Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 15 results - 706 through 720 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Semonegna
    Keymaster

    የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአገር ውስጥ ሰላም እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በሕዝቡ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር እንዲቋቋም ተወስኗል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የሚኒስትሮች ምክር ቤት መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የፌደራል መንግሥትን አስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በተዘጋጀ ረቀቅ አዋጅ ላይ መክሮ እንዲጸድቅ ለተወካዮች ምክር ቤት እንዲላክ ወስኗል።

    በውይይቱ ላይ የአስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን ያስፈለገበት ዋና ዋና ምክንያቶች እንደሚከተለው ቀርቧል፦

    1. የሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በቀሪው ጊዜ ያልተጠናቀቁ ሥራዎችን አካክሶ ለመፈጸም የሚያስችል አደረጃጀት በማስፈለጉ፤
    2. አገራችን የተያያዘችውን የለውጥ ጉዞ ለማስቀጠልና የማይቀለበስበት ደረጃ ላይ ለማድረስ የሚያስችል አደረጃጀትን መከተል በማስፈለጉ፤
    3. የአስፈጻሚ አካላትን ቁጥር ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢና ውጤታማ ለማድረግ በማስፈለጉ፤
    4. ተደራራቢና ድግግሞሽ ሥልጣንና ተግባር የያዙ የመንግሥት ተቋማትን መቀነስ ወይም ለሥራቸው ቅርብ ከሆነ ሌላ የመንግሥት ተቋም ጋር እንዲዋሃዱ ማድረግ በማስፈለጉ፤

    እንደሆነ በስብሰባው ላይ ተብራርቷል።

    በምክር ቤቱም ውሳኔ የካቢኔ አባላት ቁጥር ከ28 ወደ 20 እንዲቀንስ ተደርጓል፤ ዋና ዋናዎቹ ለውጦችም:-

    • የንግድ ሚኒስቴር እና የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተዋህደው – የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እንዲሆን ፤
    • በየሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተዋህደው – የኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሆን ፤
    • የከተማ ልማት ሚኒስቴር እና የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ተዋህደው – የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር እንዲሆን
      ወስኗል።

    ሌሎች ተጠሪ ተቋማትም በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲዋሃዱ ውሳኔ የተሰጠባቸው ይገኛሉ።

    ሌላው ቁልፍ ውሳኔ በአገር ውስጥ ሰላም እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በሕዝቡ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር እንዲቋቋም ተወስኗል።

    ከትምህርት ሚንስቴር ሁሉንም ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን በመውሰድ እንዲሁም ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ስር የሚገኙት ሁለቱን ዩኒቨርሲቲዎች በመጨመር “የከፍተኛ ትምህርትና የሳይንስ ሚንስቴር” ተብሎ እንዲደራጅ ተወስኗል።

    በተጨማሪም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የገቢዎች ሚኒስቴር እና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ የሆነ የጉምሩክ ኮሚሽን በመሆን ሁለት ተቋማት ሆነው እንዲደራጁ ተወስኗል።

    በአዲሱ አደረጃጀት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሚንስቴር ቀርቶ በቀጣይነት የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ለማስተዳደር መሠረታዊ ሚናቸው ንግድ የሆኑትን በመለየት የመንግስትን የባለቤትነት ሚና በተገቢው ሁኔታ የሚያስተዳደር “የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ” በገንዘብ ሚኒስቴር ሥር እንዲቋቋም ተወስኗል። ይህም የመንግሥት ቁልፍ ሚና የሆነው ቁጥጥር (regulation) በልማት ድርጅቶች ላይ ካለው የባለቤትነት ሚና ተለይቶ እንዲታይ እንደሚያግዝ ታምኖበታል።

    ረቂቅ አዋጁ ሌሎች መለስትኛ ለውጦችንም የያዘ ሲሆን፥ በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍጹም አረጋ የፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የሰላም ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ መመረቅ ስኳር የሚያመርቱትን ፋብሪካዎች ቁጥር ወደ ስምንት (ወንጂ ሸዋ፣ መተሐራ፣ ፊንጫአ፣ ከሰም፣ ተንዳሆ፣ አርጆ ዲዴሳ፣ ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 እና 3) ያደርሰዋል።

    ኩራዝ ከተማ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ – የኦሞ ወንዝን በሚያዋስኑ በካፋና ቤንች ማጂ ዞኖች የሚገኘውና የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን ያስገነባው የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በሚገኙበት እሁድ ጥቅምት 4 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 2 ሰዓት ላይ ይመረቃል።

    በኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን ንብረትነት በኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት ስር ከሚገነቡት አራት ስኳር ፋብሪካዎች አንዱ የሆነው ይህ ፋብሪካ የግንባታ ሥራው በይፋ የተጀመረው በመጋቢት ወር መጀመሪያ 2008 ዓ.ም ከቻይና ልማት ባንክ በተገኘ ከ8 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ነው።

    ዋና መቀመጫውን ሃናን ክልል ከተማ ባደረገው ጄንግጆ ከተማ ባደረገው ቻይና ኮምፕላንት ግሩፕ በተባለ የቻይና ኩባንያ የተገነባው ይህ ፋብሪካ በቀን ከ8 ሺህ አስከ 10 ሺህ ኩንታል ስኳር የማምረት አቅም ያለው ግዙፍ ፕሮጀክት ነው።

    ፋብሪካው እጅግ ዘመናዊ ከመሆኑ አንጻር የዓለም ገበያ ፍላጎትን መሠረት በማድረግ ጥሬ ስኳር (raw sugar)፣ ነጭ ስኳር (plantation white sugar) እና የተጣራ ስኳር (refined sugar) ማምረት ይችላል።

    ለአራቱም ስኳር ፋብሪካዎች በ100 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ሸንኮራ አገዳ ለማልማት በኦሞ ወንዝ ላይ የመስኖ መሠረተ ልማት ግንባታ እየተካሄደ ይገኛል። በአጠቃላይ እስካሁን 30 ሺህ ሄክታር መሬት ውሃ ገብ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 16 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ሸንኮራ አገዳ ተተክሏል።

    ሰሞነኛ ዜና፦ በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ የተገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ተመረቀ፤ በዚህም ወደሥራ የገቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ቁጥር አምስት ደርሷል

    የሰው ኃይልን በተመለከተ፥ የኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት ከተቋቋመ ከ2003 ዓ.ም አንስቶ በፕሮጀክቱ፣ በኮንትራክተሮች እንዲሁም በጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት በቋሚ፣ በኮንትራትና ጊዜያዊነት ከ110 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ዜጎች የሥራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ከ300 በላይ የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማትን አደራጅቶ ወደ ሥራ ለማስገባት ተችሏል።

    በኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት እየተገነቡ ከሚገኙ አራት የስኳር ፋብሪካዎች ውስጥ የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 ስኳር ፋብሪካ ከመጋቢት 14 ቀን 2009 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል።

    የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ መመረቅ ስኳር የሚያመርቱትን ፋብሪካዎች ቁጥር ወደ ስምንት (ወንጂ ሸዋ፣ መተሐራ፣ ፊንጫአ፣ ከሰም፣ ተንዳሆ፣ አርጆ ዲዴሳ፣ ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 እና 3) ያደርሰዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን

    የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ

    Semonegna
    Keymaster

    የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ መመረቅ ስኳር የሚያመርቱትን ፋብሪካዎች ቁጥር ወደ ስምንት (ወንጂ ሸዋ፣ መተሐራ፣ ፊንጫአ፣ ከሰም፣ ተንዳሆ፣ አርጆ ዲዴሳ፣ ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 እና 3) ያደርሰዋል።

    ኩራዝ ከተማ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ – የኦሞ ወንዝን በሚያዋስኑ በካፋና ቤንች ማጂ ዞኖች የሚገኘውና የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን ያስገነባው የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በሚገኙበት እሁድ ጥቅምት 4 ቀን 2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 2 ሰዓት ላይ ይመረቃል።

    በኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን ንብረትነት በኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት ስር ከሚገነቡት አራት ስኳር ፋብሪካዎች አንዱ የሆነው ይህ ፋብሪካ የግንባታ ሥራው በይፋ የተጀመረው በመጋቢት ወር መጀመሪያ 2008 ዓ.ም ከቻይና ልማት ባንክ በተገኘ ከ8 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ነው።

    ዋና መቀመጫውን ሃናን ክልል ከተማ ባደረገው ጄንግጆ ከተማ ባደረገው ቻይና ኮምፕላንት ግሩፕ በተባለ የቻይና ኩባንያ የተገነባው ይህ ፋብሪካ በቀን ከ8 ሺህ አስከ 10 ሺህ ኩንታል ስኳር የማምረት አቅም ያለው ግዙፍ ፕሮጀክት ነው።

    ፋብሪካው እጅግ ዘመናዊ ከመሆኑ አንጻር የዓለም ገበያ ፍላጎትን መሠረት በማድረግ ጥሬ ስኳር (raw sugar)፣ ነጭ ስኳር (plantation white sugar) እና የተጣራ ስኳር (refined sugar) ማምረት ይችላል።

    ለአራቱም ስኳር ፋብሪካዎች በ100 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ሸንኮራ አገዳ ለማልማት በኦሞ ወንዝ ላይ የመስኖ መሠረተ ልማት ግንባታ እየተካሄደ ይገኛል። በአጠቃላይ እስካሁን 30 ሺህ ሄክታር መሬት ውሃ ገብ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 16 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ሸንኮራ አገዳ ተተክሏል።

    ሰሞነኛ ዜና፦ በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ የተገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ተመረቀ፤ በዚህም ወደሥራ የገቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ቁጥር አምስት ደርሷል

    የሰው ኃይልን በተመለከተ፥ የኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት ከተቋቋመ ከ2003 ዓ.ም አንስቶ በፕሮጀክቱ፣ በኮንትራክተሮች እንዲሁም በጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት በቋሚ፣ በኮንትራትና ጊዜያዊነት ከ110 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ዜጎች የሥራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ከ300 በላይ የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማትን አደራጅቶ ወደ ሥራ ለማስገባት ተችሏል።

    በኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት እየተገነቡ ከሚገኙ አራት የስኳር ፋብሪካዎች ውስጥ የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 ስኳር ፋብሪካ ከመጋቢት 14 ቀን 2009 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል።

    የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ መመረቅ ስኳር የሚያመርቱትን ፋብሪካዎች ቁጥር ወደ ስምንት (ወንጂ ሸዋ፣ መተሐራ፣ ፊንጫአ፣ ከሰም፣ ተንዳሆ፣ አርጆ ዲዴሳ፣ ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 እና 3) ያደርሰዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን

    የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ

    Semonegna
    Keymaster

    የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአገር ውስጥ ሰላም እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በሕዝቡ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር እንዲቋቋም ተወስኗል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የሚኒስትሮች ምክር ቤት መስከረም 30 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የፌደራል መንግሥትን አስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በተዘጋጀ ረቀቅ አዋጅ ላይ መክሮ እንዲጸድቅ ለተወካዮች ምክር ቤት እንዲላክ ወስኗል።

    በውይይቱ ላይ የአስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን ያስፈለገበት ዋና ዋና ምክንያቶች እንደሚከተለው ቀርቧል፦

    1. የሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በቀሪው ጊዜ ያልተጠናቀቁ ሥራዎችን አካክሶ ለመፈጸም የሚያስችል አደረጃጀት በማስፈለጉ፤
    2. አገራችን የተያያዘችውን የለውጥ ጉዞ ለማስቀጠልና የማይቀለበስበት ደረጃ ላይ ለማድረስ የሚያስችል አደረጃጀትን መከተል በማስፈለጉ፤
    3. የአስፈጻሚ አካላትን ቁጥር ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢና ውጤታማ ለማድረግ በማስፈለጉ፤
    4. ተደራራቢና ድግግሞሽ ሥልጣንና ተግባር የያዙ የመንግሥት ተቋማትን መቀነስ ወይም ለሥራቸው ቅርብ ከሆነ ሌላ የመንግሥት ተቋም ጋር እንዲዋሃዱ ማድረግ በማስፈለጉ፤

    እንደሆነ በስብሰባው ላይ ተብራርቷል።

    በምክር ቤቱም ውሳኔ የካቢኔ አባላት ቁጥር ከ28 ወደ 20 እንዲቀንስ ተደርጓል፤ ዋና ዋናዎቹ ለውጦችም:-

    • የንግድ ሚኒስቴር እና የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተዋህደው – የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እንዲሆን ፤
    • በየሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተዋህደው – የኢኖቬሽንና የቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሆን ፤
    • የከተማ ልማት ሚኒስቴር እና የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ተዋህደው – የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር እንዲሆን
      ወስኗል።

    ሌሎች ተጠሪ ተቋማትም በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲዋሃዱ ውሳኔ የተሰጠባቸው ይገኛሉ።

    ሌላው ቁልፍ ውሳኔ በአገር ውስጥ ሰላም እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን በሕዝቡ ፈቃድ ላይ የተመሠረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ መገንባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር እንዲቋቋም ተወስኗል።

    ከትምህርት ሚንስቴር ሁሉንም ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን በመውሰድ እንዲሁም ሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ስር የሚገኙት ሁለቱን ዩኒቨርሲቲዎች በመጨመር “የከፍተኛ ትምህርትና የሳይንስ ሚንስቴር” ተብሎ እንዲደራጅ ተወስኗል።

    በተጨማሪም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የገቢዎች ሚኒስቴር እና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ የሆነ የጉምሩክ ኮሚሽን በመሆን ሁለት ተቋማት ሆነው እንዲደራጁ ተወስኗል።

    በአዲሱ አደረጃጀት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሚንስቴር ቀርቶ በቀጣይነት የመንግስት የልማት ድርጅቶችን ለማስተዳደር መሠረታዊ ሚናቸው ንግድ የሆኑትን በመለየት የመንግስትን የባለቤትነት ሚና በተገቢው ሁኔታ የሚያስተዳደር “የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ” በገንዘብ ሚኒስቴር ሥር እንዲቋቋም ተወስኗል። ይህም የመንግሥት ቁልፍ ሚና የሆነው ቁጥጥር (regulation) በልማት ድርጅቶች ላይ ካለው የባለቤትነት ሚና ተለይቶ እንዲታይ እንደሚያግዝ ታምኖበታል።

    ረቂቅ አዋጁ ሌሎች መለስትኛ ለውጦችንም የያዘ ሲሆን፥ በቅርቡ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍጹም አረጋ የፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የሰላም ሚኒስቴር

    Semonegna
    Keymaster

    የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል አገልግሎቶቹን ከማስፋት ባለፈ ለባለሙያዎች በየጊዜው በሚሰጣቸው ሥልጠናዎች ታካሚዎችን በትህትናና እንክብካቤ ለማስተናገድ የሥነልቦና ዝግጁነት እንዲኖራቸው አድርጓል።

    ዲላ (ኢዜአ) – የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ተገልጋዮች የሚያነሷቸውን ቅሬታዎች እንደ ግብዓት በመጠቀም የማሻሻያ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን ገለጸ።

    የሆስፒታሉ የአስተዳደርና ቢዝነስ ልማት ዋና ዳይሬክተር አቶ እንግዳ ኢዮብ እንደገለጹት ሆስፒታሉ ከተገልጋዮች ጋር በሚያዘጋጃቸው መድረኮች የሚነሱ ቅሬታዎችንና ሀሳቦችን እንደ ግብዓት እየተጠቀመባቸው ነው።

    በዚህም ሆስፒታሉ በቅርቡ በአምስት ሚሊዮን ብር ወጪ የገዛቸውን ዘመናዊ የራጅና የላብራቶሪ መሣሪያዎች ተገልጋዮች ወደ ግልና ሌሎች የመንግሥት ህክምና ተቋማት መሄዳቸውን ከማስቀረታቸውም በላይ ታካሚዎችን ከእንግልትና ከተጨማሪ ወጪ አድኗቸዋል። ሆስፒታሉ አሁን የሚሰጣቸውን የምርመራ ዓይነቶች ከ30 ወደ 80 መድረሳቸውንም ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

    በሆስፒታሉ የአጥንት ቀዶ ጥገና፣ የውስጥ ደዌ ህክምና ፣ መድኃኒት የተለማመደ የሳምባ ነቀርሳ በሽታ (Tuberculosis) ህክምና መስጠት ተጀምሯል ብለዋል። ብቃት ያላቸው ስፔሻሊስት ሐኪሞችንና ሌሎች ባለሙያዎችን በመቅጠርም አገልግሎቱን ለማሟላት እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

    የመድኃኒትና የህክምና ግብዓቶች አቅርቦት ከመንግሥት የመድኃኒት አቅራቢ ተቋማት ጋር ውል በመግባት እየተንቀሳቀሰ ቢሆንም፤ በአገር ደረጃ ባለው የመድኃኒት አቅርቦት እጥረት ሳቢያ ፍላጎቱን ለማሟላት እንዳልተቻለ አቶ እንግዳ አመልክተዋል።

    የዲላ ከተማ ነዋሪዎች መድኃኒት በተመጣጣኝ ዋጋ በአቅራቢያው እንዲያገኝ ከከፈተው መድኃኒት መደብር በተጨማሪ ሌሎች መደብሮችን ለመክፈት መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።

    የሆስፒታሉ ባለሙያዎች በህክምና ሥነ ምግባር የተሟላ አገልግሎት ለታካሚዎች እንዲሰጡ ሥልጠና፣ ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግላቸውም ገልጸዋል።

    የሆስፒታሉ ፅዳት አጠባበቅን የሰው ኃይል ከማሟላት ጀምሮ የመፀዳጃ ቤቶች እድሳትና አዳዲስ ግንባታዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል።

    በሆስፒታሉ ተኝተው የቀዶ ህክምና ክትትል እያደረጉ ከሚገኙ ታካሚዎች መካካል የዲላ ከተማ ነዋሪው ወጣት ሲሳይ ጂግሶ ሆስፒታሉ ከዚህ በፊት ይስተዋሉበት የነበሩት ችግሮችን በማቃለል አገልግሎት አሰጣጡን እየተሻሻለ መጥቷል ብሏል። በዚህም ታካሚዎችን በአግባቡ ያለማስተናገድና በቂ ምርመራ ያለማድረግን የመሰሉ ጉድለቶቹ እየታረሙ መጥተዋል።

    የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ከአቻ ሆስፒታሎች እኩል ለመራመድ የመድኃኒት አቅርቦትን ጨምሮ አገልግሎት አሰጣጡን ማሻሻል እንደሚገባውም አስረድቷል።

    ከቡሌ ወረዳ የመጡት ወይዘሮ ምንታምር ዘውዱ በበኩላቸው ከዚህ በፊት እህታቸውን ለማስታመም በሆስፒታሉ አገልግሎት አሰጣጥ መሻሻል አይቻለሁ ብለዋል።

    ከሲዳማ ዞን አለታ ጩኮ ወረዳ አቶ አዲሱ ቡኩላ በበኩላቸው ልጃቸው ሞተር ቢስክሌት በማሽከርከር ላይ እንዳለ ባጋጠመው የአጥንት ስብራት ስላጋጠመው ወደ ሆስፒታሉ ሊያሳክሙት መምጣታቸውን ይናገራሉ። በቂ የህክምና ክትትል እየተደረገለት መሆኑንም ይገልጻሉ።

    ከዚህ በፊት በአካባቢያቸው ተመሳሳይ አደጋ የደረሰባቸው ግለሰቦች ለህክምና ወደ ሀዋሳና ወላይታ ሶዶ ሆስፒታሎች ይሄዱ እንደነበር አውስተው፣ በዚህም ለመጉላላትና ለከፍተኛ ወጪ ይዳረጉ እንደነበር ተናግረዋል።

    በሆስፒታሉ የቀዶ ጥገናና ተኝቶ ህክምና ክፍል ምክትል አስተባባሪ ነርስ እስራኤል ብርሃኑ ሆስፒታሉ ህክምና በጀመረባቸው አዳዲስ አገልግሎቶች የታካሚዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።

    ሆስፒታሉ አገልግሎቶቹን ከማስፋት ባለፈ ለባለሙያዎች በየጊዜው በሚሰጣቸው ሥልጠናዎች ታካሚዎችን በትህትናና እንክብካቤ ለማስተናገድ የሥነልቦና ዝግጁነት እንዲኖራቸው አድርጓል ሲሉም ተናግረዋል።

    የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ከጌዲዮ፣ ከምሥራቅ ጉጂ፣ ከምዕራብ ጉጂና ከቦረና ዞኖች እንዲሁም ከሲዳማ ዞንለሚመጡ ታካሚዎች አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል

    Semonegna
    Keymaster

    የወሎ ዩኒቨርሲቲ የሚጀምረው የግዕዝ ቋንቋ ትምህርት በቋንቋው የተጻፉ ሥራዎችን ወደ ሌሎች አገርኛ ቋንቋዎች በመተርጎም ጥቅም ላይ ለማዋል እንደሚያስችል በዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊና ሥነ ሰብእ ኮሌጅ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ ጽሁፍ ትምህርት ክፍል ተጠሪ ተናግረዋል።

    ደሴ (ኢዜአ) – የወሎ ዩኒቨርሲቲ ከያዝነው የትምህርት ዘመን ጀምሮ የግዕዝ ቋንቋን በመጀመሪያ ዲግሪ ለማስተማር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታወቀ።

    ዩኒቨርሲቲው ትምህርቱን ለመጀመር በቀረጸው ሥርዓተ ትምህርት (curriculum) ዙሪያ ከምሁራንና ባለድርሻ አካላት ጋር መስከረም 29 ቀን 2011 ዓ.ም ተወያይቷል።

    በዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊና ሥነ ሰብእ ኮሌጅ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ ጽሁፍ ትምህርት ክፍል ተጠሪ ዶክተር እንድሪስ አብይ እንዳስረዱት ግዕዝ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የላቀ ሥፍራ አለው።

    ትምህርቱን ለማስጀመር አራት መምህራን የተቀጠሩ ሲሆን፣ እስከ 18 ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት ማድረጉን ገልጸዋል።

    ሥርዓተ ትምህርቱ ጋዜጠኝነትን ጨምሮ አገር በቀል ህክምናና መድኃኒት፣ የሥነ ከዋክብት ቀመርና የቀን አቆጣጠር፣ የባህልና የህግ ሥርዓቶች ተካተውበታል።

    ትምህርቱ በቋንቋው የተጻፉ ሥራዎችን ወደ ሌሎች አገርኛ ቋንቋዎች በመተርጎም ጥቅም ላይ ለማዋል እንደሚያስችል ዶክተር እንድሪስ ተናግረዋል።

    በቋንቋው በፍልስፍና፣ በህክምና፣ በሥነ ከዋክብትና በመሳሰሉት የዕውቀት ዘርፎች በርካታ ጽሁፎች ቢጻፉም፤ ህዝቡንም ሆነ አገሪቱን መጠቀም የሚገባቸውን ያህል አልተጠቀሙበትም። ዕውቀቱም ለሌሎች ሳይተላለፍ ለረጅም ዓመታት መቆየቱን ተጠሪው ገልጸዋል።

    በዩኒቨርሲቲው የታሪክና ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ትምህርት ክፍል አስተባባሪና መምህር አቶ ዘላለም ጌትነት በበኩላቸው የመጥፋት አደጋ ላይ የሚገኘውንና የዕውቀት ምንጭ የሆነውን ቋንቋ በዩኒቨርሲቲ ደረጃ መስጠቱ ታሪክን ከማቆየትና እውቀትን ከማጋራት አንጻር ጠቀሜታው ጉልህ ነው ብለዋል።

    ሥርዓተ ትምህርቱ በተለይ ቋንቋው ከኢትዮጵያ ታሪክ ጋር ያለውን ቁርኝት በሚያሳይ መልኩ ቢቀረጽ የተሻለ እንደሚሆን አመልክተዋል።

    በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቲያትር ጥበባት ትምህርት ክፍል መምህርና የሥነ ጥበባት ኮሌጅ የድህረ ምረቃ ተባባሪ ዲን ረዳት ፕሮፌሰር አሰፋ ወርቁ ”ዩኒቨርሲቲው የአገር ሃብት የሆነውን የግዕዝ ቋንቋ ለማስተማር መወሰኑ የሚያስመሰግነውና ሌሎችም ዩኒቨርሲቲዎች ተመሳሳይ ኃላፊነት እንዲወስዱ መነቃቃትን የሚፈጥርላቸው ነው” ብለዋል።

    ግዕዝ ኢትዮጵያን የምናውቅበት የዕውቀት ምንጭ መሆኑን አስታውሰው፣ ይህንን መገናኛ ብዙኃን አገራዊ ፋይዳ ያለውን የዕውቀት ዘርፍ በማስተዋወቅ ድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

    የወሎ ዩንቨርሲቲም ተማሪዎችን ካስመረቀ በኋላ የሥራ ዕድል እንዲያገኙ ከባለድርሻ አካላት ጋር መምከር እንዳለበትም አቶ አሰፋ አሳስበዋል።

    በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ወሎ አገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ መአምራን ብርሃነሕይወት እውነቱ ቋንቋው በዩኒቨርሲቲው መሰጠቱ በርካታ አገራዊ ታሪኮች፣ ቅርሶች፣ መንፈሳዊና ዓለማዊ ሥራዎች፣ ምርምርን የሚጋብዙ ሥራዎች ለማወቅና ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን በአዲስ መንፈስ ለማስቀጠል ጠቀሜታ እንዳለው አስረድተዋል።
    የአብነት ተማሪዎች እንቅስቃሴ መዳከም ቋንቋውን እንዳዳከመው አውስተው፣ የወሎ ዩንቨርሲቲ የጀመረው ጥረት እንዲሳካ ቤተክርስቲያኗ ድርሻዋን ለመወጣት ዝግጁ መሆኗን አስታውቀዋል።

    ከዚህ ጋር በተያያዘ በ1999 ዓ.ም. የተመሠረተው የወሎ ዩኒቨርሲቲ ዓመታዊ የቅበላ አቅም ዘንድሮ ከ20 ሺህ በላይ ደርሷል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የወሎ ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    ቡሬ ከተማ ውስጥ በአቶ በላይነህ ክንዴ የተቋቋመው የፊቤላ ኢንዳስትሪያል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ስር እየተገነባው ያለው የምግብ ዘይት ፋብሪካ ሥራ ሲጀምር በሀገራችን የሚስተዋለዉን የምግብ ዘይት እጥረት በ60 በመቶ ይቀንሳል።

    አዲስ አበባ – በሀገራችን በህብረተሰቡ የመሰረታዊ እቃዎች የዕለት ፍጆታ ላይ የአቅርቦት እጥረት ይስተዋላል። የምግብ ዘይት አቅርቦት እጥረት በመኖሩ መንግስት ለህብረተሰቡ በየወሩ በኮታ ልክ ያከፋፍላል። ይሁንና ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ይገኛል ሲሉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ቅሬታ ያነሳሉ። በአማራ ክልል በወር ከ23 ሚሊየን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት አቅርቦት ያስፈልገዋል። ክልሉ እያሰራጨ ያለው ግን 7 ነጥብ 7 ሚሊየን ሊትር የምግብ ዘይት እንደሆነ ከአማራ ክልል ንግድ ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

    በቡሬ ከተማ በላይነህ ክንዴ በተሰኙ ባለሀብት ፊቤላ ኢንዱስትሪያል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በሚል ስያሜ የምግብ ዘይትና ሌሎች ምርቶች ማምረቻ ፋብሪካ እየተገነባ ይገኛል። ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦለት ግንባታው የተጀመረው ፋብሪካ የምግብ ዘይት፣ ፕላስቲክ፣ ሳሙና እና የተቀነባበረ ሰሊጥ ያመርታል።

    የፊቤላ ኢንደስትሪያል ኃ/የተ/የግል ማህበር አስተዳደር እና ፋይናንስ ኃላፊ አቶ ጎጃም ዓለሙ እንደተናገሩት በ2006 ዓ.ም የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ወደ ግንባታ ገብቷል። የህንጻ እና መሠረተ ልማት አውታሮች ግንባታ ተጠናቋል። ነገር ግን የዘይት ፋብሪካው የማሽን ተከላ ዘግይቷል። ለዚህም በዋነኝነት እንደምክንያት የሚጠቀሰው ሀገሪቱ ያጋጠማት የውጭ ምንዛሪ እንደሆነ ከዚህ በፊት Mutesi የተሰኘ በአፍሪካ የንግድና ቢዝነስ እንቅስቃሴ ላይ ያተኮረ ሚዲያ ዘግቦ ነብር። አሁን ላይ ግን ማሽኑን ለመትከል ዝግጅቱ ተጠናቋል አቶ ጎጃም እንደገለጹት። በአጭር ጊዜ ውስጥም ወደ ምርት ይገባል ነዉ ያሉት። የፊቤላ ኢንደስትሪ የምግብ ዘይት ማምረት ሥራ ሲጀምር ከ1 ሚሊዮን ሊትር በላይ በቀን የማምረት አቅም ይኖረዋል። በዚህም የአማራ ክልል የዘይት አቅርቦት እጥረትን ከመፍታት አልፎ ከክልሉ ውጭ ላሉ አካባቢዎች ማድረስ ይችላል።

    “የዘይት ፋብሪካው ሥራ ሲጀምር በሀገራችን ያለውን የፋብሪካ ቁጥር ያሳድጋል። በሀገር ደረጃ የሚስተዋለዉን የምግብ ዘይት እጥረት ችግር እስከ 60 በመቶ ይቀንሳል። በየዓመቱ ከ12 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የቅባት እህሎችን በግብዓትነት ስለሚጠቀም ለአርሶ አደሩ የገበያ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ ያደርጋል” በማለት አቶ ጎጃም ተናግረዋል። ወደ ውጭ ምርቶችን በመላክ የውጭ ምንዛሪ ያስገኛልም ብለዋል።

    የመብራት እና የውሀ አቅርቦት ችግር የምርት ሂደቱ ላይ ከፍተኛ ጫና የሚያሳድር እና ጊዜ የማይሰጥ እንቅፋት፥ ምናልባትም ፋብሪካው ሊያጋጥሙት ከሚችሉት ተግዳሮቶች ዋነኛው መሆኑን ጠቁመዉ የሚመለከታቸው አካላት አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

    Ethiopian millionaire Belayneh Kinde and others awarded for investing in pulses, oilseeds & spices

    የቡሬ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድ፣ ኢንደስትሪ እና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይገርማል ሙሉሰዉ በበኩላቸዉ ፊቤላ ኢንደስትሪያል ኃ/የተ/የግል ማኅበር በሀገር ደረጃ የሚስተዋለዉን የምግብ ዘይት አቅርቦት ችግር ይቀንሳል ብለዋል። ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከማስገኘቱ በላይ ለአርሶ አደሩ የገበያ ትስስር በስፋት እንደሚፈጥርም ተናግረዋል።

    የህንጻ እና የመሠረተ ልማት ግንባታዉ ከ95 በመቶ በላይ መጠናቀቁን ጠቅሰዉ የመብራት እና ውሀ አቅርቦት ችግር ካልገጠመው በተያዘው በጀት ዓመት ፋብሪካው ሥራ ይጀምራል። ይሁን እንጂ የመብራት እና የውሀ ችግሩ ስር የሰደደ እና ከከተማ አስተዳደሩ አቅም በላይ በመሆኑ የፌዴራል መንግስት ትኩረት እንደሚያሻዉ አቶ ይገርማል ነግረውናል።

    ፋብሪካው እስከ 1500 ለሚሆኑ ሰዎች በቋሚነት እና በጊዚያዊነት የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅትን ዋቢ በማድረግ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ዘግቧል።

    አቶ በላይነህ ክንዴ ማን ናቸው?

    • የተወለዱት በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ሰቀላ ወረዳ (ቡሬ አጠገብ) ነው፤
    • የአስራ ሁለተኛ ክፍል ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ስላልመጣላቸው ሁርሳ ወታደራዊ ማሠልጠኛ ገብተው ወታደራዊ ስልጠና ተከታትለዋል፤
    • ነገር ግን በውትድርና ሕይወት ብዙም አልገፉም፤ የደርግ መንግስት ወድቆ የኢህአዴግ መንግስት ስልጣን ሲይዝ የውትድርና ሥራን ትተው እጅግ አናሳ በሆነ ገቢ የቀን ሥራ ላይ ተሰማሩ፤
    • በቀን ሥራ ገፍትው ጥቂት ገንዘብ እንዳጠራቀሙ የማር እና የቅቤ ንግድ ጀመሩ፤
    • በማር እና ቅቤ ንግድ ለአስር ዓመታት ሠርተው ንግዳቸውን በማሳደግ “በላይነህ ክንዴ አስመጪና ላኪ” የሚል ድርጅት መሠረቱ፤
    • ይህንን የአስመጪና ላኪነት ሥራ ከጊዜ ወደጊዜ በካፒታል፣ በሥራ ዘርፍ እና ሠራተኞችን በመቅጠር፣… በአጠቃላይ በሁሉም አቅጣጫዎች በማሳደግ በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ጥቂት ሚሊየነሮች ተርታ ሊሰለፉ ችለዋል (ይህንንም በዓለም ታዋቂው የቢዝነስ መጽሔት ፎርቤስ/Forbes በ2009 ዓ.ም ዘገባው አንስቷቸው ነበር)፤
    • በአሁኑ ወቅት የአቶ በላይነህ ክንዴ አጠቃላይ ሀብት ከሶስት ቢሊየን ብር (ከ111 ሚሊየን ዶላር) በላይ ሲሆን የተሰማሩበት የንግድና ምርት ዘርፍም አስመጪና ላኪነት፣ ትራንስፖት፣ የግንባታ ምርቶች፣ እርሻ እና ፋይናንስ ሲሆኑ ሀገሪቱ ውስጥ ባሉ ግዙፍ አክሲዮን ማኅበራት፥ ለምሳሌ ያህል ጎልደን ባስ ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ ሆቴል፣ አዳማ ራስ ሆቴል፣ ፀሐይ ኢንዱስትሪያል ፣ ኳሊቲ ብረታ ብረት ማምረቻ አክሲዮን ማኅበራት ውስጥ ሁነኛ ድርሻ አላቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና Mutesi

    በላይነህ ክንዴ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ – የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ የመክፈቻ ስነ-ሥርዓት በኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) የተከፈተ ሲሆን፥ ፕሬዝዳንቱ በመክፈቻ ንግግራቸው በምክር ቤቶቹ በበጀት ዓመቱ ለማከናወን የታሰቡ ተግባራትን አንስተዋል።

    በንግግራቸው ካነሷቸው ነጥቦች መካከል ሀገሪቱ በሁለተኛው እድገት እና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ (GTP II) አሳካዋለሁ ያለቻቸውን ዕቅዶች በሀገሪቱ በተከሰተ ግጭት እና አለመረጋጋት ምክንያት ማሳካት አልተቻለም ብለዋል።

    ግጭቶች እና አለመረጋጋቶች በሀገሪቱ ሲከሰቱ ከጅምራቸው እንዲቆሙ የማድረግ ውስንነት እንደነበርም ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ አንስተዋል። ይህ ደግሞ የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ አደጋ ውስጥ ከቶታል። በቀጣይ ህልውናዋን ለማረጋገጥ የሚያስችል ወሳኝ የፖለቲካ ምዕራፍ ተጀምሯል ። በዚህ የለውጥ ሂደት የሕዝቡን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውንም እንቅስቃሴዎች የህግ የበላይነትን በሚያረጋግጥ መልኩ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ቁርጠኛ አቋም ተይዟል ብለዋል።

    ከቅርብ ወራት ጀምሮ በፖለቲካው ዘርፍ የታዩ ለውጦች ለወደፊት የሀገሪቱ የለውጥ ጉዞ ትልቅ ሚና ይጫወታል። በስደት ላይ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር የተደረገው ሰላማዊ ድርድር ትልቅ ለውጥ የታየበት የፖለቲካ እንቅስቃሴ ነበር። እንደ ዶክተር ሙላቱ ገለፃ ለዚህ ፖለቲካዊ መሻሻል ምክር ቤቱ ያፀደቀው የምህረት አዋጅ ትልቁን ሚና ተጫውቷልም ነው ያሉት። የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት በተደረገው ጅምር እንቅስቃሴ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ምሁራን፣ጦማሪ እና አክቲቪስቶች በነፃነት የመሥራት እድል ተፈጥሮላቸዋል።

    ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በተቃርኖ ውስጥ የነበሩት ሁለቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክረስቲያን ሲኖዶሶች ችግር ተፈትቶ ወደ አንድ እንዲመጡ መደረጉም የለውጡ አካል ነበር። ለረጅም ዓመታት አለመግባባት ውስጥ የነበሩት አትዮጵያ እና ኤርትራ መግባባታቸው በቀጠናው የነበረውን የድህነት እና ኋላቀርነት መገለጫ ማጥፋት ችሏል።

    ———————————————-

    ———————————————-

    በደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት በዜጎች ላይ ይደርስ የነበረውን ግፍ ኢትዮጵያ መታደግ ችላለች። ከሌሎች አጎራባች እና የውጭ ሀገራት ጋርም ጥብቅ የሆነ ወዳጅነት እንዲኖራት መደረጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተመለከትነው የፖለቲካ ለውጥ ውጤት ነው ብለዋል ፕሬዝዳንቱ።

    ዶክተር ሙላቱ ተሾመ በመክፈቻ ንግግራቸው የዜጎችን ነፃነት እና መሰረታዊ መብቶች ከማስጠበቅ አንፃር የተሠራው ሥራ ውስን እንደነበር ተናግረዋል።

    በአሁኑ ወቅ የሕዝቡ የዴሞክራሲ እና የፖለቲካ ጥያቄዎች የጎለበተበት በመሆኑ መንግስት የፖለቲካ ማሻሻያ የሚያደርግበት ነው ። የተጀመረውን ለውጥ ለማስቀጠል መንግስት በበጀት ዓመቱ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ ይሠራልም ብለዋል።

    አሁን በሀገሪቱ የተጋረጠው የሰላም መደፍረስ ሕዝቡን አደጋ ውስጥ አስገብቶታል። የህግ የበላይነትም ተጥሷል። ፕሬዝዳንቱ በመክፈቻ ንግግራቸው የዜጎችን በሰላም የመኖር መብት እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር መንግስት አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስድ አሳስበዋል። የመገናኛ ተቋማት በማንኛውም የመገናኛ ዘዴ ሀሳባቸውን በነፃነት የመግለፅ ሁኔታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል።

    ተከስቶ የነበረው ሁከት እና አለመረጋጋት በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ አድርሷል።በስፋት እየታየ ያለውን የኢኮኖሚ አለመረጋጋት ለመቀነስ እና የኢኮኖሚ ምህዳሩን ለማስፋት በዚህ የበጀት ዓመት በተጨባጭ እንደሚሠራም ተናግረዋል። መንግስት የተረጋጋ እና ቀጣይነት ያለው ማክሮ ኢኮኖሚን ለማሳደግ ፅኑ አቋም እንዳለው አንስተዋል። ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የጀመረችው ድርድር በዚህ ዓመት ተጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል ፕሬዝዳንቱ።

    ከመክፈቻ ንግግሩ ለመረዳት እንደተቻለው የምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግስት (ኢጋድ) በማጠናከር እና ወደ ተግባር ገብቶ ቀጠናዊ አገልግሎቱን እንዲያሰፋ ኢትዮጵያ የበኩሏን ድርሻ ትወጣለች።

    ሀገራችን በርካታ አለማቀፍ የስብሰባ መድረክ አገልግሎት እየተካሄደባት በመሆኑ የቪዛ አገልግሎት እንዲሰጥ ይደረጋል። የሚሰጠው የቪዛ አገልግሎት ቀልጣፋ እንዲሆን እየተሠራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አንስተዋል።

    የግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ በቴክኖሎጂ እንዲታገዝ እንዲሁም የመስኖ እርሻን በማጠናከር የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ይሠራል።
    የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ አዲሱን ፍኖተ-ካርታ መሰረት ያደረገ የሥርዓት ትምህርት ማሻሻያ የደረጋል። የሴቶች እና ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በያዝነው በጀት ዓመት የጤና ተቋማት ግንባታ እና ቁሳቁስ አቅርቦት ትኩረት ተሰጥቶት ይሠራል። አሁን የተፈጠረውን ለውጥ ተከትሎ በሥርዓት አልበኞች ምክንያት እየታዩ ያሉ መፈናቀሎችን ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ያስፈልጋል ሲሉ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ በመክፈቻ ንግግራቸው አንስተዋል።

    ምንጭ፦ የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

    ሙላቱ ተሾመ

    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ኢዜአ)፦ መንግሥት በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በአገራቸው ልማት ቀጥተኛ ተሳታፊ እንዲሆኑ እያደረገ ያለውን ሁሉን አቀፍ ጥሪ ከግምት ያስገባ አዲስ አቅጣጫ እየቀየሰ መሆኑን የኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማኅበር አስታወቀ።

    አገሪቱ የጀመረችውን የለውጥ ሥራ ለማገዝ፣ እንደዚሁም በውጭ የሚኖረው ዜጋ በሌሎችም አገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሳታፊ እንዲሆን ለማስቻል ማህበሩ አደረጃጀቱን መልሶ በማዋቀር ላይ ነው ተብሏል።

    በሽርክና ወይንም በሌላ መንገድ በመደራጀት በአገሪቱ የልማት እድገት ውስጥ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ ዝግጁ መሆናቸውን ኢትዮጵያዊያን የዲያስፖራ አባላት ገልፀዋል።

    በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መዋዕለ ንዋያቸውን በማቀናጀት አገር ውስጥ መሥራት የሚሹ ከሆነ መንግሥት የተለየ ድጋፍ እንደሚያደርግ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) አረጋግጠዋል።

    ጠቅላይ ሚኒስትሩ መስከረም 27 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዳማ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የምርቃት ስነ-ስርዓት ላይ ባስተለላፉት መልዕክት፤ በውጭ የመኖሩ ኢትዮጵያዊያን በአገሪቱ ልማት ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።

    በተለይም በስቶክ ማርኬት ወይንም በአክሲዮን ንግድ ዘርፍ የተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራ አባላት በተናጠልም ሆነ በመደራጀት ወደ አገራቸው ተመልሰው በልማት እንዲሰመሩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠይቀዋል።

    ያላቸውን እውቀትና ገንዘብ በማደራጀት መቅረብ ለሚችሉ የዲያስፖራ አባላት መንግሥት የተለየ ድጋፍ እንደሚያቀርብ ነው ዶ/ር አብይ ያረጋገጡት።

    ቪድዮ፦ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎች ሀገር ውስጥ ለመሥራት ያላቸው ፍላጎት እና የሚያጋጥማቸው የቢሮክራሲ ችግር

    ኢትዮጵያዊያኑ ዲያስፖራዎች በበኩላቸው መንግሥት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እያደረገ ያለውን ጥሪ በአዎንታዊ መልኩ እንደሚመለከቱት ገልጸዋል።

    በዚህም በተለይም በሽርክና ወይንም በሌላ መንገድ በመደራጀት በአገሪቱ የልማት እድገት ውስጥ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

    በተደራጀ አግባብ ከጓደኞቻቸው ጋር ተነጋግረው ትልቅ ካምፓኒ ይዘው ለመምጣት ሃሳብ እንዳላቸው የተናገሩት በውጭ የሚኖሩት ወይዘሮ አማኒ መሃመድ ናቸው።

    “የሥራ ሁኔታ እየተመቻቸ ነው፤ ሁሉም ሰው እውቀቱንና ገንዘቡን ኢንቨስት በማድረግ የአገሪቱን እድገት ለማረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ መልካም ነው። እኔም እንደ አንድ ውጭ አገር እንደሚኖር ዜጋ ወደ ሃገሬ መጥቼ ለመሥራት ትልቅ እቅድ ይዤ እንደምመጣ ተስፋ አደርጋለሁ” ያሉት ደግሞ አቶ አማን አህመድ ናቸው።

    የኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማኅበር ዳይሬክተር አቶ አብርሃም ስዩም በበኩላቸው ማኅበራቸው ከሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት ጋር በመሆን የዲያስፖራውን የልማት ተሳትፎ ለማሳደግ እየሠራ ነው።

    በተለይ ደግሞ በኢንደዱትሪ ፓርኮች ላይ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ሊኖራቸው የሚችለውን ተሳትፎ ለማጎልበት ፓርኮቹን የሚጎበኙበት ሁኔታ እየተመቻቸ መሆኑን ተናግረዋል።

    ይህም ዲያስፖራው ስለ ፓርኮቹ በቂ መረጃ እንዲኖረው ትልቅ እድል እንደሚከፍት ገልጸው ማኅበሩ መረጃ ከመስጠቱ ሥራ ጎን ለጎን ሌሎች የውጭ ዜጎችም በዘርፉ እንዲሰማሩ የበኩሉን ጥረት ያደርጋል ብለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማኅበር

    Semonegna
    Keymaster

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያስገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የግንባታ ሥራው የተጀመረው በጥቅምት ወር 2009 ዓ.ም ሲሆን የቻይናው ግዙፍ ኩባንያ ቻይና ሲቪል እንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ግንባታውን ሲያከናውን ነበር።

    አዳማ (Semonegna) – በኦሮሚያ ክልል፣ አዳማ ከተማ የተገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በዛሬው ዕለት (መስከረም 27 ቀን 2011 ዓ.ም.) ተመርቋል። በምርቃቱ ስነ ስርዓት ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) እና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ለማ መገርሳ፣ የአማራ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ የእንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አርከበ ዕቁባይ እና የኮርፖሬሽኑዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ት ሌሊሴ ነሜ እንዲሁም ሌሎች የክልልና የፌደራል ባለስልጣናት ከፍተኛ ተገኝተዋል።

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያስገነባው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የግንባታ ሥራው የተጀመረው በጥቅምት ወር 2009 ዓ.ም ሲሆን የቻይናው ግዙፍ ኩባንያ ቻይና ሲቪል እንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን (China Civil Engineering Construction Corporation/ CCCC) ግንባታውን ሲያከናውን ነበር።

    ከአዲስ አበበ ከተማ 99 ኪሎ ሜትሮች ርቆ የሚገኘው የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተለያየ ዘርፍ ለሚሰማሩ አምራች ኩባንያዎች የሚያገለግሉ በአጠቃላይ 19 (በዝርዝር፦ ስድስት 11 ሺህ ካሬ ሜትር፣ ዘጠኝ 5 ሺህ 500 ካሬ ሜትር፣ አራቱ ደግሞ በ3 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፉ) የመሥሪያ ጠለላዎች ወይም የመሥሪያ ቦታዎችን (shades) የያዘ ነው። የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በአጠቃላይ ሊለማ ከታቀደው 2 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ በመጀመሪያው ዙር ልማት 354 ሄክታር መሬት የሚይዝ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ለምቶ ለዛሬ ምረቃ የበቃው በ100 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባው ክፍል መሆኑን፣ ይህም ግንባታ 4.1 ቢልዮን ብር መፍጀቱን፣ እንዲሁም ፓርኩ በመጀመሪያው ምዕራፍ በሙሉ አቅም ወደ ምርት ሲገባ እስከ 25 ሺህ ለሚደርሱ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ወ/ት ሌሊሴ ነሜ በምረቃው ንግግራቸው ላይ አስታውቀዋል።

    ◌ RELATED: A visit to Hawassa Industrial Park by Dire Dawa Industrial Park & City’s Administration people

    የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ሥራ መጀመር በሀገሪቱ ወደማምረት የገቡ የኢንዱስትሪ ፓርክኮች ቁጥር ወደ አምስት የሚያሳድገው ሲሆን፥ ከሌሎቹ አራቱ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለየት የሚያደርገው ፓርኩ ያለበት ከተማ (አዳማ) በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ አስተዋጽዖ ያመጣል ተብሎ የታመነበተና አምና ሥራ የጀመረው የአዲስ አበባ-ጅቡቲ የባቡር መስመር በሚያልፍባት የአዳማ ከተማ መገኘቱ ነው። ይህ የባቡር መስመርና የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ እርስ በርሳቸው ጉልህ የሆነ የጥቅም ግንኙነት ይኖራቸዋል ተብሎ ይታመናል። ከዚህ በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ፓሩኩ በከተማ ከሚገኘው የአዳማ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ጋር በማምረት ዘርፍ እና በመማር፣ ማስተማርና ምርምር ዘርፎች መካከል ቁልፍ የሆነ ግንኙነት ይፈጥራሉ ይጠበቃል።

    የሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ ሴክተር (manufacturing sector) ከኢትዮጵያ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) መጠን አራት ነጥብ አምስት በመቶ (4.5%) ድርሻ ብቻ የሚሸፍን ሲሆን፥ መንግስት እስከ 2022 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) ይህን አናሳ ድርሻ ወደ ሀያሁለት በመቶ (22%) ለማሳደግ አቅዳለች። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያ እስከ 2025 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) አሁን ያሏትን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ቁጥር ከአምስት ወደ ሀያ አምስት የማሳደግ ዕቅድ አላት። በያዝነው ዓመት ስድስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች (ድሬ ዳዋ፣ ቂሊንጦ II፣ ቦሌ ለሚ II፣ ጅማ፣ ባህር ዳር እና ደብረ ብርሃን) ግንባታቸው ተጠናቆ ወደምርት ተግባር እንደሚገቡ ዶክተር አርከበ ዕቁባይ አስታውቀዋል። 

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ

    Semonegna
    Keymaster

    የማህፀን ጫፍ ካንሰር በሽታን በዘላቂነት ለመከላከል የማህፀን ጫፍ ካንሰር ክትባትን ከዘጠኝ እስከ 14 ዓመት የዕድሜ ክልል ለሚገኙ ልጃገረዶች እንዲሰጥ መንግስት መወሰኑን የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ተወካይ አመልክተዋል።

    ባህር ዳር (ኢዜአ)፦ ከ450 ሺህ ለሚበልጡ ልጃገረዶች የማህፀን ጫፍ ካንሰር (cervical caner) መከላከያ ክትባት በዘመቻ ለመስጠት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የአማራ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።

    በቢሮው የጤና ማበልፀግ ዋና የስራ ሂደት መሪ አቶ መልሰው ጫንያለው ለኢዜአ እንደገለጹት የማህፀን ጫፍ ካንሰር በሽታ እንደሀገርም ሆነ እንደክልል ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ ይገኛል።

    ዜጎችን እየጎዳ ያለው ይህንን በሽታ ለመከላከል በክልሉ የተመረጡ 25 ጤና ተቋማት ችግሩን እየለዩ ህክምና እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

    ምርመራ ከሚያደርጉ እናቶች መካከልም 30 በመቶ የሚሆኑት የበሽታው ተጠቂዎች ሆነው መገኘታቸውን የምርመራ ውጤቱ አረጋግጧል።

    በሽታውን በዘላቂነት ለመከላከልም የማህፀን ጫፍ ካንሰር ክትባትን ከዘጠኝ እስከ 14 ዓመት የዕድሜ ክልል ለሚገኙ ልጃገረዶች እንዲሰጥ መንግስት መወሰኑን አመልክተዋል።

    በቀጣዩ ወር በሚጀምረው ዘመቻም በክልሉም ዕድሜያቸው 14 ዓመት የሞላቸው ከ450 ሺህ በላይ ልጃገረዶች የክትባቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑም ተለይተዋል።

    ክትባቱን የተሳካ ለማድረግ ለጤና ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት ቢሮው ስልጠና መስጠት መጀመሩን የስራ ሂደቱ መሪ ጠቁመዋል።

    “አዲስ የሚጀመረው የክትባት ዘመቻም ስለሚያስገኘው ጠቀሜታ በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ መሰጠት ተጀምሯል” ብለዋል።

    በክልሉ በመጪው ጥቅምት ወር በትምህርት ቤቶች፣ በጤና ተቋማትና አማካኝ በሆኑ ቦታዎች ለሚሰጠው የክትባት ዘመቻ ከአንድ ሺህ በላይ የክትባት መስጫ ጣቢያዎች መዘጋጀታቸውን የገለጹት ደግሞ የጤና ቢሮው የክትባት ፕሮግራም የቴክኒክ አማካሪ አቶ ሙሉጌታ አድማሱ ናቸው።

    RELATED: HEALTH: Breast Cancer Replaces Cervical Cancer as Top Women Illness in Ethiopia

    ክትባቱን በመጀመሪያው ዙር የሚወስዱ ልጃገረዶች ከስድስት ወር በኋላ ክትባቱን ዳግም እንዲወስዱ እንደሚደረግም ተናግረዋል።

    የማህፀን ጫፍ ካንሰር መንስኤው “ሂውማን ፓፒሎማቫይረስ” (Human papillomavirus) በሚባል ኢንፌክሽን የሚመጣ መሆኑን ጠቁመው እናቶች በበሽታው ሲያዙም ሳያውቁት እስከ 20 ዓመታት ሊቆዩ እንደሚችሉ አስረድተዋል።

    ለበሽታው ከሚያጋልጡት ምክንያቶች ውስጥ ልጃገረዶች በለጋነት እድሜያቸው የግብረ ስጋ ግንኙነት መጀመርና ከተለያዩ ሰዎች ጋር ፆታዊ ግንኙነት ማድረግ ተጠቅሰዋል።

    ወደ ህክምና ተቋማት መጥተው ምርመራ በማድረግ ራሳቸውን ከበሽታው መጠበቅ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

    በሚሰጠው የክትባት ዘመቻም ከአምስት ሺህ በላይ የጤና ባለሙያዎችና ድጋፍ ሰጪ አካላት እንደሚሳተፉም ታውቋል።

    HPV Information Centre የሚባለው ድርጅት እ.ኤ.አ በሀምሌ ወር በ2017 ዓ.ም ባወጣው ሪፖርት ኢትዮጵያ ውስጥ በየ ዓመቱ 7,095 ሴቶች ማህፀን ጫፍ ካንሰር የሚጠቁ ሲሆን፣ በየዓመቱም 4,732 ሴቶች በዚሁ ካንሰር ምክንያት ለሞት እንደሚዳረጉ ዘግቧል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    የማህፀን ጫፍ ካንሰር

    Semonegna
    Keymaster

    የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባን ይፋ ከማድረጉ በፊት ኤጀንሲው የተለያዩ የማጣራት ሥራዎችን በማከናወን ሂደት ውስጥ በመቆየቱ ምክንያት ምደባው ዘገየ በማለት ቅሬታችሁን ስታሰሙ ለነበራችሁ ተማሪዎች እና የተማሪ ቤተሰቦች ከወዲሁ ይቅርታ የጠየቀ ሲሆን ተማሪዎች በተመደባችሁባቸው የትምህርት ተቋማት በምትሄዱበት ወቅት የነገዋ ኢትዮጵያ በእናንተ ትከሻ ላይ መሆኗን በመገንዘብ በትምህርታችሁ ላይ ብቻ ትኩረት በመስጠት ውጤታማ በመሆን ለሀገራችን እድገት እና ልማት የበኩላችሁን አስተዋጽዖ ታበረክቱ ዘንድ ኤጀንሲው ከአደራ ጋር መልዕክቱን አስተላልፏል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ/NEAEA)– የመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ይፋ መሆኑን የሀገር አቀፍ የትምህርት ፈተናና ምዘናዎች ኤጀንሲ (NEAEA) አስታወቀ።

    የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ አርዓያ ገብረእግዝአብሔር ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቁት፤ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ ከዛሬ ከመስከረም 25 ቀን 2011 ዓም ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ይፋ ሆኗል።

    ምደባው የተማሪዎችን ውጤት፣ የትምህርት ዓይነት፣ የዩንቨርስቲ ምርጫ፣ የዩንቨርስቲዎችን የቅበላ አቅም፣ የወንዶችና የሴቶችን ምጠና ማዕከል ባደረገ እንዲሁም የልዩ ድጋፍ ተጠቃሚዎችን ያገናዘበ መሆኑን ነው ያመላከቱት።

    ዓይነ ስውራንን፣ መስማት የተሳናቸውን፣ አካል ጉዳተኞችን/ በተጨማሪም የጤና እክል ያለባቸው እና ከታወቀ የመንግስት ሆስፒታል የሜዲካል ቦርድ ማረጋገጫ ያቀረቡት ላይ የማጣራት ሥራዎችን ካካሄደ በኋላ ምደባው እንደተዘጋጀም እንዲሁ አስታውቀዋል።።

    በዚሁ መሰረት በዘንድሮው የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና የማለፊያ ነጥቡን ያለፉ 138 ሺ 283 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ሲሆኑ 75ሺ 338 የማህበራዊ ሳይንስ በድምሩ 213 ሺ 621 ናቸው።

    ከነዚህም መካከል 98 ሺ 576 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችና 51 ሺ 229 የማህበራዊ ሳይንስ በድምሩ 149 ሺ 805 ተማሪዎች ቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ ባሉት የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ በአጠቃላይ የሚመደቡ ይሆናል።

    ◌ RELATED: 35 Best Universities and Colleges Ethiopia (public and private)

    ከነዚህም በኤጀንሲው በኩል በ43ቱ የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት 95 ሺ 681 የተፈጥሮ ሳይንስ (natural science) እንዲሁም 51ሺ 066 የማህበራዊ ሳይንስ (social science) በድምሩ 146 ሺ 747 ተማሪዎች መመደባቸውን አስታውቀዋል።

    ተማሪዎች ወደ ተመደቡበት የትምህርት ተቋማት በሚሄዱበት ወቅትም የነገዋ ኢትዮጵያ በትከሻቸው ላይ መሆኗን በመገንዘብ ለትምህርታችሁ ትኩረት እንዲሰጡም አቶ አርአያ አሳስበዋል።

    ከግንቦት 27-30 ቀን 2010 ዓ.ም በተሰጠው የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና (የ12ኛ ክፍል ፈተና) 154,010 ወንዶች እንዲሁም 127,964 ሴቶች በድምሩ 281,974 ተማሪዎች የወሰዱ ሲሆን በሐምሌ 24 ቀን 2010 ዓ.ም ውጤት ይፋ መደረጉ ይታወሳል።

    ተማሪዎች ምደባችሁን በኤጀንሲው ድረ-ገጽ app.neaea.gov.et በመግባት ማየት እንደሚችሉም ነው የገለፁት።

    ምንጮች፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እና የሀገር አቀፍ የትምህርት ፈተናና ምዘናዎች ኤጀንሲ (NEAEA)

    የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት

    Semonegna
    Keymaster

    “በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልና በአጎራባች አካባቢዎች እየደረሰ ያለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በአስቸኳይ ይቁም! ለብሔር ተኮር ጥቃቶች እና ግጭቶች ሕጋዊና ፖለቲካዊ መፍትሔ ይሰጣቸው!!” የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ)

    የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ) ከዚህ ቀደም በቤኒሻንጉል ጉሙዝና ኦሮሚያ ክልል አጎራባች አካባቢዎች ብሔርን መሰረት ያደረጉ ግጭቶች ያስከተሉትን ከፍተኛ የሆነ የሕይወትና የንብረት ውድመት በአካባቢው በመገኘት በባለሙያዎቹ አማካኝነት በማጣራት የደረሠውን የጉዳት መጠን እና ሊወሰዱ የሚገባቸውን እርምጃዎች ይፋ አድርጓል። ለትውስታ ያህል ሐምሌ 10 ቀን 2000 ዓ.ም የሰብዓዊ መብቶች ሁኔታ በኢትዮጵያ በሚል ርዕስ ባወጣው 31ኛ መደበኛ መግለጫ በጉሙዝና ኦሮሞ ብሔረሠብ ዜጐች መካከል በ 09/09/2000 ዓ.ም በተፈጠረ ግጭት 99 (ዘጠና ዘጠኝ) ሰዎች መገደላቸውን፣ በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውን፣ 108 የሚሆኑ መኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸውን፣ እንዲሁም ከ27‚000 (ሀያ ሰባት ሺ) በላይ ህዝብ መፈናቀሉን በማስረጃ አስደግፎ ይፋ ማድረጉ ይታውሳል። በመግለጫውም መንግስት በአስቸኳይ ዘላቂና የማያዳግም መፍትሄ እንዲሰጥ ቢያቀርብም መንግስት ለሰመጉ ጥሪ ትኩረት ባለመስጠቱ ዛሬም ብሔርን መሰረት ያደረገ ጥቃትና ግጭት ሊፈፀም ችሏል።

    መስከረም 16 ቀን 2011 ዓ.ም የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከማሽ ዞን አመራሮች ከምዕራብ ኦሮሚያ አስተዳደር ጥምር ኮሚቴ ጋር የነበራቸውን ስብሰባ አጠናቀው ሲመለሱ ከማሺ ወረዳ ላይ ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች በተሰነዘረባቸው ጥቃት አራት አመራሮች በመገደላቸው ለግጭቱ መቀስቀስ ምክንያት ሆኗል። ግድያውን ተከትሎም በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ከማሽ ዞን በሎይ ጅጋንፎ ወረዳ ዳለቻ እና ታንኮና በተባሉ ቀበሌዎች ችግሩ በዋናነት ተፈጥሯል። ሰመጉ እስካሁን ባሰባሰበው መረጃ መሠረት ከጥቃቱ ጋር በተያያዘ ከ 90,000 (ከዘጠና ሺ) በላይ ዜጐች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ወደ አጎራባች አካባቢዎች ተፈናቅለዋል፣ ከ200 በላይ ቤቶች ተቃጥለዋል፣ ከ74 በላይ ክቡር የሰው ሕይወት ጠፍቷል። እንዲሁም በበርካቶች ላይ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል በርካታ ሰዎችም የደረሱበት ያልታወቀ ሲሆን በርካታ ቁስለኞችም በነቀምቴ ሆስፒታል በመታከም ላይ ይገኛሉ። መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሟቾቹ ውስጥ በርካታ የፀጥታ ሀይሎችም ይገኙበታል።

    ግድያና ማቁሰል

    • ከሀገሎ ሜጢና አካባቢው ሸሽተው በምዕራብ ወለጋ ነጆ ከተማ ውስጥ ተጠልለው የሚገኙ ተፈናቃዮች እንደገለፁት በቤኒሻንጉል ክልል አንገር ሜጢ ከተማ ውስጥ 13 ሰዎች ተገድለዋል፤ ከእነዚህም ውስጥ ሁኔታውን ለማረጋጋት ሲጥሩ የነበሩ 3 አድማ በታኝ ፖሊሶችና 2 ሴቶች ይገኙበታል፤
    • ከከማሼና አካባቢው ተፈናቅለው በምዕራብ ወለጋ ቢላ ከተማ ውስጥ የተጠለሉ ተፈናቃዮች እንደገለፁት በከማሼና አካባቢው 31 ሰዎች ተገድለዋል፤ ከእነዚህም ውስጥ 4 ሴቶችና 3 ፖሊሶች ይገኙበታል፤
    • ከሶጌ፣ በሎ አካባቢዎች ተፈናቅለው በምስራቅ ወለጋ ውስጥ ተጠልለው የሚገኙ ተፈናቃዮች እንደገለፁት በሶጌ፣ በሎና አካባቢው ውስጥ 30 ሰዎች መገደላቸውንና ከዚህም ውስጥ 13 ፖሊሶች ይገኙበታል፤
    • የቆሰሉ ሰዎችን በሚመለከት ቁጥራቸው በርካታ የሆኑት በነቀምቴ ሆስፒታል፣ በወለጋ ዩኒቨርስቲ ሪፈራል ሆስፒታልና በተለያዩ የግል ሆስፒታሎችና ክሊኒኮች ውስጥ እየታከሙ እንደሚገኙ ለሰመጉ በአካባቢው የሚገኙ ታማኝ ምንጮች አስረድተዋል።

    የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ በቅርብ ግዜ ውስጥ ከላይ የተጠቀሱትን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችና በእስካሁኑ የመረጃ አሰባሰብ ያልተደረሰባቸውን በሁለቱም ወገኖች መካከል የደረሰውን ሰብዓዊና ኢኮኖሚያዊ ውድመት እንዲሁም የችግሩን መነሻ ምክንያቶች በስፋትና በጥልቀት በመመርመር በመግለጫ ይፋ እንደሚያደርግ ከወዲሁ ይገልፃል።

    ማፈናቀል

    በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ነዋሪ የነበሩ ዜጐች በግጭቱ ምክንያት የመኖሪያ አካባቢያቸውን በመልቀቅ በምስራቅ ወለጋ በ13 ጣቢያዎች በዲጋ ወረዳ አርጆ ጉደቱ፣ ላሲጋ፣ ጊዳ ኪረሙ፣ ጊቶ ጊዳ፣ በተለያዩ ቦታዎች፣ በነቀምት ከተማ ወለጋ ዩኒቨርስቲ፣ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ፣ የነርሶች ማሰልጠኛ፣ 05 ቀበሌ፣ 07 ቀበሌ፣ ዳርጌ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት፣ ዳንዲቦሩ ኮሌጅ፣ በ 9 መጠለያ ቦታዎች፤ እንዲሁም በምዕራብ ወለጋ ነጆ ወረዳ አስተዳደር አዳራሽ ነጆ ደር መጂ ወረዳ ቢላ ከተማ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተጠልለው ይገኛሉ። በአጠቃላይ ከቤኒሻንጉል ክልል ተፈናቅለው በምዕራብና ምስራቅ ወለጋ ተጠልለው የሚገኙ ተፈናቃዮችም ከ90,000 በላይ እንደደረሰ ሰመጉ ከአካባቢዎቹ ያሰባሰባቸው መረጃዎች ያሳያሉ። ሰመጉ ከአካባቢው ያሰባሰባቸው መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ግጭቱ አሁንም ያልቆመ ሲሆን በርካታ ተፈናቃዮች በየጫካው ተበትነው ይገኛሉ፤ የተጠፋፉ ቤተሠቦችንም ማገናኘት አልተቻለም። የምስራቅ ወለጋ ዞን አስተዳደር ባሁኑ ሰዓት የተፈናቃዮች ቁጥር ከአቅማቸውና ከቁጥጥራቸው በላይ በመሆኑ የሁሉም አካላት እርብርብ እንደሚያስፈልግ ለሰመጉ ገልፀዋል። በዚህ አጋጣሚም መንግስት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ለተጎጂዎችም የምግብ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የአልባሳትና የመድሀኒት አቅርቦት በአስቸኳይ እንዲያቀርብ ሰመጉ ይጠይቃል።

    ብሔርን መነሻ ባደረጉ ጥቃቶች እና ግጭቶች ምክንያት ባለፉት አምስት ወራት ብቻ በተለያዩ ክልሎች ከሁለት ሚሊዮን በላይ ዜጐች ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተገድለዋል፤ በርካቶች ቆስለዋል። ከዚህም በላይ ዜጐች በገዛ ሐገራቸው በሰላም ወጥቶ የመግባት ዋስትናቸው ጥያቄ ውስጥ ወድቋል። መንግስት የዜጐችን በሕይወት የመኖር፣ በሐገሪቱ በፈለጉበት አካባቢ ተንቀሳቅሶ ኑሮን የመመስረትና ንብረት የማፍራት ሕገመንግስታዊ መብቶች እንዲጠብቅ እና እንዲያስከብር ሰመጉ ጥሪውን በድጋሚ ያቀርባል። በተጨማሪም መንግስት በሐገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች እየተፈፀሙ ላሉት ጥቃቶች እና ግጭቶች ተገቢዉን ትኩረት በመስጠት እየተባባሰ የመጣውን ችግር በዘላቂነት ለመቆጣጠር ሕብረተሰቡን እና የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎችን ያማከለ፣ ዘላቂ፣ ሕጋዊ እና ፖለቲካዊ መፍትሔ እንዲወስድ የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ) ያሳስባል።

    የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ) ድረ ገጽ እዚህ ጋር ያገኙታል።

    የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ) መግለጫ

    Semonegna
    Keymaster

    እንግሊዝ ለኢትዮጵያ ትምህርት ጥራት ያደረገችው ድጋፍ አንድ ሚልዮን የሚጠጉ ተማሪዎችንና 120,000 አስተማሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የእንግሊዟ ተወካይ ሚስስ ሃርየት ባልድዊን አስታውቀዋል።

    አዲስ አበባ (ኢዜአ)–እንግሊዝ ለኢትዮጵያ አጠቃላይ ትምህርት ጥራትና ኢንቨስትመንት መሰረተ ልማት የሚውል 6 ነጥብ 31 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ለመስጠት ተስማማች።

    ስምምነቱ በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አድማሱ ነበበ እና በአፍሪካ የእንግሊዝ ሚኒስትር ዲኤታ (Minister of State at the Foreign Office) ሚስስ ሃርየት ባልድዊን (Harriett Baldwin) መካከል መስከረም 25 ቀን 2011 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተፈርሟል።

    ኢትዮጵያ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል እያከናወነች ያለውን ተግባር የሚያግዝና ለኢንቨስትመንት መሰረተ ልማትና አቅም ግንባታ የሚውል 176 ሚሊዮን ዩሮ ወይም የ6 ነጥብ 31 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ለማድረግ ነው ስምምነት የተደረገው።

    ከዚህ ውስጥ 110 ሚሊዮን ዩሮ ወይንም 3 ነጥብ 94 ሚሊዮን ብር ለአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ እንዲሁም 66 ሚሊዮን ዩሮ ወይንም 2 ነጥብ 36 ቢሊዮን ብር ለኢንቨስትመንት መሰረተ ልማት የሚውል ነው።

    ለአጠቃላይ ትምህርት ጥራት የተደረገው ድጋፍ በአፋር፣ ቤኒሻንጉል ጉምዝና ሶማሌ ክልሎች በቅድመ መደበኛ፣ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን ጨምሮ ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሏል።

    ሚኒስትር ዴኤታው አቶ አድማሱ ነበበ እንደገለጹት የድጋፍ ስምምነቱ ኢትዮጵያ በትምህርት ጥራትና ኢንቨስትመንት መስኮች እየሠራች ላለው ተግባር የራሱ አስተዋጽዖ ይኖረዋል።

    የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የተደረገው ድጋፍ በታዳጊ ክልሎች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት፣ ጠንካራ የትምህርት አመራሮችን ለመፍጠርና ተጠያቂነትን ለማስፈን ይውላልም ብለዋል።

    እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ ቀሪው 66 ሚሊዮን ዩሮ ወይንም 2 ነጥብ 36 ቢሊዮን ብር ለመንግስት ኢንቨስትመንትና ለኢንዱስትሪ ፓርኮች ሙያዊ ድጋፍና የአቅም ግንባታ ስልጠና ለመስጠት የሚውል ነው።

    የተፈረመው የድጋፍ ስምምነት የሁለቱን አገራት ጠንካራ ግንኙነት እንደሚያሳይ በመግለጽም ኢትዮጵያ በቀጣይ ለምታከናውነው ሁሉን አቀፍ ልማት እንግሊዝ ድጋፏን እንድትቀጥል ጠይቀዋል።

    ሚስስ ሃርየት ባልድዊን በበኩላቸው የኢትዮጵያን ፈጣን እድገት ለማሳካት እንግሊዝ በትብብር ትሰራለች ብለዋል።

    ሚስስ ሃርየት በትዊተር ገጻቸው ላይ እንዳሰፈሩት እንግሊዝ ለኢትዮጵያ ትምህርት ጥራት ያደረገችው ድጋፍ አንድ ሚልዮን የሚጠጉ ተማሪዎችንና 120,000 አስተማሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል።

    በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በኢኮኖሚው መስክ ለውጥ ለማምጣት የሚያደርጉት ጥረት እውን እንዲሆን ሙያዊና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ በጋራ እንደሚሠሩም ገልጸዋል።

    እንግሊዝ ዶ/ር አብይ አህመድ ጠቅላይ ሚኒስትር ከሆኑ ጀምሮ በአፍሪካ ቀንድ በተለይም በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል የተፈጠረውን ሰላም ታደንቃለችም በማለት አክለዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    እንግሊዝ ለኢትዮጵያ ድጋፍ አደረገች

    Semonegna
    Keymaster

    የኢህአዴግ 11ኛ መደበኛ ድርጅታዊ ጉባዔ የአቋም መግለጫ

    የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢህአዴግ/ “ሀገራዊ አንድነት ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል 11ኛ መደበኛ ድርጅታዊ ጉባዔውን በብሄር ብሄረሰቦች መዲና፣ የህብረ ብሄራዊነትና የብዝሃነት መገለጫ እና የኢትዮጵያ ተምሳሌት በሆነችው ውቢቷ ሀዋሣ ከተማ ከመስከረም 23–25 ቀን 2011 ዓ.ም ለሶስት ተከታታይ ቀናት አካሒዶ በስኬትና በድል አጠናቅቋል።

    የድርጅታችን አባላትና የትግላችን ደጋፊዎች፣ አጋሮቻችን፣ ወዳጆቻችንና መላው የአገራችን ሕዝቦች የጀመርነውን ለውጥ አጠናክረን እንድንቀጥል፣ ድርጅታችን ከምንግዜውም በላይ እንዲጠናከር እና የመሪነት ሚናውን በአግባቡ እንዲወጣ፣ የፈነጠቀው ተስፋ የበለጠ እየለመለመ እንዲሄድ የሚያስችሉ ውሳኔዎችን አስተላልፎና አቅጣጫዎችን አስቀምጦ እንዲጠናቀቅ በጉጉት ሲጠብቁት የነበረው ታሪካዊ ጉባዔ በስኬት በማጠናቀቅ መድረኩን የሚመጥን ቁመና ተላብሰን፣ እንደ ኢህአዴግ አንድነታችንን አጠናክረን መውጣታችንን ስንገልጽ በከፍተኛ መነሳሳትና ቁርጠኝነት ነው።

    11ኛው መደበኛ ድርጅታዊ ጉባዔያችን ታሪካዊ ነው የሚያሰኙት በርካታ እውነታዎች ቢኖሩም ሁነኛ መገለጫው አገር የመበታተን፣ የአንድ አገር ሕዝብ እርስ በርስ የመተላለቅና የድርጅታችን ህልውና የማክተም አደጋ አንዣቦበት ከነበረበት ሁኔታ በማምለጥ የሰላም፣ የይቅርታ፣ የፍቅርና አንድነት ተስፋ በለመለመበት ወሳኝ ወቅት ላይ መሆኑ፤ እንዲሁም ኢህአዴግ ለውጡን በፍጥነት እና በዘለቄታ ይዞ መጓዝ የሚያስችለው ቁመና የሚያላብሱ ውሳኔዎች የተላለፉበት መሆኑ ነው።

    በ10ኛው ድርጅታዊ ጉባዔ የተቀመጡ አቅጣጫዎች አፈፃፀም ሪፖርት በመገምገም፣ ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታና ለውጡን በብቃት የመምራት አስፈላጊነት ላይ በጥልቀት በመወያየት መግባባት ላይ የተደረሰ ሲሆን እንደዚሁም የድርጅታችን የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚሽን ሪፖርት ገምግሞ የቀጣይ ርብርብ አቅጣጫዎችን አስቀምጦ ድርጅቱን እስከቀጣይ ጉባዔ የሚመሩ መሪዎችን ዴሞክራሲያዊ በሆነ መልኩ መርጦ ተጠናቅቋል።
    ጉባዔያችን እንደ ድርጅት ሕዝቡ የሚጠብቀውን ለውጡን በብቃት፣ በፍጥነት እና በቁርጠኝነት በመምራት ሕዝባችንን ከስጋት ማላቀቅ የሚያስችል የሀሳብ አንድነት የፈጠርንበት፣ በችግሮቻችንና በመፍትሄ አቅጣጫዎቹ ላይ ልብ ለልብ ተገናኝተን አንድነት ፈጥረን የወጣንበት ጉባዔ ነው።
    ኢህአዴግ ባለፉት ሶስት አስርት በሚጠጉ ዓመታት ያስመዘገብናቸው ስኬቶች እንደተጠበቁ ሆነው የሕዝቡን የለውጥ ጥማት ሊያረካ የሚችል ሥራ በሚፈለገው ደረጃ ባለመሰራቱ፣ የዴሞክራሲ ባህል አለመጐልበቱ፣ ምህዳሩ እየጠበበ መምጣቱ፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ በሚፈለገው ልክ አለመሠራቱ፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በስፋት በመታየታቸው፣ የሕዝቡ ፍትሐዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች ጐልተው በመውጣታቸው፣ የመሠረተ ልማት ተደራሽነትና ጥራት ችግሮች በመታየታቸው፣ ብልሹ አስተዳደር እየሰፋ በመሄዱ፣ የተደራጀ ሌብነት እየረቀቀና ስር እየሰደደ በመምጣቱ ምክንያት ማህበራዊ መሠረቶቻችንን ጨምሮ በሕዝቡ ዘንድ ድርጅታችን ያለው ተዓማኒነት የመሸርሸር አደጋ እንዲጋረጥበት ሆኖ ነበር። የማታ የማታ ችግሮች እየተደማመሩ መጥተው ወደ ግጭትና አለመረጋጋት ብሎም የአገራችንን ህልውና አደጋ ላይ ወደሚጥል ፖለቲካዊ ቀውስ መግባታችን ይታወቃል።

    በዚህም ምክንያት በተፈጠሩ ግጭቶች የሰው ህይወት ጠፍቷል፣ የዜጐች አካል ተጐድቷል፣ የመንግስትና ሕዝብ ንብረት ወድሟል። የችግሮቹ ምንጮቹም በዋናነት ከእኛ የመሪነት ጉድለት ጋር እንደሚያያዙ ጉባዔው በአጽንዖት ገምግሟል።

    ድርጅታችን የተስተዋሉበትን ድክመቶች ለማረምና ሀገራችንን ከጥፋት ለማዳን በሕዝቡ ግፊት ከውስጥ የመነጨ የጥልቅ ተሀድሶ ንቅናቄ ጀምሮ አሁን የምንገኝበት ተሰፋ ሰጪ የለውጥ ምህዋር ውስጥ ገብተናል።

    እኛ የ11ኛ የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ተሳታፊዎች እንደ ድርጅት የመጣንበት መንገድ፣ አሁን የምንገኝበትን ወቅታዊ ሁኔታ በጥልቀት በመገምገም በሀገራችን ሕዝቦች፣ በአጐራባች ሀገሮች እና በመላው ዓለም ዕውቅና የተቸረው የሀገራችን ጅምር የለውጥ እንቅስቃሴ ጐልብቶ ወደማይቀለበስበት ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል ይህንን ባለ 7 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተናል።

    1. በሀገራችን ሕዝቦች አነሳሽነት እና በኢህአዴግ መሪነት ሀገራችን ወደ ተስፋ ሰጪ የለውጥ ምዕራፍ ገብታለች። ይህ የለውጥ ምዕራፍ የፈነጠቀው የተስፋ ብርሃን በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ መነቃቃትን ከመፍጠሩም ባሻገር ለዘመናት ተኮራርፈው የዘለቁ ወገኖች እንዲታረቁ፣ የታሰሩ እንዲፈቱና የተለያዩ እንዲገናኙ በማድረግ ብሄራዊ መግባባት ከፍ እንዲል ትልቅ አስተዋፅዖ እንዳበረከተ በጉባዔያችን ታይቷል።

    በመሆኑም በሀገራችን እየተመዘገበ ያለው ለውጥ ሕዝባዊ፣ ህገ መንግስታዊ እና ኢህአዴጋዊ መሆኑ ላይ በመተማመን ለውጡ እንዳይቀለበስ የጉባዔው ተሳታፊዎች የየራሳችንን ታሪካዊ ኃላፊነት መወጣት እንዳለብን የጋራ አቋም ወስደናል። ኢህአዴግ እንደ ግንባር ጠንካራ የአስተሳሰብ አንድነት በመያዝ፣ ከአሰራር፣ ከአደረጃጀት እና ከአመራር ግንባታ አንፃር ያሉበትን ጉድለቶች ፈትሾ በማስተካከል እንዲሁም ጥናት ላይ በመመስረት የርዕዮተ -ዓለም ማልማትና ማሻሻልን ከግምት በማስገባት ድርጅቱ ለውጡን በብቃትና በሚፈለገው ፍጥነት መርተን ወደ ግቡ ለማድረስ በጋራ እንሠራለን።

    1. በሀገራችን የፖለቲካ ምህዳሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠበበ በመምጣቱ ምክንያት የሀሳብ ብዙሃነትን በብቃት ያለማስተናገድ፣ የሀሳብና የፖለቲካ አቋም ልዩነቶች በጠላትነት የሚፈረጁበት፣ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶች እየሰፉ የመጡበት አገራዊ ሁኔታ ውስጥ የነበርን መሆናችንን የገመገምን ሲሆን ዴሞክራሲን በማስፋት ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠርና ችግሮቻችንን በሰለጠነ መንገድ ተወያይተን ለመፍታት የሚያስችሉ ጅምር እርምጃዎች ተወስደዋል፤ እየተወሰዱም ይገኛሉ። በተለያዩ ምክንያቶች ተፈርዶባቸው ማረሚያ ቤት የነበሩ የተፎካካሪ ፓርቲ መሪዎች፣ ጋዜጠኞችን ጨምሮ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በይቅርታና በምህረት እንዲፈቱ መደረጉ፣ የዴሞክራሲ ምህዳሩ ላይ ጥያቄ የሚያስነሱ እና መሻሻል የሚገባቸው ህጐች እንዲሻሻሉ አቅጣጫ መቀመጡ፣ የትጥቅ ትግልን እንደ አመራጭ ወስደው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ቡድኖች ወደ ሠላማዊ ትግል መድረክ መመለስ መጀመራቸው ይበል የሚያሰኝ ተግባር መሆኑን ገምግመናል።

    በመሆኑም የዴሞክራሲ ምህዳሩን የበለጠ ማስፋት፣ ዜጐች በያዙት የተለየ የፖለቲካ ሀሳብ እና አመለካከት የማይገፉበትና በጠላትነት የማይታዩበት ሀገራዊ ሁኔታ እንዲፈጠር፣ የግልና የቡድን መብቶች በተሟላ መልኩ የሚከበሩበትን ሁኔታ በማመቻቸት፣ በሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት እየተጠናከረ እንዲሄድ በጽናት እንታገላለን።

    1. ህብረ – ብሄራዊ ፌደራላዊ ሥርዓቱ ባልተማከለ አስተዳደር ብሔር – ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ ዕድል የሰጠ፣ ሕዝቦች በሀገሪቷ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ያስቻለ፣ የሀገራችንን አንድነት በጽኑ መሠረት ለመገንባት ብቸኛው አማራጭ እንደሆና በእኩልነት ላይ የተመሠረተ ሀገራዊ አንድነትን ለመፍጠር ወሳኝ ሚና በመጫወት ላይ እንደሚገኝ ተገምግሟል።ይሁን እንጂ የፌደራል ሥርዓት ግንባታችን በጅምር ደረጃ ላይ ያለ እንደመሆኑ መጠን የወሰን አከላለል ጥያቄዎች፣ ማንነትን መነሻ ያደረጉ ግጭቶች፣ የዜጐች ሞትና መፈናቀል፣ እንዲሁም ከቦታ ቦታ ተዘዋውሮ በነፃነት የመሥራት ህገ – መንግስታዊ መብት ጥሰቶች ይስተዋላሉ።

    በመሆኑም እነዚህን ችግሮች ከሥረ – መሠረታቸው መነቅል የሚገባቸው ችግሮች በመሆናቸው የማንነትም ይሁን የአስተዳደር ወሰን ጥያቄዎች የሚመለከታቸውን ሕዝቦች ነፃ ፍላጐት ከግምት ውስጥ ባስገባ፣ በህገ-መንግስታዊ እና ዴሞክራሲያዊ አግባብ እንዲፈቱ፣ የዜጐች የትም ቦታ ተዘዋውሮ የመኖር፣ የመሥራት፣ በቋንቋቸው የመማር፣ የመዳኘት፣ ወግና ባህላቸውን የማሳደግ፣ ተገቢውን ዕውቅናና ውክልና የማግኘት፣ ሀብት የማፍራት፣ ህገ – መንግስታዊ መብቶቻቸው እንዲከበር እንዲሁም ብሄራዊ ማንነት እና ሃገራዊ አንድነት ሳይነጣጠሉ እንዲጐለብቱ አበክረን እንሰራለን።

    1. የምንገኝበት ወቅት የ2ኛው የዕድገት እና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዳችንን ማጠናቀቂያ ዋዜማ እንደመሆኑ በኢኮኖሚው ዘርፍ መዋቅራዊ ሽግግር ለማረጋገጥ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር የሚያስችሉ ምርት እና ምርታማነትን ማሳደግ፣ ለገበያ የሚያመርቱ አርብቶ እና አርሶ አደሮችና በመደገፍ፣ የመስኖ እና መሰል የግብርና ልማት ሥራዎችን በማፋጠን፣ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማትን በመደገፍ፣ በንግድ እና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ያሉ ማነቆዎችን በመፍታት፣ ገቢ የመሰብሰብ አቅማችንን በማጠናከር የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ መፍጠር አንገብጋቢ ጉዳይ መሆኑ በጉባዔያችን ላይ በዝርዝር ታይቷል።

    በመሆኑም በገጠርም ሆነ በከተማ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ፣ የኢንቨስትመንት ፍሰቱን የሚያጠናክሩ፣ የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር የሚያስችሉ፣ የመላውን ሕዝብ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ዕውን የሚያደርጉ፣ በተለይም የወጣቶችንና የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከመቼውም ጊዜ በላቀ ሁኔታ ለመንቀሳቀስ ቃል እንገባለን።

    1. የቀሰቀስነው ለውጥ ተስፋ ሰጪ ውጤት እያስመዘገበ ያለው በሀገር ውስጥ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በውጭ ዲፕሎማሲ ዘርፍም ጭምር መሆኑን በዝርዝር የገመገምን ሲሆን ከጐረቤት ሀገሮች፤ በተለይም ከቀይ ባህር አካባቢ አገራት ጋር የፈጠርነው ትስስር ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበበትና በምሥራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ሁነኛ ሚና የሚጫወት የሰላም፣ የትብብርና የአንድነት ተስፋ የፈጠረ ግንኙነት መሆኑ በዝርዝር የገመገምን ሲሆን የኢትዮ – ኤርትራ ግንኙነት መታደስ በቅድሚያ ሊጠቀስ የሚገባው መሆኑን፤ እንዲሁም በሁለቱ ሀገራት ወንድማማች ሕዝቦች መካከል ተዘርግቶ የነበረው ጥቁር መጋረጃ መቀደዱን ስኬታማ የዲፕለማሲ ሥራ ውጤት መሆኑን እና ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ገምግመናል።

    በመሆኑም ከሁሉም አጐራባች ሀገራት የሚኖረን ግንኙነት የጋራ ጥቅሞቻችን እና የሕዝቦቻችን አንድነት የሚያጠናክሩ እንዲሆኑ በተለይም በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል የሁለቱን ሀገራት ድንበር በተመለከተ መርህን በተከተለ፣ የሕዝባችንን አንድነት በማያናጋ እና መልካም ጉርብትናን አጠናክሮ ማስቀጠል በሚያስችል መልኩ እልባት እንዲያገኝ እንሰራለን።

    1. በሀገራችን አንዳንድ አካባቢዎች አውዳሚ ግጭቶች፣ ሥርዓት አልበኝነት እና የህግ የበላይነትን የሚጥሱ ተግባራት ሲፈፀሙ ይስተዋላል። በስርዓተ አልበኝነት እና በመንጋ ፍትህ ምክንያት የዜጐች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች የሚጣሱበት ነባራዊ ሁኔታ መኖሩን ጉባዔተኛው ገምግሟል።

    በመሆኑም ከዚህ ታሪካዊ ጉባዔ በኋላ ሃገራችን ሠላም የሠፈነባት፣ ዜጐች በነፃነት ተንቀሳቅሰው ያለ ስጋት የሚኖሩባት፣ የህግ የበላይነት የተከበረባት እንድትሆን፤ እንዲሁም ነፃነት ከህግ የበላይነት ውጪ ባርነት መሆኑን በመገንዘብ መብት ብቻ ሳይሆን ግዴታውንም ጠንቅቆ የሚያውቅ ህብረተሰብ ለመገንባት በትጋት እንሠራለን።

    1. በአገር ደረጃ የተለኮሰው የተሃድሦ እንቅስቃሴ የበለጠ እየጠራ እንዲሄድ፣ መሪው ድርጅታችን ኢህአዴግ ብቃት ያለው አመራር መሥጠት አለበት። ስለሆነም ድርጅታችን መሠረታዊ ባህሪውን ጠብቆ በውስጡ ያለውን ችግር በሚገባ አጥርቶ እንዲወጣ የተለየ ትኩረት ሰጥቶት መሠራት እንደሚገባውም ተገምግሟል። ከዚህ አኳያ የኢህአዴግ አባል ብሔራዊ ድርጅቶች ባካሄዱት ጉባዔ አዳዲስ ምሁራን፣ ወጣቶችና ሴቶችን ወደ አመራር ቋት ማስገባት መቻላቸውም በጥንካሬ ተገምግሟል። ይህ የተጀመረው ድርጅታችንን የማጠናከር ሥራ የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በማድረግ የተጀመረውን የለውጥ እንቅስቃሴ በብቃት ለመምራትና ሕዝቡን ለመካስ ቃል እንገባለን።

    የተከበራችሁ የድርጅታችን አባላት፦
    ድርጅታችሁ ኢህአዴግ በዚህ ታሪካዊ ጉባዔ ያለፉትን ድክመቶችን በዝርዝር ገምግሞና ፈትሾ የእርምት ዕርምጃ ለመውሰድና ጥንካሬዎቻችንን እንዲጐለብቱ ለማድረግ ያስችል ዘንድ የጀመርነው ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና እንዳይቀለበስ የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል። ስለሆነም በመላው ሀገራችን ተስፋ የተጣለበት ለውጥ እንዲቀጥልና የበለጠ እንዲጠናከር ግንባር ቀደም ሚና የመጫወት ታሪካዊ ኃላፊነት በትከሻችሁ ላይ የወደቀ መሆኑን በመገንዘብ ግንባር ቀደም ሚናችሁን እንድትጫወቱ ጥሪ እናቀርብላችኋለን።

    የተከበራችሁ የሀገራችን ወጣቶችና ሴቶች፦
    ድርጅታችን ኢህአዴግ የሀገራችን ወጣቶችና ሴቶች ለሰላም ለልማትና ለዴሞክራሲ መረጋገጥ ያላችሁ ሚና ተኪ የሌለው መሆኑን ከማመኑም በላይ ለውጡ የእናንተ መሆኑን ይገነዘባል። ኢህአዴግ የዛሬ ብቻ ሳይሆን የነገ ድርጅት በመሆኑ የጓጓችሁለትና መስዋዕትነት የከፈላችሁለት ለውጥ በአስተማማኝ ሁኔታ እውን እንዲሆን በማድረግ ለውጥ ለማምጣት ካደረጋችሁት ትግል እና ከከፈላችሁት መስዋዕትነት ባሻገር ለውጡን የመንከባከብና የመጠበቅ ኃላፊነት እንዳለባችሁ በመገንዘብ የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ አስተዋይነትና ብልህነት በተላበሰ ሁኔታ እንድትንቀሳቀሱ ጥሪ እናስተላልፈላችኋለን።

    የተከበራችሁ የሀገራችን ምሁራን
    አሁን ሀገራችን የደረሰችበት የለውጥ ደረጃ የእናንተን ዕውቀት፣ ልምድና ችሎታ በከፍተኛ ሁኔታ ይፈልጋል። በመሆኑም የጀመርነው ለውጥ እንዲቀጥልና እንዲሳካ ጥናትና ምርምር በማድረግ እና ሳይንሳዊ ትንታኔ በመስጠት ያላችሁን ልምድ፣ ብቃት እና ተነሳሽነት ለወገናችሁ እንድታበረክቱ ጥሪ እናስተላልፍላችኋለን።

    የተከበራችሁ የአጋር ድርጅቶች
    በጉባዔያችን መክፈቻ ስነ – ስርዓት ላይ እንዳስተላለፋችሁት መልዕክት ሁሉ ኢህአዴግም ከእናንተ ጋር በመዋሀድ አንድ ሀገራዊ ፓርቲ በመሆን ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚሳተፉበት እና የሚታገሉበት የጋራ መድረክ ይሆን ዘንድ የጥናት ሥራዎችን ተጀምረዋል። በመሆኑም እንደ አንድ ህብረ ብሄራዊና ሀገራዊ ድርጅት ለመንቀሳቀስ በሚያስችለን ህሊናዊና ነባራዊ ሁኔታ ላይ መሆናችንን እየገለጽን ለዚህ ዓላማ ስኬት ሁላችንም የበኩላችንን ድርሻ እንድንወጣ በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

    የተከበራችሁ የተፎካካሪ ፓርቲዎች
    ምንም እንኳን የተለያየ የፖለቲካ አቋም ቢኖረንም የሀገራችን ሕዝቦች የመልማት፣ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን ማረጋገጥ የጋራ አጀንዳዎቻችን መሆናቸውን በውል እንገነዘባለን። እስከ አሁን ባለው ጊዜ በጥላቻ እና በመጠፋፋት ፖለቲካ በመጠመዳችን እና በጠላትነት በመተያየታችን ብዙ ዕድሎች አምልጠውናል። ስለሆነም ወቅቱ የሚጠይቀውን የአንድነትና የአብሮነት መንፈስ በመተጋገዝ እና በመርህ ላይ የተመሠረተ ትግል በማድረግ ሀገራዊ ለውጡን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በሚደርገው ጥረት የበኩላችሁን ገንቢ ሚና እንድትጫወቱ ጥሪያችንን በአክብሮት ስናቀርብላችሁ የፖለቲካ ምህዳሩን የሚያሰፉ ተቋማትን፣ አሠራሮችን እና አደረጃጀቶችን በማሻሻል ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር በቁርጠኝነት ለመሥራት የተዘጋጀን መሆናችንን እንገልፃለን።

    የተከበራችሁ የመንግስት ሠራተኞች
    የመንግስት ሠራተኛው አገልግሎታችንን የሚፈልገውን ህብረተሰብ በተገቢው ሁኔታ በማገልገል እርካታ ሊፈጥር የሚችል ታላቅ ኃይል መሆኑን እናምናለን። በመሆኑም የህብረተሰቡ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ እና ዕርካታ እንዲረጋገጥ በቅንነት፣ በታማኝነት እና በውጤታማነት በማገልገል ለውጡን ለማስቀጠል የበኩላችሁን ሚና እንድትወጡ በዚህ አጋጣሚ ጥሪ እናስተላልፍላችኋለን።

    የተከበራችሁ የሀገራችን የፀጥታ አካላት፦
    የሀገራችንን ሕዝቦች ሰላምና ፀጥታ እንዲሁም ደህንነት ለማስከበር እስከአሁን ለሰራችሁት ሥራ እና ለከፈላችሁት መስዋዕትነት ታላቅ አክብሮት ያለን መሆኑን እየገለጽን ሀገራዊ ለውጡ በስኬት ግቡን እንዲመታ የሕዝቦችን ሰላምና የሕግ የበላይነትን የማስከበር ህገ-መንግስታዊ ግዴታችሁን በጽናት እንድትወጡ በአክብሮት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

    የተከበራችሁ የሀገራችን ሕዝቦች፦
    ኢህአዴግ በ11ኛ መደበኛ ድርጅታዊ ጉባዔው ባለፉት ዓመታት ያስመዘገብናቸው ስኬቶች እንደተጠበቁ ሆነው ባላሟላናቸው ድክመቶች ምክንያት ቅሬታ የፈጠረባችሁና በዚህም ምክንያት በድርጅታችን ላይ ያላችሁ እምነት እየተሸረሸረ መምጣቱን ገምግሞ በእናንተ ቀስቃሽነትና በድርጅቱ መሪነት ተስፋ ሰጪ ለውጥ ላይ የምንገኝ መሆኑን በመገምገም ለውጡን ወደማይቀበለስበት ደረጃ የሚያደርሱ ታሪካዊ ውሳኔዎችን አስተላልፏል። ለሀገራዊ አንድነት፣ ለጋራ ብልጽግና፣ ለዘላቂ ሠላም መረጋገጥና የመደመር መርህዎችንና እሴቶችን ይዘን በጉባዔያችን ያስተላለፍናቸው ውሳኔዎች ዕውን እንዲሆኑ ሁለንተናዊ ተሳትፎአችሁና ድጋፋችሁ እንዳይለየን በታላቅ አክብሮት ጥሪአችንን እናስተላልፍላችኋለን።

    ሀገራዊ አንድነት ለሁለንተናዊ ብልጽግና !!!
    ዘላለማዊ ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!!
    መስከረም 25/2011
    ሐዋሳ

    የ11ኛ የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ

Viewing 15 results - 706 through 720 (of 730 total)