Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 15 results - 301 through 315 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የዓረብ ሊግ በሕዳሴው ግድብ ላይ ያቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ቁልፍ ጉዳዮችን ሳያገናዝብ ለአንድ ወገን ያደላ ነው ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት አወገዘ።

    የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ ባወጣው መግለጫ፥ የዓረብ ሊግ የሕግ አስፈፃሚ ምክር ቤት የካቲት 26 ቀን 2012 ዓ.ም. የሕዳሴውን ግድብ በተመለከተ የደረሰበት ውሳኔ የሚያሳዝን ሆኖ ያገኘው መሆኑን እና ኢትዮጵያ ውሳኔውን በፍጹም የማትቀበለው መሆኑን ገልጿል።

    ኢትዮጵያ የሱዳን መንግሥት በዓረብ ሊግ ለቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ድጋፍ ላለመስጠት የወሰደውን አቋም እንደምታደንቅ በመግለጫው ተጠቅሷል።

    ሱዳን የተቀነባበረውን እና የዓረብ ሊግን አቋም ባለመደገፍ የምክንያታዊነት እና የፍትሕ ድምፅ መሆኗን ዳግመኛ ማረጋገጧን በመጥቀስ፣ ኢትዮጵያ በመርህ ላይ ለተመሠረተው እና የሁሉም ወገን አሸናፊነትን መሠረት ላደረገው የሱዳን አቋም ወደር የለሽ አድናቆቷን ገልጻለች።

    ኢትዮጵያ ከዓረብ ሊግ ሀገራት ሕዝቦች እና መንግሥታት ጋር በጋራ እሴት፣ ባሕል እና ልማድ ላይ የተመሠረተ ለረጅም ጊዜ የዘለቀ ግንኙነት እንዳላት በመግለጫው ተጠቁሟል።

    የዓረብ ሊግ የተለያዩ ሉዓላዊ ሀገራትን ያቀፈ ተቋም እንደመሆኑ መጠን የሁሉንም ወገን ፍላጎት ያካተተ እና ሚዛናዊ መስመር መያዝ እንደሚጠበቅበት በመግለጫው ተጠቅሷል።

    ከዚህ መስመር በተቃረነ መልኩ የሚሠራ ከሆነ ግን የሊጉ ተዓማኒነት እና በዚህ እጅጉን በተሳሰረ ዓለም ውስጥ ሰላምን፣ መረጋጋትን እና ትብብርን ለማምጣት ያለው አቅም ጥያቄ ውስጥ የሚገባ እንደሚሆን ተገልጿል።

    በተለያዩ ጊዜያት ስትገልጽ እንደነበረው ሁሉ ኢትዮጵያ አሁንም ቢሆን “የአሁኑን እና የመጪውን ትውልድ ፍላጎት ለማሟላት የዓባይን ውኃ ሃብት የመጠቀም መብት አለኝ” የሚለውን የዘለቀ እና የማይናወጥ አቋም በድጋሚ ገልጻለች።

    የዓባይ ወንዝ ድንበር ተሻጋሪ እንደመሆኑም ኢትዮጵያ በሌሎች ላይ ጉልህ ተፅዕኖ ሳይደርስ ውኃውን በፍትሐዊ እና ምክንያታዊ መንገድ የመጠቀም መርህን ተከትላ እንደምትሠራ ተገልጿል።

    በተጨማሪም ኢትዮጵያ በሕዳሴ ግድብ የውሃ አሞላል እና አሠራር ላይ መሠረታዊ መፍትሔ የሚሰጠውን የመርሆዎች መግለጫ ስምምነትን ተከትላ እንደምትሠራም ማረጋገጧ ተገልጿል።

    የዓረብ ሊግ እውነተኛውን መንገድ ተከትሎ እና ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የዘለቀ እና የጋራ እሴቶች ላይ የተመሠረተውን ግንኙነት መሠረት በማድረግ እንደሚሠራ ኢትዮጵያ እንደምትተማመን በመግለጫው ተጠቅሷል።

    ወዳጅነትን ማጠናከር እና ለጋራ ግቦች ተቀራርቦ መሥራት የኢትዮጵያ ፍላጎት መሆኑም ነው የተገለጸው።

      • የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ ያወጣውን መግለጫ (እንግሊዝኛ) ለማንበብ እዚህ ጋር ይጫኑ።

    ምንጭ:- የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)/ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 

    Ethiopia rejects Arab League resolution on GERD የዓረብ ሊግ

    Anonymous
    Inactive

    አቶ አቤ ሳኖ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – አቶ አቤ ሳኖ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ። አቶ አቤ ከየካቲት 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ነው ባንኩን በፕሬዚዳንትነት እንዲመሩ የተመደቡት።

    የካቲት 26 ቀንም ከቀድሞ የባንኩ ፕሬዝዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ባጫ ጊና እና ከሌሎች የባንኩ የሥራ አመራር አባላት ጋር ትውውቅና የሥራ ርክክብ አድርገዋል። በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ወቅት አቶ ባጫ ጊና በኃላፊነት ቆይታቸው የሥራ አመራሮችና ሠራተኞች ላደረጉላቸው እገዛና ትብብር ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፥ ከአዲሱ ሥራ አስፈጻሚ ጋርም በትጋትና በትብብር በመሥራት ለተሻለ ውጤት እንዲሠሩም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

    አዲስ የተሾሙት የባንኩ ፕሬዝዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቤ ሳኖ በበኩላቸው ከልጅነታቸው ጀምሮ ሥራ የጀመሩበትና በወጣት እድሜያቸው በኃላፊነት መምራት ወደቻሉበት ባንክ መምጣታቸው የሚጠበቅባቸውን ለማበርከት እንደሆነ ገልፀዋል። አቶ አቤ ሳኖ ከዚህ በፊት ከሁለት ዓመታት ከፍ ላለ ጊዜ ያህል (ከጥር ወር 1998 ዓም እስከ ኅዳር ወር 2001 ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በፕሬዝዳንትት ማገልገላቸው ይታወሳል። የዚያን ጊዜ የአንጋፋው ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲሾሙ የ30 ዓመት ወጣት ነበሩ። ይህም ሁኔታም የሥራ ልምዳቸውን ጥያቄ ውስጥ በማስገባት በዘርፉ በተሰማሩ ብዙ ግለሰቦች ዘንድ ጥርጣሬንና አግራሞትን ፈጥሮ ነበር።

    አቶ አቤ አክለውም በድጋሚ ኃላፊነቱን ተረክበው እንዲሠሩ ምክንያት የሆናቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞችን ከልብ መውደዳቸውና ሠራተኛው ለእርሳቸው የነበረው አክብሮትና ፍቅር እንደሆነ ገልፀዋል። ባንኩ ለሀገር የሚያበረክተውን አስተዋፅኦ ከፍ ለማድረግ ከአመራሩና ሠራተኛው ጋር በመሆን የአቅማቸውን እንደሚወጡም አስታውቀዋል።

    ከሐምሌ 2010 ዓ.ም. ጀምሮ የባንኩ ፕሬዝዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት አቶ ባጫ ጊና ሀገራቸውን በዲፕሎማሲው ዘርፍ ለማገልገል ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው መሾማቸውን ተከትሎ ነው አቶ አቤ ሳኖ ባንኩን እንዲመሩ በኃላፊነት የተመደቡት።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    —–
    ሌሎች ዜናዎች፦

    አቶ አቤ ሳኖ Abe Sano

    Semonegna
    Keymaster

    አቢሲንያ ባንክ በታላቁ የንግድ ሰው በሞላ ማሩ ስም ቅርንጫፍ ከፈተ፤ የባንኩ አሚን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ለሁለተኛ ጊዜ ዓለም አቀፍ ሽልማት አግኝቷል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– ቅርንጫፎቹን በሀገር ባለውለታዎች ስም እየሰየመ የሚከፍተው አቢሲንያ ባንክ አሁን ደግሞ (በየካቲት ወር 2012 ዓም) በሀገራችን ስመ-ጥር የንግድ ሰው በሆኑት ሞላ ማሩ ስም አዲስ አበባ ውስጥ ከአብነት ወደ ተክለኃይማኖት በሚወስደው መንገድ ሞላ ማሩ አካባቢ <አቢሲንያ ባንክ ሞላ ማሩ ቅርንጫፍ> ከፍቶ ሙሉ የባንክ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

    ቀኛዝማች ሞላ ማሩ ከአባታቸው ከአቶ ማሩ ዶሬ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ዳዊቴ ሁሉቃ፥ በክስታኔ ጉራጌ፣ ዋጮ ፉሌ ቀበሌ፣ በመጋቢት ወር 1918 ዓ.ም. ተወለዱ። ከሊስትሮነት፣ ከጎዳና ንግድ፣ ከአልባሳት ሽያጭ የሥራ ዘርፍ ጀምሮ እስከ ቡና ንግድ፣ ለስላሳ መጠጦች፣ ዘይትና አረቂ ፋብሪካ ማቋቋም ድረስ የዘለቀ የንግድ ሥራ ታሪክ ባለቤት ናቸው። በተጨማሪም ቀኛዝማች ሞላ ማሩ በሆቴል ሥራ፣ በብሎኬት ፋብሪካ ሥራ፣ በእርሻ ሥራ፣ በድንጋይ መፍለጫ ካባ ሥራ እና ሌሎች በርካታ የሥራ ዘርፎች ውስጥ በመሳተፍ ከፍተኛ አበርክቶ ነበራቸው። በአጠቃላይ ቀኛዝማች ሞላ ማሩ በበርካታ የሥራ ዘርፎች ላይ በመሠማራት፤ የሥራ ፈጠራን (entrepreneurship) ወርድና ቁመት በዕውን ያሳዩ የሀገር ባለውለታ ናቸው።

    በንግድና ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያከናወኗቸው ተግባራት ከራሳቸው ባለፈ ለሀገርና ሕዝብ ጠቃሚ መሆናቸውን ያመነበት የቀዳማዊ ንጉሥ ኃይለሥላሴ መንግሥት፣ በ1964 ዓ.ም. የቀኛዝማችነት ማዕረግ ሰጥቷቸዋል።

    ባለትዳርና የ6 ልጆች አባት የነበሩት ቀኛዝማች ሞላ ማሩ በ1972 ዓ.ም፣ በ54 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ቢለዩም አርአያነታቸው በርካቶችን እያነሣሣ ለትውልድ ይቀጥላል።

    ‘ቅርንጫፎቹን በሀገር ባለውለታዎች ስም እየሰየም ለትውልድ የሚዘክረው አቢሲንያ ባንክ በእኚህ የሀገር ባለውለታ ስም ቅርንጫፉን በመሰየሙ ከፍተኛ ደስታና ክብር ይሰማዋል’ – ይላል ባንኩ የሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ።

    ከአቢሲንያ ባንክ ዘገባ ሳንወጣ፥ ባንኩ አሚን (Ameen) በተሰኘው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎቱ ለሁለተኛ ጊዜ ዓለም አቀፍ ሽልማት አግኝቷል። ሽልማቱ መቀመጫውን ዱባይ ባደረገው አልሁዳ ኢስላሚክ ባንኪንግና ኢኮኖሚክስ (AlHuda Centre of Islamic Banking and Economics) በመባል የሚታወቀው ማዕከል ባዘጋጀው 2ተኛው “የአፍሪካ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎትና ታክፉል ሽልማት 2020” (African Interest-Free Banking and Takaful Awards 2020) ፎረም ላይ ተበርክቷል። ሽልማቱ አቢሲንያ ባንክን “በወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎትና ፋይናንስ” የላቀ የገበያ አበርክቶ ተሸላሚ ሲያደርገው፥ የባንኩን አሚን ማዕከል ዳይሬክተር አቶ አብዱልቃድር ሬድዋንን “በወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት አንጸባራቂ ሰብዕና እየገነባ የመጣ” በሚል የ2020 ተሸላሚ አድርጓል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አቢሲንያ ባንክ

    Anonymous
    Inactive

    የአድዋ ድል በዓል ― እኛ አንድ እንጂ 80 ኢትዮጵያ የለችንም!
    አቶ ኦባንግ ሜቶ
    ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ሊቀመንበር መሥራችና ፕሬዝደንት

    እንኳን ለ124ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ ስለድል ስናወራ ጀግንነት እና አሸናፊነት ሰውነታችንን ይወረዋል፤ ግን ጀግንነት የቱ ነው? አሸናፊነትስ ምንድን ነው?

    ትናንት አባቶቻችን የጠላትን ጦር አሸንፈዋል፤ እኛ ግን ዛሬ እራሳችንን ማሸነፍ አቅቶናል። ለሰላም አልተሸነፍንም፤ ለፍቅር እጅ አልሰጠንም፤ ታዲያ ከአበቶቻችን ተረክበን ያስቀጠልነው ጀግንነት የቱ ነው? የኛ ዘመን ድል የቱ ጋር ነው ያለው?

    ሁላችንም የአድዋ ድልን ስናስብ እና አክብረነውም ስንውል ታሪክ ነጋሪ ብቻ ሳንሆን ታሪክን በአሸናፊነት ደጋሚ፥ ብሎም አዲስን ታሪክ ሠሪ መሆን አለብን እንጂ ታሪክን የኋሊት የምናስኬድና ጀግኖች አባቶቻችን ከጠላት ኃይል ጋር ተናንቀውና ሕይወታቸውን ሰውተው ዛሬ ድል አያልን በኩራት የምናከብረውን ነፃነትና በብዙ ተጋድሎ ያስረከቡንን ሀገር አኛ እርስ በእርሳችን ተገዳድለን፣ በዘር መከፋፈል ግጭት ተላልቀን መጨረሻው ያላማረ ከንቱ ትውልድ መሆን የለብንም። የጀግኖች አባቶቻችን የነፃነት አንባ የሆነችውን ሀገር በነፃ ጦር ሰይሰበቁና ሜዳ ሳይዋደቁ ‘እንካችሁ ሀገራችንን ውሰዱ፤ ነፃነታችንን ግፈፉ፤ በዓለም ላይ በጀግኖች አባቶቻችን ደም ደምቆ የተፃፈውን ታሪካችንን አጥፉ!’ ብለን እርስ በርሳችን እየተገዳደልን ‘የእሳት ልጅ አመድ’ እንዲሉት ልንሆን አይገባንም። ሀሳቤን ወደመጠቅሉ ስመጣ ዛሬ ሦስት ነገር ብቻ ነው ልላችሁ የምፈልገው፦

    • አድዋ ትላንት! አድዋ ዛሬ! አድዋ ነገስ! ለእኛ እና ለልጆቻችን ምንድን ነው? ሁሌም ለሁላችንም አንድ ዓይነት ትርጉም ነው ሊኖረው የሚገባው – እሱም ዘር፣ ቋንቋ፣ ሃይማኖት የማይለየው ፍፁም የሆነ አንድነት ፍቅርና ሰላም ሁሌም ድል ሁሌም ማሸነፍ ብቻ ነው።
    • ትላንትና አባቶቻችን አንድ ብቻ ነበሩ፤ ዛሬም እኛ አንድ ነን፤ የነገውም ትውልድ አንድ ብቻ ይሆናል። እኛ አንድ እንጂ 80 ኢትዮጵያ የለችንም።
    • ትላንትና አባቶቻችን አሸናፊና ጀግና ብቻ ነበሩ፤ ዛሬም እኛ አሸናፊና ጀግና ብቻ ነን፤ የነገውም ትውልድ አሸናፊና ጀግና ብቻ ይሆናል። ጥላቻን፣ ክፋትን፣ መለያየትን ያሸነፈ ለሰላምና ለፍቅር ለአንድነት የተሸነፈ፣ ሃገሩንና ነፃነቱን ለማንም አሳልፎ የማይሰጥ ትውልድ ባለድል ነው። ቅድም ያልኩትን አሁንም እደግመዋለው – እኛ አንድ እንጂ 80 ኢትዮጵያ የለችንም። ስለዚህ ዛሬ ሁላችን በአድዋ ድል ስም ለራሳችን ቃል አነገባለን።

    “ጀግኖች አባቶቻንች በፅኑ ተጋድሎ ያወረሱንን ሀገርና ነፃነት እኛ እርስ በእርሳችን ተገዳድለን በነፃ ለጠላት ላንሰጥ ቃል እንገባለን” ቃላችሁን እንደምትጠብቁ አምናለሁ አመሰግናለሁ።

    መልካም የአድዋ ድል በዓል
    ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር።
    አቶ ኦባንግ ሜቶ

    የአድዋ ድል በዓል

    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአሜሪካ የግምጃ ቤት ዲፓርትመንት ሴክሬታሪ በየካቲት 21 ቀን 2012 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ. በ28 February 2020) የታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በተመለከተ ኢትዮጵያ ያልተሳተፈችበትን ስብሰባ ተከትሎ የወጣውን ጋዜጣዊ መግለጫ በከፍተኛ ቅሬታ ተመልክተውታል።

    ስብሰባው የተካሄደው ኢትዮጵያ አስቀድማ ለግብጽ፣ ለሱዳን እና ለአሜሪካ ስብሰባው ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ አሳውቃ እያለ ነው።

    የግድቡ ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ በመርሆዎች መግለጫ ስምምነቱ መሰረት የግድቡን ሙሌት ከግንባታው ትይዩ በፍትሐዊ እና ምክንያታዊ አጠቃቀም እና ጉልህ ጉዳት ያለማድረስ መርሆዎች መሠረት የምታከናውን ይሆናል።

    ኢትዮጵያ የግድቡን የመጀመሪያ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ መመሪያ እና ደንብ ለማዘጋጀት የሚደረገው ድርድር ተጠናቋል በሚል የተሰጠውን መግለጫ አትቀበልም።

    በዋሽንግተን ዲሲ የግብጽ ዐረባዊት ሪፐብሊክ ፈርሞበታል የተባለው “ረቂቅ” የሦስቱ ሀገራት የድርድርም ሆነ የሕግ እና ቴክኒክ ቡድኖች ውይይት ውጤት አይደለም። የቴክኒክ ጉዳዮች ድርድሩም ሆነ የሕግ ማዕቀፍ ዝግጅቱ ላይ የሚደረገው ድርድር አልተጠናቀቀም።

    ኢትዮጵያ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ መመሪያ እና ደንብ የሚዘጋጀው በሶስቱ ሀገራት ብቻ እንደሆነ አቋሟን ቀድማ አሳውቃለች።

    ኢትዮጵያ ግብጽ እና ሱዳን በሚያውቁት እና በተስማሙበት እንዲሁም በመርሆዎች መግለጫ ስምምነት መርህ አንቀጽ ስምንት አድናቆታቸውን በሰጡት ሂደት መሠረት ሁሉንም የግድብ ደህንነት የሚመለከቱ ጉዳዮች በዓለምአቀፍ የባለሙያዎች ቡድን ምክረ ሃሳብ መሰረት የተሰጡትን ምክረ-ሃሳቦች መፈጸሟን ትቀጥላለች።

    የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ሙሌት እና የውሃ አለቃቅ መመሪያ እና ደንብን ለማዘጋጀት ቀሪ መሰረታዊ ልዩነቶችን ለመፍታት ኢትዮጵያ ከግብጽ ዐረባዊት ሪፐብሊክ እና ከሱዳን ሪፐብሊክ ጋር የጀመረችውን ሂደት ለመቀጠል ቁርጠኛ ናት።

    ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ፥ የኢትዮጵያ መንግስት ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ብሔራዊ ጥቅምን የሚነካ ድርድር እንደማያደርግ የሚስትሮች ም/ቤት አስታወቀ።

    ታላቁ የሕዳሴ ግድብን የሚመለከት ማንኛውም ነገር የኢትዮጵያን ፍላጎትና ጥቅም በሚጠብቅ መልኩ ብቻ እንደሚከናወን የሚስትሮች ምክር ቤት ገልጿል።

    ምክር ቤቱ በዛሬው ዕለት ባካሄደው ስብሰባ ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ብሔራዊ ጥቅምን የሚነካ ድርድር የኢትዮጵያ መንግስት እንደማያደርግ አስታውቋል።

    በዛሬው ዕለት ባካሄደው 80ኛ መደበኛ ስብሰባው ምክር ቤቱ የኮሮና ቫይረስ መከላከል ስራዎችን የሚከታተል ስድስት አባላት ያሉት ብሔራዊ የሚኒስትሮች ኮሚቴ ማቋቋምን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

    የብሔራዊ የሚኒስትሮች ኮሚቴው ስድስቱ አባላትም የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል፣ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ፣ የገቢዎች ሚኒስትር ወይዘሮ አዳነች አቤቤ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊ ሞገስ እና የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሊያ ታደሰ ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    Ethiopian government's statement regarding the negotiations on GERD የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ

    Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያ የለውጥ ሂደት፣ የቀጣዩ ምርጫ አገራዊ ፋይዳ እና የተደቀኑ አደጋዎች ― ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ (ኢዜማ) ያስተላለፉት መልዕክት

    ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ፤ እንደምን ከረማችሁ?

    በዛሬው ዕለት እንደ ኢዜማ መሪም ሆነ እንደ አንድ ዜጋ፣ ከኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ጋር በዚህ መልክ ለመገናኘት ምክንያት የሆነኝ ከፊታችን በተደቀነው ምርጫ ላይ ኢዜማን እንድትመርጡ ለመቀስቀስ አይደለም። እሱ ሁሉም የፖለቲካ ድርጅቶች የምርጫው ቅስቀሳ ጊዜ በግልጽ ሲታወጅ የምናደርገው ይሆናል። ይልቁንም ዛሬ ላዋያችሁ የምፈልገው እንደ ሀገርም እንደ ሕዝብም ልንጋፈጠው የሚገባን ፊት ለፊታችን የተጋረጠ አንድ ትልቅ እውነትን ነው፤… ዛሬ በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች የሚከሰቱ አለመረጋጋቶች፣ ግጭቶችና ከዕለት ወደ ዕለት አሳሳቢ እየሆነ የመጣው የሰላም እጦት፣ ‘ነገ ደግሞ ምን ይዞ ይመጣ ይሆን?’ የሚል ስጋት/ ጭንቀት አለ።

    በየሜዲያው የሚወጡ፤ የተጨበጡና ያልተጨበጡ ሁላችንንም የሚያስጨንቁ በርካታ መረጃዎችን እንሰማለን። ተማሪዎች ታገቱ/ ተገድሉ፥ መስጊድና ቤተ-ክርስቲያን ተቃጠሉ፥ ባንኮች ተዘረፉ፥ መንገድ ተዘጋ፥ ንብረት ተዘረፈ ወይም ወደመ፣ የሚሉ ዜናዎችን መስማት ከምንግዜውም በላይ እየተለመደ ነው። ከመደበኛ ሥራችን ውጭ በተለያዩ ማኅበራዊ ስብስቦች ስንገኛኝ የምንወያያቸው ጉዳዮች ለመሆኑ ሀገራችን ወዴት እየሄደች ነው? በዚህ በምናየውና በምንሰማው ሁኔታ ከቀጠልን እንደ ሀገር መቀጠል እንችላለን ወይ? ከዚህ ከገባንበት አዘቅት መቼና እንዴትስ ነው የምንወጣው? የኛም ሆነ የልጆቻችን ዕጣ ፈንታስ ምን ይሆናል? የሚሉና ሌሎችም ብዙ ይህ ትውልድ ወደደም ጠላ መመለስ ያለባችው አንኳር ሀገራዊ ጥያቄዎች፤ አዋቂና ህጻን ሳይለይ ሁላችንንም ከምንም በላይ ያስጨነቁና እንቅልፍ እየነሱ የሚገኙ ጥያቄዎች ሆነዋል።

    ዛሬ ሀገራችን ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ቆማለች፥ በዚህ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ የሀገራችን የወደፊት እጣ ፈንታ ሲወሰን ውሳኔዉ እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ይመለከታልና በዚህ ትልቅና ታሪካዊ ውሳኔ ላይ እኛ ምን ያገባናል? ምንስ ሚና አለን? ለሀገራችን ይበጃል የምንለውና የምንፈልገው የመልካም ዘመን መዳረሻ ጋር እንድንደርስ ምን ማድረግ አለብን?” ለሚሉ ጥያቄዎች መልስ ማቅረብ የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ የነቃ ተሳትፎ የሚጠይቁ ነገር ግን ዛሬ ላይ ሁላችንንም ግራ ያጋቡ ጥያቄዎች ናቸው።

    ከፊታችን ያለውን ምርጫ እንኳን በሚመለከት የምናደርገው ውይይት በምርጫው ማን ያሸንፋል? ወይንም ማን ቢያሸንፍ ጥሩ ነው? የሚል ክርክር ሳይሆን “ለመሆኑ በዚህ አይነት ሀገራዊ ሁኔታ ነፃና ሚዛናዊ ምርጫ ማድረግስ ይቻላል ወይ?” “ቢቻልስ ሀገራችን ውስጥ የሚታዩት ዘርፈ-ብዙና ዉስብስብ ችግሮች ሀገራዊ ምርጫ በማድረግ የሚፈቱ ናቸው ወይ?” የሚሉ የጊዜው ሁኔታ የፈጠራቸው ፍርሀቶችና ጭንቀቶች ላይ ደርሰናል። ይህ ሁሉ የሚያሳየን ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ጊዜያዊ ከሆነ የራሳችንን ጥቅምና ፍላጎት ለጊዜውም ቢሆን ተወት አድርገን በጋራ ልንሰራባቸው የሚገቡ የሀገራችንን ትላልቅ ችግሮች በጋራ ለመፍታት አንድ ላይ ካልቆምን የሀገራችን የኢትዮጵያ ህልውና ከምን ጊዜውም በላይ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ ይወድቃል።

    የሀገራችንን ሁኔታ በተመለከተ ከተለያዩ የዜና ምንጮች ከምንሰማው በተጨማሪ፣ ኢዜማ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ ከተፈጠረ በሁዋላም ሆነ ከዚያ በፊት፣ በገጠርና በከተማ፣ በተለያዩ አካባቢዎች ከሚገኙ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የሀገራችንን ሁኔታ በተመለከተ ሰፊ ውይይቶች አድርገናል። አሁንም በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች በዘረጋነው የፓርቲያችን መዋቅር አማካኝነት አካባቢያዊ መረጃዎችን ስለምንሰበስብ ስለ ሀገራችን ሁኔታ፥ ፊት ለፊታችን ስለተጋረጡት ችግሮች፣ በሕዝቡ ውስጥ ስለሚንፀባረቁ ጭንቀቶች፣ ስጋቶችና ተስፋዎች በቂ መረጃ አለን ብለን እናምናለን።

    ኢዜማ በአንድ በኩል እንደ አንድ ኃላፊነት የሚሰማው ሀገር አቀፍ የፖለቲካ ድርጅት ኢትዮጵያ ውስጥ የሚከሰቱ የተለያዩ ችግሮችን እያየ ከንፈር በመምጠጥ፥ በማዘንና በመተከዝ አያልፍም። በሌላ በኩል ደግሞ ኃላፊነት በጎደለው መንገድ የሕዝቡን ስሜት አነሳስቶ ችግሮችን የበለጠ አያጦዝም። ድርጅታዊ አቅማችን እስከፈቀደ ድረስ ፊታችን ላይ የተደቀኑ አደጋዎችን በመረጃ ላይ ተመርኩዘን በመተንተን አደጋዎቹ ከቁጥጥር ውጭ ወጥተው የሀገራችንን ህልውና አደጋ ላይ ከመጣላቸው በፊት ለማኅበረሰባችን የማንቂያ ደውል እናሰማለን። አደጋዎቹን መከላከልና ብሎም ማቆም የሚያስችል ስትራቴጂ እንቀይሳለን። ከተለያዩ የሀገራችን ባለድርሻዎች፥ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ ምሁራንና ከመንግስት አካላት ጋር በመሆን፣ በሀገራችን የተደቀኑትን አደጋዎች በጋራ መመከት እንዲቻል የማስተባበር ሥራ እንሰራለን። ከሁሉም በላይ ደግም በፖለቲካ ድርጅቶች መካከል ያለው የፖሊሲና የፖለቲካ አመለካከት ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው፣ አሁን የምናያቸውን ሀገራዊ አደጋዎች መከላከል ብቻ ሳይሆን እንደገና እንዳይከሰቱም ለማድረግ “የብሔራዊ ጥቅሞቻችንና የሀገር አጠቃላይ ደኅንነት ጉዳዮች ” (National Interest & Security Agendas) ናቸው በሚባሉ ጉዳዮች ላይ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር አብሮ ለመሥራት ባለን ድርጅታዊ አቅም ሁሉ እንዘጋጃለን።

    ዛሬ በዚህ ንግግር ላይ የማተኩረው ኢዜማ እንደ ድርጅት በሀገራችን ያለውን ሁኔታ ገምግሞ የደረሰባቸውን ከፊታችን የሚታዩ አደጋዎች ምንነት፤ እነኝህን አደጋዎች በሚመለከት የጋራ ሀገራዊ ግንዛቤ ለመፍጠር የሚያስችል የሰከነ ውይይት ለመክፈትና፤ እኛ የሚታየን አደጋ በርግጥም ሌሎቹም የሀገራችን ባለድርሻዎች ይታያቸው ከሆነ፣ ይህን አደጋ ለመከላከል የሚያስፈልገውን የጋራ ስምምነትና እንቅስቃሴ ለማድረግ የሚያስፈልገውን ሀገራዊ ጥሪ ለማስተላለፍ ነው።

    እኛ ባደረግነው የሀገራዊ አደጋ ትንተና የማይስማሙ ኃይሎች ሊኖሩ እንደሚችሉ እንገነዘባለን። እነሱም ቢሆኑ ግን ዝም ብሎ የተለመደውን ጭፍን ወገንተኛ የሆነ፤ በቅጡ ያልታሰበበት የጥቅል ተቃውሞ ከማሰማት ይልቅ “በርግጥ ይህ አደጋ አለ ወይ?” ብለው በጥሞና እንዲያስቡ ካደረጋቸውና ወደ ሰከነ ውይይት ከመራቸው፣ የዚህ መልዕክት ዓላማ በከፊልም ቢሆን ተሳክቷልና ለምን ከእኛ ትንተናና ድምዳሜ ጋር ሙሉ ለሙሉ አልተስማማችሁም አንልም።

    ሙሉ መልዕክቱን ለማንበብ እዚህ ጋር ይጫኑ

    ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ (ኢዜማ) ያስተላለፉት መልዕክት

    Anonymous
    Inactive

    እናት ባንክ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የግብይት ሥርዓት ውስጥ ለመሳተፍ የሚያስችለውን ዕውቅና አገኘ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– እናት ባንክ አክስዮን ማኅበር በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን የግብይት ሥርዓት ውስጥ ለመሳተፍ የሚያስችለውን ዕውቅና አገኘ።

    የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን ለእናት ባንክ በግብይት ሥርዓቱ ውስጥ ለመሳተፍ የሚያስችለውን የዕውቅና ምስክር ወረቀት (certificate) በሰጠበት ወቅት ዋና ዳሬክተሩ ኢንጅነር ኡሌሮ ኡፒየው እንዳሉት፥ ባለስልጣኑ በምርት ገበያው ክፍያ የሚፈጽሙ ተቋማትን አፈጻጸማቸውን የመቆጣጠርና ዕውቅና የመስጠት ስልጣን በአዋጅ የተሰጠው በመሆኑ እናት ባንክ ከምርት ገበያው ጋር የሚያደርገው የኤሌክትሮኒክስ የመረጃ ልውውጥ አስተማማኝ መሆኑ በመረጋገጡ በግብይት ሥርዓቱ ውስጥ ለመሳተፍ የሚያስችል የዕውቅና ምስክር ወረቀት ሊያገኝ ችሏል። በዚህም ባለስልጣኑ ከባንኩ ጋር ለመሥራት የሚያስችለውን የሥራ ውል ስምምነት መፈራረሙን ተናግረዋል።

    እናት ባንክ አክስዮን ማኅበር ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን የተሰጠውን የዕውቅና ሰርተፍኬት በተረከበበት ወቅት የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ወንደወሰን ተሾመ እንዳሉት፥ የባንኩን የቴክኖሎጂ አቅም በማሳደግ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን የግብይት ሥርዓት ውስጥ ለመሳተፍና የፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸውን ዕውቅና ማግኘታቸው እንዳስደሰታቸው ገልጸዋል።

    እናት ባንክ በፌስቡክ ገጹ ላይ ያሰፈረው መግለጫ እንዲህ ይነበባል፦

    እንኳን ደስ አለን…
    እናት ባንክ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ (ኢ.ሲ.ኤክስ) የክፍያ ፈፃሚ ባንክ በመሆን የክፍያ ሥርዓቱን መጀመር የሚስችለውን የዕውቅና ሰርተፊኬት ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን የካቲት 17 ቀን 2012 ዓ.ም. በተካሄደው ሥነ-ሥርዓት ተቀበለ። በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የምትገበያዩ ደንበኞቻችን በዚሁ አጋጣሚ አገልግሎቱን ማግኘት እንደምትችሉ ስናሳውቅ ደስታ ይሰማናል።

    የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ሥራውን ሲጀምር ዕውቅና ተሰጥቷቸው በግብይት ሥርዓቱ ውስጥ ክፍያ ሲፈጸምባቸው የነበሩ ባንኮች ሁለት ብቻ የነበሩ ሲሆን፥ በሂደት ቁጥራቸው 15 መድረሱን አስታውሰው፥ እናት ባንክ ሲጨመር በድምሩ 16 መድረሳቸውን ተናግረዋል።

    በገበያ ሥርዓቱ ውስጥ የክፍያ መፈጸሚያ ባንኮች ዋና ዋና ተግባራትና ኃላፊነቶች የምርት ገበያው አባላትና ደንበኞች በባንኮቹ ውስጥ ገንዘብ የሚሰባሰብበትን ሁኔታ ማመቻቸት፣ የምርት ገበያው የክፍያ መፈጸሚያ ተቋም በሚሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ከግብይት በኋላ ገንዘብ ማዘዋወርና ስለ ወቅታዊ ደንበኞችና የአባላት የባንክ ሂሳብ ከባለስልጣኑ ጋር መረጃ መለዋወጥ መሆኑ ተገልጿል።

    ከግል ባንኮች በርካታ ባለአክሲዮኖችን በመያዝ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው እናት ባንክ፥ በ2011 ሒሳብ ዓመት ከታክስ በፊት 231.4 ሚሊዮን ብር እንዳተረፈ፣ የተጣራ ትርፉም 202 ሚሊዮን ብር መሆኑን አስታውቆ ነበር። ባንኩ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች 45 ቅርንጫፎችን ከፍቶ አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፣ ይህንን የቅርንጫፍ ቁጥር በ2012 ሒሳብ ዓመት ወደ 70 ለማሳደግ ዕቅድ መያዙን አምና ኅዳር ወር 2012 ዓ.ም. አስታውቆ ነበር።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    እናት ባንክ

    Semonegna
    Keymaster

    በዓመት 500 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት የሚያመርተው ፋብሪካ ዘንድሮ ሥራ ይጀምራል

    ቡሬ (አዲስ ዘመን) – የአገር ውስጥ የምግብ ዘይት ፍጆታን ከ50 እስከ 60 በመቶ መሸፈን የሚያስችልና በቡሬ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የምግብ ዘይት ፋብሪካ ከሁለት እስከ አራት ወራት ውስጥ ተጠናቆ ወደ ምርት ይገባል ተባለ። የውጭ ምንዛሬ በማዳን የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረውም አዲስ ዘመን ጋዜጣ ዘግቧል።

    በፌዴራልና በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ አመራሮች የካቲት ወር አጋማሽ፣ 2012 ዓ.ም. የተጎበኘው በኢትዮጵያዊ ባለሃብት አቶ በላይነህ ክንዴ በመገንባት ላይ ያለው ፋብሪካው፤ የአገር ውስጥ የምግብ ዘይት ፍጆታን ከ50 እስከ 60 በመቶ ይሸፍናል ተብሏል።

    በአገር ውስጥ ያለውን የምግብ ዘይት አቅርቦት ችግርን ለመፍታት ወደ ዘርፉ መግባታቸውን የገለጹት አቶ በላይነህ ክንዴ፥ ከአንድ ፋብሪካ በስተቀር ቀሪዎቹ እንደተገጣጠሙም ተናግረዋል። በዓመት 500 ሚሊዮን ሊትር ዘይት የማምረት አቅም እንዳለውና አገር ውስጥ ያለውን የምግብ ዘይት አቅርቦት እንደሚፈታም ተናግረዋል።

    ድርጅቱ ላለፉት 13 ዓመታት ሰሊጥ ወደ ውጭ በመላክ ግንባር ቀደም እንደነበር በማስታወስ፥ በተደጋጋሚ በመንግሥትና በሕዝብ ይቀርብ የነበረው ጥያቄ እውን የሚያደርገው አቀነባብሮ የሚያቀርበው ፋብሪካ ዘንድሮ ወደ ምርት እንደሚገባ ነው ባለሀብቱ የተናገሩት። ማንኛውንም አይነት የቅባት እህሎችን እንደሚያጣራና በአሁኑ ወቅት ለአምስት መቶ ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን ወደ ምርት ሲገባ ቁጥሩ እስከ ሦስት ሺህ ከፍ እንደሚልም አብራርተዋል። ፋብሪካው በግብአትነት 20 ሚሊዮን ኩንታል እህል እንደሚያስፈልገው በመጠቆም፥ ከጉትን እስከ ጎንደር ጫፍ ያሉ አርሶ አደሮችም ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ በጋራ እንሠራለን ብለዋል።

    የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተካ ገብረየሱስ፥ አሁን ባለው ሁኔታ የሕዝቡን ፍላጎት ለማሟላት አቅም ያለው የምግብ ዘይት ፋብሪካ አለ ማለት ይከብዳል፤ አብዛኛው የምግብ ዘይት ፍላጎት ከውጭ በሚገቡ ምርቶች እየተሸፈነ እንደሚገኝም ተናግረዋል። በባለሀብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ የሚገነባው 50 በመቶ ፍላጎትን ከሸፈነ ቀሪውንም ሌሎች ወደ ምርት የሚገቡ ፋብሪካዎች ይሸፍኑታል ብለዋል። ፋብሪካዎች ማሽን ስላስገቡ ይጠናቀቃል ማለት አይደለም ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፥ የመብራት ችግር እንዳያስተጓጉል ጎን ለጎን እየተሠራ መሆኑንና ፋብሪካው ወደ ምርት ሲገባ የውጭ ምንዛሬ በማዳን በኩል ፋይዳው የጎላ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።

    በአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የፕሮሞሽንና ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ይሄነው አለም፥ ባህር ዳር ዙሪያና ቡሬ ከተማም እንደቅደም ተከተላቸው ሰፊ የኢንቨስትመንት ማዕከል መሆናቸውን ተናግረዋል። ባለሀብቱ ትልቅ የዘይት ፋብሪካ እንዲተክሉ ያነሳሳቸው አካባቢው ትርፍ አምራች መሆኑ ነውም ብለዋል።

    እንደ እርሳቸው ማብራሪያ፥ ከሱዳን ጠረፍ እስከጃዊ አኩሪ አተር፣ ኑግ፣ ሰሊጥ፣ ሱፍ፣ ስንዴና በቆሎ በከፍተኛ ደረጃ ይመረታል፤ ፋብሪካው ምርቶቹን በግብአትነት በመጠቀም ዘይት በከፍተኛ ደረጃ በማምረት በዕቅዱ መሠረት የአገሪቱን ከ50 እስከ 60 በመቶ ፍላጎት እንደሚሸፍንም ተናግረዋል። ምሥራቅ ጎጃም፣ ምዕራብ ጎጃምና አዊ ደቡባዊ ጎንደር እስከ ሱዳን ጠረፍ ከፍተኛ ምርት በመኖሩ የፌዴራልና የክልሉ መንግሥት የግብርና ምርት አቀነባባሪዎች ትኩረታቸውን ወደ አካባቢዎቹ እንዲያርጉም ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል።

    በላይነህ ክንዴ ግሩፕ በተለያዩ ዘርፎች የተሰማራ ድርጅት ሲሆን፤ በገላን ከተማ የጀመረው የመኪና መገጣጠሚያ፣ ሆቴልና እርሻ ሥራ ተጠቃሽ ናቸው። በቡሬ ከተማ በግንባታ ላይ ያለው የዘይት ፋብሪካ በ2006 ዓ.ም የተጀመረና በ30 ሄክታር ላይ ያረፈ ነው። የጀሪካን፣ የማሸጊያ፣ የሳሙና፣ የማርጋሪንና የካርቶንን ጨምሮ ሰባት የተለያዩ ፋብሪካዎችን ይዟል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    በላይነህ ክንዴ የምግብ ዘይት ፋብሪካ

    Anonymous
    Inactive

    የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ያካሄደውን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ በሊቀመንበርነት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔን በአቶ በለጠ ሞላ ጌታሁን በመተካት፣ ዘጠኝ የሥራ አስፈፃሚ አመራሮችን እና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን በመምረጥ ተጠናቀቀ።

    ደብረ ብርሃን (አብን) – የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ የካቲት 14 እና 15 ቀን 2012 ዓ.ም. አንደኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔውን የምርጫ ቦርድ ታዛቢ በተገኘበት በደብረ ብርሃን ከተማ አካሂዷል።

    ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የንቅናቄው ሊቀመንበር ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ አብን የአማራን ሕዝብ ጥያቄ መመለሥ በሚያስችለውና ወቅቱ በሚፈልገው ልክ ይገኝ ዘንድ ላለፉት ጊዜያት የመጣበትን መንገድ መርምሮ በጥናት ላይ የተመሠረተ መዋቅራዊ ማሻሽያ መዘጋጀቱን ገለፀው በዚህ ላይ ጠቅላላ ጉባዔው በደንብ ተወያይቶ አቋም እንዲይዝበት ጠይቀዋል።

    ጉባዔው በመጀመረያ ቀን ውሎው የአብን መዋቅራዊ ማሻሽያ (reform) አስፈላጊነትና አላማ፣ የንቅናቄው ጥቅል የሥራ ክንውን ሪፖርት፣ የፋይናንስ ኦዲትና ኢንስፔክሽን ሪፖርት፣ የብሔራዊ ምክር ቤቱ ሪፖርት፣ የተሻሻለው የንቅናቄው መተዳደሪያ ደንብና ቀርቦ በጠቅላላ ጉባዔው አባላት ሰፊ ውይይት ካደረገ በኃላ አፅድቋል።

    ጠቅላላ ጉባዔው 5 ተለዋጭ አባላት ያሉት 45 የንቅናቄውን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን በሚስጥር ድምፅ አሰጣጥም መርጦ ያፀደቀ ሲሆን የተመረጡት አባላትም የድርጅቱን ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበር መርጠዋል። በተጨማሪም በሊቀመንበሩ የቀረቡለትን ብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚዎችን አፅድቋል። በዚህም መሠረት 9ኙ የአብን ሥራ አስፈፃሚ አመራሮች፦

    1. አቶ በለጠ ሞላ ጌታሁን – ሊቀመንበር፣
    2. አቶ የሱፍ ኢብራሂም – ምክትል ሊቀመንበር፣
    3. አቶ አዲስ ኃረገወይን – የፖሊሲ ስትራቴጂ ኃላፊ፣
    4. አቶ ጣሂር ሞሐመድ – የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ፣
    5. ዶ/ር ቴዎድሮስ ኃ/ማርያም – የውጭ ጉዳይ እና ዓለማቀፍ ግንኙነት
    6. አቶ ጋሻው መርሻ – የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ፣
    7. አቶ መልካሙ ፀጋዬ – የፅሕፈት ቤት ኃላፊ፣
    8. አቶ ጥበበ ሰይፈ – የሕግ እና ሥነ-ምግባር ኃላፊ፣ እና
    9. አቶ ክርስቲያን ታደለ – የፓለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ ናቸው።

    ምንጭ፦ አብን/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    —–
    ተመሳሳይ ዜናዎች

    በለጠ ሞላ ጌታሁን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ

    Semonegna
    Keymaster

    አዳማ ሪፈራል ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የሕክምና ዶክተሮችን አስመረቀ
    ጅማ ዩኒቨርሲቲ 3ሺህ 185 ተማሪዎችን መተመሳሳይ ዕለት አስመርቋል

    አዳማ (ኢዜአ) – አዳማ ሪፈራል ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የውስጥ ደዌና ከፍተኛ የቀዶ ሕክምና ስፔሻልስቶችን ጨምሮ በተለያዩ ሙያዎች ያሰለጠናቸውን 140 ዶክተሮችን የካቲት 14 ቀን 2012 ዓ.ም. አስመረቀ። ከተመራቂዎቹ መካከል ደቡብ ሱዳን የሕክምና ስፔሻልስቶች ይገኙበታል።

    በምረቃው ሥነ ሥርዓት የተገኙት የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ነጋሽ ስሜ እንደገለጹት፥ በክልሉ ከተሞችና ገጠራማ አካባቢዎች ካንሰርና ስኳርን ጨምሮ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች (noncommunicable diseases) እየተስፋፉ መጥተዋል። በክልሉ በሚገኙ የመጀመሪያና ሪፌራል ሆስፒታሎች የሕክምና መሣሪያና መድኃኒትን ጨምሮ የውስጥ ደዌና የቀዶ ሕክምና ሐኪሞች እጥረት መኖሩንም ተናግረዋል።

    ለዚህም አዳማ ሪፈራል ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ግንባር ቀደም መሆኑን ጠቅሰው ኮሌጁ የሰው ሕይወት ለማዳን የሚያስችል እውቅትና ክህሎት ለማስታጠቅ ተግባር ተኮር ስልጠናና ምርምር ሥራዎችን ማከናወን እንደሚገባው አቶ ነጋሽ ጠቁመዋል። ሰልጣኞቹ በቆይታቸው ያገኙትን እውቀት ወደ ተግባር በመተርጎም ማህበረሰቡን በማገልገል ምሳሌ መሆን አለባቸው ብለዋል።

    የአዳማ ሪፈራል ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መኮንን ፈይሳ በማህፀን፣ በውስጥ ደዌ፣ በህፃናትና በከፍተኛ ቀዶ ሕክምና እንዲሁም በጠቅላለ ሐክም ስፔሻልስቶችን እያሰለጠነ ነው፤ ዛሬ ለምረቃ የበቁት 140 የሕክምና ዶክተሮች አሁን በስፋት የሚስተዋለውን አጣዳፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ተናግረዋል።

    በተለይ በክልሉ የመጀመሪያ፣ ስፔሻላይዝድና ሪፌራል ሆስፒታሎች የሚታዩትን የማህፀን፣በውስጥ ደዌ፣ የህፃናትና ከፍተኛ ቀዶ ሕክምና ያለው የከፍተኛ ሙያተኞች እጥረት የሚፈታ ነው ብለዋል – ዶ/ር መኮንን።

    ሰልጣኞቹ በቆይታቸው ለህብረተሰቡ የጠቅላላ ሕክምና አገልግሎት፣ መካከለኛና ከፍተኛ የቀዶ ጥገና ሕክምና በመስጠት ሙያዊ ብቃታቸውን በተግባር ያስመሰከሩ በማለት አስረድተዋል።

    አዳማ ሪፈራል ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ከ400 በላይ አልጋ ያለው፣ ማስፋፊያ ግንባታ፣ የጥናትና ምርምር ማዕከላት፣የተማሪዎች መኖሪያና መመገቢያ ህንፃዎች ከአንድ ቢሊዮን 300 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በመገንባት ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል።

    ከተመራቂዎቹ መካከል በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀችው ዶ/ር አያንቱ በቀለ በሰጠችው አስተያየት በአሁኑ ወቅት በሀገራችን አሳሳቢ እየሆነ ያለው ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እንደሆነ ገልጻ ባገኘሁ እውቀት የድርሻዬን እወጣለሁ በማለት ተናግራለች።

    ከከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ምርቃት ጋር በተያያዘ፥ ጅማ ዩኒቨርሲቲ 3ሺህ 185 ተማሪዎችን መተመሳሳይ ዕለት አስመርቋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ጀማል አባፊጣ በምረቃው ሥነ ሥርዓቱ ወቅት እንደተናገሩት “ዛሬ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂዎች ሀገራችሁ ከእናንተ ከምንግዜውም በላይ እንድታገለግሏት ትፍልጋለች” ብለዋል።

    ዩኒቨርሲቲው ያስመረቀው ከስድስት ኮሌጆች፣ ሁለት ኢንስቲትዩቶች እና ድኅረ ምረቃ ትምህርት ቤት በተለያዩ ሙያዎች ስልጠናቸው ነው። ከተመራቂዎቹ መካከል 834 ሴቶች እንዲሁም 11 የሱማሌላንድና የሩዋንዳ ዜጎች ይገኙበታል። ዩኒቨርሲቲው ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተወጣጡ አንድ መቶ ስልሳ ስምንት ሰዎችን እያስተማረ እንደሚገኝም ተመልክቷል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አዳማ ሪፈራል ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ

    Anonymous
    Inactive

    የቀድሞው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ‹‹ሸገር ባንክ›› የተሰኘ ባንክ ለመመሥረት እንቅስቃሴ ጀመሩ

    አዲስ አበባ (ሪፖርተር ጋዜጣ)– የኦሮሚያ ክልልን በፕሬዚዳንት ከመመራት ባሻገር የተለያዩ መሥሪያ ቤቶችን በሚኒስትርነት ያስተዳደሩትና በስደት ከኢትዮጵያ ውጭ የነበሩት አቶ ጁነዲን ሳዶ ‹‹ሸገር ባንክ›› የተባለ አዲስ ባንክ ለማቋቋም እንቅስቃሴ በመጀመር የባንኩን የአክሲዮን ሽያጭ አስጀምረዋል።

    አቶ ጁነዲን ‹‹ሸገር ባንክ›› በሚል መጠሪያ የሰየሙትን ባንክ ለማቋቋም የተሰባሰበውን አደራጅ ኮሚቴ በአስተባባሪነት እየመሩ ሲሆን፣ ባንኩን ለመመሥረት የሚያስፈልገውን ካፒታል ለማሟላት ከተለያዩ ባለሀብቶች ጋር ከመከሩና አክሲዮን የሚገዙ በርካቶችን ከጎናቸውን ካሰለፉ በኋላ ወደ ካፒታል ማሰባሰብ ሥራ መግባታቸው ይጠቀሳል።

    ከሸገር ባንክ የአክሲዮን ሽያጭ በተሠራጨው መረጃ መሠረት፣ እንደ ሕጉ አግባብ አንድ አክሲዮን የአንድ ሺሕ ብር ዋጋ ይኖረዋል። አንድ ባለአክሲዮን ከአሥር አክሲዮኖች ጀምሮ መግዛት ይችላል ተብሏል። ባንኩን በተያዘው ዓመት መጨረሻ  ሥራ ለማስጀመር መታቀዱን ከአደራጅ ኮሚቴው ለመረዳት ተችሏል። ሸገር ባንክን ለመመሥረት አቶ ጁነዲን ጨምሮ 150 አደራጆች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ሲገለጽ፣ ካፒታል በማሰባሰቡ ረገድ ባንኩ ውጭ የሚገኙ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ላይ ትኩረት በማድረግ እንደሚሠራም ተጠቅሷል። የባንኩን አብላጫ ድርሻም በገጠሩ ኅብረተሰብ ላይ ትኩረት በማድረግ የአክሲዮን ሽያጩ እንደሚከናወን ይጠበቃል።

    የ‹‹ሸገር ባንክ›› አደራጆች፣ ከባንኩ ጋር ለመሥራት ፈቃደኛ የሆኑና ታዋቂ ግለሰቦችን በማካተት ሐሙስ፣ የካቲት 12 ቀን 2012 ዓ.ም. በስካይ ላይት ሆቴል የባንኩን አቅጣጫ የሚያመላክት ትንታኔ አቅርበዋል።

    በዚሁ ወቅትም የባንኩ የአክሲዮን ሽያጭ እንደተጀመረ ተገልጾ፣ ከታዋቂ ግለሰቦች መካከል ሻለቃ ደራርቱ ቱሉ፣ አቶ ጁነዲን ሳዶ፣ አቶ ጌቱ ገለቴ፣ አቶ ድንቁ ደያስና ሌሎችም ተገኝተዋል። የተለያዩ ከተሞችን የሚያስተዳድሩ ኃላፊዎችና  ከንቲባዎች እንዲሁም አባ ገዳዎች ተሳትፈዋል።

    በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕግ መሠረት ባንክ ለማቋቋም 500 ሚሊዮን ብር ካፒታል ያስፈልጋል። ይህንን ተከትሎም የሸገር ባንክ የተፈቀደ ካፒታል እስከ ሁለት ቢሊዮን ብር እንደሚደርስ ተገልጿል። የባንኩ አደራጆች ቢሮ ቦሌ መንገድ ላይ በሚገኘው ጌቱ ኮሜርሻል ሕንፃ ላይ መከፈቱም ታውቋል።

    የሸገር ባንክ አደራጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጁነዲን ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የባንኩ ባለአክሲዮኖች ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍል እንዲያቅፍ እንደሚደረግ በተለይ ግን ለገበሬው ክፍልና በተለያዩ ከተሞች በአነስተኛ ንግድ ሥራ ላይ የተሠማሩ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑና ተደራሽ የፋይናንስ አቅርቦቶችን እንዲያገኙ ይታሰባል። ባንኩ የገጠሩን ክፍል ከከተማው ጋር በማስተሳሰር የገቢ ምንጩ እንዲሰፋ የማገዝ ዓላማ እንዳለውም አቶ ጁነይዲ ጠቅሰዋል።

    ሙሉ ታሪኩን ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ያንብቡ

    ሸገር ባንክ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – ከነሐሴ ወር 2010 ዓ.ም. ጀምሮ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ያገለገሉት ዶ/ር አብርሃም በላይ በጥር ወር 2012 ዓ.ም. የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሆነው መሾማቸውን ተከትሎ በምትካቸው አቶ አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሹመዋል።

    በጥር ወር 2012 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ከነሐሴ ወር 2010 ዓ.ም. ጀምሮ ያገለገሉት ዶ/ር አብርሃም በላይ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሆነው መሾማቸውን ተከትሎ አቶ አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሹመዋል።

    በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ከተማ በ1973 ዓ.ም. የተወለዱት አቶ አሸብር የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በዚያው በአምቦ አዲስ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት፤ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ደግሞ በአምቦ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል።

    የከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በቀድሞ የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፤ በአሁኑ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተከታትለው 1995 ዓ.ም. ላይ በሜካኒካል ኢንጂነሪንግ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል። ከግሪንዊች ዩኒቨርሲቲ (Greenwich University) በዓለምአቀፍ ቢዝነስ የማስተርስ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል። ከስዊዲን ሀገር ኬ. ቲ. ኤች ሮያል ኢንስቲትዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ (KTH Royal Institute of Technology) በዘላቂ ኢነርጂ ምህንድስና ዘርፍ ተጨማሪ ኮርሶችን ወስደዋል።

    አቶ አሸብር በሜካኒካል ምህንድስና ከተመረቁ በኋላ በበደሌ ቢራ ፋብሪካ ጀማሪ ሜካኒካል ኢንጂነር የሥራ መደብ ላይ ለ7 ወራት አገልግለዋል። ከነሐሴ 1996 ዓ.ም. ጀምሮ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተቀጥረው በጊምቢ–መንዲ–አሶሳ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ሥራቸውን ጀምረዋል። በተከዜ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከጥር ወር 1997 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ግንቦት ወር 2003 ዓ.ም. ድረስ መሪ መካኒካል ኢንጂነር ሆነው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎችን በመቆጣጠር ተቋሙን አገልግለዋል።

    ከግንቦት 2003 ዓ.ም. እስከ መስከረም ወር 2012 ዓ.ም. ድረስ የገባ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ በመሆን ካገለገሉ በኋላ ከጥቅምት ወር 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ይህን ኃላፊነት እስከተቀበሉበት ቀን ድረስ የኃይል ማመንጫዎች ግንባታ ሥራ አስፈፃሚ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

    አቶ አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን በተለያዩ የሥራ መደቦች በባለሙያነትና በኃላፊነት ለ16 ዓመታት አገልግለው ከየካቲት 09 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ተቋሙን በዋና ሥራ አስፈፃሚነት እንዲመሩ በተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ተሹመዋል።

    ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት ዶ/ር አብርሃም በላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድን እንዲመሩ ተጨማሪ ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።

    ዶ/ር አብርሃም እስካሁን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ወደትክክለኛው መስመር እንዲመጣና እንዲፋጠን ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ ሲያደርጉ ቆይተዋል። በተለይም በኢፌዲሪ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ሜቴክ ተይዘው የነበሩ ሥራዎች ልምድ ላላቸው ዓለም አቀፍ ተቋራጮች እንዲሰጥና ተቋራጮቹም በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ እንዲሰሩ በማድረግ በኩል ጉልህ የአመራር ሚና ነበራቸው። የገናሌ ዳዋ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የካሳ ጥያቄ እልባት አግኝቶ ለምርቃት እንዲበቃም ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።

    ቢተገበሩ ወጪ ከማውጣት ባለፈ ውጤታማ የማይሆኑ ረዥም ዓመታት የወሰዱ ፕሮጀክቶች በህጋዊ መንገድ እንዲቋረጡ በማድረግ ተቋሙንና መንግስትን ከተጨማሪ ወጪ ማዳን ችለዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጤናማ የፋይናንስ አቅም እንዲኖረው በማድረግና በተቋሙ የአሰራር ስርዓቶችን በማሻሻል ተጨባጭ አምጥተዋል።

    የተቋሙን የዕዳ ጫና በተመለከተ ተቋሙ የሚመለከተውን ብድር ብቻ እንዲሸከምና ሌሎች ብድሮች ግን ወደ ብድሩ ባለቤቶች እንዲተላለፉ የሚያስችል ቁርጠኛ አቋም በመያዝ የብድር ጫናው እንዲቀንስ አድርገዋል።

    በመሆኑም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተጀመረው ለውጥ እንዲቀጥል በማሰብ እና በተቋሙ ላከናወኑት ሥራ እውቅና ለመስጠት ተቋሙን በሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢነት እንዲመሩ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተጨማሪ ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።

    ዶ/ር አብርሃም ባሳዩት ውጤት በተቋሙ አመራር እና ሰራተኞች ዘንድ ተወዳጅ የነበሩና የለውጥ መሪ ተምሳሌት ተደርገው የሚወሰዱ ነበር። የተቋሙ አመራርና ሠራተኞችም ዶ/ር አብርሃም በሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢነት ዳግም ወደተቋሙ በመምጣታቸው ደስታቸውን ገልፀዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

    Semonegna
    Keymaster

    የሀገሪቱ ንግድና ኢንዱስትሪ ዘርፍ ሁነኛ ደጋፊ የሆነው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2019 የግሎባል ቢዝነስ አውትሉክ ሽልማት አሸናፊ ሆነ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2019 የግሎባል ቢዝነስ አውትሉክ ሽልማት አሸናፊ ሆነ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሸናፊ የሆነው “በምርጥ የንግድ ባንክ” ምድብ ነው።

    ባንኩ በተለያዩ ዘርፎች ከቀረቡ ባንኮች ጋር ተወዳድሮ ነው “ምርጥ ንግድ ባንክ” /Best Commercial Bank/ ሽልማት አሸናፊ መሆን የቻለው። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከዚህ ቀደም በአፍሪካ ምርጥ ባንኮች ደረጃ እያገኘ የመጣ ሲሆን ለዚህ ዓለም አቀፍ ሽልማት ሲበቃ ይህ የመጀመሪያው ነው።

    ሽልማቱ ግሎባል ቢዝነስ አውትሉክ በሚያወጣቸው መስፈርቶች ተመሥርቶ የሚካሄድ ሲሆን፥ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዚህ ሽልማት አሸናፊ ለመሆን ካስቻሉት መስፈርቶች መካከል ለበርካታ ዓመታት በትርፋማነት መቀጠሉ፣ ተደራሽነቱ በፍጥነት እያደገ መሄዱ፣ የደንበኞች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ መጨመሩ፣ ለልማት ሥራዎች የሚያስፈልግ የፋይናንስ አቅርቦት ማሳደጉ፣ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን በሚገባ መወጣቱና ሌሎች የባንክ አገልግሎቶችን በተሟላ ሁኔታ መስጠት መቻሉ እንደሆነም ተጠቅሷል።

    ባንኩ የአገሪቱን ቁልፍ የልማት ሥራዎች እየደገፈና ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ የጤና፣ ትምህርት፣ አካባቢ ጥበቃና ሌሎችም ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች በግንባር ቀደምትነት ለመደገፍና በመሳተፍ ለአገራችን ልማት አጋር መሆኑን በተጨባጭ ያስመሰከረ መሆኑ ዓለም አቀፍ ሽልማቱን በቀዳሚነት እንዲያገኝ እንዳስቻለው ነው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንትና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ባጫ ጊና የገለፁት።

    በዚህ ረገድ ተጠቃሽ ከሆኑ ሥራዎች መካከል የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት ማሳደግ የሚያስችሉ ግዙፍ ኘሮጀክቶችን ፋይናንስ በማድረግ ባለፉት ዓመታት በርካታ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች እንዲከናወኑ አድርጓል። ለኃይል ማመንጫ ኘሮጀክቶች በርካታ ገንዘብ በማቅረብ ግንባታዎች እንዲከናወኑ በማድረግ ላይ መሆኑም ነው የተገለፀው።

    የሀገሪቱ ንግድና ኢንዱስትሪ ዘርፍ ዋና ደጋፊ ከሆኑ ድርጅቶች መካከል ቀዳሚ የሆነው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፥ በየዓመቱ ለግብርና ግብዓቶች አቅርቦት፣ ለክልሎች ፋይናንስ ማቅረቡ፣ ለሀገር ውስጥ ከሚያቀርበው ከፍተኛ መጠን ካለው ብድር በተጨማሪ ለህብረተሰቡ እጅግ አስፈላጊ የሆኑ የመድኃኒት፣ የምግብ ዘይት፣ ስንዴ፣ ስኳርና ቅባት ሌሎች የፍጆታ እቃዎችና የፋብሪካ ግብአቶች ከውጪ እንዲገቡ በማገዝ እየሠራ መሆኑም ለአሸናፊነቱ አስተዋፅኦ ማበርከቱ ተገልጿል። አቶ ባጫ ጊና አክለውም ሽልማቱ ባንኩ በቀጣይ ያለውን አገልግሎት ለማሳደግና በሌሎች ዘርፎችም ተሸላሚ ለመሆን የሚያነሳሳ መሆኑን ገልፀዋል።

    ግሎባል ቢዝነስ አውትሉክ በ2019 ካዘጋጃቸው የውድድር ምድቦች መካከል፦

    • Best Commercial Bank – የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
    • Best Islamic Bank – የአፍጋኒስታኑ Islamic Bank of Afghanistan፣
    • Best Innovative Bank – የአርመኑ InecoBank፣
    • Best Digital Bank – የቦትስዋናው FNB Botswana፣
    • Best Customer Service Bank – የባህሬኑ BBK፣
    • Best Retail Bank – የግብጹ National Bank of Egypt፣

    ከአሸናፊ ምርጥ ዝርዝሮች መካከል ይጠቀሳሉ። በተለያዩ ዘርፎች ያሸነፉ የባንኮችን ዝርዝር ለማየት እዚህ ጋር ይጫኑ። ከዚህ ቀደም የግሎባል ቢዝነስ አውትሉክ ሽልማት አሸናፊ ከነበሩ ሀገራት መካከል ካናዳ፣ ሩስያ፣ ቻይና፣ ፖርቹጋል፣ ህንድ፣ ኢንዶኒዥያ፣ ደቡብ አፍሪካና ናይጀሪያ ይጠቀሳሉ።

    ግሎባል ቢዝነስ አውትሉክ መቀመጫነቱ ለንደን ከተማ (እንግሊዝ) የሆነ ንግድና ኢንዱስትሪ ዘገባዎች ላይ ትኩረት ያደረገ የህትመት ድርጅት ነው።

    ንግድና ኢንዱስትሪ ዘርፍ

    Anonymous
    Inactive

    ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 221 የህክምና ዶክተሮችና ስፔሻሊስቶችን አስመረቀ

    ሀዋሳ (ኢዜአ) – የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ምንጮች ብቻ ሳይሆኑ በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፀ ዜጋን ማፍሪያ ማዕከላት ጭምር መሆን እንዳለባቸው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አሳሰቡ።

    ዩኒቨርሲቲው የካቲት 8 ቀን 2012 ዓ.ም. በአጠቃላይ 221 የጤና ባለሙያዎችን (192 የህክምና ዶክተሮችና 29 ስፔሻሊስት ዶክተሮችን) አስመርቋል። ከተመራቂዎች ውስጥ 22 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውም ተጠቁሟል።

    በምረቃ በዓሉ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አያኖ በራሶ እንደገለፁት፥ ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ ዲግሪ፣ በህክምና ስፔሻሊስትና በሦስተኛ ዲግሪ በርካታ የትምህርት መስኮችን (ፕሮግራሞችን) በመክፈት ከ43 ሺህ 800 በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና በተከታታይ ትምህርት መርሀ ግብሮች እያስተማረ ይገኛል። የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅም የመምህራን ልማት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል።

    ሀገሪቱ ካላት ውስን ሀብት ላይ አንድ አራተኛውን በጀት ለትምህርት ማዋሏን የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ፥ ተመራቂዎችም ያላቸውን ዕውቀት፣ ክህሎትና ጉልበት ላስተማራቸው ማኅበረሰብ በማበርከት ለሀገራቸው ዕድገት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ ጠይቀዋል።

    ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ምንጮች ብቻ ሳይሆኑ በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፀ ዜጋን ማፍሪያ ማዕከላትም ናቸው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፥ ተመራቂዎች ራሳቸውን ከመጥፎ ምግባር በመቆጠብና ሙያው በሚጠይቀው ሥነ-ምግባር ህሙማንን በፍቅር ማገልገል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

    በምረቃ በዓሉ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አባል ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በበኩላቸው ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

    ፕሮፌሰር በየነ እንዳሉት፥ ሀገሪቱ ባለፉት ሃያና ሰላሳ ዓመታት ውስጥ በጤናው ዘርፍ በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ እመርታ በማስመዝገብ የዓለም ጤና ድርጅትን ጨምሮ ሌሎች ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆኑ ታላላቅ ዓለም ዓቀፍ ተቋማትና መንግሥታት ዕውቅና ማግኘቷን ተናግረዋል።

    ይሁን እንጂ አሁንም የጤና ሽፋንን ከመጨመርና ጥራትና ፍትሐዊነት ያለው አገልግሎት ከመስጠት አንጻር ብዙ ርቀት መጓዝ እንደሚጠይቅ የተናገሩት ፕሮፌሰር በየነ፥ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት ጠንክረን በጋራና በትብብር መንፈስ መሥራት አለብን ብለዋል። የዛሬ ተመራቂዎችም የነገዋ ኢትዮጵያ ተስፋዎች መሆናቸውን በመረዳት ሀገራቸውን ማገልገል እናዳለባቸው ጠቁመዋል።

    በሙያቸው ገፍተው ዕውቀትና ክህሎታቸውን በማዳበርም የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡና ችግር ፈቺ በሆኑ ምርምሮች ውስጥ በመሳተፍ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተተገበረ ያለውን ፈርጀ ብዙ ለውጥ የማቀጣጠልና የማስቀጠል ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል ።

    ከተመራቂዎች መካከል ከፍተኛ ውጤት በማምጣት የሜዳልያ ተሸላሚ የሆነው ዶ/ር አቤል ጌታቸው በሰጠው አስተያየት፥ የህክምና ትምህርት ጽናትን የሚጠይቅ መሆኑን ገልፆ ሁኔታዎችን በትዕግስት በማለፍ ለዚህ መብቃቱን ተናግሯል።

    የህክምና ሙያ በራሱ ለሰዎች ክብር መስጠትና ርህራሄ መላበስን የሚያስተምር እንደሆነ የተናገረው ዶ/ር አቤል፥ ያለአድሎ ሰብዓዊነትን በመላበስ ህብረተሰቡን ለማገልገል ዝግጁ መሆኑን አስረድቷል።

    በውስጥ ደዌ ህክምና ስፔሻላይዝድ በማድረግ የተመረቀው ዶ/ር ሙባረክ ሁሴን በበኩሉ፥ የህክምና ሥነ-ምግባር ከሀሳብ ይልቅ በተግባር የሚገለፅ መሆኑንና ታካሚዎችን እንደ ቤተሰብ በማየት ያለአድሎ ለማገልገል መዘጋጀቱን ተናግሯል።

    የዩኒቨርሲቲው የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና ዶክትሬት ተማሪዎችን ሲያስመርቅ ለ11ኛ ዙር ሲሆን ስፔሻሊስት ሀኪሞችን ደግሞ ለ4ኛ ዙር መሆኑ ተዘግቧል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 221 የህክምና ዶክተሮችና ስፔሻሊስቶችን አስመረቀ

    Semonegna
    Keymaster

    “እኔ ለወገኔ” የወሎ ዩኒቨርሲቲ የበጎ አድራጎት ማኅበር በደሴ ከተማ ድጋፍ አደረገ

    በወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተመሰረተው “እኔ ለወገኔ” ማኅበር ድጋፍ ለሚሹ አቅመ ደካሞችና ሕፃናት የአልባሳት ድጋፍ አድርጓል። በቀጣይም አረጋውያንን በማዕከል በማሰባሰብ በቋሚነት የሚጦሩበትና የጎዳና ተዳዳሪ ወጣትና ሕፃናትን ደግሞ ወደ ትምህርት ቤት በማስገባት ለማስተማር ይሠራል።

    ደሴ (ኢዜአ) – በወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የተመሠረተው “እኔ ለወገኔ” የበጎ አድራጎት ማኅበር ከ700 ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸው አልባሳትና ቁሳቁሶችን አቅመ ደካሞችና ለዳና ተዳዳሪዎችን ጨምሮ ድጋፍ ለሚሹ የደሴ ከተማ ኗሪዎች ድጋፍ አደረገ። የማህበሩ አባላት በተለያዩ የመንግስት ተቋማት፣ ድርጅቶችና ግለሰቦች ያሰባሰቡትን ቁሳቁስ በከተማዋ ለሚኖሩ አቅመ ደካሞችና ሕፃናት አሰራጭተዋል።

    የማኅበሩ አባል ተማሪ አቡሽ ግርማ እንዳለው የዛሬ ሁለት ዓመት የተመሠረተው “እኔ ለወገኔ” ማኅበር ደሴ ከተማ እና በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችንና ችግረኛ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በማገዝ ሥራ ተሰማርቷል። በዚህም ተማሪዎች ከባለሃብቶች፣ ፋብሪካዎችና ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች በማሰባሰብና ጫማ በመጥረግ ሥራ የሚያገኙትን ገንዘብ በመቆጠብ ለ300 አቅመ ደካሞችና የጎዳና ተዳዳሪዎች የካቲት 2 ቀን 2012 ዓ.ም. ድጋፍ አበርትቷል። ድጋፉ የተደረገውም የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች፣ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ እና ሌሎች አልባሳት የመሳሰሉት ናቸው። በቀጣይም አረጋዊያንን በማዕከል በማሰባሰብ በቋሚነት የሚጦሩበትና የጎዳና ተዳዳሪ ወጣትና ሕፃናትን ደግሞ ወደ ትምህርት ቤት በማስገባት ለማስተማር እንደሚሠሩ ተናግሯል።

    ሌላው የ3ኛ ዓመት የሥራ አመራር (management) ተማሪ ምትኩ ደጉ በበኩሉ፥ ቁሳቁሱንና አልባሳቱን ማሰባሰብ የተቻለው የትምህርት ጊዜያቸውን በማይነካ መልኩ በመንቀሳቀስ ነው። የኢትዮጵያውያን አኩሪ እሴት ከሆኑት መካከል መረዳዳትና መደጋገፍ መሆኑን በሌሎች ተማሪዎች ዘንድ ለማስረጽ ማኅበር መሥርተው መንቀሳቀሳቸውን አስረድቷል።

    የወሎ ዩንቨርሲቲ አስተዳደርና ተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር አማረ ምትኩ በበኩላቸው፥ ተማሪዎች ከትምህርታቸው ጎን ለጎን የሚያደርጉት የተለያየ በጎ ተግባር የሚደነቅ ነው። ዩኒቨርሲቲዎች በግጭት በሚታመሱበት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት የማኅበሩ አባላት ተማሪዎች በአንድ ላይ ሕብረተሰቡን አስተባብረውና የሌሎችን ጫማ ጠርገው ደካሞችን መደጋገፋቸው አርአያነት ያለው ተግባር ነው ብለዋል። አያይዘውም ፕሬዚዳንቱ በትውልዱ እየተሸረሸረ የመጣውን መረዳዳት፣ መተዛዘን እና የተገኘውን ተካፍሎ የመጠቀም ተግዳሮቶች ምላሽ የሰጠ ሊበረታታና ሊስፋፋ የሚገባው መልካም ተግባር እንደሆነ ገልጸዋል። በቀጣይም ተማሪዎቹ ለሚያከናውኑት መልካም ምግባር ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል።

    የድጋፉ ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል አቶ ጸጋዬ ቢያድግልኝ እንደ ገለጹት፥ ረዳትና ተንከባካቢ ቤተሰብ ስለሌላቸው አንድ ሱሪና ጃኬት ለብሰው ለዓመታት ኖረዋል። በወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አማካኝነት ብርድ ልብስ፣ ሱሪ፣ ሸሚዝና ጃኬት በማግኘታቸው እየቀያየሩ በመልበስ ንጽህናና ጤንነታቸውን ለመጠበቅ እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)/ ወሎ ዩኒቨርሲቲ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    እኔ ለወገኔ ወሎ ዩንቨርሲቲ

Viewing 15 results - 301 through 315 (of 730 total)