Search Results for 'አሶሳ ዩኒቨርሲቲ'

Home Forums Search Search Results for 'አሶሳ ዩኒቨርሲቲ'

Viewing 11 results - 1 through 11 (of 11 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ከነሐሴ ወር 2010 ዓ.ም. ጀምሮ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ያገለገሉት ዶ/ር አብርሃም በላይ በጥር ወር 2012 ዓ.ም. የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሆነው መሾማቸውን ተከትሎ በምትካቸው አቶ አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሹመዋል።

    በጥር ወር 2012 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ከነሐሴ ወር 2010 ዓ.ም. ጀምሮ ያገለገሉት ዶ/ር አብርሃም በላይ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሆነው መሾማቸውን ተከትሎ አቶ አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሹመዋል።

    በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ከተማ በ1973 ዓ.ም. የተወለዱት አቶ አሸብር የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በዚያው በአምቦ አዲስ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት፤ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ደግሞ በአምቦ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል።

    የከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በቀድሞ የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፤ በአሁኑ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተከታትለው 1995 ዓ.ም. ላይ በሜካኒካል ኢንጂነሪንግ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል። ከግሪንዊች ዩኒቨርሲቲ (Greenwich University) በዓለምአቀፍ ቢዝነስ የማስተርስ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል። ከስዊዲን ሀገር ኬ. ቲ. ኤች ሮያል ኢንስቲትዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ (KTH Royal Institute of Technology) በዘላቂ ኢነርጂ ምህንድስና ዘርፍ ተጨማሪ ኮርሶችን ወስደዋል።

    አቶ አሸብር በሜካኒካል ምህንድስና ከተመረቁ በኋላ በበደሌ ቢራ ፋብሪካ ጀማሪ ሜካኒካል ኢንጂነር የሥራ መደብ ላይ ለ7 ወራት አገልግለዋል። ከነሐሴ 1996 ዓ.ም. ጀምሮ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተቀጥረው በጊምቢ–መንዲ–አሶሳ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ሥራቸውን ጀምረዋል። በተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከጥር ወር 1997 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ግንቦት ወር 2003 ዓ.ም. ድረስ መሪ መካኒካል ኢንጂነር ሆነው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎችን በመቆጣጠር ተቋሙን አገልግለዋል።

    ከግንቦት 2003 ዓ.ም. እስከ መስከረም ወር 2012 ዓ.ም. ድረስ የገባ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ በመሆን ካገለገሉ በኋላ ከጥቅምት ወር 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ይህን ኃላፊነት እስከተቀበሉበት ቀን ድረስ የኃይል ማመንጫዎች ግንባታ ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

    አቶ አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን በተለያዩ የሥራ መደቦች በባለሙያነትና በኃላፊነት ለ16 ዓመታት አገልግለው ከየካቲት 09 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ተቋሙን በዋና ሥራ አስፈፃሚነት እንዲመሩ በተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ተሹመዋል።

    ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት ዶ/ር አብርሃም በላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድን እንዲመሩ ተጨማሪ ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።

    ዶ/ር አብርሃም እስካሁን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ወደትክክለኛው መስመር እንዲመጣና እንዲፋጠን ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ ሲያደርጉ ቆይተዋል። በተለይም በኢፌዲሪ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ሜቴክ ተይዘው የነበሩ ሥራዎች ልምድ ላላቸው ዓለም አቀፍ ተቋራጮች እንዲሰጥና ተቋራጮቹም በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ እንዲሰሩ በማድረግ በኩል ጉልህ የአመራር ሚና ነበራቸው። የገናሌ ዳዋ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የካሳ ጥያቄ እልባት አግኝቶ ለምርቃት እንዲበቃም ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።

    ቢተገበሩ ወጪ ከማውጣት ባለፈ ውጤታማ የማይሆኑ ረዥም ዓመታት የወሰዱ ፕሮጀክቶች በህጋዊ መንገድ እንዲቋረጡ በማድረግ ተቋሙንና መንግስትን ከተጨማሪ ወጪ ማዳን ችለዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጤናማ የፋይናንስ አቅም እንዲኖረው በማድረግና በተቋሙ የአሰራር ስርዓቶችን በማሻሻል ተጨባጭ አምጥተዋል።

    የተቋሙን የዕዳ ጫና በተመለከተ ተቋሙ የሚመለከተውን ብድር ብቻ እንዲሸከምና ሌሎች ብድሮች ግን ወደ ብድሩ ባለቤቶች እንዲተላለፉ የሚያስችል ቁርጠኛ አቋም በመያዝ የብድር ጫናው እንዲቀንስ አድርገዋል።

    በመሆኑም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተጀመረው ለውጥ እንዲቀጥል በማሰብ እና በተቋሙ ላከናወኑት ሥራ እውቅና ለመስጠት ተቋሙን በሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢነት እንዲመሩ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተጨማሪ ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።

    ዶ/ር አብርሃም ባሳዩት ውጤት በተቋሙ አመራር እና ሰራተኞች ዘንድ ተወዳጅ የነበሩና የለውጥ መሪ ተምሳሌት ተደርገው የሚወሰዱ ነበር። የተቋሙ አመራርና ሠራተኞችም ዶ/ር አብርሃም በሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢነት ዳግም ወደተቋሙ በመምጣታቸው ደስታቸውን ገልፀዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

    Semonegna
    Keymaster

    በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሥር ከሚገኙት ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የጎንደር ዩንቨርሲቲ በርካታ ቁሳዊና መንፈሳዊ እሴት የያዙ መጻህፍት ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገሩ ለማድረግ ሥርዓተ ትምህርት (curriculum) ተቀርጾና መምህራን ተቀጥረው የግእዝ ቋንቋን ለማስተማር መዘጋጀቱን አስታውቋል።

    ጎንደር ዩንቨርሲቲ የግእዝ ቋንቋ በመጀመሪያ ዲግሪ መስጠት ሊጀምር ነው

    ጎንደር (ኢዜአ) – ጎንደር ዩንቨርሲቲ የመጥፋት አደጋ የተጋረጠበትን የግእዝ ቋንቋ ለመታደግ በአዲሱ የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ ዲግሪ የቋንቋ ትምህርት ለመስጠት መዘጋጀቱን አስታወቀ።

    የጎንደር ዩንቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኘ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደተናገሩት ኢትዮጵያ የግእዝ ቋንቋ ባለቤት ብትሆንም ለቋንቋው ማደግና መስፋፋት የተሰጠው ትኩረት አነስተኛ ነው። “በዚህም ሳቢያ ቋንቋው የመጥፋት አደጋ የተጋረጠበት ከመሆኑም በላይ በግእዝ ቋንቋ የተጻፉ በርካታ የብራና መጻፍትን ለጥናትና ምርምር ስራ ለማዋል አልተቻለም “ብለዋል።

    ዘመናት የተሻገሩና በቋንቋው የተጻፉ ለዘመናዊ ሕክምና ሙያ የሚያግዙ፣ ምጣኔ ሀብታዊ፣ ባህላዊና ታሪካዊ ፋይዳ ያላቸው በርካታ መጻሕፍት በኃይማኖት ተቋማትና ገዳማት ተወስነው መኖራቸውን አመልክተዋል።

    ዩንቨርሲቲው እነዚህን ቁሳዊና መንፈሳዊ እሴት የያዙ መጻህፍት ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገሩ ለማድረግ ሥርዓተ ትምህርት (curriculum) ተቀርጾና መምህራን ተቀጥረው የግእዝ ቋንቋን ለማስተማር መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።

    በትምህርት ዘመኑ 50 ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅት መደረጉን ያመለከቱት ዶክተር ካሳሁን፥ ትምህርቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠውም በኤክስቴንሽንና በክረምት መርሃ ግብሮች መሆኑን አስረድተዋል። ትምህርቱ ሰፊ ተቀባይነት እያገኘ ሲሄድ መደበኛ ተማሪዎችን ጭምር በቀጣይ በግእዝ ቋንቋ አሰልጥኖ ለማስመረቅ መታቀዱን አመልክተዋል።

    በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሥር ከሚገኙት ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የጎንደር ዩንቨርሲቲ፥ በአጠቃላይ 87 የመጀመሪያ ዲግሪ፤ 158 ሁለተኛ ዲግሪና 29 የሦስተኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች እንዳሉት ተገልጿል። በመደበኛ፣ በተከታታይና በክረምት መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የሚከታታሉ ከ45ሺ በላይ ተማሪዎች በዩንቨርሲቲው ይገኛሉ።

    ምንጭ፦ ኢዜአ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    —–
    ተመሳሳይ ዜናዎች

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኢትዮጵያ ― ዜናዎችና ጠቃሚ መረጃዎች


    Semonegna
    Keymaster

    የ10ኛ ክፍል ውጤት ፈተናውን ለተፈተኑ ለተማሪዎች ይፋ ተደረገ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ (NEAEA) የ2011 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ10ኛ ክፍል ውጤት መስከረም 02 ቀን 2012 ዓ.ም. ከ10 ሰዓት ጀምሮ ይፋ እንደሚሆን ባስታወቀው መሠረት ተማሪዎች በኤጀንሲው ድህረ ገጽ http://www.app.neaea.gov.et ወይም በአጭር የጽሁፍ መልእክት 8181 ላይ ID- በማለት አድሚሽን ቁጥራቸውን በማስገባት መመልከት እንደሚችሉ አሳውቋል።

    • መጀመሪያ የኢጀንሲውን ድረ ገጽ http://www.app.neaea.gov.et ይክፈቱ፤
    • ቀጥሎ Student Result የሚለውን ይጫኑ፤
    • ቀጥሎ Click here for Grade 10 result የሚለውን ይጫኑ።

    **. የተማሪዉ/ዋ/ን መለያ ኮድ ወይም አድሚሽን ቁጥር ማስገባት
    **. ከተዘረዘሩት የትምህርት አይነቶች ውስጥ የማይቀሩና በሌላ የትምህርት ዓይነት መተካት የሌለባቸው፦ ሒሳብ (Maths), እንግሊዝኛ (English) እና እና የሲቪክስ ትምህርት (Civics) ውጤቶችን በመመዝገብ እና ተጨማሪ 4 (አራት) የተሻሉ የትምህርት ዓይነት ውጤቶችን መዝገቦ በአጠቃላይ 7 የትምህርት ዓይነቶች ሲሆኑ በዚሀም መሠረት የ7ቱን የትምህርት ዓይነቶች አጠቃላይ ድምር ማግኘት አና ለ7 በማካፈል ውጤቱን ማወቅ ይቻላል ማለት ነው።

    ሌሎች ዜናዎች፦

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የ10ኛ ክፍል ውጤት


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አመራር የ 2012 ዓ.ም. መማር ማስተማርና የተማሪዎች ቅበላ ዝግጅትን አስመልክቶ ውይይት አደረገ። ዶ/ር ፋሲል ንጉሴ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ዲን ከ 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ለሚገቡ አዲስ ተማሪዎች በ4 ዓመት ቆይታ ጊዜአቸው ተማሪዎቹን መሠረታዊ ዕውቀት ሊያስጨብጧቸው የሚችሉ የትምህርት ዓይነቶች እንደሚሰጡና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደትን ለማረጋገጥ የሚያስችል በቂ የዝግጅት ምዕራፍ እንደተወጠነ ገልጸዋል።

    “ለሰላም መደፍረስ መነሻ የሚሆኑ ጉዳዮችን እየለየን ከሚመለከታቸው ጋር በማቀናጀት መፍትሔ እንዲያገኙ እንጥራለን፤ የመማር ማስተማር ሂደቱ መስመሩን ጠብቆ እንዲሄድ የቁጥጥር ሥርዓቶችን አጠናክረን እንቀጥላለን፤ ብሔርን፣ ሀይማኖትንና ፖለቲካን መሠረት ያላደረጉ የዶርም ድልድሎችን እናደርጋለን” በማለት ዶ/ር ፋሲል በ 2012 ዓ.ም. ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደትን ለማረጋገጥ የምንከተላቸው አቅጣጫዎች በሚል ርዕስ ባቀረቡት ገለጻ (presentation) ላይ ጠቁመዋል።

    የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃናም የዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ዲን የጠቆሙትን ሲያጠናክሩ “ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ በብሔር እየተደራጁ የሚመጡ ማናቸውም ዓይነት የተማሪዎች አደረጃጀት፣ የተማሪዎች ክበባት… ወዘተ አናስተናግድም” በማለት አሳስበዋል።

    ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአንዳንድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ተፈጥረው በነበሩ ብሔር-ተኮር የተማሪዎች ግጭትን አስመልክተው ዶ/ር ፋሲል የሚከተለውን ብለዋል፥ “ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ በዩኒቨርሲቲያችን ውስጥ በብሔርና በሃይማኖት መሰባሰብ፣ መከፋፈል፣ መጣላት፣ መደባደብ የንብረት የአካልና የሕይወት መጥፋት ጉዳት የማድረስ እኩይ ተግባራት እንዳይኖሩ ተቋማችን ጠንክሮ ይሠራል” በማለት አስረድተዋል።

    በዋነኝነት ለ 2012 ዓ.ም. አዲስ ገቢና ነባር የቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር ተማሪዎች የሚደረግላቸውን የአቀባበልና የመተዋወቂያ ገለጻ (orientation) አሰጣጥን አስመልክተው ፕሮፌሰር ጣሰው ሲያብራሩ፥ “ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ ሥራ ላይ መዋል የሚጀምር በተማሪዎች፣ በወላጆቻቸውና በዩኒቨርሲቲያችን መካከል የሚፈረም ውል ይኖረናል፤ ተማሪዎቹ ዩኒቨርሲቲያችን እንደገቡ በቅድመ ምረቃ ትምህርት አስተባባሪዎች እና ነባርና ልምድ ባላቸው መምህራን ስለ ዩኒቨርሲቲያችን አጠቃላይ መረጃ ይሰጣቸዋል፤ የመጀመሪያ ዓመት ለሆኑት ተማሪዎች ስለሚወስዷቸው የትምህርት ዓይነቶችና ፋይዳቸው፣ ስለተማሪዎች ሥነ-ምግባር መመሪያና ስለተቋማችን ሥነ-ሥርዓት፣ ሕግና ዲሲፕሊን ጉዳዮች ማብራሪያ እንዲያገኙ ይደረጋል” በሚል ገልጸዋል።

    የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ የምጣኔ ሃብት መምህርና በአሁን ጊዜ የተቋሙ የቦርድ አባል ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተቋሙ በሚሻሻልበት ጉዳይ ላይ ሃሳባቸውን ሲሰጡ ተቋሙን በከፍተኛ ደረጃ ለማዘመንና ከሌሎች ታዋቂና ስመ-ጥር ዩኒቨርሲቲዎች ተርታ እንዲመደብ ለማስቻል የመምህራን፣ የአስተዳደር፣ የማህበረሰቡና የመንግሥት ርብርብ በጣም አስፈላጊ እንደሆነ በመድረኩ ላይ ተናግረዋል።

    ፕሮፌሰር ብርሃኑ እንደሃገር እንድንቀጥል ባሉት ገለጻቸው ሲናገሩ፥ “የሃገሪቱ የትምህርት አወቃቀር የሚሻሻልበትን አቅጣጫ እንቀይስ፤ ፈጣሪና አምራች ዜጋ እንድናገኝ ተማሪዎቻችንን በጥልቀት የሚያስቡና የሚያስተውሉ እናድርጋቸው፤ ለዚህም ዩኒቨርሲቲው ጠቃሚ ሃሳቦች በነጻነት የሚንሸራሸሩበትና ልቆ የተገኘው ሃሳብ ተደማጭነትን አግኝቶ የሚተገበርበት ቁልፍ ቦታ እናድርገው” በሚል ገለጻቸውን ሰጥተዋል።

    ምንጭ፦ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    2012


    Semonegna
    Keymaster

    የትምህርት ሚኒስቴር፣ የአገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲና የክልል ትምህርት ቢሮዎች በጋራ በሰጡት መግለጫ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ላይ ውሳኔ ላይ ከመደረሳቸው በፊት በፈተናው ያጋጠመውን ችግር ኮሚቴ ተቋቁሞ ሲመረምር መቆየቱን ገልጸዋል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢፌዴሪ የትምህርት ሚኒስቴር በዘንድሮው የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ላይ ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት ውሳኔ አሳለፈ።

    ሚኒስቴሩ በተፈተኞች ወጤት መሰረት እስካሁን ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ባደረገው ጥናት ማረጋገጡንም አስታውቋል።

    የትምህርት ሚኒስቴር፣ የአገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ (NEAEA) እና የክልል ትምህርት ቢሮዎች በጋራ በሰጡት መግለጫ በፈተናው ያጋጠመውን ችግር ኮሚቴ ተቋቁሞ ሲመረምር መቆየቱን ገልጸዋል።

    በዚሁ መሰረት በተፈጥሮ ሳይንስ (natural science) እና ማኅበራዊ ሳይንስ (social science.) መስኮች ሰኔ 6 እና 7 ቀን 2011 ዓ.ም. ፈተናቸው የተሰጡ የትምህርት ዓይነቶች ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ ታሳቢ የተደረጉ ሲሆን ሰኔ 10 እና 11 ቀን 2011 ዓ.ም. የተሰጡ ፈተናዎች ውጤቶች ግን ተሰርዘዋል።

    ሰኔ 6 እና 7 ቀን 2011 ዓ.ም. የተሰጡ የትምህርት ዓይነቶች ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ እንዲያገለግሉ የተወሰነው ሂሳብ፣ እንግሊዝኛ፣ ፊዚክስ፣ አፕቲትዩድ እና ጂኦግራፊ የትምህርት ዓይነቶች ናቸው።

    ሰኔ 10 እና 11 ቀን 2011 ዓ.ም. የተሰጡ ፈተናዎች ከግምት ውስጥ ያልገቡት እጅግ የጋሸበ ውጤት የተመዘገበባቸው በመሆኑ እንደሆነ ተገልጿል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    —–
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት


    Anonymous
    Inactive

    አሶሳ ዩኒቨርሲቲ የ2012 ዓ.ም. ነባርም ሆነ አዲስ ተማሪዎች ላይ በጠቅላላ የመማር-ማስተማር ሂደት ሰላማዊ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት መሪዎችን በማሳተፍ ውይይት እንደሚካሄድ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት አስታውቀዋል።

    አሶሳ (ኢዜአ) – አሶሳ ዩኒቨርሲቲ የ2012 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን የመማር-ማስተማር ሒደቱን ሰላማዊ ለማድረግ የሚረዱትን ቅድመ ዝግጅቶች ማጠናቀቁን አስታወቀ።

    በአሶሳ ዩኒቨርሲቲው በ2011 ዓ.ም. የትምህር ዘመን በተከሰተ ግጭት የሶስት ተማሪዎች ህይወት ሲያልፍ ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙ ይታወሳል።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ከማል አብዱራሂም ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደገለፁት፥ ከዚህ በፊት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ለሚያነሷቸው ጥያቄዎችን በወቅቱ ምላሽ አለመስጠት ለግጭት መፈጠር ምክንያት ተደርጎ ይጠቀስ ነበር።

    በደረሰው ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጥፋት የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ በእጅጉ ማዘኑን የገለፁት ፕሬዝዳቱ፥ ችግሩ እንዳይደገም በመምህራንና በተማሪዎች ቅንጅት የሚተገበር ጠንካራ ዕቅድ አዘጋጅቷል።

    በዕቅዱ መሠረት የዩኒቨርሲቲው የ2012 ዓ.ም. ነባርም ሆነ አዲስ ተማሪዎች ላይ በጠቅላላ የመማር-ማስተማር ሂደት ሰላማዊ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት መሪዎችን በማሳተፍ ውይይት እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።

    ተማሪዎች በግጭት ላለመሳተፍ ዩኒቨርሲቲው ባዘጋጀው የጋራ መግባቢያ ሰነድ ላይ እንደሚፈራረሙም ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል። እርሳቸው እንደሚሉት ባለፈው የትምህርት ዘመን በማኅበራዊ መገናኛ ብዙሃን (social media) የተሳሳተ መረጃ በማሰራጨት በዩኒቨርሲቲው ግቢ ግጭት እንዲባባስ የሚጥሩ በርካታ መምህራን ነበሩ።

    በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ፖለቲካን ከትምህርት የመነጠል ሥራ ጀምረናል ያሉት ዶ/ር ከማል፥ ይህንን ተከትሎ በአሁኑ ወቅት ከችግሩ የተነካኩ አንዳንድ መምህራን በፈቃዳቸው የዝውውርና የሥራ መልቀቂያ እያቀረቡ ነው ብለዋል።

    በዩኒቨርሲቲው ውስጣዊ ችግር ምክንያት ግጭት ዳግም ይከሰታል ብለን አናምንም የሚሉት ዶክተር ከማል፥ የተማሪዎች መማክርት አደረጃጀት፣ ምግብ፣ መኝታ፣ ኢንተርኔትን መሠል የተማሪዎችን ጥያቄዎችን መመለስ ትኩረት እንደተሰጠው ገልጸዋል።

    ከሠላማዊ የመማር ማስተማር ተግባር ባሻገር አሶሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት (research and community services) እንዲሁም የትምህርት ጥራትን ማስጠብቅ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

    በአሁኑ ወቅት በዩኒቨርሲቲው የክረምት ትምህርት እየተከታተሉ ከሚገኙ ተማሪዎች መካከል በኬሚስትሪ የ1ኛ ዓመት የክረምት ተማሪ ለማ ታገሰ በሰጠው አስተያየት የዩኒቨርሲቲ የጸጥታ የተረጋጋ ነው። አልፎ አልፎ የምግብ አቅርቦት ችግር እንዳለበት ጠቅሶ የመጸዳጃ ቤትና ተያየዥ አገልግሎቶች ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባም ጠቁሟል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አሶሳ ዩኒቨርሲቲ


    Anonymous
    Inactive

    ክብርት ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምርቃት በዓል ላይ ያስተላለፉት መልዕክት
    —–

    ክብርት ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የምርቃት በዓል ላይ በመገኘት ለ2011 ዓ.ም. ምሩቃን (Class of 2019) “የዓመታት ልፋታችሁ ውጤት ለሚታዩበት ዕለት እንኳን በቃችሁ፤ እንኳን ደስ አላችሁ” በማለት የደስታ መግለጫ መልዕክት አስተላልፈዋል።

    ምሩቃኑ ሚዛናዊና ምክንያታዊ በሆነ አስተሳሰብ በመመራት አገራችን ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ፈታኝ ሁኔታ ለመታደግ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ፕሮፌሰር ሂሩት ጥሪ አቅርበዋል።

    መማር ማለት እውቀት መሰብሰብ ብቻ አይደለም ያሉት ሚኒስትሯ፥ የተማረ ሰው በእያንዳንዱ በሚያጋጥመው ነገር ላይ ጠለቅ ያለ ዕይታ ያለውና ለሁሉም ነገር በቂ ምርምር በማድረግ ሚዛናዊና ምክንታዊ መፍትሄ የሚፈልግ በመሆኑ ተመራቂ ተማሪዎች የቀሰሙትን ዕውቀትና ክህሎት ወደ ተግባር በመቀየር ለአገርና ለወገናቸው እንዲሰሩበትም አስገንዝበዋል።

    የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ሃይማኖት ዲሳሳ በበኩላቸው፥ ዩኒቨርሲቲው ከ3ኛ ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች (3rd Generation Universities) አንዱ ሲሆን ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ዘንድሮ ለ6ኛ ጊዜ 2,711 ተማሪዎችን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ማስመረቁን ገልጸዋል።

    ፕሬዚዳንቱ ዘንድሮ በዩኒቨርሲቲው ተከስቶ የነበረውን የፀጥታ ችግሮች ተቋቁሞ የመማር ማስተማር እና የማኅበረሰብ አገልግሎት ሥራዎችን በአግባቡ በመፈፀም ለዚህ እለት እንዲበቃ ትብብርና ድጋፍ ላደረጉት የአካባቢው ህብረተሰብ፣ የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ፣ የጸጥታ ኃይሎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

    ተመራቂ ተማሪዎችም በቀሰሙት ዕውቀት እና ክህሎት ህብረተሰባቸውን ከማገልገል ባሻገር ለሀገሪቱ ሰላምና እድገት መረጋገጥ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    null

    Semonegna
    Keymaster

    የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን አስመርቀዋል
    —–

    አዲስ አበባ – የተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎቻቸውን ሰኔ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. አስመርቀዋል።

    በዕለቱ ተማሪዎቻቸውን ካስመረቁ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥም የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ፣ መቱ ዩኒቨርሲቲ፣ ዲላ ዩኒቨርሲቲ እና አሶሳ ዩኒቨርሲቲ ይገኙበታል።

    የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተለያየ የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 313 ተማሪዎቹን በዕለቱ አስመርቋል። ከተመረቁት ውስጥም 1 ሺህ 112 በቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር (በመጀመሪያ ዲግሪ) ያስመረቀ ሲሆን፥ 201 ተማሪዎችን ደግሞ በድህረ ምረቃ መርሃ ግብር ነው ያስመረቀው።

    ጅማ ዩኒቨርሲቲም በዕለቱ በመጀመሪያ ዙር ዩኒቨርሲቲ በተለያየ የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 683 ተማሪዎቹን አስመርቋል። ከእነዚህም ውስጥ 341 በድህረ ምረቃ ሲሆን፥ 1 ሺህ 11 ደግሞ ሴቶች መሆናቸው ታውቋል።

    በተመሳሳይ ዲላ ዩኒቨርሲቲም በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 4 ሺህ 726 ተማሪዎቹን በዕለቱ አስመርቋል። በዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች የምረቃ በዓል ላይ የተገኙት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስተር ዲኤታ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ፥ በዘንድሮው ዓመት በመላው ሀገሪቱ ከ175 ሺህ በላይ ተማሪዎች እንደሚመረቁ አንስተዋል። ተመራቂ ተማሪዎች ለሀገራቸው የሚሰሩ ሊሆኑ እንደሚገባም ፕሮፌሰር አፈወርቅ መልእክት አስተላልፈዋል። ዲላ ዩኒቨርሲቲ በዕለቱ ካስመረቃቸው ተማሪዎቹ ውስጥ 500 ተማሪዎችን በሁለተኛ ዲግሪ ነው ያስመረቃቸው።

    ወለጋ ዩኒቨርሲቲም በዕለቱ በተለያየ የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 3 ሺህ 682 ተማሪዎቹን በዕለቱ አስመርቋል። ከተመረቁት ተማሪዎች ውስጥ 2 ሺህ 139 ሴቶች ሲሆኑ 1 ሺህ 543 ደግሞ ወንዶች መሆናቸው ተገልጿል። በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው 295 ተማሪዎችን በሁለተኛ ዲግሪ ያስመረቀ2 ሲሆን፥ 8 ተማሪዎችን ደግሞ በ3ኛ ዲግሪ ወይም በዶክትሬት ዲግሪ አስመርቋል።

    መቱ ዩኒቨርሲቲም በተለያየ የትምህርት መሰኮች ሲያሰለጥናቸው የነበረውን ከ2 ሺህ 300 በላይ ተማሪዎቸ በዛሬው ዕለት አስመርቋል። በምረቃ ሥነ-ስርዓት ላይ የተገኙት ግብርና ሚኒስተር ዲኤታና የመቱ ዩኒቨርሰቲ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሳኒ ሬዲ መንግስት ለሰው ሀብት ልማት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥው እየሠራ ባለበት መመረቃቸውንና ከተመራቂ ተማሪዎች የሚጠበቀው ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ተካልኝ ቃጄላ በበኩላቸው፥ ዩኒቨርሲቲው በዚህ ዓመት ብዙ ፈታኝ የሆኑ የውስጥና የውጭ ተግዳሮቶችን አልፎ ለዚህ መብቃቱን አስታውሰዋል።

    በተመሳሳይ አሶሳ ዩኒቨርሲቲ 2 ሺህ 714 ተማሪዎችን በተለያዩ የትምህርት መርሓ ግብሮች አስመርቋል። ከነዚህ ውስጥ 930 ሴት ተመራቂዎች መሆናቸው ታውቋል። ዩኒቨርሲቲው አሁን ለ6ኛ ጊዜ እያስመረቀ ሲሆን ከተመሰረተበት ከ2004 ዓም ጀምሮ አጠቃላይ 12 ሺ 450 ተማሪዎችን አስመርቋል። በዕለቱ በተካሄደው የምረቃ ሥነ-ስርዓት ላይ የሳይንስ እና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያምን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች ተገኝተዋል። ፕሮፌሰር ሂሩት ኢትዮጵያ ካለችበት ሁኔታ እንድትወጣ የተማረው ሀይል ዋነኛ አካል ነው ብለዋል።

    ምንጭ፦ ኤፍ.ቢ.ሲ

    Anonymous
    Inactive

    ከአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተመረቁ
    —–

    የአሶሳ ዩንቨርሲቲ በመደበኛና በማታ በተለያዩ መርሀ ግብሮች ሲያሰምር የነበረውን ተማሪዎች ሰኔ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. አስመረቀ። በኅዳር 2011 ዓ፣ም በተፈጠረው ግጭትና አለመግባባት የመማር ማስተማር ሂደት ተስተጓጎሎ እንደነበር እና ለሦስት ተማርዎች ሕይወት ህልፈት ምክንት መሆኑም ይታወሳል።

    ምንጭ፦ DW Amharic

    Semonegna
    Keymaster

    በሦስት መስኮች ዩኒቨርሲቲዎቹን መደልደል ያስፈለገው፥ እስካሁን የትምህርት ተቋማቱ በሁሉም የትምህርት ዘርፎች ለማስተማር ያደረጉት ጥረት እምብዛም ውጤታማ ስላልነበር እንደሆነ ተነግሯል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች የምርምር፣ የቲቺንግና የፖሊ ቴክኒክ ዩኒቨርሲቲ ተብለው ለሦስት ተከፍለው እንዲሠሩ የሚያደርግ ጥናት እያለቀ መሆኑንና በጥናቱ ውጤትም ላይ በቅርቡ ውይይት እንደሚደረግ፣ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስትር ሂሩት ወልደማርያም (ዶ/ር) ለሪፖርተር ጋዜጣ ገለጹ። ምደባው ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ብለዋል።

    ዩኒቨርሲቲዎችን በተልዕኮና በትኩረት አቅጣጫ የመደልደል ነገር በአዲሱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ ተመልክቷል ያሉት ሚኒስትሯ፥ ለምርምር የተሻለ የመሠረት ልማትና የሰው ኃይል ያላቸው ዩኒቨርሲቲዎች የጥናትና ምርምር ዩኒቨርሲቲ መደብ ውስጥ እንደሚገቡና በዶክትሬት ዲግሪ ደረጃ ፕሮግራሞችንም እንደሚሰጡ አስረድተዋል። የንድፈ ሐሳብና ተግባራዊ ትምህርት አጣምረው የሚሰጡ ፖሊ ቴክኒክ ዩኒቨርሲቲዎች መደብ ሥር የሚገቡት ለተግባር ትምህርት የተሻለ የመሠረተ ልማት ዝግጅት ያላቸው ይሆናሉ ተብሏል። ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት የሚሆኑ ሠልጣኞችን እንዲያፈሩና ለቴክኒክና ሙያ ተቋማትም የበቁ መምህራንን እንዲያወጡ ይጠበቅባቸዋል ያሉት ዶክተር ሂሩት ናቸው። የተቀሩት የማስተማር ተግባር (ቲቺንግ) ላይ የሚያተኩሩ መርሀ ግርብሮች ላይ የሚያተኩሩ ዩኒቨርሲቲዎች ሆነው እንደሚቀጥሉም ታውቋል።

    በሦስት መስኮች ዩኒቨርሲቲዎቹን መደልደል ያስፈለገው፥ እስካሁን የትምህርት ተቋማቱ በሁሉም የትምህርት ዘርፎች ለማስተማር ያደረጉት ጥረት እምብዛም ውጤታማ ስላልነበር እንደሆነ ተነግሯል።

    ሰባት ዩኒቨርሲቲዎች፣ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እና STEMpower ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ

    “ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በማስተማሩም፣ በምርምሩም፣ በቴክኖሎጂውም፣ በግብርናውም፣ በሁሉም ዘርፎች ነው የሚያስተምሩት። ይህ ደግሞ ውጤታማ ሊሆኑ በሚችሉበት መስክ እንዳይሠሩና ሀብትም እንዲበታተን አድርጓል” ያሉት ሚኒስትሯ፥ ድልድሉም ዩኒቨርሲቲዎቹ እንዳላቸው የመሠረት ልማት ዝግጅትና ያሉበት አካባቢ ከሚሰጣቸው መልካም አጋጣሚ አንፃር እየታየ ነው ብለዋል።

    እንደ ላሊበላና አክሱም ባሉ አካባቢዎች የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች አርኪዮሎጂ ላይ ያተኮሩ የልህቀት ማዕከላት (center of excellence) ቢሆኑ የተሻለ ውጤት እንደሚያስገኙ፣ በግብርና ላይ ተሞክሮና ታሪክ ያላቸው እንደ ሐሮማያ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ በግብርና ውጤታማ የሆነ ባለሙያዎች ማፍራት እንደሚችሉ አስረድተዋል። “ሁሉም ላይ እንሥራ ሲሉ ግን ችግር ነው። በሁሉም ዘመናዊ ማሽኖችን፣ የምርምር ግብዓቶችን፣ ሪፈራል ሆስፒታሎችን መገንባትና ማሟላት አይቻልም፣ የአገርም ሀብት ይባክናል” ብለዋል።

    ምንጭ፦ አሶሳ ዩኒቨርሲቲ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    ዩኒቨርሲቲዎች በሦስት መስኮች

    Semonegna
    Keymaster

    ዶ/ር ሂሩት ወልደማርያም በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በአማራ እና በኦሮሞ ብሄር ተማሪዎች መካከል በተነሳው ግጭት የሶስት ተማሪዎች ህይወት ማለፉን ገልፀው፥ የተለየ ፍላጎት ያላቸው ኃይሎች በተማሪዎች መካከል የብሄር ግጭት እንዲነሳ በማድረግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከማስተጓጎል በላይ ለስው ህይወት መጥፋት ምክንያት መሆናቸውን ተናግረዋል።

    አዲስ አበባ (የትምህርት ሚኒስቴር) – በዩኒቨርሲቲዎች ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር አጠቃላይ ማህበረሰቡ ከአካባቢው አስተዳደር ጋር በጋራ እንዲሠራ ተጠየቀ።

    በአሁኑ ወቅት በመላ ሃገሪቱ እየተካሄደ የሚገኘውን ለውጥ ለመቀልበስ የሚፈልጉ ኃይሎች ፊታቸውን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም በማዞር ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደቱን በማወክና ግጭቶች እንዲፈጠሩ በማድረግ ግጭቶቹም የብሄር ግጭት መልክ እንዲይዙ በማድርግ ከፍተኛ ሁከት እና አለመረጋጋት በዩኒቨርሲቲዎች እንዲቀሰቀስ እያደረጉ መሆኑ ተደርሶበታል።

    ይህንኑ ሰሞኑን በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች የተከሰተውን አለመረጋጋትና ሁከት አስመልክቶ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሯ ዶ/ር ሂሩት ወልደማርያም ኅዳር 12 ቀን 2011 ዓ.ም በፅህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ “ዩኒቨርሲቲዎች ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ የተለያየ አስተሳሰብና ክህሎት ያላቸው ወጣቶች የተሰባሰቡበት ቦታ መሆኑን ገልፀው፥ እነዚህን ወጣቶች ለተለያየ የፖለቲካ አጀንዳ ማስፈፀሚያ ለማድረግና እርስ በእርሳቸው ያለመተማመንና በመካከላቸውም የብሄር ግጭት በማስነሳት የመማር ማስተማር ሥራውን ከማስተጓጎላቸውም በላይ በግጭቱ ውድ የሆነውን የሰው ህይወት እንዲጠፋ ምክንያት ሆነዋል“ ብለዋል።

    ዶ/ር ሂሩት አያይዘውም ሰሞኑን በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በአማራ እና በኦሮሞ ብሄር ተማሪዎች መካከል በተነሳው ግጭት የሶስት ተማሪዎች ህይወት ማለፉን ገልፀው፥ በግጭቱ ህይወታቸውን ላጡ ውድ ተማሪዎቻችን የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገልፀው ለተማሪ ቤተሰቦችና ለማህበረሰቡ መፅናናትንም ተመኝተዋል።

    አሁን የሚስተዋለውን ችግር ለመፍታትም ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፤ የዩኒቨርሲቲ ቦርድ አባላት፤ የሁለቱም ብሄር ተወካዮችና ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ጋር በመሆን የዕርቅና ሰላም የማስፈን ሥራ ለመሥራት ወደ ዩኒቨርሲቲው እንደሚሄድ ሚኒስትሯ ጨምረው ገልፀዋል።

    ዩኒቨርሲቲዎች የዕውቀት የክህሎትና የአዳዲስ ሃሳቦች ማፍለቂያ ተቋሞች መሆናቸውን የገለፁት ሚኒስትሯ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ሙሉ ጊዜያቸውን ለትምህርትና ለምርምር በማዋል የመጡበትን ዓላማ ማሳካትና በቆይታቸውም ነገሮችን በደንብ የሚያስቡና አንዳንድ ወደ ጥፋት የሚሄዱ ተማሪዎችንም ወደ በጎነት የሚመልሱ ሊሆኑ እንደሚገባቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

    በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምቹና ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር የአካባቢው ማህበረሰብ የአስተዳደር አካላትና የፀጥታ አካላትም በጋራ ሊሠሩ እንደሚገባ በመግለጫው ተካቷል።

    ምንጭ፦ የትምህርት ሚኒስቴር

    ተጨማሪ ትምህርት ተኮር ዜናዎች

    የመማር ማስተማር ሂደት

Viewing 11 results - 1 through 11 (of 11 total)