Search Results for 'ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት'

Home Forums Search Search Results for 'ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት'

Viewing 15 results - 1 through 15 (of 26 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም መመዘኛዎች ውጤታማ አፈፃፀም ማስመዝገቡን አስታወቀ
    የባንኩ ጠቅላላ ሃብት 1 ነጥብ 3 ትሪሊየን ብር ደርሷል
    የንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ከፍተኛ ሥራ አስፈጻሚዎች ሹመት ጸደቀ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም መመዘኛዎች ውጤታማ አፈፃፀም ማስመዝገቡን ፤ እንዲሁም የባንኩ ጠቅላላ ሃብት 1 ነጥብ 3 ትሪሊየን ብር መድረሱን አስታውቋል።

    በባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከሚያዝያ 17-19/ 2015 ዓ.ም በተካሄደው የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተቀማጭ ገንዘብ አሰባሰብ፣ ብድር በመስጠትና በመሰብሰብ፣ የዲጂታል ባንክ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ፣ በውጭ ምንዛሪ ግኝትና አቅርቦት እንዲሁም በሌሎች ፋይናንስና ፋይናንስ ነክ ባልሆኑ አፈፃፀሞች ውጤታማ ሥራ መሠራቱ ተጠቁሟል።

    በዘጠኝ ወራት ውስጥ ከ123 ቢሊየን ብር በላይ ተጨማሪ ተቀማጭ ገንዘብ መሰብሰብ መቻሉ በጉባዔው የተገለፀ ሲሆን፣ የባንኩ ጠቅላላ ሃብትም 1 ነጥብ 3 ትሪሊየን ያህል ብር መድረሱ ታውቋል።

    የዲጂታል ባንክ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ ባንኩ ወጤታማ እንደነበር የተብራራ ሲሆን፤ በዘጠኝ ወራት ውስጥ በዲጂታል ባንክ አማራጮች ብቻ 2 ነጥብ 1 ትሪሊዮን ብር ተንቀሳቅሰሷል ብሏል ባንኩ በሥራ አፈፃፀም ግምገማው።

    ባንኩ በዘጠኝ ወራት ውስጥ በሁሉም መመዘኛዎች መልካም አፈፃፀም ነበሩት ያሉት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ በቀጣይ በተለይ ዋና ዋና የትኩረት ዘርፎች በሆኑት በተቀማጭ ሃብት አሰባሰብ፣ በዲጂታል ባንክ አገልግሎት፣ በብድር አሰጣጥና አሰባሰብ፣ በውጭ ምንዛሪ ግኝት እንዲሁም የባንኩን የሪፎርም (reform) ሥራዎች በማስቀጠል በትኩረት ሊሠራ ይገባል ብለዋል።

    የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ተክለወልድ አጥናፉ በበኩላቸው ፋይናንስም ሆነ ፋይናንስ ነክ ባልሆኑ ዘርፎች የታዩትን አፈፃፀሞች፤ መልካሞቹን በማጠናከር ድክመቶችን ደግሞ በማረም በቀጣይ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ሁሉም የባንኩ ማህበረሰብ በአንድ ልብ ሊሠራ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት።

    በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ላይ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት፣ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላትና ከፍተኛ የሥራ አመራሮች፣ የሁሉም ዲስትሪክቶች ዳይሬክተሮች እና የልዩ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆች ተሳትፈዋል።

    ከባንክ ዜና ሳንወጣ፥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አምስት የንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ከፍተኛ ሥራ አስፈጻሚዎችን ሹመት ማጽደቁን አስታውቋል። በዚህም መሠረት፥ አቶ ሰይፉ አገንዳ ኬርጋ – ቺፍ የከስተመርና ኦፕሬሽንስ ኦፊሰር (Chief Customer and Operations Officer)፣ አቶ ሰለሞን ጎሽሜ በጅጋ – ቺፍ የኮርፖሬት ሰርቪስስ ኦፊሰር (Chief Corporate Services Officer)፣ አቶ መልካሙ ሰለሞን ይመር – ምክትል ፕሬዚዳንት ሂዩማን ካፒታል (Vice President of Human Capital)፣ አቶ አብርሃም ተስፋዬ አበበ – ምክትል ፕሬዚዳንት የስትራቴጂና ማርኬቲንግ (Vice President of Strategy and Marketing) እና አቶ አሚነ ታደሰ ተስፉ – ምክትል ፕሬዚዳንት የኢንተርናሽናል ባንክ ኦፕሬሽን (Vice President of International Bank’s Operation) ሆነው ተሹመዋል።

    ብሔራዊ ባንክ ሹመቱን ማጽደቁን ባሳወቀበት ደብዳቤ ላይ እንደገለጸው፥ በባንክ ሥራ አዋጅ ቁጥር 592/2000፣ በተሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1159/2011 እና ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር SBB/79/2021 አንጻር የተላኩለትን ሰነዶች እና ሌሎች ማስረጃዎች ላይ ተገቢውን ማጣራት አድርጎ መሆኑን አረጋግጧል።

    ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በቅርቡ የስትራቴጂክ (መሪ) እቅድ ክለሳ ያደረገ ሲሆን፤ ይኸው የከፍተኛ ኃላፊዎች ሹመትም ከዚሁ ክለሳ ጋር ተያይዞ የተዘጋጀውን አዲስ የባንኩን አደረጃጀት መሠረት ያደረገ ነው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክንብ ኢንተርናሽናል ባንክ

    Semonegna
    Keymaster

    “መደበኛ ፓስፖርት ለማውጣት አገልግሎት አሰጣጡ ምቹ ባለመሆኑ ለእንግልት ተዳርገናል” ― ተገልጋዮች
    “በጉዳዩ ላይ በቅርቡ መግለጫ እሰጣለሁ” ― የኢምግሬሽን፣ ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ

    አዲስ አበባ (አዲስ ዘመን) – መደበኛ ፓስፖርት ለማውጣት ከፍተኛ መጉላላት እየደረሰባቸው መሆኑን ተገልጋዮች ቅሬታ አቀረቡ። የኢምግሬሽን፣ ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ በበኩሉ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ለቀረበለት ተደጋጋሚ ጥያቄ በጉዳዩ ላይ በቅርቡ መግለጫ እሰጣለሁ ከማለት ውጪ መረጃ ሊሰጥ አልቻለም።

    በአዲስ አበባ መደበኛ ፓስፖርት ለማውጣትም ሆነ ለማደስ ወደተቋሙ የሚሄዱ ተገልጋዮች በተቋሙ ባለው ምቹ ያልሆነ አሠራር ምክንያት ለከፍተኛ እንግልት እየተዳረጉ መሆኑን ይገልጻሉ። ተገልጋዮቹ እንደሚሉት በተቋሙ አገልግሎቱን ለማግኘት ከሌሊት 9፡00 ሰዓት  ጀምሮ ተሰልፎ ወረፋ ከመጠበቅ ጀምሮ ፓስፖርቱ አልቆም ለማግኘት ያለው ሂደት ውስብስብና ለከፍተኛ እንግልት የሚዳርግ ነው።

    ነዋሪዎቹ እንደሚሉት ፓስፖርት አገልግሎትን ለማግኘት በኦንላይን (online) አማካኝነት ምዝገባ የሚካሄድ ቢሆንም፥ ከዚያ በኋላ በተቀጠሩበት ዕለት ሌሊት ወጥቶ ወረፋ መጠበቅ፣ ከዚያም በኋላ ሂደቱን ሲያልፉ ፓስፖርት ለማግኘት ያለው አሠራር ተገልጋይን የሚያማርር ነው።

    የአዲስ አበባ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ መዲና ጂብሪል፥ ለልጆቻቸው ፓስፖርት ለማውጣት በስም ዝርዝር ምደባ መሠረ ከካዛንቺስ ፖስታ ቤት እንዲወስዱ የተገለጸላቸው ቢሆንም፥ ከታኅሣሥ ወር ጀምሮ ከፖስታ ቤቱ አልደረሰም የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ገልጸዋል።

    ወደ ኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት ተመልሰው መጠየቅ እንዳለባቸው የተነገራቸው ወይዘሮ መዲና፥ ከዋናው መሥሪያ ቤት ወደፖስታ ቤት በየጊዜው እያመላለሷቸው መቸገራቸውን በምሬት አስረድተዋል።

    ከዚህ ባለፈ በኢምግሬሽን መግቢያ በሮች ላይ ጥበቃዎችና ተራ አስከባሪዎች ወደ ውስጥ እንዳታስገቡ የሚል ትዕዛዝ ተሰጥቶናል በሚል ተገልጋዮችን ለመምታት የሚጋበዙ መሆናቸውን ገልጸው፤ በዚህም የሚመለከተውን አካል ለመጠየቅም ሆነ ለማነጋገር እንዳልቻሉ ጠቁመዋል።

    ችግሩን በተመለከተ ለማን አቤት ይባላል የሚሉት ወይዘሮ መዲና፥ ዜጎችን የሚያጉላሉ አሠራሮችን ማስተካከልና አገልግሎቱን የተሟላ ማድረግ ይገባል ብለዋል። መደበኛ ፓስፖርት ለማውጣት አስፈላጊውን ማስረጃ ከሰጠችና ከተመዘገበች አንድ ወር ከአሥራ አምስት ቀን እንደሆናት የምትገልጸው ሌላኛዋ የአዲስ አበባ ነዋሪ ወይዘሪት ሰናይት ንጉሴ ነች።

    የአስቸኳይ ፓስፖርት ከመከልከሉ በፊት መደበኛ ፓስፖርት ለማውጣት ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት በመሄድ ማመልከቷን ትገልጻለች። ኦርጅናል የልደት ካርድ፤ መታወቂያና የትምህርት ማስረጃዎችን እንዲሁም አስፈላጊውን መረጃ ሁሉ አሟልቻለሁ። አሻራ የሰጠሁ ቢሆንም ማስረጃውን አጣርተን እንጠራሻለን የሚል ምላሽ ቢሰጠኝም እስካሁን ምላሽ አላገኘሁም ትላለች።

    እኔ ሻይና ቡና በመሸጥ የምተዳደር ነኝ። በሕጋዊ መንገድ ወደ ሌላ አገር ሄጄ ለመሥራት ብዩ ፓስፖርት ለማውጣት ፈልጊያለሁ ስትል ሁኔታዋን አስረድታለች።፡ ከለሊቱ 9፡00 ሰዓት ጀምሮ ተራ ለመያዝ ወደኢምግሬሽን የምትሄድ መሆኑን በመግለጽ፤ እንግልቱ ግን ወደ ኢምግሬሽን በተደጋጋሚ የሄደች ቢሆንም ሳንደውል ለምን ትመጫለሽ የሚል ምላሽ እንደተሰጣትና፤ ጉዳዩን ለተቋሙ ቅሬታ ሰሚዎች ያቀረበች ቢሆንም ምንም ማድረግ እንደማይችሉ እንደተነገራት አስረድታለች።

    የጅማ ከተማ ነዋሪው አቶ አብዲሳ ታደሰ በበኩላቸው፥ በከተማው የኢምግሬሽን፣ ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በተደጋጋሚ ያቀረበው የፓስፖርት ይሰጠኝ ጥያቄ ምላሽ ባለማግኘቱ ወደዋናው መሥርያ ቤት ቢመጡም እዚህም ምላሽ ሊያገኝ እንዳተሰጣቸው ይገልጻሉ።

    አቶ አብዲሳ አስፈላጊ ናቸው የተባሉ መረጃዎችን ሁሉ ይዘው መቅረባቸውን በመጥቀስ ከጥቅምት ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎቱን ሳያገኙ እየተጉላሉ መሆኑን ገልጸዋል። የፓስፖርት ሂደቱን ሲጀምሩ በሦስት ወር እንደሚሰጣቸው የተነገራቸው ቢሆንም በተቀጠሩበት ቀን ፓስፖርቱን መውሰድ እንዳልቻሉ ጠቁመዋል።

    የቅርጫፉን ኃላፊ ስለጉዳዩ ማነጋገሩን የሚገልጸው አቶ አብዲሳ፥ ፖስታ ቤት ሂድ በማለት እንደመለሱለት ቢናገርም ፖስታ ቤት ግን ፓስፖርቱን ሊያገኝ እንዳልቻለ አስረድቷል። በዚህ የተነሳ ወደውጭ አገር ለመሄድ ያሰበውን የቪዛ ዕድል ማጣቱን በምሬት ገልጿል።

    ችግሩ ከዋናው መሥሪያ ቤት ነው የሚል ምላሽ እንደተሰጠው ጠቁሞ፤ በወቅቱ ወደአዲስ አበባ ኢምግሬሽን ለመምጣት የመሸኛ ደብዳቤ እንዲሰጡት በጠየቀበት ወቅት ተጨማሪ 600 ብር በድጋሚ መክፈል እንደሚጠበቅበት የተገለጸለት መሆኑን አስረድቷል።

    የፓስፖርት አገልግሎትለማግኘት እየተጉላሉ የሚገኙ ዜጎች ቀልጣፋ አሠራር እንዲፈጠርና በኢሚግሬሽን አገልግሎትና በፖስታ ቤቶች መካከል ተገቢው መናበብ ሊፈጠር ይገባል ሲሉ ጠይቀዋል።

    ጉዳዩን በተመለከተ የኢምግሬሽን፣ ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲን በስልክና በደብዳቤ በተደጋጋሚ በመጠየቅ ምላሽ ለማግኘት የተደረገው ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል። ኤጀንሲው በጉዳዩ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ በቃል ደረጃ ቢያሳውቅም ይህን ዜና የዘገበው የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ወደህትመት እስከገባበት ሰዓት ድረስ ምንም ዓይነት መግለጫ እንዳልተሰጠ ማረጋገጥ ተችሏል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

    Semonegna
    Keymaster

    ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያግዝ የመምህራን አቅም ማጎልበቻ ፍኖተ-ካርታ ማዘጋጀቱን ገለጸ

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያግዝ የመምህራን አቅም ማጎልበቻ ፍኖተ-ካርታ ማዘጋጀቱን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ብርሀነመስቀል ጠና ገለጹ።

    መንግሥት ዩኒቨርሲቲው በትምህርት ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን በመደገፍ ረገድ የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ብርሀነመስቀል ጠና ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ ከመዋቅር ጀምሮ ማሻሻያዎች እየተደረጉ ስለመሆናቸው ተናግረዋል።

    ለአብነትም 10ኛ ክፍል ይሰጥ የነበረው ብሔራዊ ፈተና በ12ኛ ክፍል እንዲሰጥ ከማድረግ ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች በ3 ዓመት ይመረቁ የነበረውን ወደ 4 ዓመት እንዲያድግ መደረጉን አስታውሰዋል።

    ባለፉት ዓመታት በተለይ በትምህርት ፍኃዊነትና ተደራሽነት ላይ በርካታ ሥራ የተሠራ ቢሆንም በትምህርት አግባብነትና ጥራት ላይ የተሳካ ወይንም አጥጋቢ ሥራ ባለመሠራቱ ውጤት ሊመዘገብ አልተቻለም ብለዋል። ለዚህም በቅርቡ የወጣው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት የኢትዮጵያ የትምህርት ጥራት ችግር ምን ላይ እንዳለ በግልጽ አሳይቷል ብለዋል።

    በተመሳሳይ ከዚህ ቀደም ለመምህራን ምዘና ተሰጥቶ በርካቶቹ ዝቅተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን አውስተው፤ ይህ ለትምህርት ጥራት ችግሩ ዓይነተኛ አስተዋፆኦ እንዳለው ነው ያስረዱት። ለተማሪዎቹ ዝቅተኛ ውጤት መመዝገብ መምህራንን ጨምሮ አጠቃላይ የትምህርት ማኅበረሰቡ ኃላፊነት ያለበት በመሆኑ ችግሩን በጋራ መፍታት ይገባል ነው ያሉት።

    መንግሥት የትምህርት ዩኒቨርሲቲ አለመኖር ለትምህርት ጥራት መጓደል አንዱ ምክንያት መሆኑን በመረዳት ችግሩን ለማቃለል ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ማቋቋሙን ገልፀዋል። ጨምረውም፥ በተለያዩ ችግሮች እየተፈተነ የሚገኘውን የኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ ለማከም ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ እንደሚገኝ አንስተዋል።

    ዩኒቨርሲቲው የመምህራንን ትምህርት ዋነኛ ምሰሶ በማድረግ የትምህርት አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ አማካሪዎችና ፖሊሲ አውጪዎችን ማፍራት ላይ አተኩሮ እየሠራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በመሆኑም ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ስብራቱን ለመጠገን የሚያስችል የመምህራን አቅም ማጎልበቻ ፍኖተ-ካርታ ማዘጋጀቱን ነው የተናገሩት። ፍኖተ-ካርታው በቀጣይ ለትምህርት ሚኒስቴር እንደሚቀርብም ነው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ብርሃነመስቀል ጠና የገለጹት።

    መንግሥት ዩኒቨርሲቲው በትምህርት ዘርፍ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን በመደገፍ ረገድ የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል። ሁሉም ባለድርሻ አካላት የመምህራን ሙያ በማክበርና የማስከበር ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልፀው፥ የመምህራን ዕውቀትንና አቅምን ማጎልበት ደግሞ ለነገ የማይባል የዛሬ የቤት ሥራ መሆኑን አመላክተዋል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ

    Semonegna
    Keymaster

    ተሰርዞ የነበረው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ወጣ ((የዕድለኞች ስም ዝርዝር))

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዚህ ቀደም ተሰርዞ የነበረውን የ20/80 እና የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ አወጣ። የ14ኛዉ ዙር የ20/80 እና 3ኛዉ ዙር የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች (condominium houses) ዕጣ የማውጣት ሥነ-ሥርዓት ህዳር 6 ቀን 2015 ዓ.ም ተካሂዷል።

    በዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ተወካዮች በታዛቢነት ተገኝተዋል።

    በዕጣው የ20/80 የቤት ልማት ፕሮግራም 18,930 ቤቶች፣ በ40/60 ደግሞ 6,843 ቤቶች እንዲሁም ተጨማሪ 18 ስቱዲዮ ቤቶች በድምሩ 25,791 ቤቶች በዕለቱ ዕጣ ወጥቶባቸዋል።

    የጋራ ቤቶች (condominium houses) ዕጣ ሐምሌ 01 ቀን 2014 ዓ.ም ወጥቶ የነበረ ቢሆንም በዕጣው ማውጣት ሂደት በገጠመ ችግር ምክንያት ዕጣው በመሰረዙ ነው አሁን በድጋሚ የዕጣ ማውጣት ሂደት የተከናወነው።

    የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንዳሉት፥ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ከግንባታ እስከ ዕጣ ማውጣት ሂደት ባለፉት ጊዜያት ከውስጥም ሆነ ከውጭ በርካታ ችግሮች አስተናግዷል። ከዚህ አንፃር ዛሬ የወጣው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ በርካታ ችግሮችን በማለፍ በስኬት መከናወኑን አንስተዋል።

    በተለይ በለውጡ ዋዜማ የሥራ ተቋራጮች ሥራውን አቋርጠው የመጥፋት፣ የመሠረተ ልማት ዝርፊያ የግንባታ ጥራት ችግር፣ የፋይናንስ እጥረትን ጨምሮ ዘርፉ የተወሳሰበ ሂደት ውስጥ ለማለፍ ተገድዷል ነው ያሉት።

    የከተማ አስተዳደሩ እነዚህን ውስብስብ ችግሮች ለመፍታት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ21 ቢሊዮን ብር በላይ በመበደር ጥረት ሲያደርግ መቆየቱንም እንዲሁ አስታውቀዋል።

    ሆኖም ከዚህ በፊት ዕጣ የወጣባቸውን የጋራ ቤቶች ለተጠቃሚዎች ለማድረስ የተደረገው ሙከራ በተለያዩ የሌብነት ተግባራት ምክንያት ሳንካ ገጥሞት እንደነበርም ጠቅሰዋል። ይህ ደግሞ ለረጅም ዓመታት በትዕግስት ሲጠባበቅ ለነበረው ሕዝብ አሳዛኝ ዜና እንደነበር አውስተዋል።

    በዕጣ ማውጣት ሂደቱ ከተፈጠረው ችግር ጀርባ የቤት ልማት መርሃ-ግብርን ለግል ጥቅም ማካበቻ ከማድረግ ባለፈ በመንግሥትና በሕዝብ መካከል አለመተማመን ለመፍጠር ያለመ ሴራም እንደነበር ነው የተናገሩት። የከተማ አስተዳደሩ የገጠመውን ችግር ለሕዝብ በግልፅ ይፋ በማድረግ በአጥፊዎች ላይ ተጠያቂነትን ማስፈኑን ጠቅሰዋል።

    ተዓማኒነቱ የተረጋገጠ አዲስ የዕጣ ማውጫ ሥርዓት በማልማትም ከዚህ ቀደም ተሰርዞ የነበረው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ አሁን (ህዳር 6 ቀን 2015 ዓ.ም) በድጋሚ እንዲወጣ መደረጉን ተናግረዋል። የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ በድጋሚ እንዲወጣ ያለመታከት ጥረት ያደረጉ ሰራተኞችና አመራሮችን አመስግነው ባለእድለኞችንም እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።

    ዛሬ የጋራ መኖርያ ቤት ዕጣ ለደረሳችሁ 25,791 ባለ እድለኞች እንኳን ደስ አላችሁ!!
    ለዘመናት በትዕግስት ስትቆጥቡና ስትጠባበቁ የነበራችሁ የ14ኛ ዙር የ20/80 እንዲሁም የ3ኛ ዙር የ40/60 የጋራ መኖርያ ቤት ባለ እድለኞች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ!!
    ከዚህ ቀደም በቤት የዕጣ አወጣጥ ሂደት በገጠመን የማጭበርበር ችግሮች ምክንያት የእጣ አወጣጥ ሂደቱ ቢዘገይና እክል ቢገጥመውም የህዝብን ሃብት ለማዳን ያደረግነውን ጥረት በመረዳት ከጎናችን ስለሆናችሁና በከፍተኛ የሃላፊነት ስሜት የህግ የበላይነት እንዲከበር በትዕግስትና በማስተዋል እገዛችሁ ላልተለየን የከተማችን ነዋሪዎች በሙሉ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው፡፡
    እንዲሁም ለዚህ ስራ ስኬት በትጋት የተሳተፋችሁ ፤በየደረጃው የምትገኙ የስራ ሃላፊዎች፣ አመራሮች ፣ሰራተኞች፣ ባለሙያዎችና የፌደራል ተቋማት ስላበረከታችሁት ታላቅ አስተዋፅኦ በከተማ አሳተዳደሩ ስም ልባዊ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ!!
    አሁንም የጀመርነውን ከተማችንን እንደ ስሟ ውብና ደማቅ ለነዋሪዎቿ የምትስማማ የማድረግ ስራ ቃላችንን ጠብቀን በመቀጠል ከተማችንን ተወዳዳሪ ብቁና የቱሪስት መዳረሻ የማድረግ ስራ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል፡፡
    ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን አብዝቶ ይባርክ!!
    ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

    የ14ኛ ዙር የ20/80 የጋራ መኖርያ ቤት ባለ ዕድለኞችን ለማየት ተከታዩን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ቴሌግራም ማስፈንጠሪያ ይጫኑ – EBC Telegram Link

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት

    የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ወጣ

    Semonegna
    Keymaster

    በሦስት ዓመታት ከ70 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ያገኛሉ

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – በኢትዮጵያ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ከ70 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ እንዲኖራቸው የሚደረግ መሆኑን የብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ፕሮጀክት አስታወቀ።

    የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት ከኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ጋር በመተባበር በዲጅታል መታወቂያ የሕግ አግባብነት፣ ዓላማና አዋጅ ጋር በተያያዘ ውይይት አድርጓል።

    የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮጀክት የባለድርሻ አካላት ግንኙነት መሪ ሚና አወል፤ ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ አንድን ሰው ማንነት በእርግጠኝነት መለየት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። መታወቂያው ዕድሜ፣ ፆታ፣ የአስር ጣቶች አሻራ፣ የመኖሪያ አድራሻና ሌሎች ገላጭ መረጃዎችን የሚይዝ መሆኑንም አስረድተዋል።

    በአሁኑ ወቅት አርሶ አደሮችና በገጠር አካባቢ ያሉ ሰዎች እንዴት መመዝገብ ይችላሉ የሚለውን ለማወቅ በአዲስ አበባ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብና ሲዳማ ክልሎች 125 ሺህ ዜጎች በሙከራ ደረጃ ተመዝግበው ውጤታማነቱ ተረጋግጧል ብለዋል። በ2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ የሚኖሩ 12 ሚሊዮን ዜጎችን የብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልጸዋል። ለዚህም በንግድ ባንክ፣ ኢትዮ-ቴሌኮም እና መሰል አገልግሎት በሚሰጥባቸው ተቋማት አገልግሎት ለማግኘት ሲሄዱ በቀላሉ መመዝገብ ይችላሉ ብለዋል።

    የብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ፕሮጀክት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮዳሄ ዘሚካኤል፥ ዲጅታል መታወቂያ በኢትዮጵያ የሚኖር ማንኛውም ዜጋ የራሱን ማንነት የሚገልጽበት መለያ ነው። ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ በኪስ የሚያዝ ወረቀት ሳይሆን የራሱ መለያ /ፋይዳ/ የሚባል ቁጥር ብቻ ይዞ በማንኛውም ቦታ በቁጥሩ ምክንያት አገልግሎት ማግኘት የሚችሉበት ዘመናዊ አሠራር መሆኑንም አስረድተዋል። ከቤቱ ሆኖ የባንክ አካውንት መክፈት፣ የኢንሹራንስ አገልግሎት ማግኘትና በአገልግሎት ሰጭውና ተቀባዩ ዘንድ መተማመን መፍጠር ያስችላል ብለዋል።

    በዚህም እስከ 2018 ዓ.ም ከ70 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ እንዲኖራቸው ለማስቻል ዕቅድ መያዙን አቶ ዮዳሄ ተናግረዋል። የፎቶ ኮፒና ሌሎች የህትመት ሥራዎች ሁሉ የንግዱ ማኅበረሰብ በየሱቆቹ ማስመዝገብ የሚችልበትን አሠራር እንዘረጋለን ሲሉም ተናግረዋል።

    የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ፥ ብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ ብዙ ትኩረት ሳይሰጠው የቆየ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይም ለጤናው ዘርፍ የጎላ ሚና ያለው መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ የዲጅታል መታወቂያ ባለመኖሩ ምክንያት ዲጅታል የጤና መሣሪያዎችን ወደ ሥራ ማስገባት እንዳልተቻለም ጠቅሰዋል። በመሆኑም ብሔራዊ የዲጅታል መታወቂያው ሥራ መጀመር በመላ ሀገሪቱ ያሉ ከ40 ሚሊየን በላይ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች መታወቂያቸውን በቀላሉ አድሰው የተቀላጠፈ የጤና አገልግሎት ማግኘት ያስችላቸዋል ብለዋል። የብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ የኢትዮጵያን የጤና አገልግሎት አሰጣጥ በማዘመን የጎላ ሚና እንዳለው ገልጸው በቅርቡ ወደ ሥራ እንዲገባ አስፈላጊውን ሁሉ እገዛና ትብብር እናደርጋለን ሲሉ አረጋግጠዋል። ዘገባው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ነው።

    የብሔራዊ ዲጅታል መታወቂያ

    Semonegna
    Keymaster

    ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ 70 አዳዲስ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት ክፍሎችን ሊከፍት ነው

    ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በአዲሱ የትምህርት ዘመን በሁለተኛ እና ሦስተኛ ድግሪ 70 አዳዲስ ትምህርት ዓይነቶችን ለመክፈት መዘጋጀቱን አስታወቀ። ይህም ዩኒቨርሲቲው በሁለተኛ እና ሦስተኛ ዲግሪ የሚሰጣቸውን የትምህርት ዓይነቶች 101 እንደሚያደርሰው ተጠቁሟል።

    የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታምሩ አኖሌ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንዳሉት በ2013 የትምህርት ዘመን በዩኒቨርሲቲው አዲስ ከሚከፈቱት 19 የሦስተኛ ዲግሪ መርሀግብሮች ውስጥ የገዳ እና የአስተዳደር ጥናት አንዱ ነው።

    ቀሪዎቹ የተለያዩ የሁለተኛ ዲግሪ መርሀግብሮች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ይህም ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በሦስተኛ ዲግሪ ይሰጥ የነበረውን አንድ መርሀግብር ወደ 20 ከፍ ሲያደርገው የሁለተኛ ዲግሪውን ደግሞ ከ30 ወደ 81 የትምህርት ክፍሎች እንደሚያሳድገው ዶ/ር ታምሩ አመላክተዋል። የትምህርት ክፍሎችን ፍላጎት ከመለየት አንስቶ የየሥርዓተ ትምህርት (curriculum) ቀረጻና ትችት እንዲሁም የሰው ኃይልና ግብዓት የማሟላት ሥራዎች በጥንቃቄ መከናወናቸውንም በማከል አስረድተዋል።

    የመማር ማስተማር ሂደቱን ውጤታማ ለማድረግ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የእውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ስምምነት ሰነድ መፈራረሙንም ዶ/ር ታምሩ ገልጸዋል። የመምህራን እጥረት እንዳይከሰት ረዳት ፕሮፈሰርና ከዚያ በላይ የትምህርት ደረጃ ያላቸው 73 የውጭና 43 የሀገር ውስጥ መምህራን ቅጥር መፈጸሙንም አስታውቀዋል።

    ለመማር ማስተማር ሂደት አጋዥ የሆኑ በተለይ ለኢንጅነሪግና ለተፈጥሮ ሳይንስ ቤተ-ሙከራና ቤተ-መጽሐፍት ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ በማድረግ መደራጀቱን ገልጸዋል። ይህም ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት ለማድረስ እገዛ ከማድረግ ባለፈ ከዚህ ቀደም ዩኒቨርሲቲው ለተለያዩ የተግባር ትምህርቶች ወደ ሌሎች አካባቢዎች ተማሪዎችን በመውሰድ የሚያወጣውን ውጭ እንደሚያስቀር አስረድተዋል።

    ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የልህቀት ማዕከል (Center of Excellence) አቋቁሞ ከኢትዮጵያ ምርጥ አምስት እንዲሁም ከአፍሪካ ምርጥ 10 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ አንዱ ለመሆን እየሠራ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጫላ ዋታ ናቸው።

    በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ የገዳ ሥርዓት እንዲካተት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ግንባር ቀደሚ ሚናውን ከመወጣት ባለፈ በዩኒቨርሲቲው ከኮመን ኮርስ (common course) እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ድረስ የገዳ ሥርዓት ትምህርት እየተሰጠ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

    “ዩኒቨርሲቲው በስሩ ባሉት ስምንት ኮሌጆችና በአንድ ኢንስትቲዩት ከ17 ሺህ በላይ ተማሪዎችን እያስተማረ ይገኛል” ብለዋል ዶ/ር ጫላ።

    ምንም እንኳን በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭት ምክንያት መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደቱ ለጊዜው ቢቆምም በቀጣይ ዓመታት የተማሪዎችን ቁጥር በእጥፍ ለማሳደግ እየተሠራ እንደሚገኝ ከፕሬዝዳንቱ ገለፃ ለማወቅ ተችሏል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን

    ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ

    Anonymous
    Inactive

    የገጠር ከተሞችንና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ
    ከ919 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ገለፀ

    የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኤሌክትሪክ ኃይል ባልደረሰባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሀገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት መርሀ ግብርን (National Electrification Program) በመተግበር በስፋት እየሠራ ይገኛል።

    መርሀ ግብሩ እስካሁን ብዛት ያላቸው የገጠር ከተሞችንና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን፤ በቀጣይም ፍትሃዊ ተደራሽነትን ባማከለ መልኩ ሰፊ ሥራዎች እንደሚያከናውን ተገልጷል።

    የሀገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራም ኃላፊ አቶ ሁሴን መሀመድ እንደገለፁት፥ ፅ/ቤቱ ከተመሠረተበት ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ የኤሌክትሪክ ኃይል ባልደረሰባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች ኃይል የማዳረስ ሥራ ሲሠራ መቆየቱንና ከ2010 ዓ.ም እስከ 2012 ዓ.ም መባቻ ድረስ ከ63 ሺህ 900 በላይ አዳዲስ ደንበኞችን ተጠቃሚ ማድረጉን ጠቁመዋል።

    የኤሌክትሪክ ኃይል ባልደረሰባቸው አካባቢዎች ኃይል በማዳረስ የደንበኞች ቁጥር ለመጨመር ቁልፍ ሚና ያለው ይህ መርሀ ግብር፥ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከ6 ሺህ 759 በላይ የገጠር ከተሞችና መንደሮችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ መሆናቸውን ኃላፊው ገልፀዋል። ከ1998 ዓ.ም በፊት ተጠቃሚ የነበሩት የገጠር ከተሞችንና መንደሮችን ብዛት ሲታይ ግን ከ667 የማያላፉ እንደነበሩ አስታውሰዋል።

    ኃላፊው አክለውም፥ ፕሮግራሙ በ2012 ዓ.ም በጀት ዓመት በአዲስና በመልሶ ግንባታ 405 የገጠር ከተሞችና መንደሮች በማገናኘት ከ32 ሺህ በላይ ደንበኞችን ኃይል ለማዳረስ አቅዶ፤ 325 የሚሆኑት የገጠር ከተሞችና መንደሮች በማገናኘት 25 ሺህ 232 አዳዲስ ደንበኞች የኃይል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። ለዚህም ከመንግሥት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ 919 ሚሊዮን 277 ሺህ 349 ብር ወጪ መደረጉን ጠቅሰዋል።

    በተጨማሪም ለዕቃ አቅርቦት ግዥ የሚሆን የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የኃይል ማሠራጫ ዕቃዎች በተለይ የትራንስፎርመር እና የኮንዳክተር እጥረት በዋናነት የመርሀ ግብሩ ተግዳሮቶች መሆናቸውን ተጠቅሷል።

    በመጨረሻም በያዝነው በጀት ዓመት ፕሮግራሙ 450 የገጠር ከተሞችና መንደሮች በማገናኘት 54 ሺህ አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ አቅዶ እየሠራ መሆኑን አቶ ሁሴን አስታውቀዋል።

    የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመላው ሀገሪቱ ፍትሃዊ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማሳደግ በ”ብርሃን ለሁሉ” (Lighting to All) መርሀ ግብር እ.ኤ.አ በ2025 ከዋናው የኃይል ግሪድ 65 በመቶ እና ከግሪድ ውጪ በተለያዩ የኃይል አማራጮች 35 በመቶ የሚሆነውን ሕብረተስብ ተጠቃሚ ለማድረግ ስትራቴጂ ቀይሶ በመንቀሳቀስ መሆኑ ይታወቃል።

    ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዜና ሳንወጣ፥ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ከ2.8 ቢሊዮን ኪሎ ዋትስ በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነት መቀነስ መቻሉን አስታውቋል። ተቋሙ እንዳለው በ2012 በጀት ዓመት ቴክኒካልና ቴክኒካል ያልሆነ የኃይል ብክነትን ለመከላከል ባደረገው የክትትልና ቁጥጥር ሥራ 2,823,055,758.11 ኪሎ ዋትስ የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነት ወይም በገንዘብ 1,113,863,407.24 ብር ከብክነት ማዳን ችሏል።

    ተቋሙ የኃይል ብክነቱን መቀነስ የቻለው የኤሌክትሪክ ስርቆትን በመከላከል፣ በትክክል የማይሠሩ፣ የተቃጠሉ፤ የቆሙ ቆጣሪዎች በወቅቱ እንዲቀየሩ በማድረግ፣ የታሪፍ ለውጥ የሚያስፈልጋቸውን ደንበኞች የታሪፍ ለውጥ በማድረግ፣ ቢል የማይወጣላቸው ደንበኞችን ወደ ሲስተም እንደገቡ በማድረግ፣ ያልተፈቀደ የኃይል ጭነት በመቆጣጠር፣ ከቆጣሪው ልኬት ውጪ የተገጠመ አውቶማቲክ ፊዩዝን (automatic fuse) በመቀየር፣ የዝቅተኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪ ደንበኞች የተገኘ የማባዣ ስህተት በማስተካከል፣ የገቢ ደረሰኝ የሌላቸው እንዲኖራቸው በማድረግ እና የመሳሰሉ ቴክኒካል ያልሆነ የኃይል ብክነትን ለመቀነስ የሚያስችሉ ሥራዎችን በመሥራት ነው።

    ተቋሙ ቴክኒካል የኃይል ብክነትን ለመቀነስም የ2000 Common Meter Reading Instrument (CMRI) በተስተካከለው software design መጫን፣ የደንበኞች ቆጣሪ ቅያሪ ሥራ፣ የ383 የደንበኞችን መረጃ ወደ አዱሱ ሲሰተም (SAP) ማዛወርና የመሳሰሉ ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን በ2013 በጀት ዓመትም ሊከሰቱ የሚችሉ ቴክኒካልና ቴክኒካል ያልሆኑ የኃይል ብክነቶችን ለመቀነስ ሰፊ ዕቅድ ይዞ እየተንቀሰቀሰ በይገኛል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

    የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

    Semonegna
    Keymaster

    ኢትዮ ሊዝ ከሰባት ሚሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸው የእርሻ ሜካናይዜሽን መሣሪያዎች ለገበሬዎች አስረከበ

    አዲስ አበባ – በኢትዮጵያ በሊዝ ፋይናንስ ዘርፍ በመሰማራት የመጀመርያው የውጭ ኩባንያ የሆነው ኢትዮ ሊዝ የተሰኘው የአሜሪካ ኩባንያ 16 ኮምባይነሮችን ለአርሶ አደሮች እና ለማኅበራት አስረከበ። የግብርና ሜካናይዜሽን መሣሪያዎቹን ወደ አገር ውስጥ ያስገባው የኢትዮጵያ መንግሥት በግብረናው ዘርፍ ለማዘመን የያዘውን ስትራቴጂ ለመደገፍ ከግብርና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጄንሲ ጋር ያደረውን ሰምምንት ተከትሎ ሲሆን፥ ስምምነቱም እነዚህን ውድ የሆኑ የግብርና ማቀነባበሪያ መሣሪያዎችን መግዛት የማይችሉትን አርሶ አደር ገበሬዎችን በአጭር ጊዜ ባለቤት የሚያደርግ ይሆናል።

    በዚህኛው ዙር የተካሄደው ርክክብ እስካሁን ድረስ ያስረከባችውን የግብርና መሣሪያዎች ቁጥር ወደ አንድ መቶ ያደረሰ ሲሆን፥ አጠቃላይ ወጪያቸው ከ7 ሚሊዮን ዶላር በላይ ነው። ከእነዚህም በተጨማሪ ኩባንያው በመጪው መስከረም እና በጥቅምት ወራት (2013 ዓ.ም.) ከ10 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጡ ተጨማሪ መሣሪያዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት የሚያስፈልጉትን ሥራዎች እያከናወነ ይገኛል።

    የኢትዮ ሊዝ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ግሩም ፀጋዬ በርክክቡ ውቅት እንደተናግሩት፥ “በተከታታይ ወደ ሀገር ውስጥ እያስገባናቸው ያሉት የግብርና መሣሪያዎች ኩባንያችን የሀገሪቱን የግብርና ዘርፍ የማዘመን ዕቅድ ለማሳካት የበኩሉን እየሠራ እንደሆነ የሚያሳይ ሲሆን፥ በዚህም እንቅፋት የሆነውን የውጭ ምንዛሪ እጦት መፍታት ችለናል” በማለት አስረድተዋል።

    አቶ ግሩም አክለውም፥ “ዘላቂነት ያለው ግብርናን ማዘመን ሥራ  የአርሶ አደሩን አቅም በመገንባት ረገድ ቁልፍ ሚና ሊጫወትና ምርታማነትን እና ገቢን ሊያሻሽል እንዲሁም የምግብ ዋስትናን እና አኗኗር ለማሻሻል ይረዳል” ብለዋል። የኢትዮ ሊዝ አርሶ አደሮች ከመደገፍ በተጨማሪ ለኦፕሬተሮች፣ ለረዳቶች ኦፕሬተሮች እና ለተለያዩ ባለሙያዎች፣ የሥራ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነ በሻሽመኔ ከተማ በተደረገው ርክክብ ላይ ተነግሯል።

    አትዮ ሊዝ አፍሪካን አሴት ፋይናንስ ካምፓኒ (African Asset Finance Company/AAFC) በተሰኘ የአሜሪካ ኩባንያ በ400 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተመሠረተ ኩባንያ ነው። ኩባንያው ለእርሻ፣ ለሕክምናና አምራች ኢንዱስትሪ የሚውሉ ዘመናዊ መሣሪያዎች በኪራይ ለማቅረብ የሚያስችለውን የሥራ ፈቃድ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም. አግኝቷል።

    ኢትዮ ሊዝ የካፒታል እቃዎችን እንደአስፈላጊነቱ በመለየት እና በመግዛት፣ አስፈላጊ ጥገናዎችን እና አግባብነት ባለው ሁኔታ አገልግሎት ላይ መዋላቸውን የመቆጣጠር ኃላፊነት ይኖረዋል። በተጨማሪም ተከራዩ ወይንም አገልግሎቱን ያገኘው አካል መሣሪያዎችን መግዛት የሚችልበትን መንገድ ያመቻቻል። ኢትዮ ሊዝ ወደሥራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ፥ ለግብርና፣ ለጤና፣ ለኃይል አቅርቦት (energy)፣ ለምግብ ማቀነባበር (food processing) አገልግሎት ሰጪዎች የካፒታል እቃዎችን አቅርቧል። ድርጅቱ እስካሁን ከ60 በላይ ከሚሆኑ ደንበኞች ጋር የካፒታል እቃዎች አቅርቦት ስምምነት አድርጓል።

    ስለ ኢትዮ ሊዝ
    ኢትዮ ሊዝ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የግል የሊዝ ፋይናንስ አቅራቢ ኩባንያ ሲሆን፥ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ አግኝቶ እ.አ.አ በ2017 የአፍሪካ አሴት ፋይናንስ ኩባንያ አካል በመሆን ሥራው ጀምሯል። ኩባንያው በአፍሪካ የሊዝ አገልግሎት ያልተዳረሰባቸውን ገበያዎች ለማገልገልና አቅምን ያገናዘበ ብድር ለማቅረብ የሚሠራ ኩባንያ ነው። ለበለጠ መረጃ http://www.ethiolease.com ይጎብኙ።

    ስለ አፍሪካን አሴት ፋይናንስ ካምፓኒ (AAFC)
    የአፍሪካ አሴት ፋይናንስ ኩባንያ (AAFC) ዋና መቀመጫውን በአሜሪካ ኒው ዮርክ በማድረግ በተለያዩ ሀገራት ያሉ ኩባንያዎች የፋይናንስ አቅርቦት አገልግሎት ይሰጣል። በመላው አፍሪካም የደንበኞችን ፍላጎትና አቅምን መሰረት ያደረገ የቁስ ውሰት አገልግሎቶችን ይሰጣል። ለበለጠ መረጃ http://www.aafc.com ይጎብኙ።

    ኢትዮ ሊዝ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የዓረብ ሊግ በሕዳሴው ግድብ ላይ ያቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ቁልፍ ጉዳዮችን ሳያገናዝብ ለአንድ ወገን ያደላ ነው ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት አወገዘ።

    የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ ባወጣው መግለጫ፥ የዓረብ ሊግ የሕግ አስፈፃሚ ምክር ቤት የካቲት 26 ቀን 2012 ዓ.ም. የሕዳሴውን ግድብ በተመለከተ የደረሰበት ውሳኔ የሚያሳዝን ሆኖ ያገኘው መሆኑን እና ኢትዮጵያ ውሳኔውን በፍጹም የማትቀበለው መሆኑን ገልጿል።

    ኢትዮጵያ የሱዳን መንግሥት በዓረብ ሊግ ለቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ድጋፍ ላለመስጠት የወሰደውን አቋም እንደምታደንቅ በመግለጫው ተጠቅሷል።

    ሱዳን የተቀነባበረውን እና የዓረብ ሊግን አቋም ባለመደገፍ የምክንያታዊነት እና የፍትሕ ድምፅ መሆኗን ዳግመኛ ማረጋገጧን በመጥቀስ፣ ኢትዮጵያ በመርህ ላይ ለተመሠረተው እና የሁሉም ወገን አሸናፊነትን መሠረት ላደረገው የሱዳን አቋም ወደር የለሽ አድናቆቷን ገልጻለች።

    ኢትዮጵያ ከዓረብ ሊግ ሀገራት ሕዝቦች እና መንግሥታት ጋር በጋራ እሴት፣ ባሕል እና ልማድ ላይ የተመሠረተ ለረጅም ጊዜ የዘለቀ ግንኙነት እንዳላት በመግለጫው ተጠቁሟል።

    የዓረብ ሊግ የተለያዩ ሉዓላዊ ሀገራትን ያቀፈ ተቋም እንደመሆኑ መጠን የሁሉንም ወገን ፍላጎት ያካተተ እና ሚዛናዊ መስመር መያዝ እንደሚጠበቅበት በመግለጫው ተጠቅሷል።

    ከዚህ መስመር በተቃረነ መልኩ የሚሠራ ከሆነ ግን የሊጉ ተዓማኒነት እና በዚህ እጅጉን በተሳሰረ ዓለም ውስጥ ሰላምን፣ መረጋጋትን እና ትብብርን ለማምጣት ያለው አቅም ጥያቄ ውስጥ የሚገባ እንደሚሆን ተገልጿል።

    በተለያዩ ጊዜያት ስትገልጽ እንደነበረው ሁሉ ኢትዮጵያ አሁንም ቢሆን “የአሁኑን እና የመጪውን ትውልድ ፍላጎት ለማሟላት የዓባይን ውኃ ሃብት የመጠቀም መብት አለኝ” የሚለውን የዘለቀ እና የማይናወጥ አቋም በድጋሚ ገልጻለች።

    የዓባይ ወንዝ ድንበር ተሻጋሪ እንደመሆኑም ኢትዮጵያ በሌሎች ላይ ጉልህ ተፅዕኖ ሳይደርስ ውኃውን በፍትሐዊ እና ምክንያታዊ መንገድ የመጠቀም መርህን ተከትላ እንደምትሠራ ተገልጿል።

    በተጨማሪም ኢትዮጵያ በሕዳሴ ግድብ የውሃ አሞላል እና አሠራር ላይ መሠረታዊ መፍትሔ የሚሰጠውን የመርሆዎች መግለጫ ስምምነትን ተከትላ እንደምትሠራም ማረጋገጧ ተገልጿል።

    የዓረብ ሊግ እውነተኛውን መንገድ ተከትሎ እና ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የዘለቀ እና የጋራ እሴቶች ላይ የተመሠረተውን ግንኙነት መሠረት በማድረግ እንደሚሠራ ኢትዮጵያ እንደምትተማመን በመግለጫው ተጠቅሷል።

    ወዳጅነትን ማጠናከር እና ለጋራ ግቦች ተቀራርቦ መሥራት የኢትዮጵያ ፍላጎት መሆኑም ነው የተገለጸው።

      • የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ ያወጣውን መግለጫ (እንግሊዝኛ) ለማንበብ እዚህ ጋር ይጫኑ።

    ምንጭ:- የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)/ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 

    Ethiopia rejects Arab League resolution on GERD የዓረብ ሊግ

    Semonegna
    Keymaster

    ደብረ ታቦር (ሰሞነኛ) – “የኪነጥበብ (የአዝማሪ) ሚና ትናንት፣ ዛሬና ነገ” በሚል ርዕስ የሰላም እና የኪነጥበብ መድረክ በርከት ያሉ ታዳሚዎች በተገኙበት በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ።

    በአዝማሪ ላይ የተሠሩ ጥናቶች እንደሚሉት የአዝማሪዎች አገልግሎት በማኅበራዊ ሕይወት ላይ ብቻ የተወሰነ አልነበረም፡፡ አዝማሪዎች ዘፈንን ከሚከውኑበት ሰውን የማዝናናት ተለምዷዊ ተግባር ባሻገር በኢትዮጵያ ባህላዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ነበራቸው፡፡ ለዚህም ምክንያቱ Kimberlin (1983) እንደሚገልፁት፥ ዘፈን ከኢትዮጵያ ሕዝብ አኗኗር፣ ይትብሃልና ሕይወት ጋር ከፍተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ ነው፡፡ እንደ Ashenafi (1971) እና Teclehaimanot (1986) ትንታኔ አዝማሪዎች ዋና ሥራቸው ማዝናናት ቢሆንም በተጨማሪ ግን ዜናና ታሪክ ነጋሪዎች፣ ሃያሲዎች፣ የፖለቲካ ተንታኞች፣ መዝጋቢዎች፣ አዝማቾች፣ ሆነው አገልግለዋል፡፡ ይህንን ታሳቢ ያደረገው የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ከሰላም ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር “የኪነጥበብ (አዝማሪ) ሚና ትናንት፣ ዛሬና ነገ” በሚል ርዕስ ታህሳስ 20 ቀን 2012 ዓ.ም. የግማሽ ቀን መርሐ-ግብር አካሂዷል።

    ሰላም ኢትዮጵያ፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በመተባበር ባዘጋጁት መድረክ የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አነጋግረኝ ጋሻው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፥ በንግግራቸውም እንደገለፁት ኪነጥበብ ለዕድገት ወሳኝ መሆኑንና፣ ኪነጥበብንና ባህልን ያላካተተ ዕድገት ሙሉ ሊሆን እንደማይችል እና ይህ ሰላምና ባህልን አጣምሮ የያዘ መድረክ የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚከታተለው ገልጸዋል።

    በመርሐ-ግብሩ “የኪነጥበብ (አዝማሪ) ሚና ትናንት፣ ዛሬና ነገ” በሚል ርዕስ የተካሄደ ሲሆን ከውይይቱ በተጨማሪ በመድረኩ የቀረቡት ልዩ ልዩ የኪነጥበብ ሥራዎች ድምቀት ሰጥተውታል።

    በመርሐ-ግብሩ መጨረሻ የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የም/ማ/አ/ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር መንበሩ ተሾመ ባህሉንና ትውፊቱን የማያውቅና እነዚህን ሀብቶቹን የማያለማ ማኅበረሰብ ሁልግዜም አያድግም፤ በመጤ ባህሎች የራሱን ወርቃማ የሆኑ ሀብቶቻችንን እያጣንሁልግዜ የውጭ ናፋቂ እየሆንን፤ ስልጣኔ የሚመስለን የሌሎቹ ነው። ግን እኛ ወርቃማ የሆነ ጥበብ አለን፤ እናም ይኸ ለማኅበራዊ፣ ለኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ፋይዳው ከፍተኛ ለሆነው ባህል ሁላችንም የበኩላችንን ድጋፍ ማድረግ፣ መስመር ማሳየት፣ ስልጠናዎችን ማዘጋጀት ባለሙያዎችን አይዟቹህ ማለት አለብን ሲሉ ገልጸዋል። ባለሙያዎችን ለወደፊቱ እንዴት እንደግፋቸው? እንዴት እናበረታታቸው? የውጭና የውስጥ ሀይሎችን እንዴት እናስተሳስራቸው የሚለውን ለቀጣይ የሁላችንም የቤት ሥራ መሆን አለበት ያሉ ሲሆን በመጨረሻም ለመርሐግብሩ መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱትን አካላት በሙሉ አመስግነዋል – ዶ/ር መንበሩ ።

    ማጣቀሻዎች፦

    • Ashenafi Kebede: The music of Ethiopia: its development and cultural setting. Dissertation, Wesleyan University. (1971)
    • Cynthia Tse Kimberlin: “The Music of Ethiopia“, in Music of Many Cultures, E. May, ed., Berkeley, Los Angeles: University of California Press. (1983).
    • Teclehaimanot G. Selassie: A brief survey study of the Azmaris in Addis Ababa. Proc. of the International Symposium on the Centenary of Addis Ababa. (1986).

    ምንጭ፦ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኪነጥበብ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – መገናኛ ብዙሃን ሙያዊ ሥነ-ምግባርን ጠብቀው ከመሥራትና ማህበረሰቡን ከማስተማር ይልቅ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጠሩ ግጭቶችን እያባባሱ መሆኑን ባለሙያዎች ተናገሩ።

    የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን በበኩሉ መገናኛ ብዙሃኑ የሚሠሯቸውን የዘገባ ስህተቶች እና አባባሽ ይዘቶች እንዲያስተካክሉ በቃልና በደብዳቤ እያሳወቅኩ ነው ይላል።

    ለተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የሚፅፉት አቶ በፍቃዱ ኃይሉ “የክልል መገናኛ ብዙሃን ወገንተኝነት እና ለገዥው ቡድን አጎብዳጅነት” እንደሚታይባቸው አንስተው፤ ብዙ ፖለቲካዊ ዘገባዎችን እና ትርክቶችን በተዛባ መልኩ የሚያቀርቡ እንደሆኑ ነው የገለጹት።

    ዘውግ-ተኮር የሆኑ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ሙያዊ ስነምግባርን ጠብቀው ያለመዘገብ፣ ሀቅን እንዳለ ያለማቅረብና ሚዛናዊ አለመሆን እንደሚስተዋልባቸው የሚናገሩት አቶ በፍቃዱ ኃይሉ፥ ይህ ደግሞ በሀገሪቱ ግጭት በሚስተዋልበት ወቅት የዜጎችን ደህንነት አደጋ ላይ በማይጥል መልኩ እንዳይዘግቡ አድርጓቸዋል ነው ያሉት።

    አንዳንድ መገናኛ ብዙሃን ስህተት የሚፈጽሙት ባለማወቅ መሆኑን ገልጸው፥ ከዚህ ዓይነት ስህተት እንዲወጡ መጀመሪያ በማስተማር የተለየ ሁኔታ ሲያጋጥም በተጨባጭ ማስረጃ ላይ ተመሥርቶ ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ ይገባልም ብለዋል።

    መገናኛ ብዙሃኑ የሕዝብ ማስተማሪያ አልያም የጦር መሣሪያ የመሆን ዕድል ስላላቸው ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ሀሳባቸውን በመስጠት፤ የኢትዮጵያ የብሮድካስት ባለሥልጣልም የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

    በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙዩኒኬሽን መምህርና በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሦስተኛ ዲግሪ ተማሪ አቶ ሃይማኖት ጌታቸው ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ መገናኛ ብዙሃን አዘጋገብ “ፅንፍ ይዞ እየተጓዘ” መሆኑን ጠቅሰው፥ ይህም ለግጭት አባባሽ እየሆነ ነው ይላሉ።

    በተለይ አንዳንድ “የፅንፍ ፖለቲካ” የሚያራምዱ ግለሰቦች የራሳቸውን መገናኛ ብዙሃን በመክፈት የሚፈልጉትን “ፅንፈኛና የጥላቻ አጀንዳ” እያሰራጩ መሆኑን ተናግረዋል። በመንግሥት መገናኛ ብዙሃን በኩል ደግሞ “ሕዝብ ሲሞት እና ጉዳት ሲደርስበት ተከታትሎ ከመዘገብና መፍትሔ ከማፈላለግ ይልቅ መንግሥትን እየጠበቁ የመዘገብ አዝማሚያ ይታይባቸዋል” ነው ያሉት።

    መገናኛ ብዙሃኑ አስቀድመው የስጋት ትንተናዎችን በሚዛናዊነት በማቅረብ ግጭትን የመከላከል ሚና እየተወጡ አይደለም ያሉት አቶ ሃይማኖት፥ ብሮድካስት ባለስልጣንም ለመገናኛ ብዙሃኑ የተሰጣቸው ነጻነት እንዳይታፈን ጥንቃቄ በማድረግ፤ በተሳሳተ መንገድ እየሄዱ ባሉት ላይ የእርምት እርምጃ ሊወስድ ይገባል ብለዋል።

    ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንደወሰን አንዱዓለም “የሀገሪቱ የፖለቲካ መድረክ በተረበሸ ቁጥር መገናኛ ብዙሃኑም አብረው መታመማቸው ከፍተኛ ችግር አስከትሏል” ነው ያሉት።

    አብዛኛው መገናኛ ብዙሃን ሕዝብን ከሕዝብ፣ ክልልን ከክልል፣ መንግሥትን ከሕዝብ የሚያራርቁ ዘገባዎችን እየሠሩ መሆኑን የተናገሩት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፥ ለሕዝብ የሚጠቅሙ ማኅበራዊ፣ ታሪካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ባህላዊ እና ሌሎች የሕይወት መልኮችን ትተው ፖለቲካ ላይ ብቻ የመጠመድ ችግር ይታይባቸዋል ነው ያሉት።

    ባለስልጣኑ የመገናኛ ብዙሃኑን ሥራዎች መዝኖ እርምጃ ለመውሰድ ከዚህ ቀደም የነበረውን ፖለቲካዊ መስፈርት በመቀየር ሙያዊ መመዘኛ ማዘጋጀቱን ጠቁመው፥ በመስፈርቱ መሠረት ድክመትና ጥንካሬ ተለይቶ እንዲያስተካክሉት ለተወሰኑ መገናኛ ብዙሃን ደብዳቤ መላክ መጀመሩንም ገልጸዋል።

    “ሀገሪቱ ለውጥ ላይ ናት በሚል መገናኛ ብዙሃኑ የነውጥ አራጋቢ ሆነው እንዲቆዩ መፍቀድ አይገባም” ያሉት ምክትል ዳይሬክተሩ፥ የፖለቲካ ሁኔታ በተረበሸ ቁጥር ሚዲያው አብሮ መረበሽ እንደለሌበትና በቅርቡ በሚወጣው የመገናኛ ብዘሃን አዋጅ ግልፅ ድንበር እንደሚኖረውም ጠቁመዋል።

    የፖለቲካ አመራሮች በቦርድም ሆነ በሚዲያ መሪነት እንዳይሰየሙ በረቂቅ አዋጁ መቀመጡን አንስተው፥ መገናኛ ብዙሃኑ ከባለሥልጣኑ ጋር እንደ ‘አይጥ እና ድመት’ ከሚተያዩ እርስ በራሳቸው የሚተራረሙበት፣ የሚነጋገሩበትና የሚደጋገፉበት የመገናኛ ብዙሃን ካውንስል መቋቋሙንም ነው የገለጹት።

    “በልቅነት እየሠሩ ያሉትን ለማረም ሲባል በነጻነት ላይ ያሉት መጎዳት የለባቸውም” ያሉት አቶ ወንደወሰን፥ ችግሩን ለማረምና ሁለቱን ለመለየት ከውይይትና ከአቅም ግንባታ ጀምሮ በቀጣይ በሕግ የተጠና የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    መገናኛ ብዙሃን


    Semonegna
    Keymaster

    «በ1950ዎቹ ዓመታት መጨረሻ ጋሽ ጥላሁንን፤ አለማየሁ እሸቴን እና ታምራት ሞላን የመሳሰሉ እንቁዎች ሰምቼ ከሙዚቃ ፍቅር ያዘኝ» ድምፃዊ የግጥምና ዜማ ደራሲ እንዲሁም የሙዚቃ አቀናባሪ አንጋፋዉ አርቲስት አያሌዉ መስፍን። ከሁሉ ከሁሉ የአዲስ አበቤ ፍቅረኛሞች ቀጠሮአቸዉ አያሌዉ መስፍን ሙዚቃ ቤት ጋር እንደነበር የሚያስታዉስ ያስታዉሰዋል።

    ድምፃዊ የግጥምና ዜማ ደራሲ እንዲሁም የሙዚቃ አቀናባሪ ነው፤ አንጋፋዉ አርቲስት አያሌዉ መስፍን። ወሎ የሙዚቃ ባለ ኃብቶችን የሙዚቃ ምሁራንን፤ ያፈራች ሃገር መሆንዋ አብዛኞች ይመሰክሩላታል። ወሎ ካፈራችዉ አያሌዉ መስፍን ከመሳሰሉ ከያኒዎች መካከል በባህል ሙዚቃ ገናና ስምን የተከለዉ የማሲንቆዉ ቀንድ፤ በማሞካሸት የጥበብ ጀማሪ አሰፍዬ አባተ ይባል የነበረዉ፤ አንጋፋዋ ድምፃዊ ማሪቱ ለገሰ፤ አለማየሁ እሸቴ፤ ኃብተሚካኤል ደምሴ ከአብዛኞቹ የጥበብ እንቁዎች እጅግ ጥቂቶቹ ናቸዉ።

    ወሎ ከያኒዎችን ብቻ ሳይሆን አራቱን የኢትዮጵያ የሙዚቃ ቅኝቶች ያፈራች እንደሆነችም ይነገርላታል። «በ 50 ዎቹ ዓመታት መጨረሻ ጋሽ ጥላሁንን፤ አለማየሁ እሸቴን እና ታምራት ሞላን የመሳሰሉ እንቆዎች ሰምቼ ከሙዚቃ ፍቅር ያዘኝ» ያለን አንጋፋዉ አርቲስት አያሌዉ መስፍን፤ ስለአገር ፍቅር ስለፍትህ፤ ስለአንድነት ስለፍቅር አዚሞአል፤ ገጥሞአልም። በተለይ በሙዚቃዎቹ ከኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት ጋር በጋራ የሃገር ድንበርን ማስከበሩ ይነገርለታል። በደረሳቸዉ ግጥሞች በርካታ ከያንያን ተወዳጅ ዜማቸዉን ለአድማጭ ጆሮ አድርሰዉ ታዋቂ ሆነዋል። ከሁሉ ከሁሉ የአዲስ አበቤ ፍቅረኛሞች ቀጠሮአቸዉ አያሌዉ መስፍን ሙዚቃ ቤት ጋር እንደነበር የሚያስታዉስ ያስታዉሰዋል።

    ምን እሱ ብቻ! እንዲህ እንደአሁኑ የእጀታ ስልክ (ሞባይል) ኖሮ፤ የኢንተርኔት አገልግሎት ከሞላ ጎደል ተስፋፍቶ «ሜሴጅ አድግ አድርጊልኝ» በማይባልበት በዝያ ዘመን ከክፍለሃገር የመጡ ኢትዮጵያዉያን አያሌዉ ሙዚቃ ቤት መገናኛቸዉ ነበር። የመዲናዋም ወጣቶች ቢሆኑ በአያሌዉ ሙዚቃ ቤት በራፍ ግራና ቀኝ ከቆመዉ ነጎድጓድ ድምፅን ከሚተፋዉ አምፕሊፋየር «አልያም የድምፅ ማጉያ » በተለይ አዲስ ሙዚቃ ተለቀቀ ከተባለ አካባቢዉ ላይ ቆመዉ ማድመጫቸዉ ነበር፤ የሆነ ሆነና አንጋፋዉ ሙዚቀኛ አያሌዉ መስፍን የት ይሆን? የሙዚቃዉን መድረክ ተዉዉ እንዴ?

    ስለአገር ፍቅር ስለፍትህ፤ ስለአንድነት ስለፍቅር አዚሟል

    አዘጋጆች፦ አዜብ ታደሰ እና ተስፋለም ወልደየስ (ዶይቸ ቬለ)
    —–
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    አርቲስት አያሌዉ መስፍን


    Semonegna
    Keymaster

    የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ዓላማው ክልሉን ለማተራመስና የህዝቡን ህልውና አደጋላይ ለመጣል ያለመ መሆኑን ገልጸው፥ በአሁኑ ወቅት የፌዴራል መንግስት ሁኔታውን የማስተካከልና ክልሉን የማረጋጋት ትዕዛዝ እንደተሰጠው አቶ ንጉሱ ጥላሁን ገልጸዋል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መደረጉን በኢፌዴሪ ጠቅላይ የሚኒስቴር ፅህፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ገለጹ። አቶ ንጉሱ ሐምሌ 15 ቀን 2011 ዓ.ም. ምሽት ላይ ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ኢቲቪ) በሰጡት መግለጫ በክልሉ መንግስት ላይ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተደርጓል።

    በተደራጀ ሁኔታ በመንግስት መዋቅር ላይ ጥቃት ለመሰንዘር የተሞከረው የተደራጀ እንቅስቃሴ ከሽፏል ነው ያሉት አቶ ንጉሱ ጥላሁን ።

    የአማራ ክልል ወደ መረጋጋት እየመጣ ባለበትና እና ሕዝቡ ቀደም ሲል ያነሳ የነበረውን የህግ የበላይነት ጥያቄ ለመመለስ እየተሠራ ባለበት ወቅት የተሰነዘረው ጥቃት የክልሉ መንግስት ብቻ ሳይሆን የአማራ ሕዝብ ላይ የተሞከረ ነው ብለዋል።

    ሙከራው ክልሉን ለማተራመስና የህዝቡን ህልውና አደጋላይ ለመጣል ያለመ መሆኑን ገልጸው፥ በአሁኑ ወቅት የፌዴራል መንግስት ሁኔታውን የማስተካከልና ክልሉን የማረጋጋት ትዕዛዝ እንደተሰጠው ገልጸዋል።

    የፌዴራል መንግስቱ ጣልቃ በመግባት ይህን መሰሉን ተግባር የመግታት ሥራ እንደሚሠራና ህብረተሰቡም አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላልፈዋል።

    ጸረ-ህገ መንግስትና መፈንቅለ መንግስቶች እንዲሁም በታጠቁ ኃይሎች የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ተቀባይነት እንደሌላቸው ገልጸው፥ ክልሉን ወደነበረበት ሰላማዊ ሁኔታ ለመመለስ ህብረተሰቡ ከመንግስት ጋር በትብብር እንዲሠራ ጥሪ አቅርበዋል።

    አቶ ንጉሱ ጥላሁን በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢትዮጵያ ቴለቭዥን ጋዜጠኛ ጋር ያደረጉትን አጭር ቃል ምልልስ እዚህ ጋር በመጫን ያዳምጡ።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ


    Anonymous
    Inactive

    የጉራጌ ሕዝብ አውራጃውን ከራሱ በተወለዱ አበጋዞች ያስተዳድር የነበረው ኦሮሞ በገዳ መተዳደር ከመጀመሩ ቢያስ ከ208 ዓመታት በፊትና ኦሮሞ ደቡብ፣ ምዕራብ፣ ምስራቅና መካከለኛው ኢትዮጵያን መውረር ከመጀመሩ ከ200 በላይ ዓመታት በፊት ነበር።

    የጉራጌ ሕዝብ ከ158 ዓመታት በፊት…
    (አቻምየለህ ታምሩ)

    ሰማዩም ምድሩም የኛ ነው የሚሉን ኦነጋውያን የሚይዙት ቅጣምባሩ ጠፍቷቸዋል። ከሰሞኑ ደግሞ ባሰራጩት በምስል የታገዘ ዜና በጉራጌ ምድር ከ158 ዓመታት በፊት ተቋርጦ ነበር ያሉን የገዳ ስርዓት ማስጀመራቸውን ነግረውናል። እንዲህ ዓይነት ዜና ሲሰማ ዝም ማለት ተገቢ ባለመሆኑ ከ158 ዓመታት በፊት የጉራጌ ሕዝብ ከኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግሥት ጋር ስለነበረው ግንኙነት፣ የነበረውን የውስጥ አስተዳደር ታሪክና “ገዳ” የሚባለው የወረራና የዘመቻ ስርዓት ወደ በአካባቢው በደረሰበት ወቅት ስለተከተሉ ሁኔታ ሳነብ ከተማርሁት የሚከተለውን ጀባ ብያለሁ።

    የጉራጌ ምድር ከጥንት ጀመሮ የኢትዮጵያን መንግሥት ያቆሙ ዋና ዋና የጦር መሪዎችን ያፈራ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ አውራጃ ነበር። ተመዝግቦ ከምናገኘው ታሪክ ብንነሳ እስከ ሞቃድሾ ድረስ የነበረውን የኢትዮጵያ ግዛት ባስተዳድሩት ዐፄ ዐምደ ጽዮን [እ.ኤ.አ. ከ1314 ዓ.ም.–1344 ዓ.ም. ድረስ የነገሡ] ዜና መዋዕል ውስጥ ጉራጌ ከኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግሥት ጋር ቅርብ ቁርኝት የነበረው ሕዝብ እንደነበር ተጽፎ እናገኛለን። በዘመኑ የጉራጌ አውራጃ የውስጥ አስተዳደር ይመራ የነበረው በጉራጌ ተወላጅ አበጋዞች ነበር።

    ጉራጌ አውራጃውን ከራሱ በተወለዱ አበጋዞች ያስተዳድር የነበረው ኦሮሞ በገዳ መተዳደር ከመጀመሩ ቢያስ ከ208 ዓመታት በፊትና ኦሮሞ ደቡብ፣ ምዕራብ፣ ምስራቅና መካከለኛው ኢትዮጵያን መውረር ከመጀመሩ ከ200 በላይ ዓመታት በፊት ነበር። የኦሮሞ ብሔርተኛው ፕሮፌሰር መሐመድ ሐሰን “The Oromo and the Christian Kingdom of Ethiopia” በሚል ባሳተመው መጽሐፉ ገጽ 158 ላይ እንደጻፈው ኦሮሞ በገዳ መመራት የጀመረው እ.ኤ.አ. በ1522 ዓ.ም. እንደሆነና የመጀመሪያው ገዳ “ገዳ መልባ” እንደሚባል ነግሮናል። ጉራጌ ግን ኦሮሞ ገዳ ከጀመረበት ከ1522 ዓ.ም. በመቶዎቹ በሚቆጠሩ ዓመታት በፊት ቆዬት ብዬ የማቀርብላችሁ ከገዳ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላው የራሱ የውስጥ አስተዳደር ስርዓት ነበረው።

    የጉራጌ ምድር ክርስትና ቀድሞ በሰፊው ከተሰበከበትና ከጸናበት የኢትዮጵያ አውራጃዎች አንዱ ነበር። በወቅቱ የተጻፈው ድርሳነ ዑራኤል ይህንን ያረጋግጣል። ከድርሳነ ዑራኤሉ በተጨማሪ ራሳቸው የጉራጌ ተወላጆችም ይህንን ታሪክ ጽፈዋል። የጨቦ ኡዳደ ኢየሱስ ሕዝብ ታሪክ ጸሐፊው አቶ ምስጋናው በላቸው “የጨቦ ኡዳደየሱስ ሕዝብ አጭር ታሪክና ባሕል” በሚል በመጋቢት 1985 ዓ.ም. ከጀርመን በጻፉት የታሪክ መጽሐፋቸው ገጽ 66 ላይ እንደጻፉት አይመለል በሚባለው የጉራጌ ምድር የሚኖረው «ክስታኔ» የሚባለው ሕዝብ መጠሪያ «ክስተነ» ከሚል ከቦታው ቋንቋ የመጣ መሆኑንና ትርጉሙም ክርስቲያን ማለት እንደሆነ ነግረውናል። አይመለል የመጀመሪያዎቹ ክስታኔዎች ወይንም ክርስቲያኖች የሰፈሩበት ምድር ነው።

    ክስታኔ፣ ጉራጌ በመባል በወል ከሚጠሩት የቤተ ጉራጌ ማኅበረሰቦች ውስጥ አንዱ ሲሆን ሶዶ ጉራጌ እየተባለም ይጠራል። የክስታኔ ሕዝብ ቋንቋ ክስታኒኛ ይባላል። አቶ ምስጋናው በላቸው በመጽሐፋቸው ገጽ 63 እንደነገሩን በጨቦ ምድር ብቻ ከግራኝ ወረራ በፊት 40 ጥንታዊ አብያተ ክርስቲያናት የነበሩ ሲሆን ከወረራው በኋላ የተረፉት ግን 13 ስደተኛ ታቦቶች የተዳበሉበት ታሪካዊው የዋሻ ሥላሴ ቤተክርስቲያንና በወንጭት ደሴት ላይ የነበረው የቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ብቻ መሆናቸውን ነግረውናል። አቶ ምስናጋው ጨምረው እንደጻፉት የዋሻ ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በዐፄ ካሌብ ዘመነ መንግሥት የተሠራ መሆኑን ከጉራጌ ታሪክ አዋቂ አባቶች አገኘሁት ያሉትን ታሪክ ነግረውናል። ይህ የጉራጌ ሕዝብ ክርስትናን ከተቀበሉ ቀደምት የኢትዮጵያ ነገዶች መካከል መሆኑን ያሳየናል።

    ጉራጌ የኢትዮጵያን ሰለሞናዊ መንግሥት በሸዋ ምድር ካቆሙ የኢትዮጵያ ዋና ዋና ነገዶች መካከል ቀዳሚው ስለመሆኑ ሌላው ማስረጃ በዐፄ ናዖድ ዘመነ መንግሥት የተጻፈው ድርሳነ ዑራኤል ነው። በዘመኑ ድርሳነ ዑራኤል እንደተጻፈው እግዚአብሔር መስፍንነት ከጉራጌ፥ ከመንዝና ከወረብ እንዳይወጣ ለአጼ ናዖድ [የንግሥና ዘመናቸው እ.ኤ.አ. ከ1494–1508 ዓ.ም. ድረስ ነው] ቃልኪዳን ገባለት ይለናል። ይህ በድርሳነ ዑራኤሉ ከገጽ 311–315 ተጽፎ የሚገኝ ሲሆን ሙሉው ቃል እንዲህ ይነበባል፦

    ወእምድኅረ፡ ዝንቱ፡ ወሀቦ፡ ለናዖድ፡ እግዚእነ፡ ኢየሱስ፡ ክርስቶስ ኪዳነ ምሕረት፡ ከመ፡ ኢይጥፋእ ምስፍና፡ ወምልክና፡ በምድረሸዋ፡ ወመንዝህ ወበሀገረ፡ ጐራጌ፡ ዘይብልዎ ምድረ፡ ወረብ፡ ወምሁር።

    ትርጉም፦

    ከዚሀ፡ በኋላ፡ ጌታ ኢየሱስ፡ ክርስቶስ፡ ከምድረ፡ ሸዋ፡ ምሁርና፡ ምድረ፡ ወረብ፡ ከሚባለው ከጐራጌ፡ አገር፡ ከመንዝም፡ አገዛዝና፡ መስፍንነት፡ አንዳይጠፋ፡ ለናዖድ፡ ቃል፡ኪዳን፡ ሰጠው።

    በድርሳኔ ዑራኤሉ እንደተገለጠው የጉራጌ ሕዝብ በዘመኑ የኢትዮጵያ መስፍን ሆነው እንዲሾምላቸው ከተወሰነላቸው ሦስት የኢትዮጵያ አካባቢዎች መካከል አንዱ ነበር። በዚህ መልክ እስከ መካከለኛው ዘመን የማዕከላዊው የኢትዮጵያ መንግሥት ዋልታ የነበረው ጉራጌ ከግራኝ ወረራ በኋላም ለኢትዮጵያ ቤተመንግሥት በጣም ቅርብ ነበር። ከግራኝ ወረራ በኋላ ዋናኞቹ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ራሶች ጉራጌዎች ነበሩ።

    ከግራኝ ወረራ በኋላ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ የመንግሥት ስልጣን ከነበራቸው አራጊ ፈጣሪ ጉራጌዎች መካከል በዐፄ ያዕቆብ [እ.ኤ.አ. ከ1597 ዓ.ም.–1603 ዓ.ም.፤ እንዲሁም ከ1604 ዓ.ም.–1607 ዓ.ም. ድረስ የነገሡ] እና በዐፄ ዘድንግል [ እ.ኤ.አ. ከ1603 ዓ.ም.–1604 ዓ.ም. ድረስ የነገሡ) ዘመናት የነበሩትን ራስ ዘሥላሴን ለአብነት መጥቅስ ይቻላል። የጉራጌ ተወላጁ ራስ ዘሥላሴ ዐፄ ዘድንግል “መልከ ሐራ” በሚል ያቋቋሙትን የንጉሥ ሠራዊት ይመሩ ነበር። ዐፄ ሰርጸ ድንግል እ.ኤ.አ. በ1597 ዓ.ም. ከሞቱ በኋላ ደግሞ ለሚቀጥሉት 10 ዓመታት ኢትዮጵያን የገዙት ራስ ዘሥላሴ ነበሩ ማለት ይቻላል።

    ራስ ዘሥላሴ በዐፄ ሰርጸ ድንግል ዘመን «ቁርባንና ሚዛን» የተባለው ደምብያ የሰፈረው ሠራዊት መሪ ነበር። ዐፄ ዘድንግል ለወታደሩ አመጽ ምክንያት የሆነ ገባሩን ነጻ የሚያወጣ አዋጅ አውጀው ነበር። ይህ አዋጅ ወታደሩንና ገባሩን ወይም ዜጋውን እኩል ያደረገ አዋጅ ነበር። በዚህ ምክንያት ራስ ዘሥላሴና ቁርባንና ሚዛን የተባለው ሠራዊት በንግሡ ላይ አምጾ ደምብያ ውስጥ ባርጫ ከተባለ ስፍራ ዐፄ ዘድንግልን ገደሉት። ጣሊያናዊው የታሪክ ተመራማሪ ኮንቲ ሮሲኒ (Carlo Conti Rossini) ያሳተመው በዘመኑ የተጻፈው ታሪከ ነገሥት መንግሥት በጉራጌው በራስ ዘሥላሴ እጅ ገብቶ ነበር ይላል። ኮንቲ ሮሲኒ ያሳተመው ታሪከ ነገሥት ውስጥ የሚገኘው ይህ ታሪክ የሚከተለውን ይመስላል፦

    ወበውዕቱ ፩ ዓመት ተጻልዕዎ ሐራሁ ለሐጼ ዘድንግል እለ ይብልወሙ ቁርባን፥ ወሚዛም ወእርስ ዘሥላሴ በምክንያተ ዝንቱ አዋጅ ዘአንገረ ውእቱ እንዘ ይብል ሰብእ ሐራ፤ ወገብራ ምድር። እስመ ዓመፁ ኩሉ ዜጋሆሙ ወቀተልዎ በኵናት ማዕከለ ደምብያ ዘውእቱ ባርጫ [1604 ዓመተ ምኅረት] ። […] ወእምድኅረ አዘዘ እራስ ዘሥላሴ ከመ ያንስእዎ ለሐጼ ዘድንግል ወአንሥእዎ ወወሰድዎ ውስተ ደሴተ ዳጋ ወቀበርዎ ህየ። ወነበረት መንግሥት በዕዴሁ ለጉራጌ ራስ ዘሥላሴ።” [ምንጭ፦ C. Conti Rossini, C. (1893). Due squarci inediti di cronica etiopica. Rendiconti della reale accademia dei Lincei. Classe di Scienze Morali, Storiche e Filologiclre; Page 807.

    ትርጉም፦

    በአንድ ዓመት ውስጥ ቁርባንና ሚዛን የተባሉት ወታደሮች እንዲሁም ራስ ዘሥላሴ “ሰው ነጻ ነው፤ ምድር ገባር ነው” በሚለው አዋጅ ምክንያት ዐፄ ዘድንግልን ተጣሉት። ዜጎች [ንጉሡን ደግፈው አመጹ]። በደምብያ መካከል ባርጫ ውስጥ በጦር ወግተው ገደሉት። ከዚህ በኋላ ራስ ዘሥላሴ ዐፄ ዘድንግልን እንዲያነሱት አዘዘ፤ አንስተው በዳጋ ደሴት ቀበሩት። መንግሥት በጉራጌው በራስ ዘሥላሴ እጅ ነበረች።

    ከዚህ የምንረዳው በዘመኑ በኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግሥት አራጊ ፈጣሪ የነበሩት የጉራጌ ተወላጁ ራስ ነበሩ።

    ወደ ውስጥ አስተዳደሩ ስንመጣ የጉራጌ ሕዝብ አውራጃውን የሚያስተዳድረው ከተወላጆቹ በሚመረጡ አበጋዞች ነበር። የጨቦ ተወላጁ አቶ ምስጋናው በላቸው የጉራጌ ሕዝብ አካል የሆነውን የጨቦ ሕዝብ የውስጥ አስተዳደር በሚመለከት “የጨቦ ኡዳደየሱስ ሕዝብ አጭር ታሪክና ባሕል” በሚለው መጽሐፋቸው ከገጽ 85–89 የሚከተለውን ጽፈዋል፤

    “አበጋዙ የሕዝቡ ጠቅላይ አስተዳዳሪ ሆኖ እንደ አባት የሚታይ መሪ ነው። አበጋዙ እንደኃላፊነቱ ሥፋትና የሥራው ክብደት ከእጩነት አስንቶ እስከተሾመበት ድረስ በጥልቅ ተጠንቶ የሚመረጥበት ሁኔታ ጥንቃቄ የተሞላበት ነው። ይህም የሚሆነው በየሁለት ዓመት ግፋ ቢል በሦስት ዓመት አንድ ጊዜ ነው። የአንድ አበጋዝ የአገልግሎት ዘመኑ ለሁለት ዓመት ብቻ ሲሆን በዚሁ ሁለት ዓመታት ውስጥ ዳኝነቱና ተወዳጅነቱ ከፍ ያለ ምስክርነት ካገኘ ያለ ምንም ተቃውሞ አንድ ዓመት ተመርቆለት ለሦስት ዓመታት ያስተዳድራል። ድጋሚ መመረጥ የለም።…

    አበጋዝ ሲመረጥ በጊዜው ሥልጣን ላይ ያለው የአመራር አካል ሥልጣን ከመልቀቁ ከብዙ ወራት በፊት አበጋዝ መመረጥ የሚገባው ሰው ስም ከየጎሣው በሚስጥር ይጠየቃል። አበጋዝ መሆን ይችላል ተብሎ ከየጎሳው ከየአካባቢው የተጠቆመውን አዛውንት የእያንዳንዱን ሁኔታ ማለት ባኅሪው፣ ተቀባይነቱና የማስተዳደር ችሎታውን በሚስጥር አጥንቶ አበጋዝ ይሆናል ብሎ ያመነበትን ለጠቅላላው የሕዝብ ጉባዔ ያቀርባል።

    ሕዝቡ ካመነበት በኋላ የሹመቱ ሥነ ስርዓት የሚፈጸምበትን ቀን ራቅ አድርጎ ይቀጥራል። ቀጠሮው ራቅ የሚለው በሕዝቡ ጥያቄ ሆኖ እንደተለመደው በስርዓተ ሹመቱ ቀናት ሕዝቡ በፈቃዱ የሚደሰትበትን የእርድ በሬዎች፣ የሚበላና የሚጠጣውን ከየጎሳውና ከየአካባቢው አጠራቅሞ ለማምጣት እንዲመቸው ብሎ ነው። የተሿሚው ጎሳ አብዛኛውን ያቀርባል።

    በስርዓተ ንግሡ ቀን አበጋዙ በሻሽ ጥምጥም ዘውድ ሰሠርቶላቸው፣ የአበጋዙ ባለቤት በፀጉራቸው ጉንጉን ዘውድ ተሠርቶላቸው አበጋዙ በሠንጋ ፈረስ፣ ባለቤታቸው “እቴ” ተብለው [እቴጌ ማለት ይመስላል] በሰጋር በቅሎ ላይ ተቀምጠው በጎሳቸው እጀብና ሆታ ሰንበት ወራቡ ሲደርሱ እዚያ ተሰብስቦ የሚጠብቃቸው ሕዝብ በዘፈንና በእልልታ ይጠብቃቸዋል። ሰንበት ወራቡ የመጀመሪያ ስርዓተ ንግሥ የሚፈጸምበት ቦታ ነው። እዚያ ቦታ ከመድረሳቸው ቀደም ብሎ አበጋዙና “እቴ” የሚቀመጡበት በሦስት ድርብ የተሰራ የእንጀራ መደብ ይዘጋጃል። እንጀራ ላይ የሚቀመጡበት ምክንያት እነሱ በሚያስተዳድሩበት ክልል ጥጋብ እንዲሆን ተመኝተው ነው ተብሎ ይታመናል።

    ተሿሚዎቹ የክብር ሥፍራቸውን ከያዙ በኋላ በገንዙና በአባጅልባዎች አማካኝነት ሕዝብ በተሰበሰበበት ሥርዓተ ንግሡ ይፈጸማል። ወዲያውኑ ቃለ መሐላ ሲፈጸም ወይፈኖች፣ በሬዎች ታርደው ፈንጠዝያው ይቀጥላል። ይህ የደራ ድግስ በየደረጃው እየተበላ አምስት ቀን ይቆያል። በአምስተኛው ቀን አበጋዙና “እቴዋ” ዋሻ ሥላሴ ቤተክርስቲያን እንደዚያ ታጅበው ሄደው የመጨረሻ ሥርዓተ ንግሥ ከተፈጸመ በኋላ አበጋዙ ወደ ጅሎት ቦታው ተመልሶ አገልግሎቱን ከፈጸመው አበጋዝ መንበሩን ይረከባል። አንዴ አበጋዝ ሆኖ የተመረጠ አዛውንት መንበሩንና አስተዳደሩን በፍቅርና ራሱ ቃለ ቡራኬ ሰጥቶ ለአዲሱ አበጋዝ ሲያስረክብ በትረ መንግሥቱ [በእጁ ይይዘው የነበረው ዘንድ] ለክብሩ ሲባል በእጁ ይቀራል። የአገልግሎቱ ዋጋም ዕድሜውን ሙሉ አበጋዝ ተብሎ መጠራት ሆኖ ይኸው የማዕረግ ስሙና የሚይዘው አንድ ነበሩ።”

    የጉራጌ ሕዝብ የውስጥ አስተዳደር በዚህ መልክ የተገለጸውን ይመውላል። አበጋዞቹ በሕዝብ ፊት ሥርዓተ ንግሥና ከፈጸሙ በኋላ የሥርዓት ንግሥናው ፍጻሜ የሚሆነው አበጋዙና እቴዋ በጥንታዊው ዋሻ ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሄደው የመጨረሻውን ሥርዓተ ንግሥ ከፈጸሙ በኋላ ነው። በዚህ መልክ አውራጃውን ሲያስተዳድር የኖረው የጉራጌ ሕዝብ ከኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግሥት ጋር የነበረው ግንኙነት የተቋረጠው በኦሮሞ ወረራ ምክንያት ነው። በኦሮሞ ወረራ ምክንያት ከማዕከላዊው የኢትዮጵያ መንግሥት ጋር የነበረው ግንኙነት የተቋረጠው የጉራጌ ሕዝብ በተለይም የጨቦ ክስታኔና ምሑር ሕዝብ በኦሮሞ ወረራ ምክንያት ክሥታኔና ምሑር የነበረውን ቋንቋውን በአባገዳዎች ተገዶ እንዲተውና ኦሮምኛ እንዲናገር በመገደዱ ብዙ ስቃይ እንደደረሰበት አቶ ምስጋናው በመጽሐፋቸው አትተዋል። አቶ ምስጋናው በመጽሐፋቸው ገጽ 50 ላይ እንደጻፉት ኦሮሞ በገዳ ስርዓት እየተመራ የጉራጌን ምድር ሲወር የነበረውን ጥፋት እንዲህ ይገጹታል፦

    በዚህ ጊዜ [ኦሮሞ ወደ ጉራጌ ምድር በተስፋፋበት ወቅት ማለታቸው ነው] ስለ ቋንቋ የነበረው እምነት ኦሮምኛ የሚናገር “ቢርመዱዳ እንጡቂና” ኦሮምኛ የማይናገር “ዲና በሌሣ” የሚል ሆነ። ትርጉሙም ኦሮምኛ የሚናገር ወገናችን ነው ይገብር፤ ኦሮምኛ የማይናገር ጠላታችን ነው ይጥፋ” ማለት ነው።

    እንግዲህ! ኦነጋውያን በጉራጌ ምድር ከ158 ዓመታት በፊት ነበረ ያሉትን ገዳ ለማቋቋም እየተንቀሳቀሱ ያሉት ገዳ የሚባለው የወረራ ስርዓት ሳይመሰረት የራሱ የውስጥ አስተዳደር የነበረውን የጉራጌ ሕዝብ “ኦሮምኛ የሚናገር ወገናችን ነው ይገብር፤ ኦሮምኛ የማይናገር ጠላታችን ነው ይጥፋ” እያሉ አባገዳዎች የጉራጌን ሕዝብ ያጠፉበትን፣ ከርስቱ ያፈለሱበትን የወረራና የጦርነት ስርዓት መልሰው ለመትከል ነው። አባገዳዎች ወደ ጉራጌ ምድር ብቻ ሳይሆን ወደ ምዕራብ፣ መካከለኛውና ደቡብ ኢትዮጵያ የተስፋፉት “ኦሮምኛ የሚናገር ወገናችን ነው ይገብር፤ ኦሮምኛ የማይናገር ጠላታችን ነው ይጥፋ” እያሉ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት እየፈጸሙ ነው። ኦነጋውያን በጉራጌ ምድር መልሰው ሊተክሉ እየፈለጉት ያለው የገዳ ስርዓትም “ኦሮምኛ የሚናገር ወገናችን ነው ይገብር፤ ኦሮምኛ የማይናገር ጠላታችን ነው ይጥፋ” እያሉ አባገዳዎች ዘር ያጠፉበትን፣ ባላመሬቱን ከርስቱ ያለፈሉበትን የወረራና የዘር ማጥፋት ስርዓት ነው።

    የጨቦ ተወላጁ አቶ ምስጋናው በላቸው በመጽሐፋቸው ገጽ 66 እንደነገሩን አባገዳ አካባቢውን ከወረረው ጀምሮ የነበረው ስቃይ፣ ጭቆና መከራ ተወግዶ በጨቦ ምድር ፍቅርና ሰላም የወረደው ዳግማዊ ምኒልክ ሲደርሱላቸውና ከአባገዳ ባርነት ሲያላቅቋቸው እንደሆነ ጽፈዋል። «የሰላሙ ዘመን» ያሉት የዐፄ ምኒልክ ፀሐይ በጨቦ ምድር መውጣት ከጀመረችበት ጊዜ ጀምሮ የጨቦ ካህናት ከዐፄ ምኒልክና ራሶቻቸው ጋር እየዞሩ በኦሮሞ ወረራ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የጥንቱን ወንጌል የማስፋፋት ተግባራቸውን በመቀጠል እስከ ዳር አገር ድረስ እየዞሩ ክርስትና መነሳት የሚፈልገውን ክፍል እንዳጠመቁና ከመሀል ኢትዮጵያ እስከ ኖኖና ጡቁር ምድር ድረስ በመሄድ አዳዲስ አማኞችን ያጠምቁት የጨቦ ቄሳውስት እንደነበሩ አውስተዋል።

    ባጭሩ የጉራጌ ሕዝብ ለሺህ ዘመናት የኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግሥት ዋልታ የነበረ፣ የራሱ የሕዝብ አስተዳደር ስርዓት የነበረው ሠራተኛ ሕዝብ እንጂ ገዳ የሚባል ከዲሞክራሲ ጋር የስናፍጭ ቅንጣት ታህል ግንኙነት የሌለው የወረራ፣ የጦርነት፣ የመስፋፋት ዘመቻና የዘር ማጥፋት የተካሄደበት ስርዓት ባለቤት አልነበረም!

    አቻምየለህ ታምሩ

    የጉራጌ ሕዝብ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – የአጼ ቴዎድሮስ ልጅ የልዑል አለማየሁ አፅም ከሀገረ እንግሊዝ ወደ እናት ሀገሩ እንዲመለስ ኢትዮጵያ ተጠየቀ። በተጨማሪም ለንደን ከተማ ውስጥ በቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም (Victoria and Albert Museum) የሚገኙ የኢትዮጵያ ቅርሶች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ጥያቄ ቀርቧል።

    በኢፌዴሪ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶ/ር ሂሩት ካሳው የተመራው የልዑካን ቡድን መጋቢት 13 ቀን 2011 ዓ.ም. በለንደን ጉብኝት አድርገዋል።

    በዚሁ ወቅትም በለንደን የዊንዶዘር ቤተመንግስት (Windsor Castle) የልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስን መካነ መቃብር እና በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አፄ ሃይለስላሴ ይጸልዩበት የነበረውን ወንበር ጎብኝተዋል።

    ዶ/ር ሂሩት ካሳው በአጼ ቴዎድሮስ ልጅ ልዑል አለማየሁ መቃብር ላይ የአበባ ጉንጉን ማስቀመጣቸውን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴርን እንደመረጃ ምንጭነት በመጥቀስ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዘግቧል።

    በጉብኝቱ ወቅትም “የአጼ ቴዎድሮስን ፀጉር ማግኘታችን ደስ ብሎናል፤ ይሁን እንጂ ከትውልድ ቦታው ተለይቶ ህይወቱ ያለፈው ልዑል አለማየሁ አፅም በትውልድ ሀገሩ እንዲያርፍ የኢትዮጵያዊያን ጥያቄ ስለሆነ በክብር ወደ አገሩ እንዲመለስ” ሲሉ ዶክተር ሂሩት ጠይቀዋል።

    አፅሙ ወደኢትዮጵያ ተመልሶ ከአባቱ አጼ ቴዎድሮስና ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር መቀላቀል እንደሚገባውና የዊንዶዘር ቤተመንግስት ለሚመለከተው አካል ጥያቄውን አቅርቦ በአፈጣኝ ምላሽ እንዲሰጥም ጥሪ አቅርበዋል።

    በዕለቱ ልዑካን ቡድኑን በመቀበል ከቡድኑ ጋር የተወያዩት የዊንዶዘር ቤተ-መንግስት ሃላፊ ዶ/ር ማርክ ፓወል በበኩላቸው በጉዳዩ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንነጋገርበታለን ብለዋል። ሂደቱን በተመለከተ በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በመከታተል እልባት እንዲያገኝ አስፈላጊውን ጥረት እንደሚያደርግም ሚኒስቴሩ ተገልጿል።

    በሌላ በኩል የልዑካን ቡድኑ መጋቢት 12 ቀን 2011 ዓ.ም. ለንደን የሚገኘውን የቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም ጎብኝቷል። በዶ/ር ሂሩት ካሳው የተመራው የልዑካን ቡድኑና በለንደን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከሙዚየሙ ዳይሬክተር ዶ/ር ትሪስታራም ኸንት (Tristram Hunt, PhD) ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ ወቅት በቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም የሚገኙ የመቅደላ ስብስብ ቅርሶች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ጥያቄ ቀርቧል።

    እ.አ.አ በ2018 የቪክቶሪያ እና አልበርት ሙዚየም የሚገኙ የመቅደላ ስብስብ ቅርሶች ለኢትዮጵያ መመለስ እንደማይችል፤ ነገር ግን በረጅም ጊዜ ውሰት ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ማድረግ እንደሚቻል መገለጹ ይታወቃል። የሙዚየሙ ዳይሬክተር ዶ/ር ትሪስታራም ኸንት ጥያቄው ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው ውሰት የሚለው ቃልም ለኢትዮጵያውያን ከባድ መሆኑን እንደተረዱት ተናግረዋል። በመሆኑም “የተቸገሩት ጉዳዩ የሕግ ጉዳይ በመሆኑና ምላሽ ለመስጠት ያለን አማራጭ ይህ ብቻ ስለሆነ ነው ” ብለዋል።

    “ያለን አማራጭ ይህን ቀዳዳ በመጠቀም ሊስተካከሉ የሚችሉ አባባሎችን ተጠቅመን የሚመለሱበትን ሁኔታ መፍጠር፤ ይህን ካላደረግን ግን በሕጉ ላይ ጸንተን ወደፊት የሚሆነውን ነገር መመልከት ይኖርብናል” ሲሉም ዶ/ር ኸንት አክለዋል።

    የባህል ሚኒስትሯ ዶ/ር ሂሩት ቅርሶቹ የኢትዮጵያ በመሆናቸው በረጅም ጊዜ ውሰት ሳይሆን በቋሚነት ቅርሶቹ ለኢትዮጵያ መመለስ የሚችሉበት አማራጭ መፍትሄ ሙዚየሙ ሊያበጅ እንደሚገባ አመልክተዋል።

    በኤምባሲውና በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በኩል በአስቸኳይ መግባቢያ ሰነድ በመፈራረም፣ ካለው ሕግ ጋር በማይጋጭና የኢትዮጵያን ጥያቄ ሊመልስ በሚችልበት ሁኔታ በመንቀሳቀስ ጉዳዩ በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት እልባት እንደሚያገኝ ዳይሬክተሩ ገልጸፀዋል።

    በለንደን ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲም ባለው ሙሉ አቅምና ጊዜ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በመወጣት ቅርሶቹ ወደ አገራቸው እንዲገቡ እንደሚያደርጉ በብሪታኒያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍስሃ ሻወል ገብሬ ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ልዑል አለማየሁ


Viewing 15 results - 1 through 15 (of 26 total)