በኋላ የሚኖራችሁን የሕይወት ምዕራፍና አማራጭ መንገዶችን የመምረጥና የመወሰን አቅምና ብቃት ጊዜን ያማከለ ማድረግ ያስፈልጋል። ጊዜ እጅግ በጣም ዉድ ሀብት ነዉ፤ ከጊዜ ጋር አብሮ መጓዝ ያስፈልጋል።

    የተለመደዉን በ‘ሥራ አላገኘሁም’ እና በ‘ሥራ አልፈጠርኩም’ አባባሎች መካከል ያለዉን ሰፊ ልዩነት የሚሞላዉ ያካበታችሁት ዕዉቀትና ክህሎት ሊሆን ይገባል።

    ሀገራችን ኢትዮጵያ ወደ ዕዉቀት-መር ኢኮኖሚ እየገሰገሰች ትገኛለች። ይህ ደግሞ የዕዉቀትና የክህሎት ባለቤት የሆኑትን እንደእናንተ ዓይነት ዜጎችን በጽኑ ትፈልጋለች። ኢትዮጵያ መንገዷንም መዳረሻዋንም ለይታለች፤ ጉዞዋንም ጀምራለች። ዕዉቀት-መር ማኅበረሰብ ግንባታ ለፖሊቲካል ኢኮኖሚ ልህቀትና ዘላቂ የሀገር ሉዓላዊነት ወሳኝነቱ ሊረጋገጥ የሚችለዉ፤ ዕዉቀታቸሁና ክህሎታችሁ በተግባር ሲታይ ብቻ ነዉ።

    ዕዉቀት-መር ማኅበረሰብ መገንባት ለዕዉቀት-መር ፖሊቲካል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚኖረዉን ፋይዳ በአግባቡ ያለመገንዘብ የዋህነት ነዉ። የብዙ ታዳጊ ሀገሮች ዕድገታቸዉና ልማታቸዉ ዘገምተኛ ሆኖ ባለበት የሚሄደዉ፥ ምንም እንኳን ሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች ቢኖሩም፥ በዋናነት ግን ማኅበረሰባቸዉን የማንቃት ኃላፊነትን በአግባቡ ሳይወጡ ለረዥም ዘመናት ፖሊሲና ስትራቴጂ እንዲሁም የረዥምና አጭር ዘመን ዕቅድ ያለበቂና ብቁ ፈጻሚ ዝግጅትና ስምሪት ለማከናወን የሚታትሩ በመሆኑ ነዉ። ሀገራችንም ይህን ዓይነት አዙሪት ባለፉት በርካታ ዓመታት አስተናግዳለች።

    ስለሆነም፥ ዕዉቀት-መር ማኅበረሰብና ፖሊቲካል ኢኮኖሚን ነጣጥሎ ማየት፤ የሀገራትን ዕድገትና ልማት እንዲሁም ብልጽግና በእጅጉ እንደጎዳ የሀገራችንን ተጨባጭ ሁኔታ ማስታወሱ በቂ ይመስለኛል።

    ሰፊ መሬት፣ የወሃ ሀብት፣ የተመቻቸ የአየር ንብረት ያላት ኢትዮጵያ የዕፅዋትና የእንስሳት ልማት በዕዉቀት፣ በክህሎት፣ እና በጥበብ ያልመራች በመሆኗ፥ ፈጠራና ቴክኖሎጂ የመጠቀም ደረጃዋ ዝቅተኛ በመሆኑ፥ ምርትና ምርታማነትን ከተጨባጭ አቅም አንጻር በበቂ መጠን የማሳደግ ዕድል እስካሁን አጋጥሟት አያዉቅም። ለራሷ ዜጎች እንኳን በበቂ መጠን ምርት ማቅረብ አልቻለችም፤ እንደእኛ ድሃ የነበሩ ሀገራት ዛሬ ላይ የበለጸጉት እርሻቸዉንና ግብርናቸዉን በዕዉቀት፤ በፈጠራ፣ እና በቴክኖሎጂ በማዘመን ዜጎቻቸዉን ከመመገብ አልፈው ለዓለም ገበያ በአቅራቢነት እስከመምራት ደርሰዋል።

    የተፈጥሮ ሀብቶቻችንን ከተመለከትን፥ በደከመና የሰዉን ጉልበት በሚፈጅ ያረጀ ተክኖሎጂ በመጠቀም ወደምርት እንቀይራለን። ለምሳሌ ያህል፥ ደኖቻችንን ተጠቅመን የቤትና የቢሮ ቁሳቁስ እንኳን በጥራት ለማቅረብ ባለመቻል በገቢ ገበያ አቅርቦት ተወስነናል። ጥጥ እና ቆዳ አምራች ሀገር ሆነን ሳለ፥ የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን አብዛኛዉን ግብዓት ከዉጭ የሚያስገቡ በመሆኑ በኋልዮሽ ትስስርና በእሴት ሰንሰለት የሀገራችን ተጠቃሚነት ምጣኔ በሚፈለገዉ ደረጃ ላይ አይደለም። የማዕድናት ሀብት ልማታችን ከፍተኛ ካፒታልና ዕዉቀት የሚፈለገዉን ለጊዜዉ በሌሎች አማራጮች ማየቱ አግባብ ቢሆንም፥ በአነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ደረጃ በበርካታ ወጣት ምሩቃንና ሰልጣኞች ሊለሙ የሚችሉ ማዕድናትን እሴት ከመጨመር ይልቅ በጥሬዉ በማቅረብና መጠነኛ ገቢ በማግኘት ላይ የተወሰነ ሆኖ ዘልቋል። ለዚህም፤ ዋናዉ የመፍትሄ አካል መሆን የሚችለዉ በተለዩ አዋጭ አማራጮች ተግባር-ተኮር የክህሎት ሥልጠና ማበራከትና መጠነኛ መነሻ ካፒታል ማቅረብ ነዉ።

    እንደእኛ ባሉ በአብዛኛዉ የሕዝብ ድርሻ በወጣቱ በሚወከልበት ኢኮኖሚ፥ በመረጃ እና ግንኙነት ቴክኖሎጂ (ICT) መስክ ለዜጎች የሚፈጠረዉ የሥራ ዕድል በየዓመቱ በርካታ ቢሆንም፥ የክህሎት ልማታችን በሚፈለገዉ የተግባር ስልጠና ሳይሆን በንድፈ-ሀሳብ የታጨቀ በመሆኑ በሀገር ዉስጥና ከሀገር ዉጭ ባሉ የሥራ ዕድሎች ያለንን ተሳትፎ ዝቅተኛ አድርጓል።

    የመንግሥት የትኩረት አቅጣጫ ሆኖ የዘለቀዉና በርካታ መልካም ዕድሎች ያሉት፣ የምርት ኢንዱስትሪ ዘርፍ (manufacturing) ዘርፍ የዉጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትና የሀገር ዉስጥ ተዋናዮች እየተበራከቱ ቢመጡም፥ በተሻለ ዋጋ የሠራተኛ ዕዉቀትና ክህሎት ለመጠቀም ባቀዱት ልክ ምርታማ ሆኖ ያለማግኘት፣ ኢንዱስትሪዎችም በተቻለ ፍጥነት እንዳያድጉ እንቅፋት ሆኖ እንደቆየ የሚያመላክቱ መረጃዎች አሉ።

    በሌላ በኩል ደግሞ ምርታማና ትርፋማ የሆነ ኢንዱስትሪ እስካልተፈጠረ ድረስ ዕዉቀትና ክህሎት አቅራቢዉ ሠራተኛና ባለሙያ በበቂ መጠን ሊከፈለዉ አይችልም።

    በኢንዱስትሪዎቹ መቋቋም ዘርፈ-ብዙ ጥቅሞች ያሉ ቢሆንም፥ ከሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ከግብዓት እስከ ምርት ድረስ ባለዉ የእሴት ሰንሰለት ሀገራዊ ተሳትፏችን እጅግ አናሳ በመሆኑ፥ ሥራና ሀብት የመፍጠር ዉጤታማነታችን ደካማ ሆኖ እናገኘዋለን። ለዚህም በእያንዳንዱ አምራች ኢንዱስትሪ የእሴት ሰንሰለት በሀገር ዉስጥ አቅም ሊቀርብ የሚገባ ግብዓት፣ ሊፈጠር የሚገባ የሥራ ዕድልና ካፒታል እንዲሁም ሊተካ የሚገባ የገቢ ገበያ አቅርቦት ዕዉቀት-መር ነዉ ማለት አይቻለም። ይህን ጉድለት ማረም እንደእናንተ ላሉ የዕዉቀት፤ የክሎት፣ እና የጥበብ ባለጸጋዎች ሌላ መልካም አጋጣሚ ይፈጥራልና ጥረታችሁንና ትጋታችሁን ልታክሉበት ይገባል እላለሁ።

    የሀገራችን የቱሪዝም ልማት ዘርፈ-ብዙ አማራጮች ያሉት በመሆኑ፥ ብዙ ጀማሪ ምሩቃንና ሰልጣኞች ሊሳተፉበት የሚገባ ምቹ ዘርፍ ነዉ። ለዚህም የቋንቋ ችሎታን የማሻሻል፣ የዲጂታል አሠራር ሥርዓትን የመፍጠር፣ አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎችን መረጃ በማልማትና በማዘመን፣ አለፍ ብሎም በትብብርና በትስስር መጠነኛ ልማት በማከናወን የቱሪዝም ግብይት ተዋናይ መሆን፣ ከብዙ በጥቂቱ እንደዕድሎች ሊታዩት ይገባል።

    በመሆኑም፥ ዉድ ምሩቃንና ሰልጣኞች፡-

    ወደዕዉቀት-መር ማኅበረሰብና ፖሊቲካል-ኢኮኖሚ እየገሰገሰች ያለች ኢትዮጵያ እንደእናንተ ያሉ የዕዉቀት፤ የክህሎት፣ እና የጥበብ አርበኞችን በእጅጉ ትሻለች። በተለይም የኢትጵያንና የሕዝባችንን አንድነት በማጠናከር፣ ሉዓላዊነታችንን በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚያስፈልገዉን ጠንካራና የማይበገር ፖሊቲካል-ኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት ለማፋጠን ሚናችሁ እጅግ የላቀ በመሆኑ፥ በትጋት እንድትሠሩ አደራ እላለሁ።

    በመጨረሻም፥ የምሩቃንና የሰልጣኝ ጥራት ባለቤቶች መምህራንና አሰልጣኞች በመሆናቸዉ፥ በ2013 ትምህርትና ሥልጠና ዘመን የላቀ ምርምርና የማስተማር ሥራችሁን በማበርከታችሁ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ያገኛችሁት ምሁራን፥ እናንተም የልፋታችሁን ፍሬ በማግኘታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ እያልኩ፥ በተገኘዉ ተጨማሪ ድልና አቅም ኢትዮጵያን በተሻለ መነሳሳት እንድታገለግሉ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

    በዕዉቀት፣ ክህሎት፣ እና ስብዕና የተገነባ ዜጋ በማፍራት፥ ወደዕዉቀት-መር ማኅበረሰብና ወደማይበገር ፖሊቲካል-ኢኮኖሚ በሚደረግ ሽግግር ድርሻችንን የጎላ እናድርግ!

    ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ
    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር

    ሰሞነኛ በተለያዩ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች የተማሪዎች ምርቃት

    ለከፍተኛ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ተመራቂዎች ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ ያስተላለፉት መልዕክት

    Anonymous
    Inactive

    የጅማ እና ዲላ ዩኒቨርሲቲዎች ከ7,390 በላይ ተማሪዎችን አስመረቁ

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ፣ በማታውና በተከታታይ የትምህርት መርሀግብሮች ያሰለጠናቸውን 3,926 ተማሪዎች በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ነሐሴ 1 ቀን፥ 2013 ዓ.ም. አስመርቋል።

    በምርቃ ሥነ-ሥርዓቱ የተገኙት የዕለቱ የክብር እንግዳ የኢፌዲሪ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል ባስተላለፉት መልዕክት፥ ከሀይማኖትና ብሔር ልዩነት ባለፈ ተዋድደንና ተፈቃቅረን እንደኖርነው ሁሉ፣ አሁንም በአንድነት እጅ ለእጅ ተያይዘን የሀገራችንን ብልጽግና እናረጋግጣለን ብለዋል።

    የኢፌዲሪ የጤና ሚኒስትር ዴኤታና የጅማ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በበኩላቸው፥ በቀጣይ ዩኒቨርሲቲውን የላቀ የምርምር ማዕከል ለማድረግ የሥራ አመራር ቦርዱ ተግቶ ይሠራል ብለዋል።

    የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ጀማል አባፊጣ ባደረጉት ንግግር፥ ከከፍተኛ ትምህርት ተልዕኮዎች መካከል የመጀመሪያው ጥራት ያለው ትምህርት በመስጠት በእውቀት፣ በክህሎት እና በሥነ-ምግባር የዳበረና ሀገር ተረካቢ ዜጋ ማፍራት ነው። ግቡም ተመራቂው ባካበተው የቴክኖሎጂ አቅም ራሱን አብቅቶ ሀገርንና ወገንን መቀየር ሲሆን፥ ጅማ ዩኒቨርሲቲም ይህንኑ ዓላማ እውን ለማድረግ ተግቶ በመሥራት ላይ ይገኛል ብለዋል። ለዚህም ምስክሩ በምርምርና ተቋማዊ አመራር የላቀ ውጤት ማስመዝገቡ ነው በማለት አክልዋል።

    በዕለቱ ከተመረቁት ተማሪዎች መካከል በቅድመ ምረቃ 2,260 ወንድ ሲሆኑ፣ 1234 ሴቶች ተመራቂዎች ናቸው።

    በድኅረ ምረቃ መርሀ ግብር ከተመረቁት 402 ተማሪዎች ውስጥ 318 ወንዶች ሲሆኑ፣ 85 ሴቶች ናቸው፡፡ ከድኅረ ምረቃ መርሀ ግበሩ 18 የሦስተኛ ዲግሪ (ፒ ኤችዲ) ምሩቃን ሲሆኑ፣ በጅማ ዩኒቨርሲቲ ታሪክ ከፍተኛው የሦስተኛ ዲግሪ መርሀግብር ተማሪዎች የተመረቁበት ነው። የሦስተኛ ዲግሪ ተማራቂዎቹ ከሒሳብ፣ ከጤና ግንኙነት (health communication)፣ እና ከኢንፎርሜሽን ሳይንስ ትምህርት ክፍሎች ናቸው።

    በተጨማሪም ጅማ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ መርሀግብር በሶፍትዌር ኢንጅነሪንግና በቪዥዋል አርት (ሥነ-ስዕል) የሰለጠኑ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ግዜ አስመርቋል።

    ከተማሪዎች ምርቃት ጋር በተያያዘ ዜና፥፥ ዲላ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛና በሁለተኛ ዲግር እንዲሁም በተከታታይ መርሀግብር ያሰለጠናቸውን ከ3,450 በላይ ተማሪዎችን እሁድ ነሐሴ 2 ቀን፥ 2013 ዓ.ም. አስመርቋል።

    ዩኒቨርሲቲው ያስመረቃቸው ተማሪዎች 2,101 ወንድና 983 ሴት በድምሩ 3,084 ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ፤ 317 ወንድና 72 ሴት በድምሩ 384 ተማሪዎችን በሁለተኛ ዲግሪ፤ በአጠቃላይ 3,468 ተማሪዎችን በዕለቱ አስመርቋል።

    የዘንድሮው የዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምርቃት ለ23ተኛ ጊዜ የተከናወነ ሲሆን፥ ከተመሠረተበት ከ1989 ዓ.ም. ጀምሮ እስካሁን ድረስ ከ71,475 በላይ ተማሪዎችን አሰልጥኖ ለሀገር ኢኮኖሚ የበኩሉን አስተዋጽኦ አበርክቷል። በአሁኑ ወቃትም ከ26ሺህ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎችን በመደበኛ እና በተከታታይ የትምህርት መርሀግብሮች እያሰለጠነ  ይገኛል።

    ዩኒቨርሲቲው በዋናው ግቢው ያከናወነው የተማሪዎች ምርቃት ሥነ-ሥርዓት በፋና ቴሌቪዥን በቀጥታ እንደተተላለፈ የዩኒቨርሲቲው የሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ዘግቧል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የጅማ እና ዲላ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን አስመረቁ

    Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በኢትዮጵያ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የልጆች የሳይንስ ማዕከል አስመረቀ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በኢትዮጵያ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የልጆች የሳይንስ ማዕከል አስመርቋል። አካዳሚዉ ከጀርመን የባህል ተቋም በኢትዮጵያ (Goethe-Institut Ethiopia) እና ጀርመን ሀገር ከሚገኘው ፌኖሜንታ ሳይንስ ማዕከል (Phänomenta e.V. Science Center) ጋር በመተባበር ማቋቋሙም ተገልጿል።

    በማዕከሉ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተዉ ንግግር ያደረጉት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሴቶችና ሕፃናትና ወጣቶች ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ የኢትዮጵያ መንግሥት ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ልማት በሰጠው ልዩ ትኩረት በርካታ ተስፋ ሰጪ ውጤቶችን ማስመዝገብ መቻሉን አብራርተዋል።

    የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ይህንኑ በማጠናከር የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑትን ሕፃናት በሳይንስና ቴክኖሎጂ እውቀት ተኮትኩተው እንዲያድጉና ለሀገራቸዉ ሁሉ አቀፍ ልማትና ብልጽግና ጉልህ ሚና እንዲጫወቱ በሀገራችን በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የልጆች የሳይንስ ማዕከል ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት ማቋቋሙ የሚበረታታ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።

    የሳይንስ አካዳሚዉ ፕሬዚደንት ፕሮፌሰር ፅጌ ገብረማርያም ባደርጉት ንግግር፥ አካዳሚው የሳይንስ ዕውቀትንና ባሕልን ለማሳደግ እንዲሁም ሕፃናት በተመቻቹ የቴክኖሎጂ ቁሳቁሶች እየተዝናኑ ስለሳይንስና ቴክኖሎጂ ፅንሰ-ሐሳብና አሠራር ዕውቀት እንዲያገኙና ለዘርፉ ያላቸው ዝንባሌ እንዲያድግ ታቅዶ መቋቋሙን አብራርተዋል።

    አካዳሚዉ በዋናነት የሳይንስ ዕውቀትንና ባሕልን የማሳደግና የማስፋፋት፤ እንዲሁም ለመንግሥትና ለሌሎች ባለድርሻ አካላት በማስረጃ ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ምክር የመስጠት ዓበይት ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸዉን ተግባራትን በማከናወን ላይ እንደሆነም ገልጸዋል።

    የማዕከሉ ግንባታ ከተጀመረ በ3 ዓመት የተጠናቀቀ ሲሆን፥ ለግንባታው የጀርመን ባህል ማዕከል 1.5 ሚሊዮን ብር፣ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ መንግሥት የሳይንስ ዘርፍን ለማጠናከር ከሰጠው 40 ሚሊዮን ብር 7.3 ሚሊዮን እና የጀርመኑ ፌኖሜንታ የሳይንስ ማዕከል 7 ሚሊዮን ብር ወጪ ተገንብቶ ለአገልግሎት መብቃቱን ገልጸዋል።

    ፕሮፌሰር ፅጌ አያይዘዉ አገራችን ወቅቱ በሚፈልገው የእድገት አቅጣጫና ፍጥነት እንድትጓዝ ለማድረግ የሳይንስ እውቀት ማበልፀጊያ ተቋማት ግንባታ የሳይንስ ማህበረሰብ ምስረታና የአገር በቀል እውቀት አጣምሮ መስራት እንዳለበት ገልጸዉ ለዚህ አላማ ስኬት የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የጀርመን የባህል ተቋም እና ጀርመን ሀገር የሚገኘው ፌኖሜንታ ሳይንስ ማዕከል ላደረጉት ቴክኒካዊና ፋይናንስ ድጋፍ በራሳቸውና በአካዳሚው ሥም ምስጋና አቅርበዋል።

    የጀርመን የባህል ተቋም እና ጀርመን ሀገር የሚገኘው ፌኖሜንታ ሳይንስ ማዕከልን ወክለዉ በምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ንግግር ያደረጉ ተወካዮቻቸዉ በተለያየ የእድሜ ደረጃና የትምህርት እርከን ላይ የሚገኙ የማኀረሰቡን አካላት ግንዛቤ ለማሳደግና የሳይንስ እውቀትን ለማስረፅ ማዕከሉ ጉልህ ሚና እንደሚኖረዉ ገልጸዋል።

    የሳይንስ አካዳሚው ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፕሮፌሰር ተከተል ዮሐንስ ባስተላለፉት መልእክት የበርካታ አገር በቀል እውቀቶች፣ የጥንታዊ ታሪክ ቅርሶችና የተፈጥሮ ጸጋ ባለቤቶች በመሆናችን እነዚህን በሳይንሳዊ መንገዶች በማዘመን ለህብረተሰባችን ህይወት መሻሻል የጀመርናቸዉን ዉጥን ተግባራት ከግብ ለማድረስ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ብርቱ ርብርብ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ

    የልጆች የሳይንስ ማዕከል

    Anonymous
    Inactive

    በሀገር አንድነት እና ሰላም ላይ የተደቀነውን አደጋ የመመከት ኃላፊነት በዋነኛነት የፌደራል መንግሥቱ ነው!
    ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የተሰጠ መግለጫ

    መንግሥት በትግራይ ያለው ግጭት ቆሞ ለሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ የተሻለ ሁኔታ ለመፍጠር እና ሌሎች ምክንያቶችን ጠቅሶ የተናጥል ተኩስ አቁም ማወጁን ተከትሎ ሰኔ 26 ቀን 2013 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ባወጣው የ‘ቢሆንስ’ ትንተና ሊሆን ይችላል ብለን ያስቀመጥነው ሁለተኛው ቢሆንስ (scenario) መንግሥት በትግራይ ክልል የተናጠል ተኩስ አቁም ካወጀ በኋላ የትግራይ አማጺዎች ግጭቱን ለማስፋት የሚያደርጉት ሙከራ ቀጥሎ ግልፅ አሸናፊ የማይኖርበት ሁኔታ ይከሰታል የሚል ነበር። ይህም ከቀጠለ በክልሉ ሕግና ሥርዓትን ማስከበር አዳጋች መሆኑ የሚፈጥረውን አጋጣሚ በመጠቀም ዘረፋዎች ሊበራከቱ እንደሚችሉ፣ የዕለት እርዳታ የሚያስፈልጋቸው የክልሉ ነዋሪዎች በሚፈለገው ደረጃ እርዳታ ሳያገኙ ቀርተው ለከፍተኛ አደጋ ሊጋለጡ እንደሚችሉ፣ መሰረታዊ ለኑሮ የሚያስፈልጉ አገልግሎቶች እና ግብዓቶች (የውሃ፣ የመብራት፣ ህክምና) ማግኘት የማይቻልበት ሁኔታ ሊፈጠር የሚችልበት ዕድል ከፍተኛ በመሆኑ የክልሉ ሕዝብ ለከፍተኛ ችግር የሚጋለጥበት ሁኔታ ሊበራክት እና ለረጅም ጊዜ ምንም ዓይነት አስተዳደራዊ አገልግሎት ሊያገኝ የማይችልበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል እና የዚህ ዓይነት የማያቋርጥ ግጭት ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ብዙ ችግሮችን ስቦ በማምጣት (ኢንቬስትመንት ይቀንሳል፤ ቱሪዝም ይቀንሳል፤ በዚህም የሥራ አጥ ቁጥር ይጨምራል) በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎችም አለመረጋጋትን ሊያስከትል ይችላል የሚል ትንተና አስቀምጠን ነበር። በትንተናችን ውስጥ ይህ ቢሆንስ (scenario) የመሆን ዕድሉ ከሌሎቹ የበለጠ መሆኑን ጠቅሰን በክልሉና ባጠቃላይ በሀገራችን ከብሔር ፖለቲካ ጋር ተያይዞ የመጣውን አደጋ በዘላቂነት የማይፈታ፣ ሀገሪቱን ቀስ እያለ ውስጧን እንደሚበላ በሽታ ከመግደሉ በፊት መፍትሄ የሚፈልግ እንደሆነ ገልፀን ነበር። በተጨማሪም በዚህ ሁኔታ ውስጥ መረጋጋትን ማስፈን ስለማይቻል የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ወደ ከፍተኛ ግጭት ማምራቱ እንደማይቀር በትንታኔያችን ውስጥ አስቀምጠን ነበር።

    የፌደራል መንግሥቱ የተናጠል ተኩስ አቁም አውጆ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት በይዞታው ስር የነበሩ ቦታዎችን ለቆ ከወጣ በኋላ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ያስተዋልነው እንቅስቃሴ በቢሆንስ (scenario) ትንተናችን ውስጥ ከሁሉም የተሻለ የመከሰት ዕድል አለው ብለን ያስቀመጥነው ሁለተኛው ቢሆንስ (scenario) እውን እየሆነ እንደሆነ የሚያመላክት ነው።

    በእርግጥ ከላይ በጠቀስነው ትንተናችን ውስጥ ህወሓት የሚያደርሳቸውን ትንኮሳዎች በኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት እየተመከቱ እና እየከሸፉ ሊሄዱ ይችላሉ የሚል ግምታችንን ብናስቀምጥም በተግባር ያየነው ግን የፌደራል መንግሥት ህወሓት ግጭቱን ለመቀጠል የወሰዳቸውን እርምጃዎች በግንባር ቀደምነት አመራር እየሰጠ ለማክሸፍ ከመሞከር ይልቅ ግጭቱን በክልሎች መካከል ያለ ግጭት እስኪመስል የወሰደው ግልፅ ያልሆነ አቋም እጅግ አስደንጋጭ ሆኖ አግኝተነዋል።

    ከዚህም በላይ ግጭቱን በተመለከተ በፌደራል መንግሥቱ በኩል የሚወሰዱ እርምጃዎች የተጣደፉ እና በቅጡ ያልታሰበባቸው መምሰላቸው በአጭር ጊዜ ከህወሓት የተደቀነውን አደጋ በማንኛውም መንገድ ከማክሸፍ ባለፈ እርምጃዎቹ ለሀገራችን ሰላም እና አንድነት በዘላቂነት የሚኖራቸውን አንድምታን ያልገመገሙ ስለመሆናቸው አመላካች ሆነው አግኝተናቸዋል።

    መንግሥት የሚወስዳቸው እርምጃዎችን በተመለከተ ጊዜውን የጠበቀ እና ትክክለኛ መረጃ ለሕዝብ ባለማድረሱ በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ መደናገጥ ከመፍጠሩም ባለፈ በመንግሥት ላይ ያለው እምነት እንዲሸረሸር ምክንያት ሆኗል። በተጨማሪም ህወሓት ያደረሳቸውን ወንጀሎች እና የሚፈጽማቸውን ኢሰብዓዊ ድርጊቶች ከተራ ክስ ባለፈ በተጨባጭ ማስረጃዎች አስደግፎ ለዜጎች እና ለዓለምአቀፉ ማኅበረሰብ እንዲደርስ ማድረግ ላይ ከፍተኛ ክፍተት እየተስተዋለ ይገኛል። እነዚህ ክፍተቶች በጊዜ መፍትሄ ካልተበጀላቸው ችግሩን የበለጠ እያባባሱት እንደሚሄዱ እናምናለን።

    መንግሥት በተጨባጭ ማስረጃዎች ላይ ተመስርቶ ለህወሓት የሚደረግ ማንኛውንም ዓይነት ድጋፍ ለማስቆም እና ተጠያቂነትን ለማስፈን ያለበትን ኃላፊነት ሙሉ በሙሉ የምንደግፍ ቢሆንም በሌሎች የሀገራችን አካባቢዎች ህወሓትን ትደግፋላችሁ በሚል ምክንያት የሚወሰዱ እርምጃዎች ማስረጃ ላይ የተመሰረቱ ከመሆን ይልቅ እንዲሁ በጅምላ የሚወሰዱ መሆናቸው የዜጎችን ሰብዓዊ መብት የሚጋፉ እና በትግራይ ያለውን ችግር የበለጠ የሚያወሳስቡ ድርጊቶች ናቸው። ለአብነት በአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ብቻ በተመሳሳይ ወቅት ቢያንስ 60 የንግድ ተቋማት/ሱቆች ከግጭቱ ጋር በተያያዙ ምክንያቶች ታሽገው ላለፉት ሁለት ሳምንታት ተዘግተው ቆይተዋል። ከግጭቱ ጋር በተያያዘ ሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚደርስ እንግልት፣ ከሕግ አግባብ ውጪ የሆነ እስር እና ጥቃት በአፋጣኝ መቆም እንደሚገባው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ሐምሌ 8 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መጠየቁ ይታወሳል።

    ከላይ የተጠቀሱትን መሰረት በማድረግ የሚከተሉት ምክረ ሀሳቦች ተግባራዊ እንዲደረጉ እንጠይቃለን፥

    1. በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች የሚገኙ የፀጥታ አስከባሪዎች ህወሓት የደቀነው አደጋን ለማክሸፍ እያደረጉ ያሉትን መረባረብ በከፍተኛ አክብሮት እናደንቃለን። ህወሓት የፌደራል መንግሥቱን በበላይነት ይቆጣጠር በነበረበት ጊዜ ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊያን ላይ በሙሉ ግፍ ሲፈጽም እንደነበረ ሁሉ አሁንም የደቀነው አደጋ በሀገር አንድነት እና ሰላም ላይ እንጂ በአንድ ወይንም በጥቂት ክልሎች ላይ ብቻ ያነጣጠረ እንዳልሆነ በመረዳት አደጋውን ለመከላከል የሚወሰደው እርምጃ አንድ ወጥ የዕዝ ሰንሰለት ኖሮት በፌደራል መንግሥት እና በኢፌደሪ መከላከያ ሠራዊት አመራር ሰጪነት ብቻ እንዲወሰድ፤
    2. በትግራይ ክልል ያለውን ችግር አሁን ከፊታችን ህወሓት ከደቀነው አደጋ እንፃር ብቻ በማየት ህወሓትን ማሸነፍን ብቻ ዓላማ ያደረገ የአጭር ጊዜ ስልት ይዞ ከመንቀሳቀስ ባለፈ በዘላቂነት ክልሉ ወደተረጋጋ ሰላም እና ዜጎች ወደ መደበኛ ሕይወታቸው ሊመለሱ የሚችሉበት እንዲሁም ግጭቱ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ተቋጭቶ የሀገር ህልውና እና አንድነትን በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚቻልበት ስልት የአካባቢውን ተወላጆች በማሳተፍ እንዲነደፍ እና ተግባራዊ እንዲደረግ፤
    3. አሁን ያለው ግጭት ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲያበቃ እና ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ በትግራይ ክልልም ሆነ በሌሎች የሀገራችን አካባቢዎች የምትገኙ የሀገር ሽማግሌዎች እና ሌሎች ልሂቃን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ የምታስፈልጉበት ወቅት ላይ መሆናችሁን ተረድታችሁ የሚጠበቅባችሁን ኃላፊነት እንድትወጡ፤
    4. የሰብዓዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ድጋፍ እንዲደርሳቸው የሚደረገው ጥረት አሁን ከምን ጊዜውም በላይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና መንግሥት የሰብዓዊ እርዳታ በክልሉ ለሚኖሩ ዜጎች እንዲዳረስ የሚያደርገውን ጥረት በግልፅ እንዲያሳውቅ፤ እንዲሁም በዚህ ተግባር የሚሳተፉ የሰብዓዊ ድርጅቶች በግልፅነት እንዲንቀሳቀሱ ተገቢው ክትትል እንዲደረግ፤
    5. የተለመዱ መንግሥትን የሚያሞግሱ የፕሮፖጋንዳ ሥራዎችን እየደጋገሙ ሕዝብን ከማሰልቸት ይልቅ መንግሥት የወሰዳቸውን እርምጃዎች በተመለከተ ትክክለኛ እና ወቅታዊ መረጃ ለሕዝብ እንዲደርስ እንዲደረግ እና ህወሓት የሚፈፅማቸውን ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶች እና ታዳጊዎችን በወታደርነት መመልመል እና በጦርነት ማሳተፍን የመሳሰሉ ወንጀሎችን በተገቢው ፍጥነት በተጨባጭ ማስረጃዎች እያስደገፉ ይፋ የማድረግ ሥራ ተገቢውን ትኩረት ተሰጥቶት እንዲሠራ፤
    6. ዜጎች ለህወሓት የሚደረግ ማንኛውም የሞራልም ሆነ ቁሳዊ ድጋፍ በሕዝብ ሠላም፣ በሀገር ደህንነት እና ሕይወቱን ለመሰዋዕትነት አዘጋጅቶ በተሰለፈው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ላይ የሚደረግ ክህደት መሆኑን በመረዳት ከተመሳሳይ ድርጊቶች እንዲታቀቡ፤
    7. ህወሓትን ደግፋቹኻል በሚል በጅምላ የሚወሰዱ እርምጃዎች ባስቸኳይ እንዲቆሙ እና እስካሁንም በዚህ መልኩ የተወሰዱ እርምጃዎች አፋጣኝ ማጣራት ተደርጎ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ እንዲሁም አሁን ያለውን ሁኔታ እንደ አጋጣሚ በመጠቀም የግል ጥቅም ለማግኘት ዜጎች ላይ እንግልት የሚፈፅሙ የመንግሥት እና የፀጥታ ሠራተኞች ላይ አስፈላጊው ማጣራት በአስቸኳይ ተደርጎ የማያዳግም ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ፤

    በመጨረሻም የሀገራችን ሰላም እና አንድነት በዘላቂነት ተረጋግጦ የሁሉም ዜጎች መብት እኩል የሚከበርበት እና እኩል ዕድል የሚሰጥበት እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ሁላችንም የምንችለውን ሁሉ የምናዋጣበት አሳሳቢ ወቅት ላይ እንዳለን እያስታወስን ሁላችንም ኃላፊነታችንን ከምር ወስደን እንድንወጣ እናሳስባለን።

    ሐምሌ 10 ቀን 2013 ዓ.ም.
    አዲስ አበባ፥ ኢትዮጵያ

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ

    የፌደራል መንግሥቱ

    Anonymous
    Inactive

    የኢፌዴሪ ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር በ2013 በጀት ዓመት በባህል ኢንዱስትሪ ልማት ዋና ዋና ክንውኖች
    ሐምሌ 2013 ዓ.ም.
    አዲስ አበባ

    • በባህል ፖሊሲ፣ በቋንቋ ፖሊሲ በባህል እሴቶችና ሀገር በቀል ዕውቀቶች፣ በዕደ ጥበብ ማበልፀግና የገበያ ትስስር ስትራቴጂዎችና አዘገጃጀት ሂደት እና አተገባበር ላይ ከ10 ክልሎች እና ከ2 የከተማ መስተዳድር ለተውጣጡ 53 የባህል ዘርፍ ሙያተኞች እና አስፈጻሚዎች ስልጠና ተሰጥቷል።
    • ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ ጋር በመተባበር ለባህል ተቋማት በሲኒማ ቤት፣ በቴአትር ቤት እና ቤተ መፃሕፍት ላይ የደረጃ ሰነድ (standard) ተዘጋጅቷል።
    • በኪነጥበብ እና በሥነ ጥበብ ተቋማት ዘርፍ ላይ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦች የማበረታቻ ሽልማት የሚሰጥበትን አሰራር ሥርዓት በመዘርጋት የመጀመሪያው ሀገር አቀፍ የሽልማትና ዕውቅና መርሃ ግብር በሙዚቃ፣ በቴአትር፣ በድርሰት፣ በሰርከስ፣ በስዕልና ቅርፃ ቅርፅ፣ በፋሽን ዲዛይን፣ በውዝዋዜ እና በፊልም 2013ዓ.ም የሽልማትና ዕውቅና ለመስጠት ሥራዎች ተሠርተዋል።
    • ኢትዮጵያ ያላትን ሀብትና የተፈጥሮ ፀጋ ለማስተዋወቅ እንዲሁም ወደ ኢንቨስትመንት አማራጭ ለመለወጥ ያለመ “የኢትዮጵያ ሳምንት” በወዳጅነት አደባባይ ተካሂዷል። ክልሎች ልዩ መገለጫችን ነው ያሉትን ባህላቸውን በተለያዩ ቅርፃ ቅርፆች፣ በተንቀሳቃሽ ምስሎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ጭፈራዎችን በማቅረብ ተከብሯል።
    • የባህል ኢንዱስትሪ መረጃዎችን ለማዘመንና ወጥነት ያላቸው እንዲሆኑ ለማስቻል ከኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽንና ቴክኖሎጂ ጋር በጋራ በመሆን የመረጃ ቋት (ዳታቤዝ) በማዘጋጀት የ2013 ዓ.ም የባህል ኢንዱስትሪ ተቋማትና ሙያተኞች መረጃ ተደራጅተዋል።
    • በባህል ዘርፍ (በባህል፣ በፊልም፣ በቋንቋ ፖሊሲዎችና በእደ ጥበብ ልማት በሀገር በቀል እውቀቶች)፣ በጎጂና መጤ ባህላዊ ድርጊቶች እና ባህል ዘርፍ ተቋማት አከፋፈት የኮቪድ 19 ጥንቃቄና ደህንነት መመሪያን ማስተዋወቅ ሥራ ለ7 ክልሎችና ከሁለት ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ ለ52 አሰልጣኞች የማስተዋወቅ ሥራ ተሠርቷል።
    • ከሙያ ማኅበራት ጋር በመተባበር በኮቪድ ወቅት ጥንቃቄና ደህንነትን መሠረት ባደረገ ሁኔታ የወረርሽኙን አስከፊነት የጥንቃቄ ትኩረትን የሚያስገነዝብና ከ100 በላይ ማስታወቂያዎች (ስፖት) በተለያዩ ሚዲያዎች ተለቋል።
    • የኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል የባህል ዘርፍ አገልግሎት ተቋማትን ሥራ ለማስጀመር እንዲቻል ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ የአሠራር መመሪያ ተዘጋጅቷል።
    • ለክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች እንዲሁም የባህል ጥበባት ዘርፍ ለባለድርሻ አካላት በሁለት ዙር መድረክ ሥልጠና ተሰጥቷል።
    • በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ የተመለከቱት ሥዕል ኤግዚቪሽን ለሶሰት ቀናት ለሕዝብ ዕይታ ቀርቧል።
    • በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያት ትምህርት ቤቶች በተዘጉ ወቅት በቤት ተቀምጠው የነበሩ ተማሪዎች እና ሕፃናት የተሳተፉበት የኪነ ጥበብ ፈጠራ ውድድር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የአንድ ወር የቴሌቪዥን ፕሮግም ተሠርቷል።
    • ኮቪድ 19 ወረርሽኝን ለመከላከል በተደረገ ዘመቻ ለተሳተፉ አካላትና መመሪያውን ተግባራዊ ላደረጉ ለሁለት ክልልና ለአንድ ከተማ መስተዳድር በድምሩ ለ25 ተቋማት እውቅና የመሥጠት ሥራዎች ተከናውነዋል።
    • የባህል ኢንዱስትሪ ዘርፍ በተመለከተ 6 የአሰራር ሥርዓት ሰነዶችና መመሪያዎች ተዘጋጅተዋል።
    • ከዩኔስኮ በተገኘው ዓለም አቀፋዊና ሀገራዊ ኤክስፐርቶቸች ድጋፍ በመታገዝ የቴክኒክ ኮሚቴ ተቋቁሞ የፈልም ፖሊሲ ማስተገበሪያ (የተቋም ማቃቋሚያ ሰነድ እና የፈልም ፖሊሲ ማስፈጸሚያ ስትራተጂ) ፕሮጀክት እየተከናወነ ነው።
    • የ2005 የዩኔስኮ ኮንቬንሽን ስምምነት መሠረት የ2020 (2012 ዓ.ም.) የሚቀርበውን በየአራት ዓመታቱ የሚዘጋጀውን ሪፖርት ለማጠናቀቅ እንዲቻል ሀገራዊ ኮሚቴውን በማስተባበር በወቅቱ ገቢ ለማድረግ ተችሏል።

    ምንጭ፦ የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር

    የኢፌዴሪ ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር

    Anonymous
    Inactive

    ይድረስ ለትግራይ ወገኖቼ!
    በአቶ ክርስቲያን ታደለ ጸጋዬ

    የትግራይ ሕዝብ ከባለጌ ልጆቹ በላይ ሀገሩን የሚመርጥበት ጊዜ ደርሷል። በተለይም የትግራይ እናቶች እና አባቶች በራሳቸው ልጆች እኩይ ስምሪት ቀደምቶቻቸው ለአንድነቷ ሰማዕትነትን የተቀበሉላት ኢትዮጵያችን ክብሯ እንዲጎድፍ በዝምታ መተባበራቸውን ይበቃል ለማለት ትክክለኛው ወቅት አሁን መሆኑን ልብ ሊሉ ይገባል።

    የዘመን ተጋሪዬ ለሆናችሁ የትግራይ ወጣቶችም “ጅብም ብሆን የወንዝህ ጅብ ስለሆንሁ፤ ልበላህ መብት አለኝ” የሚሉ ሀገር አጥፊዎችን በመተው ከሀገራችን ኢትዮጵያ እና ወንድሞቻችሁ ጎን እንድትቆሙ ወንድማዊ ጥሪዬን አቀርብላችኋለሁ።

    የሀይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ጨዋው የትግራይ ሕዝብ በሀገር አፍራሽ፣ ዘር አጥፊና ዘራፊ ብኩኖች በኩል ዘላቂ መብቶቹ፣ ጥቅሞቹና ፍላጎቶቹ እንደማይከበሩለት አውቃችሁ፤ ሁለንተናው ከኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ጋር የተሸመነውን የትግራይ ሕዝብ ታሪክ፣ ክብርና የወደፊት በጎ ተስፋ በሚመጥን ስምሪት እንድትገኙ ዝቅ ብዬ እለምናችኋለሁ።

    ታላቁ የትግራይ ሕዝብ በሌባ አይወከልም! ከዘፍጥረት ጀምሮ እስካሁን ድረስም እናት ኢትዮጵያም ሆነች ወንድሙ የአማራ ሕዝብ ለትግራይ ሕዝብ የክብሩ ምንጭ የደኅንነቱ ደጀኖች እንጂ የስጋቱ ምንጮቹኘች ሆነው አያውቁም፤ አይሆኑምም። እንዴት ሀገር ገንቢው ትግራይ በሀገር አፍራሽ ይወከላል?

    ትግራይ የምታሸንፈው ኢትዮጵያ ስታሸንፍ ብቻ ነው፤ ትግራይ አንገት ደፍታ ኢትዮጵያ አትቃናም። በትግራይ ለቅሶ ፈገግታው የሚደምቅ አንድም ኢትዮጵያዊ አይኖርምም። ሌባና ዘራፊ፤ ባንዳና ሀገር አጥፊ ግን ከየትም ይሁን የትም የጋራ ጠላታችን ነውና በጋራ ልንደመስሰው ይገባናል። በባንዳ ሞት ደረት የሚደቃና ፊት የሚነጭ ሊኖር አይገባም።

    እናም ለተከበራችሁ የትግራይ አባቶቼና እናቶቼ፣ ወንድሞቼና እህቶቼ፥ ስለደማቁ የትናንት ትናንታችን ብቻ ሳይሆን ስለብሩህ ነጋችንም ብላችሁ ለኢትዮጵያችን ኅልውና እንዲሁም ለሕዝባችን ፍትሕ፣ እኩልነትና ነፃነት መረጋገጥ በአንድነት እንድንቆም ስል ጥሪዬን ደግሜ ላቀርብላችሁ እወዳለሁ።

    ሁሉም ችግሮች ከጋራ አቅማችን በታች ናቸው። ስንደማመጥ፣ ስንከባበርና ስንተማመን ከባዱ ቀላል ይሆናል። ኢትዮጵያ ስታሸንፍ ሁላችንም እናሸንፋለን!

    አቶ ክርስቲያን ታደለ ጸጋዬ

    አቶ ክርስቲያን ታደለ ጸጋዬ በፌደራል የጤና ሚኒስቴር፥ የማኅበረሰብ ጤና ኤክስፐርት (public health expert) ሲሆኑ፤ በፖለቲካ እንቅስቃሴአቸው ደግሞ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ናቸው። እርሳቸውን በፌስቡክ ገጻቸው ወይንም በትዊተር ሃንድላቸው ሊያገኟቸው ይችላሉ።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ፦ በሰሞነኛ ድረገጽ የአማርኛ ፎረም (semonegna.com/forums) ላይ የሚገኝ ማንኛውም ጽሑፍ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንጸባርቅ ሲሆን፥ ጽሑፉ የሰሞነኛ ኢትዮጵያንንም ሆነ የተሳታፊዎችን አመለካከትና ምልከታ ላይወክል ይችላል።

    አቶ ክርስቲያን ታደለ

    Anonymous
    Inactive

    የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታ ላይ የሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ

    የኦሮሚያ ክልል ሕዝብና መንግሥት ኢትዮጵያን በመገንባት ዉስጥ የሚመጥነዉን አስተዋፅኦ ሲያበረክት ቆይቷል። የሀገርና የሕዝብ ሉአላዊነትና ነፃነትን ለማስከበር በሚከፈለዉ መስዋዕትነት ላይ እራሱን ቆጥቦ አያውቅም። በዉጪ ወረራና በታሪክ አጋጣሚ የባንዳነትን ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩት ኃይሎች ላይ በየታሪክ ምዕራፉ ራሱን ሰጥቶ ኢትዮጵያን የገጠሟትን ችግሮች ለማክሸፍ መስዋዕትነትን ከፍሏል። እንደሀገር ስናስመዘግብ በቆየናቸው ድሎች ዉስጥ ተወራራሽ ታሪክ አስመዝግቧል።

    ዛሬም እንደ ትናንቱ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የክልሉን ሕዝብ በማቀናጀት በወንድሞቻችን አብሮነት በኢትዮጵያ ላይ የሚቃጣውን የውስጥና የውጪ ትንኮሳ ለማክሸፍ ዝግጁነቱን ይገልፃል።

    የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የፌደራል መንግሥቱ የወሰደውን የአንድ ወገን ተኩስ የማቆም እርምጃ ለሕዝብ ጥሩ የጥሞና ጊዜ የፈጠረ መሆኑን አምኖ ሲደግፍ ቆይቷል። ይሁን እንጂ ከአፈጣጠሩ የተጣመመው ህወሓት ለሕዝብ ጥቅም ተብሎ ለተደረገው ጥሪ ቦታ እንደሌለዉ በግልፅ አሳይቷል። ዛሬም እንደ ትናንቱ በአሮጌ የፖለቲካ እይታ ተሞልቶ የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ ይገኛል።

    የህወሓት የፖለቲካ ፅንሰ-ሐሳብ ሕዝብን እንደ ጠላት በመፈረጅ ላይ ያተኮረ ነው። የግጭት መነሻ የአንድነት ፀርና ለሀገራዊ ብሔርተኝነት መውደቅ ምክንያት ሆኗል።

    የህወሓት ፀረ አንድነት ፈንጂ በየቀኑ እየፈነዳ ለዜጎች ሞትና ስቃይ ምክንያት በመሆን ዓመታትን አስቆጥሯል። የድህነትና የኋላ ቀርነትን እሽክርክሪት ዘመን አራዝሞብናል። ለእድገታችንና የብልፅግና ጉዞ እንቅፋት በመሆን እንድንሸማቀቅ አርጎናል። በዚህ ሁኔታ ዉስጥ ሀገርና ሕዝብ በቀዳሚነት እየተጎዱ ነው።

    አሸባሪው ህወሓት ‘እታገልላቸዋለሁ’ ብሎ የሚናገረውና በስማቸው እየኖረ ያለውን የትግራዋይ ሕዝብን ጨምሮ አስቦላቸው ወይም ተቆርቁሮላቸው አያውቅም። ይህ ቡድን ትናንት የሓውዜን ሕዝብ በሚገበያይበት ቦታ ላይ ቦምብ በማዝነብ የጅምላ ጭፍጨፋ ሲፈፅም ለፕሮፖጋንዳ ግብአትነት እንጂ ለሉአላዊነት ትግል አልነበረም። ሕዝብን በመጨፍጨፍ ሕዝብን ነፃ ማውጣት በየትኛውም መስፈርት የሚታረቅ አስተሳሰብ አይደለም።

    ዛሬም ቢሆን በተባበሩት መንግሥታት የወጣውን የሕፃናት መብት ድንጋጌ በመጣስ ጨቅላ ሕፃናትን ለጦርነት ከፊት አሰልፈው በመማገድ ላይ ይገኛል። አዛውንቶችን፣ እናቶችን እና የሀይማኖት አባቶችን እንደ ጋሻ ከፊት በማሰለፍ በእልቂታቸው የጀግንነት አክሊል ለመድፋት ይሞክራል። አሁንም ቢሆን አሸባሪው ህወሓት የፌደራል መንግሥት ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ካሳየው ፍላጎት በተቃራኒ በመሄድ ላይ ይገኛል። በፌደራል መንግሥት የታወጀው የተናጠል የተኩስ አቁም ስምምነት አርሶአደሩ በክረምት ወቅት ተረጋግቶ እንዲያርስ፣ ለዜጎች እርዳታ እንዲደርስና ግጭት እንዳይባባስ ቢሆንም፥ ህወሓት የተፈጠረበትን የጥፋት ስሜትና እጅ መቆጣጠር አልቻለም።

    የ1967ቱ ህወሓት ማኒፌስቶ ሕዝብና ሕዝብን በማጋጨት ሰላምና መረጋጋትን ለመንፈግ የተወጠነ ነበር። ለኢትዮጵያ ግንባታ ቋሚና ማገር በመሆን ለዛሬ ያደረሳትን ሕዝብ ለመበታተን ያለመ ነው።

    አሸባሪው ህወሓት ላለፉት 27 ዓመታት ሀገር ሲመራ በነበረበት ወቅት በሕዝብ ውስጥ ትቶት ያለፈው ሰቆቃ ሳያንስ፥ ዛሬም በሀገር ላይ የጭካኔ ተግባራትን እየፈፀመ ነው። ሕወሓት በማይካድራ የፈፀመው የዘር ማጥፋት ተግባር በብሔር ላይ ያተኮረ የሕዝብ ጠላትነት ላይ የተመሠረተ እኩይ ተግባር ነው። አሁንም በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ድርጊት ለመፈፀም ሲቅበዘበዝ ይታያል።

    የሕወሓት ኃይል የሕዝብና የሀገር ጥቅምን አሳልፎ ከመስጠት አይመለስም። እድገታችንንና ልማታችንን ለመግታት ከሚታገሉ የውስጥና ውጪ ጠላቶች ጋር በማበር የጥፋትና የማፍረስ ሴራዎችን በዋና ተዋናይነት ሲፈፅም እንደነበረ በገሀድ ታይቷል። አሸባሪው ህወሓት ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከማስተጓጎል ጀምሮ ከነአካቴው እስከ ማደናቀፍ ድረስ የተላላኪነት እና የባንዳነት ትወና ድርሻውን ተወጥቷል።

    የአሸባሪው ህወሓት ክህደት በሕዝብ ንቀት ብቻ የተገታ አልነበረም፤ የሀገር ሉዓላዊነትን ጭምር ጥያቄ ውስጥ እስኪገባ አስነዋሪ ተግባር ፈጽሟል። ኢትዮጵያ ብትፈርስም፣ በውጪ ወራሪ ብትወረርም ደንታ እንደሌለው እስከ መግለፅ ደርሷል።

    ስለሆነም ህወሓት ለአንዱ የሚያስብ፣ ሌላውን የሚነፍግ ሳይሆን በጅምላ የመጨፍጨፍ እና የማፈራረስ አቅጣጫን ይከተላል። ከእሱ ተወልዶ፣ ከእጁ በልቶ ላደገዉ ሕዝብ የማይራራ፣ ሌላ ዘመድ ሊኖረውም ሆነ ሊያፈቅር አይችልም። “ጅግራ ዘመድ መስሎ ወፊቱን በላት” እንደሚባለው ሁሉ፥ ለአንዱ አዝኖ፣ ሌላውን አኩርፎ፣ ሌሎችን ደግሞ የተጸየፈ መስሎ የሚቀርበውን ፕሮፖጋንዳ አምኖ መቀበል ሞኝነት ነው።

    የአሸባሪው ህወሓት ኃይል ተሸንፏል፤ በፖለቲካ ሜዳው አሸናፊ ሀሳብ ማቅረብ ተስኖት ለቆ ስደትን መርጧል። በማግስቱ የጦርነት ነጋሪትን መጎሰም ጀመረ። ውሎ ሳያድር በዜጎቻ ላብ የተገዛውን የሀገር ሉዓላዊነት የሚጠበቅበት መሣርያ በመዝረፍ ኢትዮጵያን ለማንበርከክ ዛተ። በከሀዲዎችና የውጪ ኃይሎች ማበረታቻ የሰከረው ሕወሓት በመከላከያ ሠራዊቱ ለይ የጥቃት እርምጃ ወሰደ። ከትግራይ ሕዝብ ጋር ከ20 ዓመታት በላይ የኖረውን የመከላከያ ሠራዊት በከባድ የጭነት መኪናዎች ከመጨፍለቅ ጀምሮ እጅግ አስነዋሪ እርምጃዎችን ወስዷል።

    የክልልና የሀገራችን ሕዝብ በመከላከያ ሠራዊታችን ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ መከላከያ ሠራዊቱን ለመደገፍ ሁሉ አቀፍ ድርሻውን ተወጥቷል። ዛሬም ቢሆን የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትና ሕዝብ የሀገር ሉዓላዊነት ጋሻ ከሆነው የመከላከያ ሠራዊታችን ጎን በመሆን ማናቸዉንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነው። መንግሥትም የሕዝብ ተሳትፎን በማቀናጀት ሁለንተናዊ ስኬት ለማስመዝገብ ያላሰለሰ ጥረት ያደርጋል።

    ትናንት በችግር ውስጥ የመንግሥትን ጥሪን በመስማት ሁለንተናዊ ድርሻችሁን የተወጣችሁና የአሸባሪዎች የጥፋት መርዝ እንዲደፋ ያደረጋችሁ የክልላችን የኅብረተሰብ ክፍሎች ዛሬም እንደ ትናንቱ የጎላ ተሳትፎአችሁን እንድታበረክቱ መንግሥት ጥሪውን ያቀርባል።

    በሕዝባችን የተባበረ ክንድ ዘላቂ ሉዓላዊነታችን ይረጋገጣል!!
    የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
    ሐምሌ 2013
    ፊንፊኔ

    የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት

    Anonymous
    Inactive

    “የሕዝባችንን ህልውና ከጠላት ጥቃት የምንታደግበት የታሪክ መድረክ ላይ ስለምንገኝ ከመቼውም ጊዜ በላይ ልዩነታችንን ወደጎን በመተው የሕዝባችንን አንድነት ጠብቀን በጋራ እንድንረባረብ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጥሪውን ያቀርባል።”

    የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ የሰጠው መግለጫ
    “አንድነታችንን ጠብቀን ያጋጠመንን የህልውና አደጋ በትግላችን እንቀለብሰዋለን”

    የኢትዮጵያና የአማራ ሕዝብ ጠላት የሆነው ትህነግ ወያኔ እንደሀገር ባደረሰብን ህልቆ መሳፍርት የሌለው ግፍና በደል እንዲሁም ለፈጸመብን ሀገራዊና ሕዝባዊ ክህደት የሀገራችንን የግዛት አንድነት በመሸርሸር ሉአላዊነቷ የማይከበር፣ ራሷን ችላ መቆም የማትችልና በሁሉም መስክ ተንበርካኪ ሀገር ባለቤቶች እንድንሆን በርካታ ደባ ፈጽሞብናል። በዓለም አደባባይ የምንኮራበት ሀገራዊና ሕዝባዊ የጋራ ታሪክ ባህልና እሴት እንዳይኖረን አንድነታችንንና አብሮነታችንን በፈጠራ ታሪክ እየቦረቦረ እርቃናችንን እንድንቀር፣ አንዳችን ለሌላችን ጋሻና መከታ መሆን ሲገባን እርስ በእርስ በመጠራጠር አውሎ ነፋስ ወዲያና ወዲህ እንድንላጋና በጠላትነት እንድንፈራረጅ ከሰማይ በታች ያልፈጸመብን ግፍ የለም።

    ከሁሉም የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ጋር ተባብረንና ተፈቃቅደን የጸረ ጭቆና ትግሉን አንድ ብለን ስንጀምር በጋራ ያነሳነው የፍትህና የእኩል ተጠቃሚነት ጥያቄ በትህነግ መንደር የቱን ያህል መራር የሆነ የመደፈር ስሜት እንደፈጠረ የቅርብ ጊዜ ክስተት ነው። አሸባሪው ትህነግ ከመንበረ ስልጣኑ ተምዘግዝጎ ሲወድቅና መቀሌ ሲከትም የነበረው ብቸኛ ምክንያት ዓይናችሁን ጨፍኑና ላሞኛችሁ የሚል ፖለቲካዊ ቁማር እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም። በውህድ ፓርቲ ደረጃ የተፈጠረውን አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ አደረጃጀት የአሃዳውያን ውጤት አድርጎ ያበሻቀጠው ፍላጎቱ በለመደው የአድራጊ ፈጣሪና የአዛዥነት ሚና ያልተሳተፈበትን መዋቅር ለማጣጣል ከማለም ባሻገር፥ ለኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እኩል ተጠቃሚነት ባለው ከፍ ያለ ንቀትና ጥላቻ ምክንያት መሆኑ ለሁሉም ግልጽ ነው።

    ይህንን ተከትሎ በትግራይ ክልል የሰሜን ዕዝ እንዳይንቀሳቀስ በተደጋጋሚ ያደረገው ሙከራ የልብ ልብ ሰጥቶት ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ውድ ልጆችን በግፍ ያለርህራሄ አሰቃቂ ግድያ ከፈጸመባቸው በኋላ የዕዙን ጠቅላላ ንብረት በመውረስ በመላው ኢትዮጵያውያን ላይ ጦርነት ማወጁ ይታወቃል። የአማራ ክልልን ወሰን ጥሶ በማለፍ ጥቃት ለመፈጸም ያደረገው ጥረት ባይሳካለትም በማይካድራ ንጹሀን ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ላይ የፈጸመው አረመኔያዊ የጅምላ ጭፍጨፋ የሚዘነጋ አይደለም። ይህንን ተከትሎም መንግሥት በየደረጃው የሕግ የበላይነት ለማስከበር ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን አከናውኗል። በሂደቱም በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸው የሚዘነጋ አይደለም። ይሁን እንጂ ይህ አረመኔና አሸባሪ ቡድን ዓይኑን በጨው አጥቦ ጥቃት የተፈጸመበት በማስመሰል ዓለምአቀፉን ማኅበረሰብ በተደጋጋሚ በማጭበርበር ላይ ይገኛል።

    የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት በአንድ ወገን የወሰደውን የተኩስ አቁም ውሳኔ እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም በኢትዮጵያና በአማራ ክልል ሕዝብ ላይ መሠረተ ሰፊ የሆነ ወረራና ጥቃት ማድረግ ጀምሯል። ይህ አሸባሪ ቡድን የጀመረብንን ግልጽ ወረራ ሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደሚያወግዘውና የምንጊዜም አጋርነቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ፍጹም ጥርጣሬ የለንም። በዚህ አጋጣሚ የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ በግልጽ እንደሚያውቀው የአማራ ክልልና ሕዝብ የዚህ አሸባሪ ቡድን ቀጥተኛና የቅርብ ተጠቂ መሆኑን ነው። ስለሆነም ትግላችን ለሕዝባችን ህልውናና ለሀገር ሉአላዊነት መሆኑ ግንዛቤ ውስጥ ገብቶ የጋራ ጠላታችንን በጋራ እንድንፋለመው የአጋርነት ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    አሸባሪው የትህነግ ቡድን ከአማራ ክልል ጋር በሚያዋስኑት ሁሉም አቅጣጫዎች መጠነ ሰፊ ወረራና ጥቃት እየፈጸመ የሚገኝ አረመኔና ጨካኝ ቡድን መሆኑ እንዲታወቅና ሁሉም የአማራ ክልል ሕዝብ ጉዳዩን ከህልውናው ጋር በማስተሳሰር እንዲመለከተውና ከዚህ ጨካኝና አረመኔ ቡድን ጋር ቀጣይ የምናደርገው ሁሉ አቀፍ ትግል የህልውና ትግል መሆኑን አውቆ በገንዘብ፣ በጉልበትና በህይወት መስዋዕትነት አስፈላጊውን አበርክቶ ለማድረግ ራሱን እንዲያዘጋጅና የመንግሥትን ጥሪ እንዲጠባበቅ የክልሉ መንግሥት ጥሪውን ያቀርባል።

    አሸባሪው ትህነግ የትግራይን ሕዝብ ከህጻን እስከአዋቂ በማንቀሳቀስ ዓለም አቀፍ የጦርነት ሕግጋትን በመቃረን ሕጻናትንና ሴቶችን በጅምላ ጦርነት እየማገደና ያለ የሌለውን አቅሙን ተጠቅሞ ክልላችን ላይ ወረራ የፈጸመ ሲሆን፥ በተለይም ለዘመናት የአማራ ሕዝብ የማንነትና የወሰን ጥያቄ እያነሳ ሲታገልባቸው የቆዩ የራያ፣ አላማጣና ኮረም አካባቢዎችን ዳግም በመውረር እንዲሁም ወልቃይት ጠገዴ ሴቲት ሁመራ በኃይል ለመያዝ በተለይም ጠለምትና አካባቢውን ለመያዝ አሁናዊ ሙከራ የጀመረ መሆኑ በአካባቢው የሚኖሩ አማራዎችንና የአማራ ክልል ተወላጆችን ፈጽሞ የማጥፋት ህልሙን እውን ለማድረግ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። ስለሆነም ይህንን አረመኔያዊ ድርጊትና ዳግም ወረራ የክልሉ መንግሥት በፍጹም የማይቀበለውና በጀመርነው የህልውና ትግል ተፈጥሯዊና ታሪካዊ መብታችንን የምናረጋግጥ መሆኑን አበክረን እንገልጻለን።

    ስለሆነም፡-

    1ኛ. በየግንባሩ የምትገኙ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት፣ የክልላችን ልዩ ኃይልና የሚሊሻ አባላት፣ ሕዝባዊ ፖሊስና ሰላም አስከባሪ አባላት እንዲሁም ሀገርና ሕዝብን ለማዳን የተግባር እንቅስቃሴ እያደረጋችሁ የምትገኙ የየክልሉ የጸጥታ አካላት፥ በዚህ ታሪካዊ መድረክ ከጠላት ጋር ፊት ለፊት በመግጠም ለሀገራችሁ ሉአላዊነትና ለሕዝባችሁ ህልውና የምትከፍሉትን ክቡር መስዋዕትነት ታሪክ ምንጊዜም ሲያስታውሰው ይኖራል። በቀጣይም የተሰጣችሁን ሕዝባዊና ሀገራዊ ተልዕኮ በጽናትና በቁርጠኝነት እንደምትወጡ እምነታችን የጸና ነው። ስለሆነም፥ መላው የኢትዮጵያና የአማራ ሕዝብ ከጎናችሁ መሆኑን አውቃችሁ በጀግንነት ታሪካዊ ጠላታችንን በመደምሰስ ለሀገራችሁ ዳግም የኩራት ምንጭ እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    2ኛ. መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በትህነግ ወያኔ ላይ የተጀመረው ሕግን የማስከበር ትግል ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስፈላጊውን እርብርብ ሁሉ ማድረግ አለበት ብለን እናምናለን። አሸባሪው ትህነግ ሀገር ከማፍረስ እኩይ ተልዕኮው ሊታቀብ የሚችለው የሀገራችንን ሉአላዊነትና የግዛት አንድነት በጽናትና በአላማ ቁርጠኝነት በጋራ መጠበቅ ስንችል ስለሆነ በዚህ ታሪካዊ መድረክ ላይ በጋራ እንድንቆም የአክብሮት ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    3ኛ. በየትኛውም ዘመን ሰልጥናችሁ፣ የሀገርና የሕዝብ ሉአላዊነት ለማስከበር በማንኛውም የመንግሥት ጸጥታ መዋቅር ውስጥ ተሰልፋችሁ ስታገለግሉ የቆያችሁና በታሪክ አጋጣሚ የሙያ ዘርፍ የቀየራችሁ የክልላችን ነዋሪዎች፥ ለህልውናችን የምናደርገውን የትግል ጥሪ ተቀብላችሁ በክልሉ ጸጥታ መዋቅር ውስጥ እንድትቀላቀሉ ጥሪያችንን እያቀረብን ከዛሬ ጀምሮ በየአካባቢያችሁ ሰላምና ደህንነት ጽሕፈት ቤት በአካል ተገኝታችሁ በፈቃደኝነት እንድትመዘገቡ ለማሳሰብ እንወዳለን።

    4ኛ. መላው የክልላችን ወጣቶች፥ ከፊት ለፊታችን የተደቀነብንን የህልውና አደጋ ያለበቂ ዝግጅትና ደረጃውን ከጠበቀ ስልጠና ውጭ የምንጋፈጠው አይደለም። ስለሆነም ከማንኛውም ግብታዊ እንቅስቃሴ ታቅባችሁ በየደረጃው ለሚኖረው ምልመላና ስልጠና በመሳተፍ በቂ ዝግጅት አድርጋችሁ የመንግሥትን ጥሪ እንድትጠባበቁ እናሳስባለን።

    5ኛ. መላው የክልላችን ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሲቪክና የሙያ ማህበራት፣ ማኅበራዊ አንቂዎችና የሚዲያ ባለሙያዎች፥ የጀመርነው የህልውና ትግል የሁላችንንም አንድነት፣ ኅብረትና ተቀራርቦ መሥራት የሚጠይቅ ነው። በሩቅ ሆኖ ስህተት በመፈለግና እርስ በእርስ በመነቋቆር ከጠላት መንጋጋ ፈልቅቀን የምንታደገው አንዳችም ህልውና የለንም። በቂ መረጃ ባገኘንበትም፣ ባላገኘንበትም ጉዳይ ላይ ተሳፍረን በተለያዩ አቅጣጫዎች መክነፍ ለጠላቶቻችን ተጨማሪ ጉልበት ከመሆን ባለፈ ለሕዝባችን የሚሰጠው ጥቅም የለም። ስለሆነም የጋራ ዕጣ ፋንታችንን በጋራ ጥረት የምናስከብርበትና አደጋ የተጋረጠበትን የሕዝባችንን ህልውና ከጠላት ጥቃት የምንታደግበት የታሪክ መድረክ ላይ ስለምንገኝ ከመቼውም ጊዜ በላይ ልዩነታችንን ወደጎን በመተው የሕዝባችንን አንድነት ጠብቀን በጋራ እንድንረባረብ የክልሉ መንግሥት ጥሪውን ያቀርባል።

    6ኛ. መላው የክልላችን ሕዝብ፣ በከተማና በገጠር የምትኖሩ የክልላችን ነዋሪዎች፣ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ የምትገኙ ምሁራንና የክልላችን ተወላጆች፣ በተለያየ ሙያ ተሰማርታችሁ ሀገርና ሕዝብ በማገልገል ላይ የምትገኙ የክልላችን ነዋሪዎችና ባለሀብቶች፥ የጀመርነውን የህልውና ትግል በማገዝ የትግል ሂደት አዎንታዊ ሚናችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    በመጨረሻም የጀመርነው ትግል እልህ አስጨራሽ በጣም መራርና ረዥም ጊዜ የሚጠይቅ እንደሚሆን ይጠበቃል። የፈጀውን ጊዜ ይፍጅ የእኛ አንድ መሆንና ለጋራ ግብ በጋራ መተባበር በመድረኩ አሸናፊ ሆነን እንደምንወጣ ያለምንም ጥርጥር ልናረጋግጥልችሁ እንወዳለን። ሁልጊዜም ቢሆን የአማራ ክልል ሕዝብ ትግል ከኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች የጋራ ተጠቃሚነት ውጭ እንደማይሳካ ጠንቅቀን እናውቃለን። የምናደርገው ትግል ለሀገራችን ሉአላዊነት መከበርና የጭቁን ሕዝባችን የህልውና ትግል እንጂ እላፊ ጥቅም ለማግኘት የምናደርው ትግል በፍጹም አይደለም።

    የአማራ ሕዝብ ከፉክክር ይልቅ ትብብርን ከእብሪት ይልቅ ድርድርን የሚያስቀድም፣ ‘በፍትህ ከሄደች በቅሎየ፥ ያለፍትህ ያጣኋት ጭብጦየ’ ትቆረቁረኛለች ብሎ የሚያምን ሕዝብ ነው። ስለሆነም ዛሬ የምናደርገው ትግል ለልጅ ልጆቻችን የምናወርሰው የኩራትና የክብር ምንጭ እንደሚሆን አንጠራጠርም። የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት የወሰደው ተናጠላዊ የተኩስ አቁም ውሳኔን ተከትሎ የጠላት ኃይል ሀገርና ሕዝብ ለማዋረድ የሚያደርገውን እብሪተኛ እንቅስቃሴ መሠረት በማድረግ በጠላት ላይ የማያዳግም እርምጃ እንዲወስድ በአጽንኦት እናሳስባለን።

    ትግላችን ለህልውናችን !
    ሐምሌ 6 ቀን 2013 ዓ.ም.
    የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት

    የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት

    Anonymous
    Inactive

    አቢሲንያ ባንክ እጅግ በተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ስም ቅርንጫፍ ከፈተ

    አዳዲስ ቅርንጫፎችን በሀገር ባለውለታዎች ስም እየሰየመ የሚከፍተው አቢሲንያ ባንክ፥ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ዕንቁዎች በመጀመሪያ ረድፍ ላይ በተቀመጡትና ስማቸውን በወርቅ ቀለም ባጻፉት ታላቁ የኪነ ጥበብ ሊቅ፥ እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ስም ቅርንጫፉን ከፍቶ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

    አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ በአንኮበር ከተማ፣ ከአቶ ተክሌ ማሞና ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ጥቅምት 13 ቀን፥ 1925 ዓ.ም. ተወለዱ። ዘመኑ ፋሺስት ጣልያን ሀገራችንን በግፍ የወረረበት ዘመን በመሆኑ፣ አፈወርቅ ተክሌ በጨቅላ እድሜያቸው በሰው፣ በንብረትና ባህል ላይ የደረሰው ጥፋት በአእምሮአቸው ታትሞ ቀረ። ለዛም ይመስላል በ1940 ዓ.ም. ለከፍተኛ ትምህርት ወደ ታላቋ ብሪታንያ፥ ለንደን ተጉዘው፣ የሥዕልን ጥበብ ተምረው ከተመለሱ በኋላ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍላት እየተዘዋወሩ ታሪክን፣ የብሔረሰቦችን ባህልና ወግ ሲያጠኑ የከረሙት።

    በ1944 ዓ.ም. በሃያ ሁለት ዓመት እድሜአቸው የመጀመሪያ የሆነው የሥዕል አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት አቀረቡ። ከአውደ ርዕይ ባገኙት ገቢ፣ ወደተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት በመዘዋወር የሥዕል ጥበብን ቀሰሙ። የኢትዮጵያ ጥንታዊ የብራና መጻሕፍትን አጠኑ። ሎሬት አፈወርቅ ተክሌ በኢትዮጵያ የመስታወት ስዕልን (stained glass art) ያስተዋወቁ ቀዳሚው የጥበብ ሰው ናቸው። በዚህ ጥበብ የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን መስኮቶች በመሥታወት ሥዕላት አስጊጠዋል። በሐረር ከተማ የአፄ ኃይለ ሥላሴ አባት የራስ መኮንን ሐውልትን ገንብተዋል።

    ሥራዎቻቸው በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ እጅግ ዝናን ያተረፉ በመሆናቸው በርካታ ሽልማቶችን አስገኝተውላቸዋል። በ1971 ዓ.ም. የአልጀርስ የጥበብ ፌስቲቫል የወርቅ ሽልማት፤ በፈረንሳይ በተደረገው የሥዕል ውድድር አንደኛ በመውጣት የኖቤል የሎሬት ክብር መዓረግ በማግኘት ኢትዮጵያን አስጠርተዋል። በ2000 ዓ.ም. የዓለም ሎሬትነት ክብርን በዋሽንግተን ዲሲ በተደረው 27ኛው ዓለም አቀፍ የጥበብና መገናኛ ብዙኃን የሚሊንየም ኮንግረስ (27th International Millennium Congress on the Arts and Communication) ከአሜሪካ ባዬግራፊካል ኢንስቲትዩት ተቀዳጅተዋል፤ በ2004 ዓ.ም. በአየርላንድ ለጥበብ ዕድገት ለዓለም ላበረከቱት አስተዋጽዖ “የዳቬንቺ አልማዝ ሽልማት” እና “የጀግና ክብር ኒሻን” ተበርክቶላቸው።

    እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ በተወለዱ በ79 ዓመታቸው ሚያዝያ 2 ቀን፣ 2004 ዓ.ም. በስጋ ሞት ቢለዩንም፥ እነሆ በራሳቸው ቀለምና በሀገርኛ ሥራዎቻቸው በዓለም መድረክ ላይ የኢትዮጵያን ስም ከፍ በማድረጋቸው፥ ለእኚህ የሀገር ዋልታ አቢሲንያ ባንክ አዲስ የከፈተውን ቅርንጫፍ በስማቸው ሰይሞ ዘክሯል።

    አቢሲንያ ባንክ ብዙ መሰናክሎች ሳይበግራቸው ሀገራችን ኢትዮጵያ በተለያዩ የሥራ መስኮች ማለትም፥ በመንግሥት አስተዳደር፣ ሀገርን በመጠበቅ፣ በታሪካዊ ኩነቶች፣ ቅርስ በማሰባሰብ፣ በስፖርት፣ በሥነ ጽሑፍ፣ በቴአትር፣ ሙዚቃ፣ ፋይናንስና አገልገሎት፣ በበጎ አድራጎት ሥራዎች፣ በማስታወቂያ ሞያ፣ በንግድ ሥራና በመሳሰሉት ዘርፎች ስሟን ከፍ ላደረጉ ባለውለታዎች በስማቸው ቅርንጫፎችን በመሰየም እየዘከራቸው ይገኛል። ይህም ለሀገራችን ዘመን አይሽሬ አበርክቶ ያደረጉ ባለውለታዎችን ስማቸውንና መልካም ተግባራቸውን በመዘከር ለቀጣዩ ትውልድ ለማሳወቅና አርዓያ እንዲሆን በማመን ጭምር ነው።

    ምንጭ፦ አቢሲንያ ባንክ

    አቢሲንያ ባንክ አፈወርቅ ተክሌ ቅርንጫፍ

    Anonymous
    Inactive

     ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የምርጫ ውጤት

    ሰኔ 14 ቀን፥ 2013 ዓ.ም. የተካሄደው የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውጤት ይፋ ተደረገ። ይህ ውጤት የሚገለፀው ባገኙት ወንበር ልክ ሲሆን በዚህም መሠረት፦

    • የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር
      – መስተዳድሩ ያለው የተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ: 23
      – ሰኔ 14 ቀን ምርጫ የተከናወነበት የተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ክልል ብዛት: 23
      □ ብልፅግና ፓርቲ ያገኘው መቀመጫ: 22
      □ የግል ተወዳዳሪ ያገኘው መቀመጫ: 1
    • የአፋር ብሔራዊ ክልል
      – ክልሉ ያለው የተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ: 8
      – ሰኔ 14 ቀን ምርጫ የተከናወነበት የተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ክልል ብዛት: 6
      □ ብልፅግና ፓርቲ ያገኘው መቀመጫ: 6
    • የአማራ ብሔራዊ ክልል
      – ብሔራዊ ክልሉ ያለው የተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ: 138
      – ሰኔ ቀን ምርጫ የተከናወነበት የተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ክልል ብዛት: 125
      □ ብልፅግና ፓርቲ ያገኘው መቀመጫ: 114
      □ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲ ያገኘው መቀመጫ: 5
      – ድጋሚ ቆጠራ የሚከናወንበት ምርጫ ክልል ብዛት: 1
      – ድጋሚ ምርጫ የሚከናወንበት ምርጫ ክልል ብዛት: 5
    • የቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ብሔራዊ ክልል
      – ብሔራዊ ክልሉ ያለው የተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ: 9
      – ሰኔ 14 ቀን ምርጫ የተከናወነበት የተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ክልል ብዛት: 3
      □ ብልፅግና ፓርቲ ያገኘው መቀመጫ: 3
      – ድጋሚ ምርጫ የሚከናወንበት ምርጫ ክልል ብዛት: 2
    • የድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር
      – መስተዳድሩ ያለው የተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ: 2
      – ሰኔ 14 ቀን ምርጫ የተከናወነበት የተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ክልል ብዛት: 2
      □ ብልፅግና ፓርቲ ያገኘው መቀመጫ: 1
      – ድጋሚ ቆጠራ የሚከናወንበት ምርጫ ክልል ብዛት: 1
    • የጋምቤላ ብሔራዊ ክልል
      – ብሔራዊ ክልሉ ያለው የተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ: 3
      – ሰኔ 14 ቀን ምርጫ የተከናወነበት የተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ክልል ብዛት: 3
      □ ብልፅግና ፓርቲ ያገኘው መቀመጫ: 3
    • የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል
      – ብሔራዊ ክልሉ ያለው የተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ: 178
      – ሰኔ 14 ቀን ምርጫ የተከናወነበት የተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ክልል ብዛት: 170
      □ ብልፅግና ፓርቲ ያገኘው መቀመጫ: 167
      □ የግል ተወዳዳሪዎች ያገኙት መቀመጫ: 3
    • የሲዳማ ብሔራዊ ክልል
      – ብሔራዊ ክልሉ ያለው የተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ: 19
      – ሰኔ 14 ቀን ምርጫ የተከናወነበት የተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ክልል ብዛት: 19
      □ ብልፅግና ፓርቲ ያገኘው መቀመጫ: 19
    • የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ብሔራዊ ክልል
      – ብሔራዊ ክልሉ ያለው የተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ: 104
      – ሰኔ 14 ቀን ምርጫ የተከናወነበት የተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ ክልል ብዛት: 85
      □ ብልፅግና ፓርቲ ያገኘው መቀመጫ: 75
      □ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ ያገኘው መቀመጫ: 4
      □ የጌዴኦ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት: 2
      – ድጋሚ ቆጠራ የሚከናወንበት ምርጫ ክልል ብዛት: 1
      – ድጋሚ ምርጫ የሚከናወንበት ምርጫ ክልል ብዛት: 3

    በዚህ ሐምሌ 3 ቀን፥ 2013 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው የምርጫ ውጤት መሠረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመቀመጫ ብዛት በአጠቃላይ 484 ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ በስልጣን ላይ የሚገኘው ብልፅግና ፓርቲ 410 መቀመጫ አሸንፏል። ይህም ውጤት ፓርቲውን መንግሥት ለመመሥረት ያስችለዋል።

    ይህን የምርጫ ውጤት እና የፓርቲያቸው ማሸነፍን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ያስተላለፉትን መልዕክት ለማንበብ እዚህ ጋር ይጫኑ

    የምርጫ ክርክር የምርጫ ውጤት

    Anonymous
    Inactive

    “በዚህ ሀገራዊ ምርጫ የፈጠርነው አሸናፊና ተሸናፊን ሳይሆን፣ ጠያቂና ተጠያቂ ያላበት የዲሞክራሲ ሥርዓትን ነው። በዚህ ደግሞ ያሸነፉት በምርጫው የተሳተፉት ሁሉም አካላት ናቸው።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስድስተኛው የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ ውጤትን ያስተላለፉት መልዕክት

    የተከበራችሁ ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያውያት፥

    ላለፈው ግማሽ ክፍለ ዘመናት፣ የሀገራችን ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በነጻ ፈቃዱ የመረጠው መንግሥት እንዲኖረው ብዙ ሙከራዎች ሲደረጉ ቢቆዩም፤ በተለያዩ ምክንያቶች ሲሰናከሉ ነበር። በሂደቱ አያሌ ተማሪዎችና ወጣቶች፣ ገበሬዎችና የቤት እመቤቶች፣ ምሁራንና መለዮ ለባሾች፣ መላው የሀገራችን ሕዝብ ከፍተኛ ዋጋ ከፍሏል። ካለፈ ልምዳችንና ባልተሳኩ ጉዞዎች ጠባሳ ሰበብ፣ የአሁኑም ምርጫ ዴሞክራሲያዊነቱ ተጠብቆ ባይጠናቀቅስ በሚል ስጋት፣ ያለፉትን ወራት እንደ ሀገር በፍርሃት ተወጥረን መክረማችን ሊካድ አይችልም። ኢትጵያውያን ግን ጨዋ ብቻ ሳይሆኑ አርቆ አሳቢ መሆናቸውን ዛሬም አስመስክረዋል። የተሰጋውን ሳይሆን የሚፈልጉትን ማድረግ እንደሚችሉ በግብር አሳይተዋል። ዝናብና ፀሐይ ሳይገድባቸው፣ በረጃጅም ሰልፎች ሳይሰለቹ፣ እስከ እኩለ ሌሊት ታግሰው ፍላጎታቸውን በካርዳቸው ገልጸዋል። እንደ እኛ እምነትም በዚህ ምርጫ አሸናፊ የሆነው ሕዝባችን ነው። ከሕዝባችን በመቀጠል፣ በብዙ ውሱንነቶች ውስጥ አልፈው በዲሞክራሲና በሕዝብ ድምፅ ላይ ባላቸው ጽኑ እምነት፣ ሀሳብና ፖሊሲያቸውን ለሕዝብ አቅርበው ብርቱ ውድድር ያደረጉ ተፎካካሪ ፓርቲዎች የዴሞክራሲያዊ ሂደቱ ድል አድራጊዎች ናቸው።

    ይህንን ምርጫ ልዩና ታሪካዊ የሚያደርጉት ብዙ ጉዳዮች አሉ። በታሪካችን ለመጀመሪያ ጊዜ ከተጽዕኖዎች በተላቀቀ የምርጫ ቦርድ ዳኝነት ያደረግነው ምርጫ መሆኑ አንደኛው ነው። የምርጫ ቦርድ ዳኝነት እንዲሳካ ደግሞ ቁጥራቸው የበዙ የግልና የመንግሥት ሚዲያዎች፣ የሲቪል ተቋማት፣ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን፣ ፍርድ ቤቶችና ሌሎችም ተቋማት በግልጽ የተከታተሉት መሆኑ ሂደቱን ከመቼም ጊዜ በላይ ተአማኒና ዲሞክራሲያዊነቱ የተጠበቀ ምርጫ ያደርገዋል። ምርጫው ዴሞክራሲን የመትከል ግባችንን አንድ እርምጃ ያስኬደ በመሆኑ፣ ፓርቲያችን ከምንም በላይ ቀዳሚ ድሉ አድርጎ ይቆጥረዋል። በታሪካዊው ምርጫ ተሳታፊ መሆን በራሱ የሚፈጥረው ደስታ እንዳለ ሆኖ፣ ፓርቲያችን በሕዝብ ይሁንታ አግኝቶ ሀገር ለማስተዳደር መመረጡ አስደስቶናል። በውጤቱም ከአሸናፊነት ይልቅ ኃላፊነት፣ ከድል አድራጊነት ይልቅ ታላቅ የሆነ ሀገራዊ አደራ እንዲያድርብን አድርጎናል።

    መንግሥት የሚመሠረተው በሕዝብ በተመረጡ ፓርቲዎች ቢሆንም ሀገርን መምራትና ማስተዳደር ግን ለተመረጡ ፓርቲዎችና መሪዎች ብቻ የሚተው አይደለም። ተፎካካሪ ፓርቲዎችና መሪዎቻቸውም እስከሚቀጥለው ምርጫ በመንግስት አስተዳድርና ሕዝብን በማገልገል ሂደት ውስጥ ሚናቸው ሰፊ ሊሆን እንደሚገባ ለማስታወስ እወዳለሁ። በቀጣይ ወራት ብልጽግና በሚመሠርተው መንግሥት ውስጥ በአስፈጻሚው አካልም ሆነ በፍርድ ቤቶች፣ በሌሎችም የፌደራልና የክልል ተቋማት ላይ ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው፣ በዘንድሮው ምርጫ በኃላፊነትና በብቃት የተወዳደሩ የሕዝብ አለኝቶችን ከዚህ በፊት ካደረግነው በእጅጉ ከፍ ባለና አዎንታዊ ለውጥ በሚፈጥር መልኩ እንደምናካትታቸው ለመግለጽ እወዳለሁ። በተጨማሪም እስከሚቀጥለው ምርጫ የበለጠ ተጠናክረውና ተቋማዊ አቅማቸው ደርጅቶ ብርቱ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ከማድረግ ወደ ኋላ አንልም። በዚህ ምርጫ የፈጠርነው አሸናፊና ተሸናፊን ሳይሆን፣ ጠያቂና ተጠያቂ ያላበት የዲሞክራሲ ሥርዓትን ነው። በዚህ ደግሞ ያሸነፉት በምርጫው የተሳተፉት ሁሉም አካላት ናቸው።

    ውድ የኢትዮጵያ ልጆች፥

    በምርጫ ካርዳችሁ ስትመርጡን በዕቅድና በፖሊሲ የያዝናቸውን የብልጽግና ግቦች እንድናሳካ የድፍረትና የጥንካሬ ስንቅ እንደሚያቀብለን ሁሉ፣ እኛና እናንተን ያስተሳሰረው ቃል ኪዳን ተጠብቆ እንዲቆይ ነገሮች አልጋ በአልጋ እንደማይሆኑን እንገነዘባለን። ቢሆንም ግን ከመቼውም ጊዜ በላይ ትከሻችንን አስፍተን፣ ኢትዮጵያን ከሚወዱ አካላት ጋር ሁሉ በትብብር ዐቅማችን አማጥጠን ለመሥራት ቆርጠን እንደተነሣን ሳበስራችሁ ደስ እያለኝ ነው። በቀጣይ ዓመታት ሀገራችን በእውነትም በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ከፍ የምትልበት ዘመን ይሆናል። ይህ እንዲሳካ የሐሳብና የሞራል ስንቅ እንደምታቀብሉን፣ መንገድ ስንስት እንደምትመልሱን፣ ስናጠፋም እንደምታርሙን ተስፋ በማድረግ ነው።

    በሀገራችን ሁለንተናዊ ብልጽግና እውን እንዲሆን በቀጣዩ አምስት ዓመት ፈር ጠራጊ እንሆናለን የምንለው፣ በዙሪያችን ባሉና ብልጽግና በሚቀላጠፍባቸው አራት ማዕዘኖች መሐል ቆመን ነው። የመጀመሪያው ማዕዘናችን የመሠረተ ልማት ግንባታ ሲሆን፥ ሀገራችን እንድትበለጽግ በኢኮኖሚውም ሆነ በማኅበራዊና ፖለቲካ ዘርፎች ዘላቂ መሠረት የሚሆኑ፣ በፍጥነት የሚጠናቀቁ፣ ጥራታቸው የተጠበቁ፣ ከብክነት ነጻ የሆኑ እና የምንፈጥራቸውን ተቋማት መሸከም የሚችሉ ትውልድ ተሻጋሪ መሠረተ ልማቶችን መገንባታችንን እንቀጥላለን። ጥቂትም ቢሆኑ ባለፉት 3 ዓመታት አመርቂ ሥራዎችን ለመሥራታችን ምስክሮቹ እናንተው ናችሁ።

    ሁለተኛው ማዕዘናችን የተቋማት ግንባታ ሲሆን፣ በጥቂት ግለሰቦችና ነጠላ ተቋማት ላይ ከማተኮር ባለፈ ሀገራችንን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያቆሙ ጠንካራ ተቋማት ያስፈልጉናል። ዘመን ተሻጋሪ ሥርዓት ለማጽናት የሚስችሉ ገለልተኛና ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ዜጋ የሚያገለግሉ ተቋማትን መገንባት ላይ ትኩረት ይደረጋል። ይሄ ማሕቀፍ ከፌደራል እስከ ክልል የሚገኙ ተቋማትን የሚያካትት ይሆናል።

    በሦስተኛ ደረጃ እንደ ሀገር የሚያስተሳስሩን የጋራ አመለካከቶችና የጋራ ትርክቶች ላይ ትኩረት ሰጥተን ልንሠራባቸው ይገባል። እርስ በእርስ የሚቃረኑና የሚጠፋፉ ትርክቶች ምን ያህል ለጠላቶቻችን ተመችቷቸው እኛን ደካማ እንዳደረገን ያሳለፍናቸው ዓመታት ሕያው ምስክሮች ናቸው። ስለዚህ ክፍተቶቻችንን በሚደፍን መልኩ ብቻ ሳይሆን እንደ ሀገር አጠንክረው በሚያቆሙን እሴቶች ላይ የተመሰረተ፣ ገዢና ሁላችንንም አሸናፊ የሚያደርግ ትርክት ለመገንባት ጠንክረን እንሠራለን።

    በአራተኛ ደረጃ የሞራል ልዕልናና ግብረገባዊነት ተመጣጣኝ ትኩረት አግኝተው እስካልተሠራባቸው ድረስ በሀገራችን ኃላፊነት የሚሰማቸው ዜጎች ቁጥር እየቀነሰ፣ በተቃራኒው ኢ-ሞራላዊ ድርጊቶች እየተስፋፉ እንዲመጡ በር ይከፍታል። ይኼንን ችግር የመቅረፍ ኃላፊነት መንግሥትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ላይ ብቻ የሚጣል ሳይሆን፣ ከግልና ከቤተሰብ ጀምሮ የሚሠራ ሥራ ነው። ሁሉም አካላት ተረባርቦ ሀገርና ትውልዱን እያቆሸሹ ያሉ መጥፎ ተግባሮችን ጠርጎ ሊጥላቸው ይገባል። በቀጣይ ዓመታት በሞራል ንጽህና የተገነቡ ተቋማትንና መሪዎችን አንጥረን የምናወጣበት እንዲሆን ተስፋ አደርጋለሁ።

    ውድ የሀገሬ ዜጎች፥

    ባለፉት ሦስት ዓመታት በከፍተኛ ጥንቃቄ የቀረጽነው የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለተግባራዊነቱ በጋራ ከተጋን ያለ ጥርጥር ቀጣዩቹ ዓመታት ለሀገራችን ብልጽግና እንደ ወሳኝ የመታጠፊያ ኩርባ ይሆናል። ዕምቅ ዐቅሞቻችን ምንድን ናቸው? ምን ዓይነት የመበልጸግ ዕድል እጃችን ላይ አለ? ምን ብናደርግ ኢኮኖሚያችን መዋቅራዊ ለውጥ ያመጣል? የሚሉትን በሚገባ ፈትሸን ያረቀቅነው ዕቅድ ነው።

    በሀገራችን ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ለነገ የማይባል ጉዳይ ነው። በፍጥነት የምግብ ፍላጎታችንን በማሟላት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከውጭ የምግብ ድጎማ መላቀቅ አለብን። ምግብ ለእኛ ቅንጦት መሆን አይገባም። ጠግቦ መብላት ቅንጦት የሆነበት ሕዝባችንን መርጦ መብላት እንዲጀምር ለማድረግ ቆርጠን መነሳት አለብን። በብዝኃ ዕጽዋትና በብዝኃ እንስሳት የምትታወቅ ሀገራችን የእንስሳት ተዋጽዖና ፍራፍሬዎች ለገበታችን ከቅንጦትነት ወደ አዘቦትነት መለወጥ አለባቸው። ዶሮና ዕንቁላል፣ ወተትና ቅቤ፣ ተርፎን ለገበያ የምናቀርባቸው እንጂ ለዓመት በዓል አይተናቸው የሚሰወሩ የሩቅ እንግዳ መሆናቸው ሊያከትም ይገባል።

    እዚህ ጋር አንድ መታወቅ ያለበት ሀቅ አለ። መንግስትና ሕዝብ እጅና ጓንት ሆነው እስካልሠሩ ድረስ ሕልማችን ይሳካል ማለት ዘበት ነው። በቀጣይ 5 ዓመታት ተባብረን በተለይ በግብርናው ዘርፍ ምርታማነት ለማሳደግ ጠንክረን መስራት አለብን። ከዚህ ቀደም ጀምረናቸው ውጤት እያመጡ ያሉ ተግባራት አሉ። የበጋ ሰብሎችና ፍራፍሬዎች ላይ ለውጥ ለማምጣት ከተጀመሩ አነስተኛ መስኖዎች ባለፈ፣ ዝናብ አጠርነት ለመዋጋት በቴክኖሎጂ አማካኝነት ደመናን ወደ ዝናብ የመቀየር ልምምዳችን እያደገ ይገኛል። በቅርቡም ምርትን የሚያሳድጉ ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅመን ችግሮቻችንን ወደ ዕድል መቀየር ጀምረናል።

    አየር ንብረታችንን የሚያስተካክለውና የብዝኃ ዕጽዋትና የብዝኃ እንስሳት ሀብታችንን በእጅጉ ያሳድጋል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብራችን እንዲሁ ተጠቃሽ ነው። በቁጥር ግንባር ቀደም ያደረጉን የቀንድ ከብቶቻችን ከመቀንጨር ወጥተው ምርታማ እንዲሆኑ ያደርጋል። ወደየጎረቤት ሀገሩ የሸሹ የዱር አራዊትም ተመልሰው፣ ከታሪካዊና ባህላዊ መስህቦች ጋር የተዋደደ ተፈጥሮአዊ መስህብ በመሆን የቱሪስት ፍስትን እንዲጨምርና ኢኮኖሚያችን መስፈንጠር እንዲችል መደላድል ይሆናል ብዬ አምናለሁ።

    የሀገራችን ሕዝብ ሆይ፥

    ባለፉት ጥቂት ዓመታት ትኩረታችንን ሰቅዘው ከያዙት ጉዳዮች መካከል ሌላኛው የሕዳሴ ግድብን የተመለከተ ጉዳይ ነው። የዴሞክራሲ ጥያቄን አንድ ምዕራፍ ለማሳደግ የምርጫችን መሳካት ወሳኝ እንደነበረው ሁሉ፣ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግራችንን ለመቅረፍና ለዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች መቀላጠፍ ጉልህ አስተዋጽዖ ከሚያበረክቱ ፕሮጀክቶቻችን መካከል አንዱና ወሳኙ የሕዳሴ ግድብ ግንባታችን እንደሆነ ይታወቃል።

    የሕዳሴ ግድብ አጀንዳ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ከግድብም፣ ከኤሌክትሪክ ኃይል ምንጭነትም በላይ ነው። ከኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ባለፈ ዳግም የመነሣታችን ተምሳሌት ነው። በራስ ዐቅም የመቆም፣ በራስ ፍላጎት የመመራት፣ የሉዓላዊነታችን ምልክት፤ የሀገራዊ አንድነታችን ገመድ ነው። በሕዳሴ ጉዳይ ብዙ አይተናል፣ ብዙ ተፈትነንበታል። በራሳችን ዐቅም መቆማችን የሚያስደነግጣቸው፣ በፍላጎታችን መመራት መጀመራችን የሚቆጫቸው ብዙ ጋሬጣዎችን ሲጥሉብን ነበር። “ሚስማር አናቱን ሲመቱት ይበልጥ ይጠብቃል” እንዲሉ ሆኖ፤ በዓባይ ጉዳይ በገፉን ቁጥር እየቆምን፣ በተጫኑን ቁጥር እየበረታን፣ ባዋከቡን ቁጥር ይበልጥ እየጸናን አሁን የደረስንበት ቦታ ላይ ቆመናል። በቅርቡ ሁለተኛውን ዙር የውኃ ሙሌት አድርገን፣ በምርጫው ስኬት የተደሰትነውን ያህል፣ በሕዳሴያችንም ሐሴት እንደምናደርግ አልጠራጠርም።

    በሕዳሴ ግድብ ላይ ፍትሐዊ ተጠቃሚነታችን እንዲጠበቅልን እንጂ መቼም ቢሆን ሌሎች ሀገራትን የመጉዳት ፍላጎት ኖሮን አያውቅም። አሁንም ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ደግመን ማረጋገጥ የምንፈልገው ሐቅ፣ የዓባይ ወንዝ እንደሚያስተሳስራቸው ወንድም ሕዝቦች በእናንተ ላይ ምንም ዓይነት አሉታዊ ተጽዕኖ የመፍጠር ፍላጎት የለንም። ዛሬም ሆነ ወደፊት በጋራ ተጠቃሚነት ዙሪያ ለመመካከር በራችን ክፍት ነው። እኛንም ሆነ እናንተን ነጥሎ ተጎጂ ወይም ተጠቃሚ በሚያደርጉ አካሄዶች ላይ እንድንሳተፍ ኢትዮጵያዊ ማንነታችን አይፈቅም።

    ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለንም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከዚህ ኢትዮጵያዊ ማንነታችን የሚቀዳ ነው። በጋራ ተጠቃሚነት ዙሪያ ለመሥራት ሁሌም ዝግጁዎች ነን። የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ሰላሙ እንዲጠበቅ፣ የጋራ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ማኅበረሰብ እንዲፈጠር፣ በትብብርና በመግባባት እንድናድግ ኢትዮጵያ ትፈልጋለች፤ ጥሪም ታቀርባለች።

    የተከበራችሁ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፥

    የሀገራችን መጻኢ ጊዜ ብሩህ ለማድረግ በተገቢው መወጣት ከሚገቡን የቤት ሥራዎች መካከል አንዱና ዋነኛው ፖለቲካዊ ጉዳዮቻችንን በሠለጠነ መንገድ መምራት ነው። ከላይ በመግቢያዬ እንደገለጽኩት ይኼ ኃላፊነት በመንግሥትና በተመረጠው ፓርቲ ላይ ብቻ የሚጣል አይደለም፤ አንድ አካል ልሥራው ብሎ ቢነሣ እንኳን በአግባቡ የሚወጣው ጉዳይ እንዳልሆነ በተደጋጋሚ አይተናል። እንኳንስ የሠለጠነ የፖለቲካ ሥርዓት መገንባትን የሚያህል ነገር ይቅርና፣ አንድ ዙር ምርጫን ዴሞክራሲያዊ አድርጎ ለማጠነቀቅ ብዙ አካላት መረባረብ እንዳለባቸው ካለፍናቸው ምርጫዎች በሚገባ ተረድተናል። የዘንድሮውንም ምርጫ ካለ እናንተ ድጋፍና ትብብር ፍትሐዊና ዴሞራሲያዊ በሆነ መንገድ ማከናወን ባልተቻለ ነበር።

    በቀጣይም ዓመታት የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሂደታችን መሬት እንዲረግጥ የተለመደ ትብብራችሁና በየምዕራፉ ያላሰለሰ ድጋፋችሁ እንደሚያሻን ከወዲሁ ለመግለጽ እወዳለሁ። በሀገራችን የብልጽግና ጉዞ ውስጥ የሚኖራችሁ ድርሻ ወሳኝ እንደሆነ እናምናለን።

    የፖለቲካ ልዩነቶቻችን እንዳሉ ሆነው፣ ለሀገርና ለሕዝባችን በሚጠቅሙ ማናቸውም የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ አጀንዳዎች ላይ ከእናንተ ጋር በመግባባት ለመሥራት ዝግጁዎች ነን።

    ምርጫውን ስኬታማ ያደረጋችሁ ውድ የተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች፣

    ይህ ምርጫ የተሳካ እንዲሆን የምርጫ ቦርድ አመራሮችና ሠራተኞች፣ እንዲሁም የምርጫ አስፈጻሚዎችና ታዛቢዎች ሁሉ ከደም መሥዋዕትነት በመለስ ያለ ከፍተኛ ዋጋ ከፍላችኋል። ከግራ ከቀኝ የሚመጡትን ጫናዎች ተቋቁማችሁ በውጣ ውረዶች ሳትበገሩ ለሀገራችን የማይደበዝዝ የዴሞክራሲ አሻራ አትማችኋል፤ በዚህም ታሪክ ስማችሁን አድምቆ ይጽፈዋል።

    የጸጥታ አካላት፤ ምርጫው ሰላማዊ እንደሆን ጉልህ ሚና ተጫውታችኋል፤ እናንተ ዕንቅልፍ አጥታችሁ ሥጋቶቻችን ሁሉ እንደ ጉም እንዲተንኑ ስላደረጋችሁ ክብር ይገባችኋል። በተመሳሳይ፣ ፈጣንና ሚዛናዊ መረጃን ወደ ሕዝቡ በማድረስ በኩል የግልና የመንግስት ሚዲያዎች፤ እንዲሁም አጭር የጽሑፍ መልዕልት ስርጭት በኩል የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ሠራተኞች፣ ላበረከታችሁት አስተዋጽዖ ኢትዮጵያ ታመሰግናችኋለች።

    ውድ የፓርቲያችን አመራሮችና አባላት፥

    በዚህ ምርጫ ሕዝቡ ያስተላለፈውን መልእክት በሚገባ መረዳት የወደፊቱን መንገዳችንን ቀና እንደሚያደርገው እናምናለን። ሕዝቡ በአብላጫ ድምጽ እኛን የመረጠው ፓርቲያችን እንከኖች ስለሌሉበት አይደለም፤ ከነስሕቶቻችንን ዕድል ሰጠን እንጂ ድል አላደረግንም። ሕዝብ የመረጠን በአንድ በኩል ያጠፋናቸውን እንድናርም፣ በሌላ በኩል መልካም ጅማሮዎቻችንን እንድናስቀጥል፣ ከሀገር ግንባታ አንጻር በወሳኝ ደረጃ ላይ ያሉ የለውጥ ሥራዎችን በቀጣይ ጊዜያት ፈጽመን እንድናሰረክብ ነው። ሕዝባችን ጉድለቶቻችንን በሚገባ ያውቃል። ከስርቆት ዓመል ያልተላቀቁ፣ ለሰው ነፍስ ግድ የሌላቸው፣ ሕግን የማያከብሩ፣ ኃላፊነታቸውን የማይወጡ አመራሮች በመካከላችን መኖራቸውን ጠንቅቆ ያውቃል። ድምፁን ሲሰጠን ታረሙ፣ ውስጣችሁን አጥሩ እያለን ጭምር ነው። እኛም በተግባር ሆነን ማሳየት አለብን። ይኼን ማድረግ ካልቻልን ከአምስት ዓመት በኋላ በካርዱ እንደሚቀጣን እናውቃለን።

    በአሁኑ ምርጫ መምረጥ ያልቻላሁ ወገኖቻችን በሙሉ፥

    በልዩ ልዩ የጸጥታና የደኅንነት ምክንያቶች፣ እንዲሁም በሎጅስቲክና በተለያዩ ውሱንነቶች ምርጫው በተያዘለት ክፍለ ጊዜ መሠረት ከተቀረው ሕዝብ ጋር አብራቸሁ ድምፅ ባለመስጠታችሁ ታላቅ የሆነ ቅሬታ ፈጥሮብናል። ይኼ የሆነው ባልተጠበቁ ምክንያቶች እንደሆነ ግንዛቤ ትወስዳላችሁ የሚል ግምት አለን። ሁኔታዎች ተስተካክለው የምርጫ ቦርድ በወሰነው ቀን ምርጫው እንደሚደረግ እምነቴ ነው።

    ትግራይን በተመለከተ የትግራይ ሕዝብ በሚፈልገው መንገድ ከተደራራቢ ችግር የሚወጣበትን፣ ተያያዥ ሀገራዊ ችግሮች የሚፈቱበትን እና ሰላምና ደኅንነት የሚረጋገጥበትን የመፍትሔ አቅጣጫ እንከተላለን።

    በመጨረሻም፣ ከለውጡ ጊዜ አንሥቶ እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ሀገር አንድነትና ስለ ሕዝባችን ተጠቃሚነት ቀና ቀናውን በማሰብ በመንገዳችን ሁሉ ድጋፍ ሲያደርጉልን የነበሩ አካላትን ከልብ ሳላመሰግን አላልፍም። ኢትዮጵያ በታሪክ ለውጥ ላይ ናት። በዚህ የለውጥ ሂደት ተሳፍረን የተሻለች ሀገር እንገነባለን። በዚህ ምርጫ ኢትዮጵያችን አሸናፊ ስለሆነች በድጋሚ ለመግለጽ እወዳለሁ። ቀጣይ ዘመናችንን ብሩህ ያድርግልን፤ ሁላችንም እንኳን ደስ አለን።

    ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!
    ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
    ሐምሌ፣ 2013 ዓ.ም

    • በስድስተኛ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብልጽግና ፓርቲ 410 መቀመጫዎችን ማሸነፉን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሐምሌ 3 ቀን  2013 ዓ.ም. አስታውቋል። ዝርዝሩን ለማንበብ እዚህ ጋር ይጫኑ
    • የስድስተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ውጤት መታወቅን ተከትሎ የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ “ኢትዮጵያ ሀገራችን ተከብራ የምትኖረው ስንቻቻል፣ ስንደማመጥና የሌላውን ሃሳብ ስንቀበል ብቻ ነው” በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
    • ይህ ሀገራዊ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድ ትልቁን ሚና የተጫወተውን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን የሚመሩት ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ “ሀገራዊ ምርጫው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገለልተኝነት በይፋ የታየበት ነው” ብለዋል።

    ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ

    Anonymous
    Inactive

    ህወሓት ጠቡ ከኢትዮጵያ እና ከኢትዮጵያዊነት ጋር ነው

    በአቶ ዮሐንስ መኮንን

    “ከማዕከላዊው የመንግሥት የሥልጣን ማማ ተገፍቼያለ” ብሎ ያኮረፈው የህወሓት ቡድን ከሦስት ዓመታት በፊት የጦርነት ዳርዳርታ በጀመረ ሰሞን መገዳደል ማንንም አትራፊ ስለማያደርግ የጦርነት ጉሰማውን እንዲተው በሀገር ሽማግሌዎች፣ በልኂቃንም ሆነ በተራ ዜጎች ሳይቀር ተለምኖ ነበር። የህወሓት ሰዎች ግን “ጦርነት ባህላዊ ጨዋታችን ነው” እያሉ ያፌዙ እንደነበር ኢትዮጵያውያን ሁላችንም የምናስታውሰው የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው።

    የጦርነት ጉሰማው ድንበሩን አልፎ “የ45 ደቂቃ መብረቃዊ ጥቃት” ሲሉ በራሳቸው አንደበት በነገሩን አረመኔያዊ የክህደት እርምጃ ወገናቸው በሆነው የሀገር መከላከያ ላይ የፈጸሙት ጥቃት እና በማይ ካድራ ንጹሐን ላይ የፈጸሙት ጭፍጨፋ ለህወሓት ሰዎች እና ደጋፊዎቻቸው ዛሬ ላይ “ጀብድ” ይምሰላቸው እንጂ የፈጸሙት ተግር በታሪክ ፊት አንገታቸውን የሚያሰደፋ የነውር ጥግ ነበር።

    ይህንኑ የህወሓት አረመኔያዊ ተግባ ተከትሎ የመከላከያ ሠራዊታችን በወሰደው የአጸፋ እርምጃ ዋንኛው ዓላማ ህወሓትን ከነመዋቅሯ መደምሰስ ቢሆንም ጦርነቱ በንጹሓን ዜጎች ይልቁኑም በሴቶች እና በሕጻናት ላይ ያደረሰው ጉዳት የሚያሳዝነን እና የሚያሳፍረን ክስተት ነበር።

    ዛሬ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት በውጪ መንግሥታት ተጽእኖም ይሁን በጦርነቱ አክሳሪነት የተነሳ “የጽሙና ጊዜ ለመስጠት” የተናጥል የተኩስ አቁም ውሳኔ አሳልፎ ከክልሉ ሠራዊታችን ማስወጣቱ ተገቢ እርምጃ ነው። ይህ ማለት ግን “ትግራይን የራሱ ሉዓላዊት ሀገር አካል መሆኗ አበቃ” ማለት አይደለም። በግልጽ ቋንቋ ለመግለጥ “ህወሓት ይሻለናል” ለሚሉ አባላቶቿ ደጋፊዎቿ “ዕድል ለመስጠት ያለመ” መሆኑን እገነዘባለሁ።

    ይሁን እንጂ መንግሥት ተገፍቶ ሕግ ወደማስከበር ጦርነት ሲገባም ሆነ አሁን ትግራይን ለቅቆ ሲወጣ ጉዳዩን ያየዘበት መንገድ ሌላ ዘላቂ ሀገራዊ ችግር ተክሎብን እንዳያልፍ ሊጠነቀቅባቸው የሚገቡ ጉዳዮች እንዳሉ ይሰማኛል። በምክንያት ላስረዳ፡

    ህወሓት ያኮረፈውም ሆነ የተጣላው ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር እንጂ ከአንድ ሕዝብ ጋር እንዳልነበረ የሚስተው ያለ አይመስለኝም። ጦርነቱ እንደተጀመረ ተደራጅቶ በቅርብ ርቀት ላይ ገኝ የነበረው የአማራ ልዩ ኃይል ቀድሞ የህወሓትን ተስፋፊ ጦር መመከቱ የሚያስመሰግነው ተግባር መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በሂደት ግን በዓለም ዓቀፉ ማኅበረሰብም ሆነ በአንዳንድ “ልኂቃን” ጭምር የህወሓት ጠብ “ከአማራ ልዩ ኃይል” ጋር አስመስለው መግለጻቸው ተገቢ ካለመሆኑም በላይ የአንድን ጠባብ ቡድን የእብሪት ጦርነት በሁለት ሕዝቦች መካከል የተደረገ ጦርነት አስመስሎ ማቅረቡ ጉዳቱ ውሎ አድሮ የሚያመረቅዝ ቁስል እንዳተርፈን ያሳስበኛል። በእርግጥ የመከላከያ ሠራዊታችን ከሁሉም ብሔሮች የተውጣጣ ጦር መሆኑ እየታወቀ ተደጋግሞ “አማራ ልዩ ኃይል” የጦርነቱ ፊት አውራሪ ተደርጎ መሳሉ የህወሓት ጠብ ከአንድ ሕዝብ ጋር አስመስሎታል።

    በቀደም እለት ጠቅላይ ሚንስትሩ በፓርላማ ባደረጉት ንግግርም “የአማራ ሕዝብ ለህወሓት አይንበረከክም” የሚለው ንግገራቸው ምንም እኳን ሕዝቡን ለማጀገን እንደተጠቀሙበት ብረዳውም የአማራ ልዩ ኃይል ለሀገር አንድነት የከፈለውን መስዋእትነት ክልሉን ለመከላከል እንደተከፈለ መስዋእትነት አሳንሶ ወደማየት እንዳይተረጎም ያሳስበኛል።

    ዛሬ ደግሞ የጀርመኑ ዶቼቬሌ ሂውማን ራይት ዎችን ጠቅሶ እንደዘገበው ህወሓት “በአማራ ክልል ልዩ ኃይሎች ተይዘውብኛል” የሚላቸውን አካባቢዎች መልሶ ለመንጠቅ በርካታ ታጣቂዎቹን እያንቀሳቀሰ መሆኑን ሰምተናል። እንደዘገባው ከመጠለያ ካምፖች ሳይቀር ወጣቶችን በገፍ እየመለመለች ነው። (ህወሓት ሰንአፌ በረሃ አርቅቃ ኢትዮጵያ ላይ የጫነችውን “ሕገመንግሥት” ሳይቀር በተቃረነ መንገድ የአማራ ገበሬዎችን በማፈናቀል በወረራ የቀማቻቸውን ወልቃይት እና ሁመራን የመሳሰሉ ለም መሬቶች በግፍ መንጠቋ ይታወሳል)

    የህወሓትን ትፍራፊ ጦር እንደ አመጣጡ ለመመለስ የአማራ ልዩ ኃይል የሚያንስ ባይሆንም ትንኮሳውን ማስቆም ያለበት ዋንኛው ፊትአውራሪ ጦር ግን የሀገር መከላከያ ኃይል ነው ብዬ በጽኑ አምናለሁ። የልዩ ኃይል ተሳፎ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም የአማራ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ክልሎች ልዩ ኃይሎች በመከላከያ ሠራዊት ሥር ታቅፈው ስምሪት ሊሰጣቸው ይገባል።

    “ኢትዮጵያን ሳላፈርስ እንቅልፍ አይወስደኝም” ብሎ የማለውን የህወሓት ትርፍራፊ ጦር መመከት እና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም መደምስ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የቅድሚያ ቅድሚያ ኃላፊነት ነው። ምክንያቱም የህወሓት ጸብ ከኢትዮጵያ እና ከኢትዮጵያዊነት ጋር ነው!

    በአቶ ዮሐንስ መኮንን

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ፦ በሰሞነኛ ድረገጽ የአማርኛ ፎረም (semonegna.com/forums) ላይ የሚገኝ ማንኛውም ጽሑፍ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንጸባርቅ ሲሆን፥ ጽሑፉ የሰሞነኛ ኢትዮጵያንንም ሆነ የተሳታፊዎችን አመለካከትና ምልከታ ላይወክል ይችላል።

    ህወሓት ጠቡ ከኢትዮጵያ እና ከኢትዮጵያዊነት ጋር ነው

    Anonymous
    Inactive

    አዋሽ ባንክ እ.ኤ.አ. በ2020/21 የሂሣብ ዓመት ብር 5.58 ቢሊዮን ዓመታዊ ትርፍ አስመዘገበ

    አዲስ አበባ (አዋሽ ባንክ) – ላለፉት አምስት ተከታታይ ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የግል ባንኮች የመሪነት ስፍራውን ይዞ የቆየው አዋሽ ባንክ አሁን በተገባደደው የሂሣብ ዓመትም በዋና ዋና የባንኪንግ ዘርፎች የመሪነት ስፍራውን ይዞ መቀጠሉን ሰኔ 29 ቀን 2013 ዓ.ም ባካሄደው ዓመታዊ የበጀት መዝጊያ ስብሰባ ላይ አስታውቋል።

    ባንኩ በተጠናቀቀው ሂሣብ ዓመት ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ የተቀማጭ ሂሣብ መጠን በማስመዝገብ በባንኩም ሆነ በግል ባንኮች ታሪክ የመጀመሪያው የሆነውን ውጤት አስመዝግቧል። የባንኩ አጠቃላይ ተቀማጭ ሂሣብ ኤልሲ ማርጅንን (letter of credit margin) ጨምሮ ብር 107.7 ቢሊዮን ሲሆን፣ ይህም አሀዝ ከባለፈው ሂሣብ ዓመት ተመሣሣይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የብር 33.8 ቢሊዮን /የ46 በመቶ/ ዕድገት አሣይቷል።

    አዋሽ ባንክ ባሣለፍነው የሂሣብ ዓመት 100 አዳዲስ ቅርንጫፎችን ከፍቶ ለአገልግሎት ማብቃት የቻለ ሲሆን፤ ከሁለት ሚሊዮን በላይ አዳዲስ የተቀማጭ ሂሣብ ደንበኞችን በማፍራት ጠቅላላ የተቀማጭ ሂሣብ ደንበኞቹን ከ5 ሚሊዮን በላይ ማድረስ ችሏል። የቅርንጫፎች መስፋፋት ሕብረተሰባችን በየአካባቢው የባንክ አገልግሎቶችን እንዲያገኝ ከማስቻሉም በተጨማሪ አዳዲስ ደንበኞች የቁጠባ ባህላቸውን እንዲያሳድጉ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል። አዋሽ ባንክ ሕብረተሰቡ በቦታና በጊዜ ሳይገደብ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ የኤቲኤም (ATM)፣ የሞባይል እና የኢንተርኔት አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ባደረገው ጥረት እ.ኤ.አ. ሰኔ 2021 መጨረሻ ላይ 4 ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ አድርጓል። ይህም መንግሥት የፋይናንስ አካታችነትን እና ተደራሽነትን ለማስፋፋት የሚያደርገውን ብርቱ ጥረት አጋዥ እንደሆነ ይታመናል።

    አዋሽ ባንክ ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች የሰጠው ብድር መጠን በ2020/21 የሂሣብ ዓመት መጨረሻ ላይ የብር 30 ቢሊዮን /የ53 በመቶ/ እድገት በማሣየት ብር 87.1 ቢሊዮን ደርሷል።

    በውጭ ምንዛሪ ረገድም በ2020/21 የሂሣብ ዓመት ከተለያዩ የውጭ ምንዛሪ ምንጮች ከ906 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ማግኘት የቻለ ሲሆን፤ ይህም አሀዝ ከአምናው ተመሣሣይ ጊዜ አንጻር የ37 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ጭማሪ አሳይቷል። ለዚህም ዋና ዋና ምክንያቶች የአለም ኢኮኖሚ ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ተጽዕኖ ማገገም፣ የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ግኝት ማደግ እና ባንኩ የወሰዳቸው የተለያዩ የፖሊሲ እርምጃዎች ናቸው።

    አዋሽ ባንክ ከዛሬ 5 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የግል ባንኮች ታሪክ ከብር 1 ቢሊዮን በላይ ያልተጣራ ትርፍ አስመዝግቦ ታሪክ እንደሠራው ሁሉ ባሳለፍነው በጀት ዓመትም ከብር 5.58 ቢሊዮን በላይ ያልተጣራ ትርፍ በማስመዝገብ ሌላ ታሪክ ሠርቷል። ለዚህም ዋናው ምክንያት የባንኩ ገቢ አምና ከነበረበት ከብር 10.2 ቢሊÄን ወደ ብር 13.7 ቢሊዮን ማደጉ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።

    ባንኩ በተቀማጭ ሂሣብ፣ በብድር እና በትርፋማነት ብቻ ሳይሆን በተከፈለ ካፒታል መጠኑም የመሪነት ሥፍራውን እንደያዘ ቀጥሏል። የአዋሽ ባንክ የተከፈለ ካፒታል በዓመቱ በብር 2.23 ቢሊዮን ያደገ ሲሆን፤ እ.ኤ.አ. ሰኔ 2021 መጨረሻ ላይ ብር 8.2 ቢሊዮን ደርሷል። ይህ መጠን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሁሉም ነባር የግል ባንኮች ለወደፊቱ በ5 ዓመት ጊዜ ውስጥ እንዲደርሱበት ካስቀመጠው የ5 ቢሊዮን ብር መጠን በእጅጉ የላቀ ነው። አዋሽ ባንክ በአሁኑ ጊዜ በ566 ቅርንጫፎች እና ከ12 ሺህ በላይ በሆኑ ሠራተኞች አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

    በየዓመቱ ከፍተኛ በጀት በመመደብ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት የሚታወቀው አዋሽ ባንክ እ.ኤ.አ. በ2020/21 የሂሣብ ዓመት በተለያዩ የማኅበረሰብ ልማት ሥራዎች እና በበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ ለተሰማሩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ከብር 30 ሚሊዮን በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል።

    ምንጭ፦ awashbank.com

    አዋሽ ባንክ

Viewing 15 results - 61 through 75 (of 730 total)