Search Results for 'ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል'

Home Forums Search Search Results for 'ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል'

Viewing 6 results - 1 through 6 (of 6 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሞታ በተገኘችው ተማሪ (ሃይማኖት በዳዳ) የተጠረጠረው ግለሰብ በቁጥጥር መዋሉን ፖሊስ አስታወቀ

    አዲስ አበባ (ኢፕድ) – ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ውስጥ የተገደለችው የወጣት ሃይማኖት በዳዳ ተጠርጣሪ ገዳይ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ስር ያዋለው የአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪ የሆነውና በ20ዎቹ እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ ደግነት ወርቁ የተባለ ወጣት ሲሆን፥ ወጣት ደግነት ወርቁን ፖሊስ የ27 ዓመቷን ሃይማኖት በዳዳ ሕይወት በማጥፋት ጠርጥሮት በቁጥጥር ስር አውሎታል።

    ግንቦት 20 ቀን 2012 ዓ.ም. ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት ባካሄደው ክትትል ነው ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር የዋለው። ቀን ከሌሊት በተካሄደው በዚህ ክትትል የተያዘው ወጣቱ ደግነት ወርቁ ከሟች ጋር ምንም ዓይነት ትውውቅ እንዳልነበራቸው በቁጥጥር ስር በኋላ ለሰዓታት በተደረገ ምርመራ የወንጀሉን ዝርዝር ለፖሊስ አስርድቷል።

    ግለሰቡ የ12ኛ ክፍል ተማሪ እንደነበርና የኤች አይ ቪ ኤድስ መድኃኒት ለማግኘት ምርምር ላይ ስለሆንኩ የጥቁር አንበሳ ሐኪሞች ይርዱኝ በማለት ወደ ግቢው በተለያዩ ጊዜያት ይመላለስ እንደነበር ዘርዝሯል። ከዚያም በግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደልማዱ ለዚሁ ጉዳይ እንደመጣ ገንዘብ እንደተቸገረና ቢላዋ ይዞ በግቢው ውስጥ ከሚገኙ ቢሮዎች በአንዱ ላፕቶፕ ወይም ሞባይል ካገኘ ሰርቆ ሽጦ ለመጠቀም ሲዟዟር የሟች ክፍል ክፍት በመሆኑ መግባቱን አስረድቷል። ሟች ሃይማኖት በዳዳ ሞባይሏን እንድትሰጠው ጠይቋት እምቢ ስትለው መታገላቸውንና ከዚያም በያዘው ስለት ወግቷት ንብረቱን ይዞ መውጣቱን ተናግሯል።

    ፖሊስ ከሟች ጋር የቅርብ ግንኙነት የነበራቸው 12 ተጠርጣሪዎችን ይዞ ተጨማሪ ምርመራ ማድረጉን የግድያ ወንጀሎች ምርመራ ዳይሬክቶሬት ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ኢቲቪ) ገልጿል። ለፖሊስ ምርመራ ትልቅ አቅም የሆነው የሟች ወላጅ አባት ከሳምንት በፊት ለልጃቸው የሰጧት የ5 ሺ ብር ቼክ ነው።

    ገዳዩ በወቅቱ የሟችን ላፕቶፕና ሞባይል ፓስፖርት መታወቂያና ይህንን ቼክ ወስዶ ስለነበር ቼኩን የካ አካባቢ በአንድ ባጃጅ ተሳፍሮ አሽከርካሪውን መታወቂያ ስላልያዝኩ በአንተ መታወቂያ ይህንን ብር አውጣልኝ ብሎት የባጃጁ ሹፌርም (አቶ እንዳለማው ታረቀኝ) መልኩን አስተውሎ ስለነበር ምርመራው ከዚህ እንደጀመረ ፖሊስ ገልጿል፡

    ኮሚሽኑ በወቅቱ የሆስፒታሉ የደኅንነት (security) ካሜራ ከአገልግሎት ውጪ መሆኑን (‘update’ እንዳልተደረገ) እና የጥበቃ ሠራተኞችም ቢላዋ ተይዞ እስከሚገባ ፍተሻቸው አጋላጭ መሆኑንም ጠቁሟል ሲል የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ዘግቧል።

    ሃይማኖት በዳዳ ማነች?

    ወጣት ሃይማኖት በዳዳ ተወልዳ ያደገችው መተሃራ ከተማ ሲሆን፥ ወላጆች በአሁኑ ወቅት በአዳማ ከተማ ጎሮ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ይኖራሉ። በ2009 ዓ.ም. ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በ’ክሊኒካል ፋርማሲ’ የመጀመሪያ ዲግሪዋን በማዕረግ ያገኘች ሲሆን፥ በዚያው በተማረችበት ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት ስታገለግል ነበር። ከዚያም በ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሁለተኛ ዲግሪዋን በመከታተል ላይ እንደነበረች አባቷ አቶ በዳዳ ፈይሳ ተናግረዋል።

    የሃይማኖት አባት አቶ በዳዳ ፈይሳ ልጃቸው 2009 ዓ.ም ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ በ’ክሊኒካል ፋርማሲስት’ በማዕረግ ተመርቃ በዩኒቨርስቲው በመምህርነት ስታገለግል መቆየቷን ያስታውሳሉ። ከዚያም ሁለተኛ ዲግሪዋን ለመማር ወደ ጥቁር አንበሳ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተልካ ትምህርቷን በመከታተል ላይ እንደነበረች ይናገራሉ።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) እና ቢቢሲ አማርኛ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 

    ሃይማኖት በዳዳ

    Anonymous
    Inactive

    የተሻሻለው የወሎ ቴሪሸሪ የህክምናና የማስተማሪያ ሆስፒታል ዲዛይን ለሕዝብ ይፋ ሆነ

    ደሴ (ወሎ ዩኒቨርሲቲ) – በጥቂት ሀገር ወዳድ ግለሰቦች ሀሳቡ ተጠንስሶ ሀገራዊ የሕዝብ ፕሮጀክት የሆነው የወሎ ልዕለ ህክምና የማስተማሪያ ሆስፒታል /ሦስተኛ ትውልድ ሆስፒታል/ (Wollo Tertiary Care and Teaching Hospital) ያጋጠሙትን ተግዳሮቶች በየጊዜው እየፈታ ከመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ተዳርሷል።

    ይህንን የሕዝብ ፕሮጀክት ነሐሴ 24 ቀን 2008 ዓ.ም. ያለ በጀትና ዲዛይን በባለቤትነት የተረከበው ወሎ ዩኒቨርሲቲ ወደ ሥራ ለመግባት ከሕዝብ የተሰበሰበውን በጀትና ዲዛይን ሊያስረክብ የሚችል አካል በመጥፋቱ ተቸግሮ ቆይቷል።

    ዩኒቨርሲቲው የሕዝቡ ፍላጎትና ጥያቄዎች እየተበራከቱ ሲመጡበት የዋና ሆስፒታል ዲዛይን መረከብ እስኪችል ድረስ በራሱ ወጭ በ460 ሚሊዮን ብር የተማሪዎች መኖሪያ G+4 10 ህንጻዎችን በመገንባት ላይ ይገኛል።

    የሆስፒታሉን ዲዛይን የተረከበው አማካሪ ድርጅት ሰርቶ ማቅረብ ባለመቻሉ በ2011 ዓ.ም. አጋማሽ ዩኒቨርሲቲው ውለታውን በማቋረጥ ከአዲሱ የኤምቲቲ አማካሪ አርክቴክቶችና ምህንድስና ኃ/የተ/ የግል ኩባንያ (MTT Consulting and Architects and Engineers PLC) ድርጅት ጋር ውለታ በመፈጸም ዲዛይኑን ለአዲሱ ድርጅት አስረክቧል።

    የኤምቲቲ አማካሪ ድርጅት የተረከበው ዲዛይን ከዓለም የቴክኖሎጅ እድገትና ከዘመኑ የኪነ ህንጻ ጥበብ ጋር ሊዛመዱ በማይችሉ የመዋቅር፣ የኤሌክትሮ መካኒክ፣ የፍሳሽ ማስወገጃና መሰል በርካታ ተግዳሮቶች ያሉበት በመሆኑ የዲዛይን ማሻሻያዎችን ሠርቶ ለሕዝብ ይፋ አድርጓል።

    የኤምቲቲ አማካሪ ድርጅት የሆስፒታሉን ዲዛይን ከማሻሻሉም ባሻገር የሆቴል ቱሪዝምን ለማበረታታት ባለ 5 ኮኮብ ሆቴል፣ የባሕላዊ ህክምና መስጭያ ማዕከልና ከአካባቢው ባህልና ሥነ-ምህዳር ጋር የሚዛመዱ ተያያዥ ማዕከላትን የሆስፒታሉ አካል እንድሆኑ በማካተት ይፋ አድርጓል።

    ይህንን ይፋ የሆነ የሆስፒታል ዲዛይን የተመለከቱት የደሴ ከተማ የሕዝብ ተወካዮች፣ የዘርፉ ባለሞያዎች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ባለሙያዎች በተሻሻለው ዲዛይን ላይ የተሰማቸውን ስሜት በመግለጽ ቢካተቱ ያሏቸውን ጥያቄዎች አቅርበዋል።

    የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አባተ ጌታሁን ዋናውን ሆስፒታል ወደ መሬት ለማውረድ ያጋጠማቸውን ተግዳሮቶች በመጥቀስ ዩኒቨርሲቲው የሕዝብን ስሜት ለመጠበቅ በራሱ የተጓዘውን ርቀት አብራርተዋል። ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው ከሕዝብ የተሰበሰበውን አምስት ሳንቲም እንኳን እንዳልተረከቡ በመግለጽ ፕሮጀክቱን እውን ለማድረግ አማካሪው ኤምቲቲ አማካሪ ድርጅት የሀሳቡ ጠንሳሽ ዶ/ር በላይ አበጋዝን ጨምሮ በጤና ሚኔስተርበአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲበጥቁር አንበሳና በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታሎች ያሉ የዘርፉ ምሁራንን በማሳተፍ ሆስፒታሉ እውን እንድሆን ለተሠራው ሥራ አመስግነዋል።

    የኤምቲቲ አማካሪ ድርጅት በበኩሉ በሕዝብ የተነሱትን ጥያቄዎችና አስተያየቶች በማካተት ፕሮጀክቱ ወደ መሬት በቅርብ ቀን እንዲወርድ የቻለውን ሁሉ እንደሚሠራ ቃል ገብቷል።

    ምንጭ፦ ወሎ ዩኒቨርሲቲ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የወሎ ልዕለ ህክምና የማስተማሪያ ሆስፒታል


    Semonegna
    Keymaster

    ብርሃን ባንክ የ10ኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ በዓሉን ሲያከብር ለኢትዮጵያ ልብ ህሙማን ሕፃናት መርጃ ድርጅት የ3 ሚሊዮን ብር እንዲሁም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የአጥንት ህክምና ክፍል የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ብርሃን ባንክ የ10ኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ በዓሉን ህዳር 16 ቀን 2012 ዓ.ም. በተለያዩ ሥነ-ሥርዓቶች በስካይላይት ሆቴል በደማቅ ሁኔታ አክብሯል። በዝግጅቱ ባንኩ ለአገልሎት ክፍት ከሆነበት ከከፈረንጆች ጥቅምት (October) ወር 2009 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ዛሬ ያሉ የተለያዩ ዋነኛ ስኬቶቹን በማወደስ፣ የወደፊት ጊዜያትን ደግሞ በጠንካራ አቅም ሊጓዝ እንዳቀደ ነው ያስረዳው። የእለቱ ዝግጅት በሦስት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያነጣጠረ ሆኖ በተለያዩ መርሃግብሮች በስኬት ተጠናቅቋል።

    ከተለያዩ የህትመት እና ኤሌክተሮኒክስ ሚዲያ ተቋማት ተጋብዘው በቀረቡ የሚዲያ አካላት በተዘጋጀው የባንኩ የዲሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ እና የባንኩ ፕሬዚዳንት በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ እስከ 11፡45 ድረስ ተከናውኗል። በማስከተልም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ወንበሮቻቸውን እንደያዙ በመድረኩ ላይ በእውቅ የሙዚቃ ተጫዋቾች አማካኝነት ድንቅ የሆነ የቫዮሊን የሙዚቃ ኮንሰርት ለታዳሚያኑ ቀርቧል። ይህንንም ተከትሎ በአርቲስት ሃረገወይን አሠፋ የመድረክ አጋፋሪነት ለእንግዶቹ የሚቀርበው የአዳራሽ ውስጥ ዝግጅቱ በይፋ ተጀመረ። አርቲስት ሃረገወይን የባንኩን የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ካቀረበች እና አጠር ያለ የ10 ዓመታት የባንኩን የአመሰራረት አፅመ ታሪክ በአጭሩ አቅርባ መድረኩን እንዲረከቧት እና የእለቱን የክብር እንግዶች ወደ መድረክ እንዲጋብዙ የባንኩን ፕሬዚዳንት አቶ አብሃም አላሮን ወደ መድረኩ ጋበዘች።

    የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አብሃም አላሮ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት እንዲያስተላልፉ የብሔራዊ ባንክ ገዥ የሆኑትን ይናገር ደሴ (ዶ/ር) ወደ መድረክ ጋብዘው ገዥው ባንኩ በርካታ ባለአክሲዮኖችን በመያዝ ቀዳሚው የንግድ ባንክ መሆኑን ገልፀው ለመላው የባንኩ ማህበረሰብ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አቅርበዋል። በማስከተልም የቀረበው የባንኩ የዲሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጉማቸው ኩሴ የእንኳን አደረሳችሁ እና እንኳን ደስ ያላችሁ መልክት ሲሆን፥ ሰብሳቢው በመልዕከታቸው የባንኩን ስኬቶች በማወደስ ቀጣይ ሥራዎችን በተሻለ አቅም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ እምነታቸውን ገልፀዋል። ይህ ዝግጅት እንዲህ ባለው መልኩ ቀጥሎ በባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አብርሃም አላሮ አጠር ያለ የኢትዮጵያ ባንኮችን ታሪክ እና እድገት እንዲሁም ብርሃን ባንክ በ10 ዓመታት ዕድሜው ያሳየውን የአፈፃፀም ጉዞን የሚያሳይ ጥናት ቀርቧል። ፕሬዚዳንቱ ባንኩ ከምሥረታው ጀምሮ በተለያዩ ልኬቶች ያስመዘገባቸው ስኬቶቹ እጅግ አመርቂ እና ፍሬያማ የሚባሉ መሆናቸውን አብራርተው በቀጣይም እነኚህ ስኬቶቹ በላቀ መልኩ አሸብርቀው እንደሚቀጥሉ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።

    በማስከተል የቀረበው ለባንኩ መመሥረት እንዲሁም በተለያዩ መንገዶች ባንኩን ከምሥረታው ጀምሮ ላገዙ መሥራቾች፣ አመራሮች እንዲሁም ላለፉት አስር ዓመታት በባንኩ ላገለገሉ ሠራተኞች የእውቅና እና የምስጋና ስጦታዎችን የማበርከት ሥነ-ሥርዓት ነበር። ከምስጋና የምስክር ወረቀት (certificate) ጀምሮ 13 ሠራተኞቹን ጨምሮ ለተለያዩ ባለድርሻዎች በወርቅ በተሠሩ ስጦታዎች ተበርክቶላቸዋል። ይህንኑ መርሀ ግብር ተከትሎ ብርሃን ባንክ ለኢትዮጵያ ልብ ህሙማን ሕፃናት መርጃ ድርጅት የ3 ሚሊዮን ብር እንዲሁም በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የአጥንት ህክምና ክፍል 2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል። ይህንኑ ስጦታ የማዕከላቱ ተጠሪዎች ዶክተር ሄለን በፈቃዱ (የልብ ሕሙማን ህፃናት ድርጅትን በመወከል) እና ዶክተር ብሩክ ላምቢሶ (የአጥንት ህክምና ክፍልን በመወከል) ከባንኩ የዲሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ እጅ ተቀብለዋል። ይሀንን ስጦታ ሲቀበሉም ድጋፉ በሚደረግላቸው እና የህክምና ወጪዎቻቸውን መሸፈን በማይችሉ አቅመ ደካማ ህፃናት እና አረጋውያን ስም አመስገነው ገንዘቡን ሙሉ በሙሉ ለታለመለት ዓላማ እንደሚያውሉ ከምስጋና ጋር ቃል ገብተዋል።

    በዝግጅቱ መጨረሻ ላይም የባንኩ ቀጣይ የንግድ ምልክት ወይም መለያ ምልክት ሆኖ የሚያገለግለውን አዲስ አርማ ለታዳሚያን ተዋውቆ የዕለቱ ዝግጅት በእራት መርሀ ግብር በደማቅ ሁኔታ ተገባዷል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ብርሃን ባንክ

    Semonegna
    Keymaster

    የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የካንሰርና የልብ ህክምና ማዕከል ግንባታ 56 በመቶ ደርሷል

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ከ986 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የሚያስገነባው የካንሰርና የልብ ህክምና ማዕከልን በተያዘለት ግዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑን ተገለጸ።

    የሆስፒታሉ የምህንድስና ኢንጂነሪንግ ክፍል አስተባባሪ ኢንጅነር ሞቲ አሰፋ ለ ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደገለጹት እየተገነቡ ያሉት የካንሰርና የልብ ህክምና ማዕከላት መጀመሪያ አካባቢ ቶሎ ወደ ሥራ ያለመግባትና በብረት ዋጋ ንረት ምክንያት መዘግየት የታየበት ቢሆንም ግንባታው 56 በመቶ ደርሷል።

    የማዕከላቱ መሠረት በ12 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን ባለ12 እና 10 ወለል ህንፃዎች ይኖሩታል ብለዋል። ህንፃዎቹ ከ600 በላይ የመኝታ ክፍሎች እንደሚኖራቸው ነው ኢንጂነር ሞቲ ያብራሩት።

    ከዚሁ ጎን ለጎን ከተጀመረ ስምንት ዓመታትን ያስቆጠረውና ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የእናቶችና ህጻናት ማዕከል ባለ 8 ወለል ህንፃም በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

    በህንጻ ተቋራጩ እና ክትትል በሚያደርገው ተቆጣጣሪ ድክመት ምክንያት ተጓትቶ የነበረው ፕሮጀክቱ ባለሙያዎችን በመቀየር በአሁኑ ወቅት ሥራው በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝና በዚህ ሳምንት ከፊሉን ሥራ ለማስጀመር እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው ብለዋል።

    ◌ Ethiopia: Are Ethiopian hospitals constructed in environment-suitable and climate-friendly way?

    የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ሜዲካል አገልግሎት ዋና ፕሮቮስት ዶ/ር ወንድማገኝ ገዛኸኝ በበኩላቸው ማዕከላቱ አገልግሎት መስጠት ሲጀምሩ በሀገሪቱ በካንሰርና በልብ ህመም ለሚሰቃዩ ዜጎች የሚሰጡት ጥቅም ከፍተኛ ነው ብለዋል። በተለይ ህክምናዎቹ የሚጠይቁት ወጪ ከፍተኛ በመሆኑ አብዛኛውን ህብረተሰብ ተጠቃሚ ያደርጋል ነው ያሉት።

    ከሰባት ዓመት በፊት ሆስፒታሉ በቀን ከ500 ያልበለጡ ህሙማንን ብቻ ያስተናግድ እንደነበር የተናገሩት ዶክተር ወንድማገኝ፥ በአሁኑ ወቅት በየቀኑ ለሁለት ሺህ ሰዎች ህክምና አገልግሎት እያገኙ ነው ብለዋል።

    በአሁኑ በወቅት በወር ለ1 ሺህ 500 እናቶች የወሊድ አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን በግንባታ ላይ የሚገኘው የእናቶችና ህፃናት ህንፃ ሲጠናቀቅ በቀን ለ400 እናቶች የወሊድ አገልግሎት መስጠት እንደሚችል ጠቁመዋል።

    ህንፃው 15 የማዋለጃ ክፍሎች እንደሚኖሩት የጠቀሱት ዶ/ር ወንድማገኝ በቅርቡ አገልግሎቱን ለማስጀመር ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን አንስተዋል።

    የሆስፒታሉ ሀኪም ዶ/ር ዮናስ ገብረጊዮርጊስ በበኩላቸው የሚገነቡት የካንሰርና የልብ ህክምና ማዕከላት በሀገሪቱ በመንግስት በብቸኝነት አገልግሎት እየሰጠ ካለው የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተጨማሪ በመሆን ህብረተሰቡ የጤና አገልግሎቱን በአቅራቢያው እንዲያገኝ ያስችላል ብለዋል።

    የማዕከላቱ መገንባት በሀገሪቱ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ የመጣውን የካንሰር ህመም ለመከላከል የሚሰጠው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩት ዶክተር ዮናስ ግንባታው በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

    ፕሮጀክቱ በሁለት ዓመት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምርም ተነግሯል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የካንሰርና የልብ ህክምና ማዕከል

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የጃፓን መንግስት በኢትዮጵያ ለትምህርትና ጤና አገልግሎት የሚውል ከ452 ሺህ ዶላር በላይ ድጋፍ አደረገ። የጃፓን መንግስት አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲው በኩል ያደረገው የገንዘብ ድጋፍ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚገኙ አራት ፕሮጀክቶችን ለመገንባትና ለማስፋፋት ያስችላል።

    በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ዲያሱኬ ማሱናጋ (Daisuke Matsunaga) የፕሮጀክት ግንባታና ማስፋፊያ ከሚደረግላቸው ትምህርት ቤቶች ኃላፊዎች ጋር የድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል።

    ፕሮጀክቶቹ በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን የጉንችሬ እና እነሞር ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታና በኦሮሚያ ክልል በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የሀሮ ሾጤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ማስፋፊያ ናቸው።

    በተጨማሪም ለሻሻመኔ ከተማ የአረጋዊያንና አካል ጉዳተኞች የምግባረ ሰናይ መጠለያ ግንባታና ለጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የዩሮሎጂ እና ድንገተኛ ክፍል የህክምና መሣሪያዎች ግዥ የሚውል ነው።

    እነዚህ አራት የትምህርት እና የጤና ፕሮጀክቶች ከአራት ሺህ በላይ ህዝብ ተጠቃሚ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲል የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዘግቧል።

    አምባሳደር ዲያሱኬ ማሱናጋ እንዳሉት አገራቸው ለኢትዮጵያ ልማት ተሳትፎ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ ትቀጥላለች። ጃፓን በኢትዮጵያ እ.አ.አ ከ1989 ጀምሮ በተለያዩ ክልሎች ከ400 በላይ ፕሮጀክቶችን በመሥራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረገች ነው።

    በትምህርት፣ በቴክኒክና ሙያ ስልጠና፣ በንጹህ ውሃ አቅርቦት፣ በኢኮኖሚ ልማትና ሌሎችም መስኮች ድጋፍ ስታደርግም ቆይታለች።

    በስምምነቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ስፖርት ኮሚሽነር እርስቱ ይርዳው የተደረገው ድጋፍ የዝቅተኛውን የህብረተሰብ ክፍል የትምህርት ፍላጎት ለማሟላት እንደሚያስችል ገልጸዋል።

    ድጋፉ በተለይም ትምህርት ቤት ባልተዳረሰባቸው አካባቢዎች መሆኑ የትምህርት ሽፋንን በማስፋት የመንግስትን ጥረት እንደሚያግዝም ተናግረዋል፡፡

    ከዚህ ጋር በተያያዘ የጃፓን ኤምባሲ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚገኘውን የራስ መኰንን አዳራሽ ለማደስ የ85 ሺሕ 679 ዶላር (2,403,500 ብር) ዕርዳታ መለገሱን ሪፖርተር ጋዜጣ በእሁድ ታህሳስ 7 ቀን 2011 ዓ.ም. እትሙ ዘግቧል።

    አምባሳደር ዲያሱኬ ማሱናጋ እና የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ዳይሬክተር አህመድ ሐሰን (ዶ/ር) የእርዳታ ስምምነቱን የተፈራረሙ ሲሆን፣ ገንዘቡም የራስ መኰንን አዳራሽ ባህላዊና ታሪካዊ ዳራው ሳይጠፋ ለማደስ፣ የተበላሹ ክፍሎችን ለመጠገን፣ ውስጣዊ ክፍሉን ለማደስ እና አዳዲስ ቁሳቁስ ለማስገባት መሆኑ ታውቋል።

    የጃፓን መንግስት ትምህርታዊ ድጋፍ ከማድረጉም በተጨማሪ የራስ መኰንን አዳራሽን ለማደስ መነሳቱ፣ የኢትዮጵያ ጥናት ተቋም ኢትኖሎጂካል ሙዚየም በርካታ ጎብኚዎች እንዲስብ ያስችላል ተብሏል።

    በሙዚየሙ ከአሥር ሺሕ በላይ የኢትዮጵያ ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶች የሚገለጹባቸው አልባሳትና ቁሳቁሶች አሉ፤ ይህም በአፍሪካ አንዱ ታዋቂ ሙዚየም እንዲሆን አስችሏል።

    በቀድሞው የገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ሕንፃ ውስጥ የሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም፣ ከ50 ዓመታት በላይ ዕድሜው በስሩ ያቀፋቸው ቤተ-መጻሕፍት፣ የኢትኖግራፊክ ሙዚየም የምርምርና የጥናት ማዕከልን ነው። በውስጡም መጻሕፍት፣ ታሪካዊ ሰነዶችና መዛግብት፣ የዳግማዊ ምኒልክና የእቴጌ ጣይቱን ጨምሮ የድምፅና የምስል ቅጂዎች፣ ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ማሟያ የጥናት ድርሳኖች፣ ጆርናሎች፣ ረጅም ዕድሜን ያስቆጠሩ የብራና መጻሕፍትንም ይዟል።

    እንዲሁም እስከ 20 ሺሕ የሚደርሱ የኅትመት ክምችቶች ከቅድመ ምረቃ እስከ ድኅረ ምረቃ ተማሪዎች፣ ለተመራማሪዎች ጥናትና ምርምር አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

    የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2010 ዓ.ም. መስከረም ወር ከጃፓኑ ኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ ጋር ትምህርታዊ ልውውጥና የጥናት ትብብር ለማድረግ የመግባቢያ ሰነድ መፈረሙ ይታወሳል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ እና ሪፖርተር ጋዜጣ

    የጃፓን መንግስት

    Semonegna
    Keymaster

    ኢትዮጵያ ውስጥ እስካሁን ድረስ የካንሰር ህክምና አገልግሎት በብቸኝነት ሲሰጥ የነበረው የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንደነበረና የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ይህን አገልግሎት መጀመሩ ለታካሚዎች ትልቅ አስተዋጽዖ ይኖረዋል።

    አዲስ አባባ (ዋልታ/ ሰሞነኛ) – የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ከመስከረም 2 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ የካንሰር ህክምና አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ አስታውቋል። ሆስፒታሉ ህክምናውን ከጀመረበት ቀን አንስቶ እስካሁን ድረስ ከ300 በላይ የካንሰር ታማሚዎችን በተመላላሽ ማከሙንም ገልጿል።

    በሆስፒታሉ የካንሰር ህክምና ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር አብዲ አደም የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ይህንን ህክምና መጀመሩ ከዚህ በፊት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በቦታ ጥበት ምክንያት በወረፋ ለሚንገላቱ ታካሚዎች መፍትሔ ይዞ መምጣቱን ገልጸዋል።

    እስካሁን በተመላላሽ ህክምና ለታካሚዎች አገልግሎት ሲሠጥ መቆየቱን የገለጹት ዶ/ር አብዲ በቅርቡ አስተኝቶ ማከም የሚያስችል ወደ 350 የሚጠጋ አልጋ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታውቀዋል።

    ዋልታ ያነጋገራቸው በሆስፒታሉ የካንሰር ታካሚዎች እንደገለጹት ከዚህ በፊት ህክምናውን ለማግኘት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እስከ ስድስት ወር እንደሚወስድ ገልጸው አሁን ግን በቅዱስ ጳውሎስ አገልግሎት መጀመሩ ያለምንም ወረፋ ህክምናን ለማግኘት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

    Ethiopia: Are Ethiopian hospitals constructed in environment-suitable and climate-friendly way?

    በኢትዮጵያ የተደራጀ የጥናት ውጤት ባይኖርም በግምት በዓመት ከ160 ሺህ በላይ የካንሰር ተጠቂዎች እንደሚኖሩ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። እ.ኤ.አ በ2012 በተደረገ ጥናት ኢትዮጵያ ውስጥ በዓመት ውስጥ ከሚሞቱ ሰዎች ውስጥ 5.8 በመቶ የሚሆኑት በካንሰር ምክንያት እንደሚሞቱ ይጠቁማል። በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ስር የብሔራዊ የካንሰር ቁጥጥር ፕላን ባወጣው በዚህ ጥናት ምንም እንኳን ከአዲስ አበባ ከተማ ውጪ አጠቃላይ የሕዝብ ቆጠራን ተገን ያደረገ አሀዝ (population-based data) ባይኖርም ኢትዮጵያ ውስጥ በየዓመቱ 60,960 ሰዎች በተለያዩ ዓይነት የካንሰር በሽታዎች እንደሚጠቁና 44,000 ሰዎች ደግሞ በካንሰር ምክንያት እንደሚሞቱ ያትታል። በዚህም የካንሰር በሽታ በከፍተኛ ቁጥር ሰዎችን ከሚያጠቁ አራት ተለላፊ ካልሆኑ በሽታዎች [non-communicable diseases] ውስጥ ከልብ በሽታ ቀጥሎ ሁለተኛው ነው። (እነዚህ አራቱ ተለላፊ ከሆኑ በሽታዎች የልብ በሽታ፣ ካንሰር፣ የስኳር በሽታ እና የሳንባ በሽታ ሲሆኑ ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎ ከሚሞቱት ሰዎች ቁጥር 80 በመቶ የሚሆነው ከእነዚህ በሽታዎች በአንዱ ምክንያት የሚሞት ነው።) ኢትዮጵያ ውስጥ ወንዶች ላይ የደምየ አንጀት ካንሰሮች፣ ሴቶች ላይ ደግሞ የጡት ካንሰር በከፍተኛ መጠን እንደሚታይ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ሪፖርት ያሳያል።

    የዓለም ጤና ድርጅት ለአንድ ሚሊዮን ሰዎች አንድ የካንሰር ህክምና ተቋም ሊኖር እንደሚገባ ቢመክርም በኢትዮጵያ ግን ከ1987 ዓ.ም ጀምሮ የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በብቸኝነት የህክምናውን አገልግሎት ይሰጥ እንደነበርና እ. ኤ.አ በ2017 በወጣ አሃዝ ከ6,000 በላይ የካንሰር ታካሚዎችን እያከመ እንደሚገኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ። የስዊዘርላንዱ መድኃኒት አምራች ግዙፍ ኩባንያ ኖቫትሪስ (Novartis) እ.ኤ.አ በ2017 ባወጣው ዘገባ ከ100 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ በቁጥር ስምንት ኦንኮሎጂስቶች (የካንሰር ሀኪሞች) ብቻ እንዳላት አስታውቋል። ሌላ ተመሳስይ ጥናት ደግሞ ብቸኛው የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ካሉት 627 ነርሶች ውስጥ 26ቱ ብቻ የካንሰር ህክምና ነርሶች እንደሆነ ይጠቁማል።

    ዋልታ | ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል

Viewing 6 results - 1 through 6 (of 6 total)