Search Results for 'አዲስ አበባ'

Home Forums Search Search Results for 'አዲስ አበባ'

Viewing 15 results - 481 through 495 (of 495 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአገር ውስጥ ሰላም እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በሕዝቡ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር እንዲቋቋም ተወስኗል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የሚኒስትሮች ምክር ቤት መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የፌደራል መንግሥትን አስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በተዘጋጀ ረቀቅ አዋጅ ላይ መክሮ እንዲጸድቅ ለተወካዮች ምክር ቤት እንዲላክ ወስኗል።

    በውይይቱ ላይ የአስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን ያስፈለገበት ዋና ዋና ምክንያቶች እንደሚከተለው ቀርቧል፦

    1. የሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በቀሪው ጊዜ ያልተጠናቀቁ ሥራዎችን አካክሶ ለመፈጸም የሚያስችል አደረጃጀት በማስፈለጉ፤
    2. አገራችን የተያያዘችውን የለውጥ ጉዞ ለማስቀጠልና የማይቀለበስበት ደረጃ ላይ ለማድረስ የሚያስችል አደረጃጀትን መከተል በማስፈለጉ፤
    3. የአስፈጻሚ አካላትን ቁጥር ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢና ውጤታማ ለማድረግ በማስፈለጉ፤
    4. ተደራራቢና ድግግሞሽ ሥልጣንና ተግባር የያዙ የመንግሥት ተቋማትን መቀነስ ወይም ለሥራቸው ቅርብ ከሆነ ሌላ የመንግሥት ተቋም ጋር እንዲዋሃዱ ማድረግ በማስፈለጉ፤

    እንደሆነ በስብሰባው ላይ ተብራርቷል።

    በምክር ቤቱም ውሳኔ የካቢኔ አባላት ቁጥር ከ28 ወደ 20 እንዲቀንስ ተደርጓል፤ ዋና ዋናዎቹ ለውጦችም:-

    • የንግድ ሚኒስቴር እና የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተዋህደው – የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እንዲሆን ፤
    • በየሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተዋህደው – የኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሆን ፤
    • የከተማ ልማት ሚኒስቴር እና የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ተዋህደው – የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር እንዲሆን
      ወስኗል።

    ሌሎች ተጠሪ ተቋማትም በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲዋሃዱ ውሳኔ የተሰጠባቸው ይገኛሉ።

    ሌላው ቁልፍ ውሳኔ በአገር ውስጥ ሰላም እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በሕዝቡ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር እንዲቋቋም ተወስኗል።

    ከትምህርት ሚንስቴር ሁሉንም ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን በመውሰድ እንዲሁም ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ስር የሚገኙት ሁለቱን ዩኒቨርሲቲዎች በመጨመር “የከፍተኛ ትምህርትና የሳይንስ ሚንስቴር” ተብሎ እንዲደራጅ ተወስኗል።

    በተጨማሪም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የገቢዎች ሚኒስቴር እና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ የሆነ የጉምሩክ ኮሚሽን በመሆን ሁለት ተቋማት ሆነው እንዲደራጁ ተወስኗል።

    በአዲሱ አደረጃጀት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሚንስቴር ቀርቶ በቀጣይነት የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ለማስተዳደር መሠረታዊ ሚናቸው ንግድ የሆኑትን በመለየት የመንግስትን የባለቤትነት ሚና በተገቢው ሁኔታ የሚያስተዳደር “የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ” በገንዘብ ሚኒስቴር ሥር እንዲቋቋም ተወስኗል። ይህም የመንግሥት ቁልፍ ሚና የሆነው ቁጥጥር (regulation) በልማት ድርጅቶች ላይ ካለው የባለቤትነት ሚና ተለይቶ እንዲታይ እንደሚያግዝ ታምኖበታል።

    ረቂቅ አዋጁ ሌሎች መለስትኛ ለውጦችንም የያዘ ሲሆን፥ በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍጹም አረጋ የፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የሰላም ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    የወሎ ዩኒቨርሲቲ የሚጀምረው የግዕዝ ቋንቋ ትምህርት በቋንቋው የተጻፉ ሥራዎችን ወደ ሌሎች አገርኛ ቋንቋዎች በመተርጎም ጥቅም ላይ ለማዋል እንደሚያስችል በዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊና ሥነ ሰብእ ኮሌጅ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ ጽሁፍ ትምህርት ክፍል ተጠሪ ተናግረዋል።

    ደሴ (ኢዜአ) – የወሎ ዩኒቨርሲቲ ከያዝነው የትምህርት ዘመን ጀምሮ የግዕዝ ቋንቋን በመጀመሪያ ዲግሪ ለማስተማር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታወቀ።

    ዩኒቨርሲቲው ትምህርቱን ለመጀመር በቀረጸው ሥርዓተ ትምህርት (curriculum) ዙሪያ ከምሁራንና ባለድርሻ አካላት ጋር መስከረም 29 ቀን 2011 ዓ.ም ተወያይቷል።

    በዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊና ሥነ ሰብእ ኮሌጅ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ ጽሁፍ ትምህርት ክፍል ተጠሪ ዶክተር እንድሪስ አብይ እንዳስረዱት ግዕዝ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የላቀ ሥፍራ አለው።

    ትምህርቱን ለማስጀመር አራት መምህራን የተቀጠሩ ሲሆን፣ እስከ 18 ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት ማድረጉን ገልጸዋል።

    ሥርዓተ ትምህርቱ ጋዜጠኝነትን ጨምሮ አገር በቀል ህክምናና መድኃኒት፣ የሥነ ከዋክብት ቀመርና የቀን አቆጣጠር፣ የባህልና የህግ ሥርዓቶች ተካተውበታል።

    ትምህርቱ በቋንቋው የተጻፉ ሥራዎችን ወደ ሌሎች አገርኛ ቋንቋዎች በመተርጎም ጥቅም ላይ ለማዋል እንደሚያስችል ዶክተር እንድሪስ ተናግረዋል።

    በቋንቋው በፍልስፍና፣ በህክምና፣ በሥነ ከዋክብትና በመሳሰሉት የዕውቀት ዘርፎች በርካታ ጽሁፎች ቢጻፉም፤ ህዝቡንም ሆነ አገሪቱን መጠቀም የሚገባቸውን ያህል አልተጠቀሙበትም። ዕውቀቱም ለሌሎች ሳይተላለፍ ለረጅም ዓመታት መቆየቱን ተጠሪው ገልጸዋል።

    በዩኒቨርሲቲው የታሪክና ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ትምህርት ክፍል አስተባባሪና መምህር አቶ ዘላለም ጌትነት በበኩላቸው የመጥፋት አደጋ ላይ የሚገኘውንና የዕውቀት ምንጭ የሆነውን ቋንቋ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ መስጠቱ ታሪክን ከማቆየትና እውቀትን ከማጋራት አንጻር ጠቀሜታው ጉልህ ነው ብለዋል።

    ሥርዓተ ትምህርቱ በተለይ ቋንቋው ከኢትዮጵያ ታሪክ ጋር ያለውን ቁርኝት በሚያሳይ መልኩ ቢቀረጽ የተሻለ እንደሚሆን አመልክተዋል።

    በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቲያትር ጥበባት ትምህርት ክፍል መምህርና የሥነ ጥበባት ኮሌጅ የድህረ ምረቃ ተባባሪ ዲን ረዳት ፕሮፌሰር አሰፋ ወርቁ ”ዩኒቨርሲቲው የአገር ሃብት የሆነውን የግዕዝ ቋንቋ ለማስተማር መወሰኑ የሚያስመሰግነውና ሌሎችም ዩኒቨርሲቲዎች ተመሳሳይ ኃላፊነት እንዲወስዱ መነቃቃትን የሚፈጥርላቸው ነው” ብለዋል።

    ግዕዝ ኢትዮጵያን የምናውቅበት የዕውቀት ምንጭ መሆኑን አስታውሰው፣ ይህንን መገናኛ ብዙኃን አገራዊ ፋይዳ ያለውን የዕውቀት ዘርፍ በማስተዋወቅ ድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

    የወሎ ዩንቨርሲቲም ተማሪዎችን ካስመረቀ በኋላ የሥራ ዕድል እንዲያገኙ ከባለድርሻ አካላት ጋር መምከር እንዳለበትም አቶ አሰፋ አሳስበዋል።

    በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ወሎ አገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ መአምራን ብርሃነሕይወት እውነቱ ቋንቋው በዩኒቨርሲቲው መሰጠቱ በርካታ አገራዊ ታሪኮች፣ ቅርሶች፣ መንፈሳዊና ዓለማዊ ሥራዎች፣ ምርምርን የሚጋብዙ ሥራዎች ለማወቅና ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን በአዲስ መንፈስ ለማስቀጠል ጠቀሜታ እንዳለው አስረድተዋል።
    የአብነት ተማሪዎች እንቅስቃሴ መዳከም ቋንቋውን እንዳዳከመው አውስተው፣ የወሎ ዩንቨርሲቲ የጀመረው ጥረት እንዲሳካ ቤተክርስቲያኗ ድርሻዋን ለመወጣት ዝግጁ መሆኗን አስታውቀዋል።

    ከዚህ ጋር በተያያዘ በ1999 ዓ.ም. የተመሠረተው የወሎ ዩኒቨርሲቲ ዓመታዊ የቅበላ አቅም ዘንድሮ ከ20 ሺህ በላይ ደርሷል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የወሎ ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    ቡሬ ከተማ ውስጥ በአቶ በላይነህ ክንዴ የተቋቋመው የፊቤላ ኢንዳስትሪያል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ስር እየተገነባው ያለው የምግብ ዘይት ፋብሪካ ሥራ ሲጀምር በሀገራችን የሚስተዋለዉን የምግብ ዘይት እጥረት በ60 በመቶ ይቀንሳል።

    አዲስ አበባ – በሀገራችን በህብረተሰቡ የመሰረታዊ እቃዎች የዕለት ፍጆታ ላይ የአቅርቦት እጥረት ይስተዋላል። የምግብ ዘይት አቅርቦት እጥረት በመኖሩ መንግስት ለህብረተሰቡ በየወሩ በኮታ ልክ ያከፋፍላል። ይሁንና ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ይገኛል ሲሉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ቅሬታ ያነሳሉ። በአማራ ክልል በወር ከ23 ሚሊየን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት አቅርቦት ያስፈልገዋል። ክልሉ እያሰራጨ ያለው ግን 7 ነጥብ 7 ሚሊየን ሊትር የምግብ ዘይት እንደሆነ ከአማራ ክልል ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

    በቡሬ ከተማ በላይነህ ክንዴ በተሰኙ ባለሀብት ፊቤላ ኢንዱስትሪያል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በሚል ስያሜ የምግብ ዘይትና ሌሎች ምርቶች ማምረቻ ፋብሪካ እየተገነባ ይገኛል። ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦለት ግንባታው የተጀመረው ፋብሪካ የምግብ ዘይት፣ ፕላስቲክ፣ ሳሙና እና የተቀነባበረ ሰሊጥ ያመርታል።

    የፊቤላ ኢንደስትሪያል ኃ/የተ/የግል ማህበር አስተዳደር እና ፋይናንስ ኃላፊ አቶ ጎጃም ዓለሙ እንደተናገሩት በ2006 ዓ.ም የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ወደ ግንባታ ገብቷል። የህንጻ እና መሠረተ ልማት አውታሮች ግንባታ ተጠናቋል። ነገር ግን የዘይት ፋብሪካው የማሽን ተከላ ዘግይቷል። ለዚህም በዋነኝነት እንደምክንያት የሚጠቀሰው ሀገሪቱ ያጋጠማት የውጭ ምንዛሪ እንደሆነ ከዚህ በፊት Mutesi የተሰኘ በአፍሪካ የንግድና ቢዝነስ እንቅስቃሴ ላይ ያተኮረ ሚዲያ ዘግቦ ነብር። አሁን ላይ ግን ማሽኑን ለመትከል ዝግጅቱ ተጠናቋል አቶ ጎጃም እንደገለጹት። በአጭር ጊዜ ውስጥም ወደ ምርት ይገባል ነዉ ያሉት። የፊቤላ ኢንደስትሪ የምግብ ዘይት ማምረት ሥራ ሲጀምር ከ1 ሚሊዮን ሊትር በላይ በቀን የማምረት አቅም ይኖረዋል። በዚህም የአማራ ክልል የዘይት አቅርቦት እጥረትን ከመፍታት አልፎ ከክልሉ ውጭ ላሉ አካባቢዎች ማድረስ ይችላል።

    “የዘይት ፋብሪካው ሥራ ሲጀምር በሀገራችን ያለውን የፋብሪካ ቁጥር ያሳድጋል። በሀገር ደረጃ የሚስተዋለዉን የምግብ ዘይት እጥረት ችግር እስከ 60 በመቶ ይቀንሳል። በየዓመቱ ከ12 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባት እህሎችን በግብዓትነት ስለሚጠቀም ለአርሶ አደሩ የገበያ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ ያደርጋል” በማለት አቶ ጎጃም ተናግረዋል። ወደ ውጭ ምርቶችን በመላክ የውጭ ምንዛሪ ያስገኛልም ብለዋል።

    የመብራት እና የውሀ አቅርቦት ችግር የምርት ሂደቱ ላይ ከፍተኛ ጫና የሚያሳድር እና ጊዜ የማይሰጥ እንቅፋት፥ ምናልባትም ፋብሪካው ሊያጋጥሙት ከሚችሉት ተግዳሮቶች ዋነኛው መሆኑን ጠቁመዉ የሚመለከታቸው አካላት አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

    Ethiopian millionaire Belayneh Kinde and others awarded for investing in pulses, oilseeds & spices

    የቡሬ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድ፣ ኢንደስትሪ እና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይገርማል ሙሉሰዉ በበኩላቸዉ ፊቤላ ኢንደስትሪያል ኃ/የተ/የግል ማኅበር በሀገር ደረጃ የሚስተዋለዉን የምግብ ዘይት አቅርቦት ችግር ይቀንሳል ብለዋል። ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከማስገኘቱ በላይ ለአርሶ አደሩ የገበያ ትስስር በስፋት እንደሚፈጥርም ተናግረዋል።

    የህንጻ እና የመሠረተ ልማት ግንባታዉ ከ95 በመቶ በላይ መጠናቀቁን ጠቅሰዉ የመብራት እና ውሀ አቅርቦት ችግር ካልገጠመው በተያዘው በጀት ዓመት ፋብሪካው ሥራ ይጀምራል። ይሁን እንጂ የመብራት እና የውሀ ችግሩ ስር የሰደደ እና ከከተማ አስተዳደሩ አቅም በላይ በመሆኑ የፌዴራል መንግስት ትኩረት እንደሚያሻዉ አቶ ይገርማል ነግረውናል።

    ፋብሪካው እስከ 1500 ለሚሆኑ ሰዎች በቋሚነት እና በጊዚያዊነት የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅትን ዋቢ በማድረግ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ዘግቧል።

    አቶ በላይነህ ክንዴ ማን ናቸው?

    • የተወለዱት በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ሰቀላ ወረዳ (ቡሬ አጠገብ) ነው፤
    • የአስራ ሁለተኛ ክፍል ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ስላልመጣላቸው ሁርሳ ወታደራዊ ማሠልጠኛ ገብተው ወታደራዊ ስልጠና ተከታትለዋል፤
    • ነገር ግን በውትድርና ሕይወት ብዙም አልገፉም፤ የደርግ መንግስት ወድቆ የኢህአዴግ መንግስት ስልጣን ሲይዝ የውትድርና ሥራን ትተው እጅግ አናሳ በሆነ ገቢ የቀን ሥራ ላይ ተሰማሩ፤
    • በቀን ሥራ ገፍትው ጥቂት ገንዘብ እንዳጠራቀሙ የማር እና የቅቤ ንግድ ጀመሩ፤
    • በማር እና ቅቤ ንግድ ለአስር ዓመታት ሠርተው ንግዳቸውን በማሳደግ “በላይነህ ክንዴ አስመጪና ላኪ” የሚል ድርጅት መሠረቱ፤
    • ይህንን የአስመጪና ላኪነት ሥራ ከጊዜ ወደጊዜ በካፒታል፣ በሥራ ዘርፍ እና ሠራተኞችን በመቅጠር፣… በአጠቃላይ በሁሉም አቅጣጫዎች በማሳደግ በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ጥቂት ሚሊየነሮች ተርታ ሊሰለፉ ችለዋል (ይህንንም በዓለም ታዋቂው የቢዝነስ መጽሔት ፎርቤስ/Forbes በ2009 ዓ.ም ዘገባው አንስቷቸው ነበር)፤
    • በአሁኑ ወቅት የአቶ በላይነህ ክንዴ አጠቃላይ ሀብት ከሶስት ቢሊየን ብር (ከ111 ሚሊየን ዶላር) በላይ ሲሆን የተሰማሩበት የንግድና ምርት ዘርፍም አስመጪና ላኪነት፣ ትራንስፖት፣ የግንባታ ምርቶች፣ እርሻ እና ፋይናንስ ሲሆኑ ሀገሪቱ ውስጥ ባሉ ግዙፍ አክሲዮን ማኅበራት፥ ለምሳሌ ያህል ጎልደን ባስ ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ ሆቴል፣ አዳማ ራስ ሆቴል፣ ፀሐይ ኢንዱስትሪያል ፣ ኳሊቲ ብረታ ብረት ማምረቻ አክሲዮን ማኅበራት ውስጥ ሁነኛ ድርሻ አላቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና Mutesi

    በላይነህ ክንዴ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ – የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ የመክፈቻ ስነ-ሥርዓት በኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) የተከፈተ ሲሆን፥ ፕሬዝዳንቱ በመክፈቻ ንግግራቸው በምክር ቤቶቹ በበጀት ዓመቱ ለማከናወን የታሰቡ ተግባራትን አንስተዋል።

    በንግግራቸው ካነሷቸው ነጥቦች መካከል ሀገሪቱ በሁለተኛው እድገት እና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ (GTP II) አሳካዋለሁ ያለቻቸውን ዕቅዶች በሀገሪቱ በተከሰተ ግጭት እና አለመረጋጋት ምክንያት ማሳካት አልተቻለም ብለዋል።

    ግጭቶች እና አለመረጋጋቶች በሀገሪቱ ሲከሰቱ ከጅምራቸው እንዲቆሙ የማድረግ ውስንነት እንደነበርም ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ አንስተዋል። ይህ ደግሞ የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ አደጋ ውስጥ ከቶታል። በቀጣይ ህልውናዋን ለማረጋገጥ የሚያስችል ወሳኝ የፖለቲካ ምዕራፍ ተጀምሯል ። በዚህ የለውጥ ሂደት የሕዝቡን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውንም እንቅስቃሴዎች የህግ የበላይነትን በሚያረጋግጥ መልኩ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ቁርጠኛ አቋም ተይዟል ብለዋል።

    ከቅርብ ወራት ጀምሮ በፖለቲካው ዘርፍ የታዩ ለውጦች ለወደፊት የሀገሪቱ የለውጥ ጉዞ ትልቅ ሚና ይጫወታል። በስደት ላይ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር የተደረገው ሰላማዊ ድርድር ትልቅ ለውጥ የታየበት የፖለቲካ እንቅስቃሴ ነበር። እንደ ዶክተር ሙላቱ ገለፃ ለዚህ ፖለቲካዊ መሻሻል ምክር ቤቱ ያፀደቀው የምህረት አዋጅ ትልቁን ሚና ተጫውቷልም ነው ያሉት። የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት በተደረገው ጅምር እንቅስቃሴ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ምሁራን፣ጦማሪ እና አክቲቪስቶች በነፃነት የመሥራት እድል ተፈጥሮላቸዋል።

    ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በተቃርኖ ውስጥ የነበሩት ሁለቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክረስቲያን ሲኖዶሶች ችግር ተፈትቶ ወደ አንድ እንዲመጡ መደረጉም የለውጡ አካል ነበር። ለረጅም ዓመታት አለመግባባት ውስጥ የነበሩት አትዮጵያ እና ኤርትራ መግባባታቸው በቀጠናው የነበረውን የድህነት እና ኋላቀርነት መገለጫ ማጥፋት ችሏል።

    ———————————————-

    ———————————————-

    በደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት በዜጎች ላይ ይደርስ የነበረውን ግፍ ኢትዮጵያ መታደግ ችላለች። ከሌሎች አጎራባች እና የውጭ ሀገራት ጋርም ጥብቅ የሆነ ወዳጅነት እንዲኖራት መደረጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተመለከትነው የፖለቲካ ለውጥ ውጤት ነው ብለዋል ፕሬዝዳንቱ።

    ዶክተር ሙላቱ ተሾመ በመክፈቻ ንግግራቸው የዜጎችን ነፃነት እና መሰረታዊ መብቶች ከማስጠበቅ አንፃር የተሠራው ሥራ ውስን እንደነበር ተናግረዋል።

    በአሁኑ ወቅ የሕዝቡ የዴሞክራሲ እና የፖለቲካ ጥያቄዎች የጎለበተበት በመሆኑ መንግስት የፖለቲካ ማሻሻያ የሚያደርግበት ነው ። የተጀመረውን ለውጥ ለማስቀጠል መንግስት በበጀት ዓመቱ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ ይሠራልም ብለዋል።

    አሁን በሀገሪቱ የተጋረጠው የሰላም መደፍረስ ሕዝቡን አደጋ ውስጥ አስገብቶታል። የህግ የበላይነትም ተጥሷል። ፕሬዝዳንቱ በመክፈቻ ንግግራቸው የዜጎችን በሰላም የመኖር መብት እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስድ አሳስበዋል። የመገናኛ ተቋማት በማንኛውም የመገናኛ ዘዴ ሀሳባቸውን በነፃነት የመግለፅ ሁኔታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል።

    ተከስቶ የነበረው ሁከት እና አለመረጋጋት በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ አድርሷል።በስፋት እየታየ ያለውን የኢኮኖሚ አለመረጋጋት ለመቀነስ እና የኢኮኖሚ ምህዳሩን ለማስፋት በዚህ የበጀት ዓመት በተጨባጭ እንደሚሠራም ተናግረዋል። መንግስት የተረጋጋ እና ቀጣይነት ያለው ማክሮ ኢኮኖሚን ለማሳደግ ፅኑ አቋም እንዳለው አንስተዋል። ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የጀመረችው ድርድር በዚህ ዓመት ተጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል ፕሬዝዳንቱ።

    ከመክፈቻ ንግግሩ ለመረዳት እንደተቻለው የምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግስት (ኢጋድ) በማጠናከር እና ወደ ተግባር ገብቶ ቀጠናዊ አገልግሎቱን እንዲያሰፋ ኢትዮጵያ የበኩሏን ድርሻ ትወጣለች።

    ሀገራችን በርካታ አለማቀፍ የስብሰባ መድረክ አገልግሎት እየተካሄደባት በመሆኑ የቪዛ አገልግሎት እንዲሰጥ ይደረጋል። የሚሰጠው የቪዛ አገልግሎት ቀልጣፋ እንዲሆን እየተሠራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አንስተዋል።

    የግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ እንዲሁም የመስኖ እርሻን በማጠናከር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ይሠራል።
    የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ አዲሱን ፍኖተ-ካርታ መሰረት ያደረገ የሥርዓት ትምህርት ማሻሻያ የደረጋል። የሴቶች እና ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በያዝነው በጀት ዓመት የጤና ተቋማት ግንባታ እና ቁሳቁስ አቅርቦት ትኩረት ተሰጥቶት ይሠራል። አሁን የተፈጠረውን ለውጥ ተከትሎ በሥርዓት አልበኞች ምክንያት እየታዩ ያሉ መፈናቀሎችን ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ያስፈልጋል ሲሉ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ በመክፈቻ ንግግራቸው አንስተዋል።

    ምንጭ፦ የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

    ሙላቱ ተሾመ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኢዜአ)፦ መንግሥት በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በአገራቸው ልማት ቀጥተኛ ተሳታፊ እንዲሆኑ እያደረገ ያለውን ሁሉን አቀፍ ጥሪ ከግምት ያስገባ አዲስ አቅጣጫ እየቀየሰ መሆኑን የኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማኅበር አስታወቀ።

    አገሪቱ የጀመረችውን የለውጥ ሥራ ለማገዝ፣ እንደዚሁም በውጭ የሚኖረው ዜጋ በሌሎችም አገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሳታፊ እንዲሆን ለማስቻል ማህበሩ አደረጃጀቱን መልሶ በማዋቀር ላይ ነው ተብሏል።

    በሽርክና ወይንም በሌላ መንገድ በመደራጀት በአገሪቱ የልማት እድገት ውስጥ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ ዝግጁ መሆናቸውን ኢትዮጵያዊያን የዲያስፖራ አባላት ገልፀዋል።

    በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ንዋያቸውን በማቀናጀት አገር ውስጥ መሥራት የሚሹ ከሆነ መንግሥት የተለየ ድጋፍ እንደሚያደርግ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) አረጋግጠዋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትሩ መስከረም 27 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዳማ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የምርቃት ስነ-ስርዓት ላይ ባስተለላፉት መልዕክት፤ በውጭ የመኖሩ ኢትዮጵያዊያን በአገሪቱ ልማት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።

    በተለይም በስቶክ ማርኬት ወይንም በአክሲዮን ንግድ ዘርፍ የተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራ አባላት በተናጠልም ሆነ በመደራጀት ወደ አገራቸው ተመልሰው በልማት እንዲሰመሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠይቀዋል።

    ያላቸውን እውቀትና ገንዘብ በማደራጀት መቅረብ ለሚችሉ የዲያስፖራ አባላት መንግሥት የተለየ ድጋፍ እንደሚያቀርብ ነው ዶ/ር አብይ ያረጋገጡት።

    ቪድዮ፦ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች ሀገር ውስጥ ለመሥራት ያላቸው ፍላጎት እና የሚያጋጥማቸው የቢሮክራሲ ችግር

    ኢትዮጵያዊያኑ ዲያስፖራዎች በበኩላቸው መንግሥት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እያደረገ ያለውን ጥሪ በአዎንታዊ መልኩ እንደሚመለከቱት ገልጸዋል።

    በዚህም በተለይም በሽርክና ወይንም በሌላ መንገድ በመደራጀት በአገሪቱ የልማት እድገት ውስጥ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

    በተደራጀ አግባብ ከጓደኞቻቸው ጋር ተነጋግረው ትልቅ ካምፓኒ ይዘው ለመምጣት ሃሳብ እንዳላቸው የተናገሩት በውጭ የሚኖሩት ወይዘሮ አማኒ መሃመድ ናቸው።

    “የሥራ ሁኔታ እየተመቻቸ ነው፤ ሁሉም ሰው እውቀቱንና ገንዘቡን ኢንቨስት በማድረግ የአገሪቱን እድገት ለማረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ መልካም ነው። እኔም እንደ አንድ ውጭ አገር እንደሚኖር ዜጋ ወደ ሃገሬ መጥቼ ለመሥራት ትልቅ እቅድ ይዤ እንደምመጣ ተስፋ አደርጋለሁ” ያሉት ደግሞ አቶ አማን አህመድ ናቸው።

    የኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማኅበር ዳይሬክተር አቶ አብርሃም ስዩም በበኩላቸው ማኅበራቸው ከሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት ጋር በመሆን የዲያስፖራውን የልማት ተሳትፎ ለማሳደግ እየሠራ ነው።

    በተለይ ደግሞ በኢንደዱትሪ ፓርኮች ላይ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ሊኖራቸው የሚችለውን ተሳትፎ ለማጎልበት ፓርኮቹን የሚጎበኙበት ሁኔታ እየተመቻቸ መሆኑን ተናግረዋል።

    ይህም ዲያስፖራው ስለ ፓርኮቹ በቂ መረጃ እንዲኖረው ትልቅ እድል እንደሚከፍት ገልጸው ማኅበሩ መረጃ ከመስጠቱ ሥራ ጎን ለጎን ሌሎች የውጭ ዜጎችም በዘርፉ እንዲሰማሩ የበኩሉን ጥረት ያደርጋል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማኅበር

    Semonegna
    Keymaster

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያስገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የግንባታ ሥራው የተጀመረው በጥቅምት ወር 2009 ዓ.ም ሲሆን የቻይናው ግዙፍ ኩባንያ ቻይና ሲቪል እንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ግንባታውን ሲያከናውን ነበር።

    አዳማ (Semonegna) – በኦሮሚያ ክልል፣ አዳማ ከተማ የተገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በዛሬው ዕለት (መስከረም 27 ቀን 2011 ዓ.ም.) ተመርቋል። በምርቃቱ ስነ ስርዓት ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) እና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ለማ መገርሳ፣ የአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ የእንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አርከበ ዕቁባይ እና የኮርፖሬሽኑዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ት ሌሊሴ ነሜ እንዲሁም ሌሎች የክልልና የፌደራል ባለስልጣናት ከፍተኛ ተገኝተዋል።

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያስገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የግንባታ ሥራው የተጀመረው በጥቅምት ወር 2009 ዓ.ም ሲሆን የቻይናው ግዙፍ ኩባንያ ቻይና ሲቪል እንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን (China Civil Engineering Construction Corporation/ CCCC) ግንባታውን ሲያከናውን ነበር።

    ከአዲስ አበበ ከተማ 99 ኪሎ ሜትሮች ርቆ የሚገኘው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተለያየ ዘርፍ ለሚሰማሩ አምራች ኩባንያዎች የሚያገለግሉ በአጠቃላይ 19 (በዝርዝር፦ ስድስት 11 ሺህ ካሬ ሜትር፣ ዘጠኝ 5 ሺህ 500 ካሬ ሜትር፣ አራቱ ደግሞ በ3 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፉ) የመሥሪያ ጠለላዎች ወይም የመሥሪያ ቦታዎችን (shades) የያዘ ነው። የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በአጠቃላይ ሊለማ ከታቀደው 2 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በመጀመሪያው ዙር ልማት 354 ሄክታር መሬት የሚይዝ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ለምቶ ለዛሬ ምረቃ የበቃው በ100 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባው ክፍል መሆኑን፣ ይህም ግንባታ 4.1 ቢልዮን ብር መፍጀቱን፣ እንዲሁም ፓርኩ በመጀመሪያው ምዕራፍ በሙሉ አቅም ወደ ምርት ሲገባ እስከ 25 ሺህ ለሚደርሱ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ወ/ት ሌሊሴ ነሜ በምረቃው ንግግራቸው ላይ አስታውቀዋል።

    ◌ RELATED: A visit to Hawassa Industrial Park by Dire Dawa Industrial Park & City’s Administration people

    የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ሥራ መጀመር በሀገሪቱ ወደማምረት የገቡ የኢንዱስትሪ ፓርክኮች ቁጥር ወደ አምስት የሚያሳድገው ሲሆን፥ ከሌሎቹ አራቱ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለየት የሚያደርገው ፓርኩ ያለበት ከተማ (አዳማ) በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ አስተዋጽዖ ያመጣል ተብሎ የታመነበተና አምና ሥራ የጀመረው የአዲስ አበባ-ጅቡቲ የባቡር መስመር በሚያልፍባት የአዳማ ከተማ መገኘቱ ነው። ይህ የባቡር መስመርና የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ እርስ በርሳቸው ጉልህ የሆነ የጥቅም ግንኙነት ይኖራቸዋል ተብሎ ይታመናል። ከዚህ በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ፓሩኩ በከተማ ከሚገኘው የአዳማ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ጋር በማምረት ዘርፍ እና በመማር፣ ማስተማርና ምርምር ዘርፎች መካከል ቁልፍ የሆነ ግንኙነት ይፈጥራሉ ይጠበቃል።

    የሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ ሴክተር (manufacturing sector) ከኢትዮጵያ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) መጠን አራት ነጥብ አምስት በመቶ (4.5%) ድርሻ ብቻ የሚሸፍን ሲሆን፥ መንግስት እስከ 2022 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) ይህን አናሳ ድርሻ ወደ ሀያሁለት በመቶ (22%) ለማሳደግ አቅዳለች። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያ እስከ 2025 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) አሁን ያሏትን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ቁጥር ከአምስት ወደ ሀያ አምስት የማሳደግ ዕቅድ አላት። በያዝነው ዓመት ስድስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች (ድሬ ዳዋ፣ ቂሊንጦ II፣ ቦሌ ለሚ II፣ ጅማ፣ ባህር ዳር እና ደብረ ብርሃን) ግንባታቸው ተጠናቆ ወደምርት ተግባር እንደሚገቡ ዶክተር አርከበ ዕቁባይ አስታውቀዋል። 

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ

    Semonegna
    Keymaster

    የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባን ይፋ ከማድረጉ በፊት ኤጀንሲው የተለያዩ የማጣራት ሥራዎችን በማከናወን ሂደት ውስጥ በመቆየቱ ምክንያት ምደባው ዘገየ በማለት ቅሬታችሁን ስታሰሙ ለነበራችሁ ተማሪዎች እና የተማሪ ቤተሰቦች ከወዲሁ ይቅርታ የጠየቀ ሲሆን ተማሪዎች በተመደባችሁባቸው የትምህርት ተቋማት በምትሄዱበት ወቅት የነገዋ ኢትዮጵያ በእናንተ ትከሻ ላይ መሆኗን በመገንዘብ በትምህርታችሁ ላይ ብቻ ትኩረት በመስጠት ውጤታማ በመሆን ለሀገራችን እድገት እና ልማት የበኩላችሁን አስተዋጽዖ ታበረክቱ ዘንድ ኤጀንሲው ከአደራ ጋር መልዕክቱን አስተላልፏል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ/NEAEA)– የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ይፋ መሆኑን የሀገር አቀፍ የትምህርት ፈተናና ምዘናዎች ኤጀንሲ (NEAEA) አስታወቀ።

    የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ አርዓያ ገብረእግዝአብሔር ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቁት፤ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ከዛሬ ከመስከረም 25 ቀን 2011 ዓም ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ይፋ ሆኗል።

    ምደባው የተማሪዎችን ውጤት፣ የትምህርት ዓይነት፣ የዩንቨርስቲ ምርጫ፣ የዩንቨርስቲዎችን የቅበላ አቅም፣ የወንዶችና የሴቶችን ምጠና ማዕከል ባደረገ እንዲሁም የልዩ ድጋፍ ተጠቃሚዎችን ያገናዘበ መሆኑን ነው ያመላከቱት።

    ዓይነ ስውራንን፣ መስማት የተሳናቸውን፣ አካል ጉዳተኞችን/ በተጨማሪም የጤና እክል ያለባቸው እና ከታወቀ የመንግስት ሆስፒታል የሜዲካል ቦርድ ማረጋገጫ ያቀረቡት ላይ የማጣራት ሥራዎችን ካካሄደ በኋላ ምደባው እንደተዘጋጀም እንዲሁ አስታውቀዋል።።

    በዚሁ መሰረት በዘንድሮው የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና የማለፊያ ነጥቡን ያለፉ 138 ሺ 283 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ሲሆኑ 75ሺ 338 የማህበራዊ ሳይንስ በድምሩ 213 ሺ 621 ናቸው።

    ከነዚህም መካከል 98 ሺ 576 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችና 51 ሺ 229 የማህበራዊ ሳይንስ በድምሩ 149 ሺ 805 ተማሪዎች ቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ ባሉት የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ በአጠቃላይ የሚመደቡ ይሆናል።

    ◌ RELATED: 35 Best Universities and Colleges Ethiopia (public and private)

    ከነዚህም በኤጀንሲው በኩል በ43ቱ የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት 95 ሺ 681 የተፈጥሮ ሳይንስ (natural science) እንዲሁም 51ሺ 066 የማህበራዊ ሳይንስ (social science) በድምሩ 146 ሺ 747 ተማሪዎች መመደባቸውን አስታውቀዋል።

    ተማሪዎች ወደ ተመደቡበት የትምህርት ተቋማት በሚሄዱበት ወቅትም የነገዋ ኢትዮጵያ በትከሻቸው ላይ መሆኗን በመገንዘብ ለትምህርታችሁ ትኩረት እንዲሰጡም አቶ አርአያ አሳስበዋል።

    ከግንቦት 27-30 ቀን 2010 ዓ.ም በተሰጠው የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና (የ12ኛ ክፍል ፈተና) 154,010 ወንዶች እንዲሁም 127,964 ሴቶች በድምሩ 281,974 ተማሪዎች የወሰዱ ሲሆን በሐምሌ 24 ቀን 2010 ዓ.ም ውጤት ይፋ መደረጉ ይታወሳል።

    ተማሪዎች ምደባችሁን በኤጀንሲው ድረ-ገጽ app.neaea.gov.et በመግባት ማየት እንደሚችሉም ነው የገለፁት።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እና የሀገር አቀፍ የትምህርት ፈተናና ምዘናዎች ኤጀንሲ (NEAEA)

    የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት

    Semonegna
    Keymaster

    እንግሊዝ ለኢትዮጵያ ትምህርት ጥራት ያደረገችው ድጋፍ አንድ ሚልዮን የሚጠጉ ተማሪዎችንና 120,000 አስተማሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የእንግሊዟ ተወካይ ሚስስ ሃርየት ባልድዊን አስታውቀዋል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ)–እንግሊዝ ለኢትዮጵያ አጠቃላይ ትምህርት ጥራትና ኢንቨስትመንት መሰረተ ልማት የሚውል 6 ነጥብ 31 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ለመስጠት ተስማማች።

    ስምምነቱ በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አድማሱ ነበበ እና በአፍሪካ የእንግሊዝ ሚኒስትር ዲኤታ (Minister of State at the Foreign Office) ሚስስ ሃርየት ባልድዊን (Harriett Baldwin) መካከል መስከረም 25 ቀን 2011 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተፈርሟል።

    ኢትዮጵያ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል እያከናወነች ያለውን ተግባር የሚያግዝና ለኢንቨስትመንት መሰረተ ልማትና አቅም ግንባታ የሚውል 176 ሚሊዮን ዩሮ ወይም የ6 ነጥብ 31 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ለማድረግ ነው ስምምነት የተደረገው።

    ከዚህ ውስጥ 110 ሚሊዮን ዩሮ ወይንም 3 ነጥብ 94 ሚሊዮን ብር ለአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ እንዲሁም 66 ሚሊዮን ዩሮ ወይንም 2 ነጥብ 36 ቢሊዮን ብር ለኢንቨስትመንት መሰረተ ልማት የሚውል ነው።

    ለአጠቃላይ ትምህርት ጥራት የተደረገው ድጋፍ በአፋር፣ ቤኒሻንጉል ጉምዝና ሶማሌ ክልሎች በቅድመ መደበኛ፣ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን ጨምሮ ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሏል።

    ሚኒስትር ዴኤታው አቶ አድማሱ ነበበ እንደገለጹት የድጋፍ ስምምነቱ ኢትዮጵያ በትምህርት ጥራትና ኢንቨስትመንት መስኮች እየሠራች ላለው ተግባር የራሱ አስተዋጽዖ ይኖረዋል።

    የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የተደረገው ድጋፍ በታዳጊ ክልሎች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት፣ ጠንካራ የትምህርት አመራሮችን ለመፍጠርና ተጠያቂነትን ለማስፈን ይውላልም ብለዋል።

    እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ ቀሪው 66 ሚሊዮን ዩሮ ወይንም 2 ነጥብ 36 ቢሊዮን ብር ለመንግስት ኢንቨስትመንትና ለኢንዱስትሪ ፓርኮች ሙያዊ ድጋፍና የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመስጠት የሚውል ነው።

    የተፈረመው የድጋፍ ስምምነት የሁለቱን አገራት ጠንካራ ግንኙነት እንደሚያሳይ በመግለጽም ኢትዮጵያ በቀጣይ ለምታከናውነው ሁሉን አቀፍ ልማት እንግሊዝ ድጋፏን እንድትቀጥል ጠይቀዋል።

    ሚስስ ሃርየት ባልድዊን በበኩላቸው የኢትዮጵያን ፈጣን እድገት ለማሳካት እንግሊዝ በትብብር ትሰራለች ብለዋል።

    ሚስስ ሃርየት በትዊተር ገጻቸው ላይ እንዳሰፈሩት እንግሊዝ ለኢትዮጵያ ትምህርት ጥራት ያደረገችው ድጋፍ አንድ ሚልዮን የሚጠጉ ተማሪዎችንና 120,000 አስተማሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል።

    በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በኢኮኖሚው መስክ ለውጥ ለማምጣት የሚያደርጉት ጥረት እውን እንዲሆን ሙያዊና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ በጋራ እንደሚሠሩም ገልጸዋል።

    እንግሊዝ ዶ/ር አብይ አህመድ ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆኑ ጀምሮ በአፍሪካ ቀንድ በተለይም በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል የተፈጠረውን ሰላም ታደንቃለችም በማለት አክለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    እንግሊዝ ለኢትዮጵያ ድጋፍ አደረገች

    Semonegna
    Keymaster

    በፌዴራል ፖሊስ አባላት መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የሶስት ፖሊሶች ሕይወት ጠፋ ― የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን

    አዲስ አበባ (ኢዜአ) – ዛሬ [መስከረም 24 ቀን 2011 ዓም] ማለዳ በአዲስ አበባ ቦሌ ወሎ ሰፈር አካባቢ በፖሊስ አባላት መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የሶስት ፖሊሶች ሕይወት መጥፋቱን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ።

    ምክትል ጀኔራል ኮሚሽነር መላኩ ፋንታ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደገለጹት በፌዴራል ፖሊስ አባላቱ መካከል በተፈጠረው አለመግባባት አንድ አባል በያዘው መሳሪያ በከፈተው ተኩስ ሁለት ፖሊሶችን ገድሏል።

    ድርጊቱን የፈጸመውን አባል በቁጥጥር ስር ለማዋል ጥረት ተደርጎ ባለመሳካቱ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ለመከላከል ሲባልም እርምጃ ተወስዶበታል።

    ወንጀሉን ከፈጸመ በኋላ ወደፎቁ የላይኛው ክፍል በመውጣት ላይ ሳለ በቁጥጥር ስር ሊያውሉት ሲከታተሉት የነበሩትን ስድስት የስራ ባልደረቦቹን በመተኮስ አቁስሏቸዋል።

    ለጥበቃ በታጠቀው ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ተኩሱን እንደከፈተ የተረጋገጠው ይህ የፖሊስ አባል አለቆቹን ከገደለ በኋላ ተጨማሪ መሳሪያ ከባልደረቦቹ በመቀማት ሊይዙት በመጡት የጸጥታ ሃይሎች ላይ እስከ ማለዳ ደረስ ሲተኩስ ቆይቷል።

    አለመግባባቱ የተከሰተበት ስፍራ በርካታ ነዋሪዎች የሚገኙበት የመኖሪያ አፓርተማ በመሆኑ ፖሊስ በሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ማድረጉን ምክትል ጀኔራል ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።

    ”አባሉ በሥራ ቦታ ላይ መጥቶ ምድብ ቦታው ላይ ከነበሩ አባላት ጋር የሥራ ርክክብ ሲያደርጉ ግጭት ተፈጥሮ የከፋ ችግር እንዳያደርስ ምክር ቢሰጠውም መቀበል አልቻለም፤ በያዘው መሳሪያ የሥራ ጓዶቹ በሆኑ ሁለት ፖሊሶች ላይ የሞት አደጋ አድርሷል” ብለዋል።

    በተደረገው መከላከል የከፋ አደጋ ሳይደርስ አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድ መደረጉንና ፖሊስ በሲቪል ሰዎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ የመከላከል ሥራ መሥራቱንም አክለዋል።

    አባሉ ተደጋጋሚ የስነ-ምግባር ችግር ባይመዘገብበትም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሚደረግ የሥራ ግምገማ ሊያርማቸው የሚገቡ ጉዳዮችን እንዲያስተካክል ቢነገረውም ያልተቀበለው በመሆኑ የዛሬውን ችግር ሊፈጥር እንደቻለ ምክትል ጀኔራል ኮሚሽነር መላኩ ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እና ARTS TV

    የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር)– ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ የ20ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን እያከበረ ሲሆን ይህን ተከትሎም ኦርቢስ በራሪው የአይን ሆስፒታል በቦሌ ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ የስልጠና አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

    የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ከበደ ወርቁ በመክፈቻ ስነ ሥርዓቱ ላይ በመገኘት እንደተናገሩት ሀገሪቱ በአይን ህክምና ዙሪያ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች። ለነዚህ ሥራዎች መሳካትም በርካታ በአይን ህክምና ዙሪያ የሚሠሩ አጋር አካላት ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በትብብር እየሠሩ መሆናቸውን የተናገሩት ዶ/ር ከበደ ወርቁ በተለይም ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ሊታከም የሚችል አይነ-ስውርነትን አስቀድሞ በመከላከል ረገድ፣ የዘርፉን ባለሞያዎች በዕዉቀት እና በክህሎት በማብቃት፣ በአይን ህክምና ዙሪያ የሚሠሩ የትምህርት ተቋማትን አቅም በመገንባት፣ ለአይን የሚደረጉ ጥንቃቄዎችን አስመልክቶ ግንዛቤ በመፍጠር እንዲሁም በዘርፉ የሚደረጉ ጥናትና ምርምሮች ላይ በመሥራት እና የተለያዩ ግብአቶችን በማቀረብ ላለፉት ሀያ አመታት ከፍተኛ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው አመስግነዋል።

    በቀጣይም ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በአይን ህክምና ዙሪያ ለሚያከናውናቸው ስራዎች በትብብር እንደሚሰራ እና ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱም አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል። በዕለቱም ዶ/ር ከበደ ወርቁ በቦሌ ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ በመገኘት ኦርቢት በራሪውን የአይን ሆስፒታል ወይም የአውሮፕላን ውስጥ የአይን ሆስፒታል ጎብኝተዋል።

    ኦርቢስ ኢንተርናሽናል

    በኢትዮጵያ የኦርቢስ ዳይሬክተር ዶ/ር አለማየሁ ሲሳይ በበኩላቸው ስለበራሪው የአይን ሆስፒታል እንደተናገሩት ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህክምና ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር ለአምስተኛ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ የመጣ ሲሆን አውሮፕላኑ በረቂቅ ቴክኖሎጂ የበለጸገ የማስተማሪያ ተቋም በመሆን ያገለግላል።

    በዚህም ለዶክተሮች፣ ለነርሶች እና ለህክምና ቴክኒሺያኖች ስልጠና ከመስጠት በተጨማሪ ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በመተባበር የአይን ህክምና ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲደርስ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። በራሪው የአይን ሆስፒታል በውስጡ እጅግ ዘመናዊ የቀዶ ጥገና፣ የመማሪያና የማገገሚያ ክፍሎች ያሉት እንደሆነ የተናገሩት ዳይሬክተሩ፥ የበጎ ፈቃደኛ ሀኪሞች ስልጠናን በአውሮፕላን ወስጥ እና በአካባቢው ከሚገኙ ሆስፒታሎች ጋር በመተባበር ይሰጣልም ብለዋል።

    በራሪው የአይን ሆስፒታል ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ ከከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህክምና ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር ለአምስተኛ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣም ገልጸዋል። ለሚቀጥሉት 15 ቀናትም በራሪው ሆስፒታል በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚቆይ ለማወቅ ተችሏል።

    ኦርቢስ ኢንተርናሽናል መንግስታዊ ያልሆነና የበጎ አድራጊ ዓለማቀፋዊ ድርጅት ሲሆን ዋነኛ ተግባሩም ዓይነ ስውርነትን መከላከልና የዓይን ህክምናን መስጠት ነው። ኦርቢስ ኢንተርናሽናል እ.ኤ.አ በ1960ዎቹ አሜሪካዊ የዓይን ህክምና ባለሙያ ዶ/ር ዴቪድ ፓተን (Dr. David Paton) ጽንሰ ሀሳቡን ጀምሮት በድርጅት ደረጃ የተቋቋመው  ደግሞ እ.ኤ.አ በ1982 ዓ.ም ሲሆን ዋና መቀመጫውን ኒው ዮርክ ከተማ (ኒው ዮርክ፣ አሜሪካ) አድርጎ ከ90 በላይ ሀገራት ይሠራል።

    ምንጭ፦ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኢ.ም.ባ.ኮ)– የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን በአፍሪካ (ኢ.ም.ባ.ኮ) ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ የባቡር አካዳሚ በቢሾፍቱ ከተማ ለመገንባት በርካታ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እያከናወነ መሆኑን የኮርፖሬሽኑ ባቡር አካዳሚ ዘርፍ ም/ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አብይ ጌታቸው ገለፁ።

    ለባቡር አካዳሚው ግንባታ የቻይና መንግስት ሳውዝዌስት ጂአኦቶንግ ዩኒቨርሲቲ (Southwest Jiaotong University) ባካሄደው አማካሪ የአዋጭነት ጥናት መነሻነት የገንዘብ ድጋፍ የፈቀደ መሆኑን የገለፁት አቶ አብይ በተጠናው የአዋጭነት ጥናትና በኮርፖሬሽኑ ፍላጎት መሠረት የትግበራ ስምምነት (Implementation Agreement) እ.ኤ.አ ታህሳስ 19 ቀን 2017 ከቻይና ኤምባሲ የንግድና ኢኮኖሚክ ካውንስለር ቢሮ፤ እንዲሁም የግንባታ ዲዛይን መነሻ ሃሳብ (Scheme design) ጥር 6 ቀን 2018 እ.ኤ.አ ከአማካሪ ድርጅቱ ጋር መፈራረማቸውን ተናግረዋል።

    በግንባታው የዲዛይን መነሻ ሃሳብ መሰረትም የግንባታው የመጀመሪያ ዲዛይን (Preliminary Design) ተዘጋጅቶ በአሁኑ ወቅት በቻይና መንግስት በኩል ግንባታውን የሚያከናውን የኮንትራክተር መረጣ ሂደት ላይ መሆኑንና እስከ ቀጣይ ህዳር ወር ድረስ ኮንትራክተሩ ተለይቶ ግንባታው ከታህሳስ አጋማሽ እስከ ጥር ወር መጀመሪያ ባለው ጊዜ ሊጀመር እንደሚችልም አቶ ዓቢይ ገልፀዋል።

    ግንባታውን ተቆጣጥሮ በጥራት ከመረከብ በተጨማሪ ግንባታው የሚከናወንበትን ቦታ ማዘጋጀት ከኮርፖሬሽኑ ሃላፊነቶች አንዱ ሲሆን ለአካዳሚው ግንባታ ማስፋፊያውን ጨምሮ ከሚያስፈልገው 157.7 ሄክታር መሬት ውስጥ የ62 ሄክታር መሬት ከኦሮሚያ ክልል የከተማ ልማትና ቤቶች ቢሮ እና ከከተማ መሬት ማኔጅመንት ኤጀንሲ ጋር በመነጋገር ከክልሉ መንግስት ህጋዊ ፈቃድ ለማግኘት በሂደት ላይ መሆኑን የገለፁት አቶ ዓቢይ የመሬት ፈቃዱ እንደተገኘ ዲዛይኑ ቀርቦ ግንባታው እንደሚጀመር፤ በተጨማሪም የግንባታ ግብዓቶችን ማምረቻ ሳይቶች ለኮንትራክተሩ ማቅረብ፣ የተለያዩ መሠረተ ልማቶችን (ውሃ፣ መብራት…) ወደ ሳይቱ ማቅረብ የኮርፖሬሽኑ ኃላፊነት መሆኑንና ይህን ተግባር የሚያከናውን ፕሮጀክት ጽ/ቤት ተቋቁሞ በእንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን

    ከግንባታው ጋር ተያይዞ ከሥራ ቦታቸው ለሚፈናቀሉ የአካባቢው ማህበረሰበም በካሳ ክፍያ ብቻ የሚተው ሳይሆን በጋራ የሚሠሩ ሥራዎችን በማቅረብ፣ ቴክኒካል ድጋፍ በመስጠትና የበለጠ ተጠቃሚ መሆን የሚችሉበት ፕሮፖዛል በማቅረብ ከክልሉ ከተማ ልማትና ቤቶች ቢሮ ጋር በመሆን ህብረተሰቡን ያማከለ የተቀናጀ ልማት ፕሮፖዛል ቀርቧል ያሉት አቶ አቢይ የመሬት ፈቃዱ እንደተገኘ ወደ ሥራ እንገባለን ብለዋል።

    ኮርፖሬሽኑ በአካዳሚ ዘርፍ የባቡር አካዳሚ ከማስገንባት ባለፈም የባቡር ዘርፉ የሚፈልገውን የሰው ኃይል ለማብቃት የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት ባለሙያዎችን በተለያዩ የትምህርት መስኮች በሃገር ውስጥና በውጭ እያሰለጠ ይገኛል።

    በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመሆን ከ1ኛ እስከ 4ኛ ዙር ከ400 በላይ የሚሆኑ ባለሙያዎችን በማስተርስ ፕሮግራም ያስተማረ ሲሆን የ1ኛ ዙር ተመራቂዎች ሁሉም በኮርፖሬሽኑ በስራ ላይ እንደሚገኙ የገለፁት አቶ አብይ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ዙር የተማሩት ደግሞ ኮርፖሬሽኑ በቀጣይ የሀገራዊ ሴክተሩን አቅም በመገንባት ለሚያከናውነው የራስ ኃይል ሥራዎች በመደራጀት ላይ በሚገኙ ቢዝነስ ዩኒቶች ስር ለስድስት ወር በሥራ ላይ ስልጠና በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ ስልጠናቸውን እንዳጠናቀቁ ወደ ሥራ የሚገቡ መሆናቸውን ገልፀዋል።

    ምንጭ፦ ኢ.ም.ባ.ኮ

    Semonegna
    Keymaster

    በ2010 ዓ.ም ወደ ከፍትኛ ትምህርት ተቋማት የሚገቡ 280 ኤርትራውያን ስደተኞች የመግቢያ ፈተና እንዲወስዱ መደረጉንና በአሁኑ ወቅት ፈተናውን ያለፉ 150 ተማሪዎች መለየታቸውን አስረድተዋል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ/UNHCR)፦ በኢትዮጵያ በስደት ላይ ከሚኖሩ ኤርትራውያን መካከል 150 ተማሪዎች በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ገብተው የመማር ዕድል እንደሚያገኙ በኢትዮጵያ የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር አስታወቀ።

    በተያዘው ዓመት ሌሎች ቁጥራቸው ከ11ሺህ በላይ የሆኑ ህጻናት (የስደተኛ ኤርትራውያን ልጆች የሆኑ) የቅድመ መደበኛ ትምህርት ዕድል ማግኘታቸውም ተመልክቷል።

    በኢትዮጵያ የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ አስተዳደር (Ethiopia Administration for Refugee and Returnee Affairs/ ARRA) የሰሜን ጽህፈት ቤት የትምህርት ኦፊሰር አቶ ኤፍሬም ሀጎስ ለኢዜአ እንደገለጹት ከ180 ሺህ የሚበልጡ ኤርትራውያን ስደተኞች በተለያዩ መጠለያ ጣቢያዎች ይገኛሉ፡፡

    የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ ኤርትራውያን ስደተኞች መካከል 150 ተማሪዎች ዘንድሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በነጻ ለመማር እድል እንደሚሰጣቸውም ተናግረዋል።

    ወደ ከፍትኛ ትምህርት ተቋማት የሚገቡ 280 ስደተኞች የመግቢያ ፈተና እንዲወስዱ መደረጉንና በአሁኑ ወቅት ፈተናውን ያለፉ 150 ተማሪዎች መለየታቸውን አስረድተዋል።

    ፈተናውን ያለፉ 150 ስደተኞችም በተለያዩ የኢትዮጵያ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እንደሚከታተሉም ነው አቶ ኤፍሬም የገለጹት።

    ኤርትራውያን ስደተኛ ተማሪዎች በኢትዮጵያ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ መደረጉ በሁለቱ አገራት መካከል አሁን የተጀመረውን ሰላማዊ ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክረውም ተናግረዋል።

    ◌ ቪድዮ፦ ኢትዮጵያ የቀይ ባህር እና የምጽዋ ወደቦችን ለመጠቀም ቅድመ ዝግጅቶችን እያጠናቀቀች ነው

    የኢትዮጵያ መንግስት ለኤርትራውያን ስደተኞች የትምህርት ዕድል ሲሰጥ የአሁኑ ለሰባተኛ ጊዜ ሲሆን በየዓመቱ ከ100 ያላነሱ ተማሪዎችም የዕድሉ ተጠቃሚ ሆነዋል።

    በተመሳሳይ በትግራይ ክልል በሚገኙ አራት የኤርትራውያን ስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ 11ሺህ 87 ኤርትራውያን በቅድመና በመደባኛ ትምህርት እንዲሁም በሙያ ክህሎት ማበልጸጊያ እንዲማሩ መደረጉን አቶ ኤፍሬም አክለው ተናግረዋል።

    በተለያዩ ምክንያቶች ከአገራቸው ተሰደው ወደኢትዮጵያ ቢመጡም ልጆቻው እዚህ የትምህርት ዕድል በማግኘታቸው መደበኛ ትምህርታቸውን መቀጠላቸውን የተናገሩት ደግሞ በማይዓይኒ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙት አቶ ተስፋልደት ይህደጎ የተባሉ ስደተኛ ናቸው።

    በአዲ ሓሩሽ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ሌላው ስደተኛዋ ወይዘሮ ለምለም ዘካሪያስ እንደተናገሩት በአካባቢያችን የሚገኙ ትምህርትቤቶች ለኤርትራውያን ተማሪዎች በራቸው ክፍት መሆኑ ትልቅ እድል መሆኑን ገልጸዋል።

    “ልጆቻቸው ከኢትዮጵያውያን ወንደሞቻቸው ጋር በአንድ ክፍል ውስጥ እንዲማሩ መደረጉ በሁለቱ አገራት ህዝቦች መካከል ጠንካራ ግንኙነት ለመፍጠር ለሚደረገው ጥረት የላቀ አስተዋፅኦ አለው” ብለዋል።

    የኢትዮጵያ መንግስት ለኤርትራውያን ስደተኞች እየሰጠ ያለው የከፍተኛ የትምህርት እድል ለሌሎች አገራት በመልካም አርአያነት የሚጠቀስ መሆኑን የገለጸው ደግሞ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለማግባት የመግቢያ ፈተና የወሰደው ተማሪ ዓንዶም ፍሳሃየ ነው።

    እስከ ግንቦት ወር 2010 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በአጠቃላይ 71,833 ኤርትራውያን ስደተኞች ትግራይ ክልል ውስጥ በሚገኙ አራት መጠለያ ጣብያዎችና አፋር ክልል ውስጥ በሚገኙ ሁለት መጠለያ ጣብያዎች ውስጥ እንደሚገኙ የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች መርጃ ድርጅት (UNHCR) ዘግቧል።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እና የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች መርጃ ድርጅት (UNHCR)

    ኤርትራውያን

    Semonegna
    Keymaster

    የጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ መርክል ባደረጉላቸው ግብዣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር አብይ አህመድ በጥቅምት ወር ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ጀርመን የሚያቀኑ ሲሆን፥ በአውሮፓ የሚገኙ ኢትዮጵያዊንን አግኝተው ያነጋግራሉ ተብሏል።

    አዲስ አበባ (የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር አብይ አህመድ በጥቅምት ወር ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ጀርማን የሚያቀኑ ሲሆን፥ በዚሁ ጉብኝታቸውም ከጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ መርክል (Angela Merkel) እና ሌሎች የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በጀርመን ዋና ከተማ በርሊን እንደሚገናኙም ነው የተገለጸው።

    የጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ መርክል በፈረንጆቹ ነሃሴ ወር በኢትዮጵያ እየመጣ ያለውን ለውጥ በመደገፍ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ጎን መሆናቸውን በስልክ በገለጹበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጀርመን ይፋዊ ጉብኝት እንዲያደረጉ መጋበዛቸውም ታውቋል።

    በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር አብይ አህመድ በጥቅምት ወር መጨረሻ ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ጀርመን የሚያቀኑ ሲሆን፥ በአውሮፓ የሚገኙ ኢትዮጵያዊንን አግኝተው ያነጋግራሉ ተብሏል።

    በፈረንሳይ ፓሪስ፣ ጀርመን ፍራንክፈርት ከተሞችም በሚዘገጁ መድረኮችም ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር አብይ ከኢትዮጵያዊያኑ ጋር እንደሚገናኙ የተገለጸው።

    ሀገራዊ ዜና፦ አብይ አህመድ (ዶ/ር) እና ደመቀ መኮንን በድጋሚ የኢህአዴግ ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ

    በፈረንጆቹ ጥቅምት 31 ቀን 2011 (ጥቅምት 21 ቀን 2011 ዓም) ዓም በጀርመን ሁለተኘዋ ከተማ ፍራንክፈርት ላይ መድርክ እንደሚዘጋጅ እና ጠቅላይ ሚኒትሩ በአውሮፓ የሚገኙ ኢትዮጵያዊንን አግኝተው እንደሚያነጋግሩም ታውቋል።

    ለዚሁ ፕሮግራምና የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አቀባበልን እስመልክቶ ከ80 ማህበራት የተውጣጡ አበላት ያሉት ኮሚቴ አየሰራ መሆኑንም ነው የተገለጸው።

    በጀርመን የኢትዮጵያ ቆንሰላ ጄኔራል ምህረት አብ ሙሉጌታ እንደገለጹት አሁን ላይ በኢትዮጵያ እየታየ ያለውን ለውጥ በመደገፍ 25 ሺህ ያህል ኢትዮጵያን ፍርንክፈረት ኮመርዝባክ አረና ስታዲየም (Commerzbank-Arena) በሚዘጃጀው ፕሮግራም ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

    ምንጭ፦ የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት

    ጀርመን

    Semonegna
    Keymaster

    በሺዎች የሚቆጠሩ ግለሰቦች አዲስ አበባ ላይ መታሰራቸው በተለይም ከሺሻ ቤቶችና ጫት ቤቶች መወሰዳቸው ጋር ተያይዞ ሺሻ ህገ-ወጥ ነው? ከሆነስ ግለሰቦቹ ወደ ፍርድ ቤት ለምን አልቀረቡም? ወደ ተሐድሶ ካምፕ ለምንድን ነው? የሚላኩት የሚሉ ክርክሮች መነሳት ጀምረዋል።

    አዲስ አበባ (ቢቢሲ አማርኛ)– ሰሞኑን በአዲስ አበባ በተከሰተው ቀውስ የሟቾች ቁጥር 28 መድረሱን ፖሊስ ገልጿል። ቀውሱንም ተከትሎ በአዲስ አበባ የተለያዩ መጠጥ ቤቶችን ጨምሮ የመዝናኛ ቦታዎች ወደ ሦስት ሺ ሁለት መቶ የሚሆኑ ሰዎች በጅምላ እንደታሰሩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት አምነስቲ አስታውቋል።

    ፖሊስ በበኩሉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልፆው መቶ ሰባ አራት ለፍርድ እንደሚቀርቡ እንዲሁም አንድ ሺ ሁለት መቶ አራት ሰዎችን ለማነፅና ለማስተማር በሚል ወደ ጦላይ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፕ ለተሐድሶ ስልጠና ተልከዋል።

    የአዲስ አበባ ፖሊስ ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር የሞከሩትን እንዳሰረ ቢገልፅም አምነስቲ (Amnesty International) በበኩሉ እስሩን አውግዞ በአሁኑ ሰዓት እየታዩ ያሉ ለውጦችን ወደ ኋላ የሚጎትት ነው ብሏል።

    በሺዎች የሚቆጠሩ ግለሰቦች አዲስ አበባ ላይ መታሰራቸው በተለይም ከሺሻ ቤቶችና ጫት ቤቶች መወሰዳቸው ጋር ተያይዞ ሺሻ ህገ-ወጥ ነው? ከሆነስ ግለሰቦቹ ወደ ፍርድ ቤት ለምን አልቀረቡም? ወደ ተሐድሶ ካምፕ ለምንድን ነው? የሚላኩት የሚሉ ክርክሮች መነሳት ጀምረዋል።

    ደኅንነታቸውና ያልተረጋገጠ የስፈተ ወሲብና ጸጉርን ለማሳድግ የሚረዱ እና የከንሰር መድኃኒቶች በህገወጥ መንገድ ሊገቡ ሲሉ ተያዙ

    የኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድሃኒት እና የጤና ክብካቤ አስተዳደር ባለስልጣን የትምባሆ ቁጥጥር መመሪያ መጋቢት ወር 2007 ዓ.ም ያወጣ ሲሆን፤ በመመሪያውም መሰረት የትምባሆ ምርቶች በማለት የሚዘረዝራቸው በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ከትምባሆ ቅጠል የተዘጋጁ በማጨስ፣ በመሳብ፣ በማኘክ፣ በማሽተት ወይም በሌላ መንገድ የሚወሰድ ማንኛውም ንጥረ ነገር ሆኖ የጋያ ወይም የሺሻ ትምባሆን፣ የኤሌክትሮኒክ ኒኮቲን ይጨምራል።

    የመመሪያው ዓላማም በዝርዝር የተቀመጠ ሲሆን ትምባሆን በመጠቀምና ለትምባሆ ጢስ በመጋለጥ በማህበረሰቡ ላይ የሚደርሰውን የጤና፣ የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና አካባቢያዊ ጉዳቶችን ለመከላከልና ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የፈረመማቻቸውን የትምባሆ ቁጥጥር ኮንቬንሽንም ለማስፈፀም ነው።

    መመሪያው ከባለስልጣኑ ፈቃድ ሳያገኝ የትምባሆ ምርትን ለንግድ ተግባር ወደ ሃገር ውስጥ ማስገባት፣ ማከፋፈል ወይም በጅምላ መሸጥ እንደማይቻል ያስቀመጠ ሲሆን፤ የትምባሆ ምርትን ማስተዋወቅና ስፖንሰር ማድረግ በፍፁም የተከለከለ እንደሆነ በግልፅ አስቀምጧል።

    በዚህም መሰረት ማጨስ የተከለከለባቸው ቦታዎች ተብለው የተቀመጡት፤ በህዝብ መጓጓዣዎች፣ በጤናና በትምህርት ተቋማት፣ በምግብ ቤቶች፣ በመዝናኛ ቦታዎች፣ በአውሮፕላን ማረፊያ፣ በፋብሪካዎችና በህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሾች ናቸው።

    ምንም እንኳን በነዚህ ቦታዎች ቢከለከልም ከትምህርት ተቋማት፣ ከመንግሥት መስሪያ ቤትና ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት አገልግሎት ከሚሰጡ ተቋማት ውጭ ለማጨስ የተከለለ ወይም የተሰየመ ክፍል ለብቻው የአየር ማናፈሻ (ventilation) የተገጠመለት ከሆነ በሌሎቹ ቦታዎች ማጨስ እንደሚቻል ተቀምጧል።

    በዩኒቨርስቲ፣ በኮሌጅና በሌሎች ተቋማት የተከለለ ክፍል ካለ ትምባሆንም ሆነ የትምባሆን ምርት መገልገል እንደሚቻልም መመሪያው ያትታል።

    ማንበብዎን ይቀጥሉ፦ በኢትዮጵያ ህግ ሺሻ ማጨስ ህገ- ወጥ ነውን?

    ሺሻ


    Semonegna
    Keymaster

    በኦሮሚያ ውስጥ ከፍተኛ ተቃውሞን ቀስቅሶ የነበረው አዲስ አበባን በዙሪያዋ ካሉ የኦሮሚያ ከተሞች ጋር ያስተሳስራል የተባለው ማስተር ፕላን ተራማጅና አንድ ቀን ተመልሶ ይመጣል ብለው እንደሚያስቡ ኦህዴድ ሊቀ መንበር እና የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ኩማ ደመቅሳ ለቢቢሲ ተናገሩ።

    ባለፈው ሳምንት ኦዴፓ (የቀድሞው ኦህዴድ) በጅማ ከተማ ድርጅታዊ ጉባኤውን ባደረገበት ወቅት ተሳታፊ የነበሩት አቶ ኩማ ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት አጭር ቆይታ አወዛጋቢ ስለነበሩና እርሳቸው በከፍተኛ የስልጣን ሃላፊነት ላይ በነበሩበት ጊዜ ስለታቀዱና ተግባራዊ ስለተደረጉ ጉዳዮች ምላሽ ሰጥተዋል።

    «ኦሮሞ እና አማራን የሚነጣጥሉ አይሳካላቸውም»

    በተለይ በኦሮሚያ ውስጥ ተቀስቅሶ ለረጅም ጊዜ ለዘለቀው ሕዝባዊ ተቃውሞ መነሻ ምክንያት እንደሆነ የሚነገርለትና ከ2006 ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ የነበረው የአዲስ አበባና በዙሪያዋ ያሉ የኦሮሚያ ከተሞች የተቀናጀ ማስተር ፕላንን በተመለከተ የተሳሳተ አመለካከት እንዳለ ተናግረዋል።

    ጉዳዩ ከመፈናቀል ጋር አብሮ ስለመጣ እንጂ «ተራማጅ አስተሳሰብ ነው ብዬ አስባለሁ» በማለት የሚናገሩት አቶ ኩማ፤ ጊዜ ሊወስድ ይችላል እንጂ ማስተር ፕላኑ አንድ ቀን ተመልሶ ይመጣል ብለው እንደሚያስቡ ገልፀዋል።

    ከዚህ በተጨማሪም በተመሳሳይ ኦሮሚያ ውስጥ ለጠንካራ ጥያቄና ተቃውሞ ምክያት የነበረው የአዳማ ከተማን የኦሮሚያ ክልል መዲና እንድትሆንና የክልሉ መስሪያ ቤቶች ወደዚያው እንዲዘዋወሩ መደረጋቸው ይጠቀሳል።

    ስለዚህ ጉዳይ የተጠየቁት አቶ ኩማ ውሳኔው ስህተት እነደሌለበት ያምናሉ። አሁንም ወደኋላ መለስ ብለው ሲመለከቱ «አሁንም ያኔ የነበረኝ አቋም ስህተት ነው ብዬ አላምንም» ካሉ በኋላ፤ «አዳማ የክልሉ ዋና ከተማ ሆና እንደተቀየረች ብትዘልቅ ኖሮ ከተማዋ ታድግ እንደነበር» ሲሉ ገልጸዋል።

    ማንበብዎን ይቀጥሉ፦ «ማስተር ፕላኑ ተመልሶ ይመጣል» አቶ ኩማ ደመቅሳ

Viewing 15 results - 481 through 495 (of 495 total)