Search Results for 'ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ'

Home Forums Search Search Results for 'ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ'

Viewing 15 results - 1 through 15 (of 28 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    ዶክተር ድረስ ሣህሉ ጎሹ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሆነው ተሾሙ

    ባህር ዳር (ሰሞነኛ)– የባህር ዳር ከተማ ምክር ቤት ጥቅምት 6 ቀን 2013 ዓ.ም ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ዶክተር ድረስ ሣህሉ ጎሹን የባህር ዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ በማድረግ በሙሉ ድምፅ ሹሟል።

    በባህር ዳር ከተማ ምክር ቤት በከተማው የተቀዳሚ ከንቲባነት የተሾሙት ዶክተር ድረስ ሣህሉ ጎሹ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን በምድረ ፅፍ እና አካባቢ ጥናት (geography and environmental study) ከሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ያገኙ ሲሆን፤ የሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በአመራር እና መልካም አስተዳደር (leadership and good governance) ከኢትዮጵያ ሲቪል ሠርቪስ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል። በመቀጠልም የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በሥራ አመራር (management)  ቻይና ከሚገኘው ኋጆንግ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂያገኙ ዩኒቨርሲቲ (Huazhong University of Science and Technology) ሲሆን፥ ሁሉንም የትምህርት ደረጃዎች በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቁ ናቸው።

    ዶክተር ድረስ ሣህሉ የአማራን ሕዝብና መንግሥት በተለያዩ የሥራ ኃላፊነት ቦታዎች ከወረዳ እስከ ክልል ድረስ ባሉ የተለያዩ የመንግሥት መዋቅሮች በውጤታማነት እና በታማኝነት ያገለገሉ ሲሆን፥ ከእነዚህም መካከል በዞን ደረጃ የምዕራብ ጎጃምዞን የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ እንዲሁም የዞኑ የሕዝብ ግንኙነትና የከተማ አደረጃጀት አማካሪ በመሆን አገልግለዋል። ከዚህ በተጨማሪም በክልሉ የምሁራን ተሳትፎና አደረጃጀት ዘርፍ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል። በአጠቃላይ የዶክተር ድረስ ሣህሉ የሥራ ልምድ የሚከተለውን ይመስላል፦

    • በምስራቅ ጎጃም ዞን በደባይ ጥላት ግን እና በባሶ ሊበን ወረዳ የደን እርቻ ልማት (agro forestry) እና የመሬት አስተዳደር ባለሙያ በመሆን ለአራት ዓመታት አገልግለዋል፤
    • በምስራቅ ጎጃም ዞን በባሶ ሊበን ወረዳ የአስተዳደር እና ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በመሆን አገልግለዋል፤
    • በአነደድ ወረዳ የግብርና ኃላፊ፣ የመሬት አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ፣ የሕዝብ ተሳትፎና አደረጃጃት አማካሪ በመሆን አገልግለዋል፤
    • በምዕራብ ጎጃም ዞን ቋሪት ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በመሆን አገልግለዋል፤
    • በጃቢ ጠህናን ወረዳ የመሬት አስተዳደር ጽኅፈት ቤት ኃላፊና የሕዝብ ግንኙነት አማካሪ በመሆን አገልግለዋል።
    • የምዕራብ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ፣ የሕዝብ ግንኙነትና የከተማ አደረጃት አማካሪ በመሆን አገልግለዋል፤
    • በአማራ ክልል የምሁራን ተሳትፎና አደረጃጀት ዘርፍ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል።

    ዘገባው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት እና የአማርኛ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ቤት ነው።

    ዶክተር ድረስ ሣህሉ ጎሹ

    Semonegna
    Keymaster

    በኢትዮጵያ ስምንት ዩኒቨርሲቲዎች የምርምር ልህቀት ማዕከል ተብለው ተለዩ

    ጎንደር (ኢዜአ) – በኢትዮጵያ ስምንት የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የምርምር ልህቀት ማዕከል (Center of Excellence) በመባል መለየታቸውን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

    የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተመረጡ ትምህርት ቤቶች በትምህርት ጥራት ዙሪያ ያካሄደውን የምርምር ግኝቶች ላይ መስከረም 29 ቀን 2013 ዓም ከባለድርሻዎች ጋር ተወያይቷል።

    የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ከፍተኛ አማካሪ ዶ/ር ወርቁ ነጋሽ በወቅቱ እንደገለጹት፥ በሀገሪቱ የሚገኙ 46 ዩኒቨርሲቲዎች በምርምር፣ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በአጠቃላይ ትምህርት በሚል በሦስት ደረጃዎች ተለይተዋል።

    ባለፉት ዓመታት በርካታ ችግር ፈቺ የምርምር ውጤቶችን ሲያበረክቱ የቆዩና ወደፊትም አስተዋጽዖ ይኖራቸዋል የተባሉ ስምንት ዩኒቨርሲቲዎች በምርምር ዘርፍ የልህቀት ማዕከል እንዲሆኑ መለየታቸውን ተናግረዋል።

    ጎንደርአዲስ አበባባህር ዳርመቀሌጅማሀዋሳአርባ ምንጭ እና ሐረማያ ዩኒቨርሲቲዎች የምርምር ልህቀት ማዕከል እንዲሆኑ ተለይተዋል” ብለዋል ዶ/ር ወርቁ።

    ለአንድ ሀገር ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ችግር ፈቺ ምርምር ቁልፍ ሚና እንዳለው የገለጹት ዶ/ር ወርቁ፥ “ያደጉ ሀገሮች የእድገት ምስጢርም ከዚህ የመነጨ ነው” ብለዋል። የምርምር (Research) ዩኒቨርሲቲዎቹ በዓለምአቀፍ ደረጃ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር አቻ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አቅማቸውን ለመገንባት በትኩረት እንደሚሠራ አመላክተዋል።

    ሌሎች 15 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ በሳይንስና ቴክኖሎጂ (Science and Technology) ዘርፍ ትምህርትና ስልጠና እንዲሰጡ መለየታቸውን ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲዎቹ በቂ እውቀትና ክህሎት ያዳበረ ዜጋ ማፍራት እንዲችሉ ተከታታይ ድጋፍ እንደሚደረግላቸው አመላክተዋል።

    ቀሪዎቹ 23 ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ አጠቃላይ ትምህርትና ስልጠና እንዲሰጡ የተለዩ መሆኑን ዶ/ር ወርቁ አስታውቀዋል።

    የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር መርሻ ጫኔ ዩኒቨርሲቲው በርካታ ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምር በማካሄድ ለማህበረሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረጉን ተናግረዋል።

    ላለፉት ሶስት አመታት ጎንደር ከተማን ጨምሮ በሰሜን፣ በማእከላዊና በምዕራብ ጎንደር ዞኖች በተመረጡ 1,343 የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ በትምህርት ጥራት ዙሪያ ጥናትና ምርምር መካሄዱን ገልጸዋል። በምርምር ውጤቶቹ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይትና ምክክር እየተካሄደ መሆኑን አስታውቀዋል።

    “በዩኒቨርሲቲው የሥነ-ትምህርት ኮሌጅ መምህራን የተዘጋጀው የምርምር ውጤት ለፖሊሲ አውጪዎች ጠቃሚ ግብዓት ሆኖ የሚያገለግል ነው” ያሉት ደግሞ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሥራት አጸደወይን ናቸው።

    ባለፈው ዓመት ዩኒቨርሲቲው ከ200 በላይ የምርምር ሥራዎችን ማካሄዱን ዶ/ር አሥራት አስታውሰዋል፤ ዘንድሮም በተለያዩ ዘርፎች ምርምር ለማካሄድ የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እያካሄደ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ማሳወቃቸውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ዘግቧል።

    ለአንድ ቀን በተካሄደው ውይይት የዩኒቨርሲቲው መምህራንና የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከጎንደር ከተማ አስተዳደር የተውጣጡ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ተሳትፈዋል።

    ምንጭ፦ ኢዜአ

    የምርምር ልህቀት ማዕከል

    Anonymous
    Inactive

    በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በተፈጠረው የሰላም እጦት ጋር በተያያዘ ከ640 በላይ ተማሪዎች፣ 40 መምህራን እና ከ240 በላይ የአስተዳደር ራተኞች ላይ የተለያዩ እርምጃዎች መወሰዳቸው ተገለጸ

    አዲስ አበባ (ኢብኮ) – ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ተፈጥሮ የነበረው የጸጥታ ችግር ለማረጋጋት በ22 ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በነበሩ ከ640 በላይ ተማሪዎች፣ 40 መምህራን እና ከ240 በላይ የአስተዳደር ሠራተኞች ላይ የተለያዩ እርምጃዎች እንደተወሰደ የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

    በዩኒቨርሲቲዎች በተፈጠረ የሰላም እጦት 35 ሺህ ተማሪዎች ትምህርት ጥለው መውጣታቸውን የገለጸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፥ እነዚህን ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ እየተሠራ መሆኑን አስታውቋል። የተማሪዎችን አደረጃጀት በኅብረ ብሔር ለማሰባጠር መታሰቡንም ሚኒስቴሩ ገልጿል።

    የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዩኒቨርሲቲዎች ሰላም ባጡባቸው ጉዳዮች ላይ ከተለያዩ አካላት ጋር ግምገማ እና ምክክር እያደረገ ይገኛል።

    በ22 ዩኒቨርሲቲዎች ተፈጥሮ የነበረውን የጸጥታ ችግር ለማጣራት የተዋቀረው ኮሚቴ ባደረገው የመስክ ምልከታ ያዘጋጀው ሪፖርት በመድረኩ ላይ ቀርቧል። በቀረበው ሪፖርትም የዩኒቨርሲቲዎች የሰላም መታወክ የፖለቲካ አመራሮች ትልቅ ሚና እየተጫወቱ እንዳለ ተገልጿል።

    በተለያዩ ክልሎች ባሉ የተለያዩ የፖለቲካ አመራሮች የሚወጡ መግለጫዎች እና ከግቢ ውጭ ተማሪዎችን ሰብስቦ ተልእኮ የመስጠት ሥራዎች ለመማር ማስተማሩ መታወክ እንደ አንድ ምክንያት ተጠቁሟል። ተልእኮ የተቀበሉ ተማሪዎች መማር የሚፈልጉ ተማሪዎች ላይ የሥነ ልቦና፣ አካላዊ፣ የሕይወት እና ንብረት ጉዳት በማድረስ ግጭት እንደሚያነሳሱም ተጠቁሟል። በሚዲያዎች፣ በሶሻል ሚዲያዎች እና በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን የተጋነኑ እና የተዛቡ መረጃዎች መሰራጨት፣ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ችግሮችን ውጫዊ ማድረግ ወይም ቸልተኝነትም ሌላው ለዩኒቨርሲቲዎች የሰላም እጦት የተነሣ ተግዳሮት ነው። በዩኒቨርሲቲዎች ያለው በቤተ ዘመድ የተሳሳበ የሠራተኛ አደረጃጀት እንዲሁ እንደ አንድ ችግር ተጠቅሷል።

    ችግር የፈጠሩ እና ምንም ዓይነት የሕግ እርምጃ ሳይወሰድባቸው በነፃ የሚለቀቁ እና እንዲማሩ የሚፈቀድላቸው ተማሪዎችም በዩኒቨርሲቲዎች ለሚታየው የሰላም እጦት ሌላው ምክንያት መሆናቸው ተጠቁሟል።

    በዩኒቨርሲቲ አመራሩ በኩል ውጫዊ ማስፈራሪያዎችን በመፍራት ውሳኔ ሰጭነት ላይ የሚታየውን ማፈግፈግ እንዲሻሻል እና ጠንካራ አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድም ተገልጿል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢብኮ) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በዩኒቨርሲቲዎች የሰላም እጦት

    Semonegna
    Keymaster

    ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ጥፋት ፈፅመው በተገኙ 77 ተማሪዎች ተማሪዎች ላይ ዛሬ እርምጃ ወሰደ

    ሐረማያ (ሰሞነኛ) – ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተወሰኑት የአገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ሰላማዊ መማር ማስተማርን ለማረጋገጥ አስቸጋሪ ችግሮች እንደጋጠማቸው ይታወቃል። በተለይ በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ያለምንም ምክንያት ውድ የሆነው የሰው ሕይወት በሚያሳዝን ሁኔታ ጠፍቷል።

    ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ይህ እንዳይሆን ጠንካራ እና ሁሉን አቀፍ ቅንጅት በማድረግ ሲሠራ በመቆየቱ የሰው ሕይወት ባያልፍም የጥፋት አላማን አንግበው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ጥቂት ተማሪዎች ግን ሰላማዊ መማር ማስተማር እንዲታወክ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ የዩኒቨርሲቲውን አጠቃላይ ህልውናን ጭምር አደጋ ውስጥ በመክተት የጥፋት ተልዕኮአቸውን ሲያከናውኑ ቆይተዋል። እነዚህ ለጥፋት የተሰማሩ ተማሪዎች ከጥፋታቸው እንዲመለሱና እንዲታረሙ ተደጋጋሚ ምክርና ጊዜ የተሰጣቸው ቢሆንም ከጥፋታቸው ሊታረሙ አልቻሉም።

    በመሆኑም የዩኒቨርሲቲውን ሰላማዊ መማር ማስተማርን ለማስቀጠል እንዲቻል በተለያዩ ጊዜያት በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሥራው እንዲስተጓጎል ምክንያት በሆኑ 77 ተማሪዎች ላይ እርምጃ የተወሰደባቸው ሲሆን ለእርምጃው መወሰድ ምክንያቶች በዋናነት የሚከተሉትን ያካትታል፦

    • በዩኒቨርሲቲው ሰላማዊ መማር ማስተማር እንዳይኖር በተደራጀ ሁኔታ ሰላማዊ ተማሪ ላይ ጥቃት በማድረስ፣ ሕገ-ወጥ ሰልፍ በማደራጀት እና መማር ማስተማር እንዳይካሄድ የተለያዩ እንቅፋቶችን በመፍጠር፣
    • በቡድን ተደራጅተው በማንነት ላይ የተመሠረተ ጥቃት ማድረስ ፣ የማሸማቀቅ እና የማስፈራራት ተግባርን በመፈፀም፣
    • በሕገ-ወጥ ሰልፍ በዩኒቨርሲቲው ንብረት ላይ ውድመት ማድረስ፥ ለምሳሌ፡- ታህሳስ 30 ቀን 2012 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ በዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ተቋም 3 (ሦስት) ተሸከርካሪዎችን አውድመዋል፤ የባንክ ኤቲኤም (ATM) ማሽን ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጪ አድርገዋል፤ ዩኒቨርሲቲው ላይም ከፍተኛ ውድመት እንዲከሰት እሳት አቀጣጥለዋል።
    • የብሔር ግጭት የሚቀሠቅሱ ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸውን ንግግሮችን በማጉላት በተማሪዎች መሀከል የስጋት ድባብ እንዲነግስ ማድረግ እና ብሔርን መሠረት አድርጎ ተማሪን በመከፋፈል ትምህርት አቋርጠው እንዲበተኑ ማድረግ ይጠቀሳል።

    በዚሁ መሠረት ሰላማዊ ተማሪዎችን ሕይወት ለመጠበቅና ሰላማዊ የመማር ማስተማሩን ሥራ ለማስቀጠል ሲባል እርምጃ ከተወሰደባቸው አጥፊ ተማሪዎች መካከል 2 (ሁለቱ) ሙሉ ለሙሉ እንዲሰናበቱ የተደረገ ሲሆን 75 ተማሪዎች ደግሞ ለ2 (ሁለት) ዓመት ከትምህርት ገበታቸው እንዲታገዱ ተወስኗል።

    በተጨማሪም ሁለት መምህራን ተማሪዎችን በማስኮብለል ድርጊት ላይ ተሳትፈው በመገኘታቸው በደመወዝ ቅጣትና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲደርሳቸው ተደርጓል።

    ዩኒቨርሲቲው ድብቅ ዓላማን አንግበው በተለያዩ ማደነጋገሪያ ሽፋኖች የሚንቀሣቀሱ እና ተቋሙ የጥፋት ዓላማዎች ማራመጃ ሜዳ እንዲሆን ሁኔታዎችን ለማመቻቸት የሚሠሩ ተማሪዎች፣ መምህራን እና የአስተዳደር ሠራተኞች ላይ በቀጣይ የማጣራት ሥራ የሚሠራ ሲሆን፥ እንደጥፋታቸው ደረጃ እና ጥልቀት ሕጋዊ እና ተቋሟዊ እርምጃ ለመውሰድ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ እያሳወቅን፥ ዩኒቨርሲቲው የሚያደርገው ጥረት ስኬታማ እንዲሆን ሁሉም ጉዳዩ የሚመለከታቸው እና የሀገራቸው እና የዩኒቨርሲቲያቸው ሰላም የሚያሳስባቸው የአስተዳደር፣ ፀጥታ እና ማኅበረሰብ አካላት እንደተለመደው ከዩኒቨርሲቲው ጐን እንዲቆሙ በአክብሮት እንጠይቃለን። በተጨማሪም የተማሪ ቤተሰቦች ልጆቻችሁን በመምከር እንድታግዙን ዩኒቨርሲቲው ጠይቋል።

    ምንጭ፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ


    Semonegna
    Keymaster

    በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሥር ከሚገኙት ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የጎንደር ዩንቨርሲቲ በርካታ ቁሳዊና መንፈሳዊ እሴት የያዙ መጻህፍት ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገሩ ለማድረግ ሥርዓተ ትምህርት (curriculum) ተቀርጾና መምህራን ተቀጥረው የግእዝ ቋንቋን ለማስተማር መዘጋጀቱን አስታውቋል።

    ጎንደር ዩንቨርሲቲ የግእዝ ቋንቋ በመጀመሪያ ዲግሪ መስጠት ሊጀምር ነው

    ጎንደር (ኢዜአ) – ጎንደር ዩንቨርሲቲ የመጥፋት አደጋ የተጋረጠበትን የግእዝ ቋንቋ ለመታደግ በአዲሱ የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ ዲግሪ የቋንቋ ትምህርት ለመስጠት መዘጋጀቱን አስታወቀ።

    የጎንደር ዩንቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኘ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) እንደተናገሩት ኢትዮጵያ የግእዝ ቋንቋ ባለቤት ብትሆንም ለቋንቋው ማደግና መስፋፋት የተሰጠው ትኩረት አነስተኛ ነው። “በዚህም ሳቢያ ቋንቋው የመጥፋት አደጋ የተጋረጠበት ከመሆኑም በላይ በግእዝ ቋንቋ የተጻፉ በርካታ የብራና መጻፍትን ለጥናትና ምርምር ስራ ለማዋል አልተቻለም “ብለዋል።

    ዘመናት የተሻገሩና በቋንቋው የተጻፉ ለዘመናዊ ሕክምና ሙያ የሚያግዙ፣ ምጣኔ ሀብታዊ፣ ባህላዊና ታሪካዊ ፋይዳ ያላቸው በርካታ መጻሕፍት በኃይማኖት ተቋማትና ገዳማት ተወስነው መኖራቸውን አመልክተዋል።

    ዩንቨርሲቲው እነዚህን ቁሳዊና መንፈሳዊ እሴት የያዙ መጻህፍት ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገሩ ለማድረግ ሥርዓተ ትምህርት (curriculum) ተቀርጾና መምህራን ተቀጥረው የግእዝ ቋንቋን ለማስተማር መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።

    በትምህርት ዘመኑ 50 ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ዝግጅት መደረጉን ያመለከቱት ዶክተር ካሳሁን፥ ትምህርቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠውም በኤክስቴንሽንና በክረምት መርሃ ግብሮች መሆኑን አስረድተዋል። ትምህርቱ ሰፊ ተቀባይነት እያገኘ ሲሄድ መደበኛ ተማሪዎችን ጭምር በቀጣይ በግእዝ ቋንቋ አሰልጥኖ ለማስመረቅ መታቀዱን አመልክተዋል።

    በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሥር ከሚገኙት ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የጎንደር ዩንቨርሲቲ፥ በአጠቃላይ 87 የመጀመሪያ ዲግሪ፤ 158 ሁለተኛ ዲግሪና 29 የሦስተኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች እንዳሉት ተገልጿል። በመደበኛ፣ በተከታታይና በክረምት መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የሚከታታሉ ከ45ሺ በላይ ተማሪዎች በዩንቨርሲቲው ይገኛሉ።

    ምንጭ፦ ኢዜአ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    —–
    ተመሳሳይ ዜናዎች

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በኢትዮጵያ ― ዜናዎችና ጠቃሚ መረጃዎች


    Semonegna
    Keymaster

    ኤ.ቢ.ኤች. ፓርትነርስ (ABH Partners) የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ እና አምስት የሥራ ኃላፊዎቹ ላይ ጉዳት አድርሰውብኛል በሚል በመሠረተው የ174.6 ሚሊዮን ብር ክስ ነሐሴ 29 ቀን 2011 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀረቡ።

    አዲስ አበባ (አዲስ ዘመን ጋዜጣ) – የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ (HERQA) እንዲሁም አምስት የሥራ ኃላፊዎቹ በድርጅቱ ላይ ላደረሱትና ለሚደርሰው ጉዳት የ174.6 ሚሊዮን ብር ተከፍሎ እስከሚያልቅ ከሚታሰብ ሕጋዊ ወለድ ጋር ክስ እንዳቀረበባቸውና ነሐሴ 29 ቀን 2011 ዓ.ም. ረፋድ ላይ ፍርድ ቤት እንደቀርቡ ኤ.ቢ.ኤች. ፓርትነርስ (ጥምረት ለተሻለ ጤና) /ABH Partners/ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል አማካሪ ድርጅት አስታወቀ።

    የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ማርቆስ ፈለቀ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፥ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ከማምራቱ በፊት ኤጀንሲው የድርጅቱን መልካም ሥምና ዝናን በማጠልሸቱ ይቅርታ እንዲጠይቅና ችግሩን እንዲያርም ቢጠየቅም ፈቃደኛ ሊሆን አልቻለም።

    በዚህም ድርጅቱ ነሐሴ 23 ቀን 2011 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፍትሐ-ብሔር ስድስተኛ ምድብ ችሎት የመዝገብ ቁጥር 241863 ክስ ለመመሥረት ተገዷል። የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አንዱዓለም አድማሴን ጨምሮ አምስት የሥራ ኃላፊዎችም ተከሰዋል።

    ኤጀንሲው ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከኤ.ቢ.ኤች. ፓርትነርስ (ABH Partners) ጋር በጥምረት የሚሠሩትን ሥራ እንደማያውቀው ቢያስተባብልም፤ ሁለቱ ተቋማት ውል ተፈራርመው ሥራውን ሲጀምሩ በወቅቱ የነበሩት የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በቦታው ተገኝተው መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ቃል ገብተው እንደነበር ዶ/ር ማርቆስ አስታውሰው፤ “ይህም መንግሥት አያውቀውም የሚለውን ሐሳብ ትክክል እንዳልሆነ አመላካች ነው። ከወራት በፊት ትምህርት የሚሰጥበትን ቦታ ተገኝተው የጎበኙ የሣይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታዎች ግን ‘ሥራው የዩኒቨርሲቲውን አቅም ለማዳበር ያገዘ ነው’ ሲሉ አሞካሽተውታል። ለጅማ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመስጠት የመምህራን ፍልሰት እንዲቀንስ አዎንታዊ አስተዋፅዖ ማበርከቱንና ለትምህርት ጥራት እንዲተጋ የሚያግዙ ሁኔታዎች መመቻቸታቸውንም ሚኒስቴሩ ምስክርነቱን በደብዳቤ ሰጥቷል” ብለዋል።

    ሚኒስቴሩ፥ የዚህ መሰል የግሉ ዘርፍና የመንግሥት አጋርነት ለትምህርት ጥራትም ሆነ ተደራሽነት ሚናው የላቀ መሆኑን በመግለጽ፥ ለዚህ ሊበረታታ ለሚገባው ድርጅት አገራዊ ፋይዳውን በማየት የግንባታ መሬት በመስጠት ትብብር እንዲደረግላቸው ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ የትብብር ደብዳቤ እንደፃፈላቸውም ጠቁመዋል።

    ሚኒስቴሩ ለዩኒቨርሲቲውና ለድርጅቱ ምስክርነት በመስጠት ከመንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያገኙ ሲያደርግ፥ ኤጀንሲው ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር 650/2001 ከሰጠው ሥልጣን ውጪ “ዩኒቨርሲቲው ከዋናው ግቢ ውጪ በአዲስ አበባ የሚሰጠው ትምህርት ዕውቅና የለውም፤ ሕጋዊም አይደለም” በማለት እግድ ማስተላለፉ “ባለፉት ሰባት ዓመታት የት ነበረ?” የሚል ጥያቄንም የሚጭር እንደሆነ ዶ/ር ማርቆስ አብራርተዋል።

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ የማስተማር ሥራውን ሊሰራ፤ አማካሪ ድርጅቱ ደግሞ አስተዳደራዊ ድጋፍ ሊሰጥ በገቡት ስምምነት መሠረት ዩኒቨርሲቲው አዲስ አበባ ባለው ካምፓስ ምንም ዓይነት የመንግሥት ድጋፍ ሳይደረግለት ኤ.ቢ.ኤች. ፓርትነርስ ሙሉ ድጋፍ በማድረግ ለመማር-ማስተማሩ አስፈላጊ ግብዓቶችን አሟልቶ በውሉ መሠረት ግዴታውን ሲወጣ መቆየቱንም ተናግረዋል።

    ዩኒቨርሲቲው ከዋናው ግቢ ውጪ ማስተማርም ሆነ ከሌሎች አካላት ጋር በትብብር መሥራት እንደማይችል ኤጀንሲው ቢገልጽም፣ በዩኒቨርሲቲው እንደገና ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 240/2003 ግን ዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ ከሚገኝበት ጅማ ከተማ ውጪ በሌሎች ቦታዎች የትምህርት ክፍሎችን እንዲሁም የምርምርና የማኅበረሰብ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን ሊያቋቁም እንደሚችል ተደንግጓል።

    በተመሳሳይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አዋጅ ዩኒቨርሲቲዎች ተልዕኳቸውን ለማሟላት ድጋፍ ሊሰጣቸው ከሚችል ከማንኛውም ተቋም ጋር መሥራት እንደሚችሉ ይደነግጋል። በዚህም በአዋጁ ያልተከለከለን ሥልጣን ኤጀንሲው በደብዳቤ መሻሩ ተገቢነት እንደሌለው ዶ/ር ማርቆስ ገልፀዋል። በመሆኑም ለቀጣይ የትምህርት ዘመን አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውንና ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች በሁኔታው መደናገጥ እንደማይገባቸው ተናግረዋል።

    የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ (ቁጥር 650/2001) አንቀጽ 93፣ ንዑስ አንቀጽ አንድ አገልግሎት በሌሎች ወገኖች እንዲሰጥ ስለማድረግ ይደነግጋል። በዚህም ማንኛውም የመንግሥት ተቋም ተገቢና ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል ሆኖ ሲያገኘው የድጋፍ ሰጪ አገልግሎቶችን በሌሎች አገልግሎት አቅራቢዎች እንዲሰጥ ሊያደርግ እንደሚችል አስቀምጧል።

    በተመሳሳይ በጅማ ዩኒቨርሲቲ እንደገና ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ (ቁጥር 240/2003) በአንቀጽ ሦስት መሠረት የዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ ጅማ ከተማ ሆኖ በሌሎች ቦታዎች የትምህርት ክፍሎችን፣ የምርምርና የሕብረተሰብ አገልግሎት ማዕከሎችን ሊያቋቁም እንደሚችል ተቀምጧል።

    ባለፉት 15 ቀናት ኤጀንሲው “የትብብር ሥልጠና ትክክል ባለመሆኑ እንዲያቆሙ” በሚል ሚኒስቴሩ በደብዳቤ ማሳወቁን መግለጹ ይታወሳል። በዚህ መልኩ ሲሠሩ የነበሩ የጅማየደብረ ማርቆስየባህር ዳር እና የሐረማያ ዩኒቨርሲቲዎች እንደታገዱ አሳውቋል።

    ሆኖም ጅማ ዩኒቨርሲቲ እና ኤ.ቢ.ኤች. ፓርትነርስ ሥራቸውን በመቀጠላቸው “አደብ ሊገዙ ይገባል” ብሎም ነበር። ከዚህ በተጨማሪም ኤጀንሲው በተቋማቱ በመማር ላይ ያሉትን ተማሪዎች ዝርዝር እንዲላክለት የጠየቀ ሲሆን፤ ተመርቀው የወጡ ተማሪዎች ዕጣ ፈንታ ግን ቀጣይ ውይይት እንደሚያስፈልገው አሳውቆ ነበር።

    ምንጭ፦ አዲስ ዘመን ጋዜጣ/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ABH Partners vs HERQA brawl


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – አድማስ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ የጥራት ደረጃዎች ኤጀንሲ የተዘጋጁት ስታንዳርዶች በተገቢው መልክ በመፈፀም በ2012 ዓ.ም. በተቋም ደረጃ አይ ኤስ ኦ የምስክር ወረቀት (ISO Certificate) ለማግኘት የሚያስችለውን ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ገለጸ።

    የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ብሩ አስማረ እንደገለጹት፥ ዩኒቨርሲቲው የትምህርት አሰጣጥ ጥራት ደረጃውን በማሳደግ ለዚሁ ተገቢ የሆነ እውቅና ለማግኘት የሚያስችለው ብቃት ላይ ይገኛል።

    በቴክኒክና ሙያ ኮሌጀች የትምህርት ሥልጠና ጥራት ለማስጠበቅና በየሙያ ደረጃው የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ አድርጓል ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ የማስልጠኛ መሳሪያዎች (Training Teaching and Learning Materials /TTLM) ዝግጅት በሁሉም የብቃት አሃዶች ማዘጋጀቱንና የትብብር ሥልጠናን አፈፃፃምን የሚያሻሻሉ የተለያዩ ተገባራት እያከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።

    አቶ ብሩ አስማረ አያይዘውም የምዘና ሥርዓቱን ለማጠናከርና በዩኒቨርሲቲው የሚተገበረውን የተከታታይ ማጠቃለያና ተቋማዊ ምዘና ዝግጅትና አፈፃፃም ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን መደረጉንም አስረድተዋል።

    በኢትዮጵያ የደረጃ ኤጀንሲ (Ethiopia Standard Agency) የተዘጋጁ የጥራት ምዘናዎችን (stadards) ማለትም የስርዓተ ትምህርት (Curriculum Requirement ES. 6259-1: 2018)፣ የመሣሪያዎች ማሽነሪዎች (Tools, Machines and Equipment Requirement ES 6259-8: 2018)፣ የምዘናና የማሰልጠኛ መሣሪያዎች (Assessment & Instructional Materials ES 6299-9: 2011 ) እና የመሳሰሉትን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን አቶ ብሩ ገልጸዋል።

    ምክትል ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም በዩኒቨርሲቲው የሚስጠውን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና በምርምር ለማገዝ እንዲቻል የተለያዩ ጥናቶች በማካሄድ ያሉ ችግሮችን የመለየት ሥራ በየጊዜው እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመዋል።

    በጥቅምት ወር 1990 ዓ.ም. “አድማስ የቢዝነስ ማሰልጠኛ ማዕከል” በሚል ሥራውን የጀመረው ይህ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም፥ በፍጥነት ራሱን በማሳደግ በሚያዝያ ወር 1991 ዓ.ም. የኮሌጅነት ደረጃ አግኝቶ ስሙን “አድማስ ኮሌጅ” ብሎ በመሰየም ሥራውን አስፋፋ። ቀጥሎም በመጋቢት ወር 1999 ዓ.ም. “አድማስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ” በሚል ስም የትምህርትና የስልጠና ተግባሩን አሳደገ። የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር 650/2009 የሚጠይቃቸውን አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶች በሙሉ በማሟላት በሐምሌ ወር 2006 ዓ.ም. የሙሉ ዩኒቨርሲቲ ደረጃን አግኝቶ “አድማስ ዩኒቨርሲቲ” ተባለ።

    አድማስ ዩኒቨርሲቲ የዘንድሮን ተመራቂዎችን ጨምሮ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከ70 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በተለያዩ የትምህርት ዘርፎችና እርከኖች አስመርቋል።

    በአሁኑ ወቅትም በውጭ/ጎረቤት ሀገራት ሶማሌላንድና ፑንትላንድ በሚገኙት ካምፓሶቹ ያሉትን ጨምሮ በጠቅላላው ከ20 ሺህ በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ ነው።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    አድማስ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ብሩ አስማረ


    Semonegna
    Keymaster

    ሐረማያ ከተማ (ሰሞነኛ) – ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን በባቢሌ ወረዳ ለሚገኙና ከቀዬአቸው ተፈናቅለው ለነበሩ አርሶ አደሮች ከ750ሺህ ብር በላይ የሚያወጣ 266 ኩንታል በአጭር ጊዜ የሚደርስ የተሻሻለ የቦቆሎና የማሽላ ዘሮችን በእርዳታ አከፋፈለ።

    ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ምርጥ ዘሩን ያከፋፈለው ከኢትዮጵያ ሶማሌና ከኦሮሚያ ክልሎች ድንበር አዋሳኝ ዘጠኝ ቀበሌዎች ከ2 እስከ 8 ወር ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የባቢሌ ንዑስ ምርምር ጣቢያና በተለያዩ ቦታዎች ተጠልለው ለነበሩ 964 ወደ ቄያቸው ተመላሽ አርሶ አደሮች ነው።

    ዩኒቨርሲቲው ያከፋፈለው የቦቆሎና የማሽላ ምርጥ ዘሮች በሦስት ወር ውስጥ የሚደርሱ በሽታንና ድርቅን የሚቋቋሙ ሲሆን ለገመቹ፣ ኤረር ጐዳ፣ ኢፋዶኒ፣ ቱላ፣ ሼካ አብዲ፣ አውሸሪፍ፣ ኤረር ኢባዳ፣ ራመታ ሠላማ እና አባዳ ገመቹ ለሚኖሩ 964 አባ እና እማወራዎች 241 ኩንታል መልካሣ-2 የተባለ የቦቆሎና 25 ኩንታል መልካም የተባለ የማሽላ ዘር ነው።

    የቱላ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ነዋሪ የሆነችው ነኢማ ዑመር ቀደም ሲል ከቀዬዋ ተፈናቅላ በባቢሌ ስትኖር እንደ ነበርና አሁን ሠላም ወርዶ ወደ ቀዬዋ ብትመለስም የምትዘራው ዘር አጥታ ስትጨነቅ እንደነበርና አሁን ከሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ያገኘችው ዘር እንደደረሰላት በመግለፅ ዩኒቨርሲቲውን አመስግናለች።

    ሌላው ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ያነጋገራቸው የገመቹ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ሊቀመንበር አቶ አብዱረህማን ሽኩር፥ በኢትዮ ሶማሌና ኦሮሚያ አዋሳኝ በተቀሰቀሰ ግጭት አጠቃላይ የቀበሌው ነዋሪ ከ8 ወራት መፈናቀል በኋላ በሀገር ሽማግሌዎች፣ በመከላከያ እና የፀጥታ ዘርፍ አመራሮች ጥረት በሁለቱ ወንድማማች ህዝቦች መካከል እርቅ ተደርጐ ወደ ቄያቸው ቢመለሱም ቀደም ሲል የነበራቸው ንብረት በመዘረፉ እና በመውደሙ የእርሻ ማሳቸውን አዘጋጅተው የመግስትን እርዳታ ሲጣባበቁ እንደነበር ጠቁመዋል። ከሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ያገኙት ምርጥ ዘር ለ700 አባና እማወራዎች እንደተከፋፈለና ይህም በ355 ሄክታር መሬት ላይ ለመዝራት ቅድመ ዝግጅት መደረጉን አቶ አብዱረህማን ገልፀው ምንም እንኳን ፍላጎቱ ከአቅርቦቱ ጋር ሲነፃፀር ብዙ ቢቀረንም ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ላዳረገው አስቸኴይ እርዳታ በራሳቸውና በቀበሌው አርሶ አደሮች ስም አመስግነዋል።

    በምስራቅ ሐረርጌ ዞን የባቢሌ ወረዳ ተፈጥሮና ግብርና ልማት ፅህፈት ቤት ተወካይ አቶ ኢዳ አቦንሣ እንደገለጹት ተፈናቃዮችን ወደቄያቸው መልሶ ለማቋቋም በምናደርገው ጥረት ምርት አምርተው ለመኖር እንዲችሉ ለማድረግ የግድ ዘር በማስፈለጉ ይህንኑ ዩኒቨርሲቲው እንዲረዳን በደብዳቤ በጠየቅነው መሰረት ፈጣን ምላሽ በመስጠት ከመጋዘኑ ባይኖረውም ካለው በጀት ላይ 750000 (ሰባት መቶ ሃምሳ ሺህ) ብር የሚያወጣ ዘር በመግዛት በራሱ ትራንስፖርት ወረዳው ድረስ በማምጣት በዘጠኝ ቀበሌ ለሚገኙ 964 አባና እማወራዎች 266 ኩንታል የተለያዩ የተሻሻሉ ዘሮችን አከፋፍሏል። ላሣየው የህዝብ ወገንተኝነት ከፍተኛ ምስጋና ይገባዋል ብሏል።

    ይህ በእንዲህ እንዳለ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በያዝነው የ2011 ዓ..ም በጀት ዓመት ከአንድ ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የተለያዩ የሰብል፡ የአትክልት እና ፍራፍሬ፣ የእንቁላል ጣይ ዶሮ ፤ የቦሎቄ ዘሮችንና የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎች ለተጠቃሚዎች በነፃ ማከፋፈሉን ከዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ያገኘነው ማስረጃ ያሳያል ሲል ሲሣይ ዋቄ ለዩኒቨርሲቲው ዘግቧል።

    ምንጭ፦ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ (ኤፍ ኤም 91.5) / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ


    Semonegna
    Keymaster

    እ.ኤ.አ በ2011 የተመሠረተው ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዶክተሮችን ሲያስመርቅ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ጊዜ እንደሆነ ተገልጿል። ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት ስድስት ኮሌጆች፣ አንድ ትምህርት ቤት እና አንድ ተቋም (ኢንስቲትዩት) አለው። 

    ዓዲግራት (ሰሞነኛ)– ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለመጀመርያ ግዜ ሰባት ሴቶች 25 ወንዶች በድምሩ 32 የሕክምና ዶክተሮችን (medical doctors) እንዲሁም በድኅረ መሠረታዊ መርሃግብር (post basic program) 30 ተማሪዎችን አስተምሮ መጋቢት 1 ቀን 2011 ዓ.ም. አስመርቋል። በዕለቱ የክብር እንግዳ የነበሩ የትግራይ ክልል ም/ር/መስተዳደር ክቡር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ባስተላለፉት መልዕክት፥ በሃገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ከፍተኛ የጤና ባለሙያዎች እጥረት እንዳለና ችግሮቻችን በማቃለል አንዳንዱን በመፍታት ልዩነት የሚያመጣ ድርሻ እንደሚኖራችሁ ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ ብለው መልእክታቸው አስተላልፍዋል።

    በዕለቱ የምርቃት ሥነ ስርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ወ/ሮ ስሃረላ ኣብዲላሂ በበኩላቸው የጤና ባለሙያ ማለት የግል ምቾትን እንደ መስዋዕትነት በመክፈል እንብካቤ ለሚያስፈልጋቸው እንክብካቤ መስጠት መሆኑን በማወቅ በየተኛውም የሃገሪቱ ክፍል ሄዳችሁ ያስተማራችሁን ህብረተሰብ ለማገልገል ዝግጁ እንድትሆኑ በማለት ለዕለቱ ተመራቂዎች መልዕክታቸውን አስተላለፈዋል። ዩኒቨርሲቲው የነበሩበትን ፈተናዎች ኣልፈው ለመመረቅ መብቃታችው በጣም የሚያኮራ ታሪክ መሆኑ የዩኒቨርሲቲው ግዝያዊ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገ/መስቀል ገልፀዋል።

    ኬር ኢትዮጵያ በ7 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ወጭ ያስገነባውን የምርምርና የስልጠና ማዕከል ለሐረማያ ዩኒቨርሲቲ አስረከበ

    ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዶክተሮችን ሲያስመርቅ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ ተገልጿል። ዩኒቨርሲቲው የተመሠረተው እ.ኤ.አ በ2011 ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ስድስት ኮሌጆች፣ አንድ ትምህርት ቤት እና አንድ ተቋም (ኢንስቲትዩት) አለው። ከሁለት ዓመታት በፊት ዩኒቨርሲቲው ባወጣው የአሃዝ ዘገባ በአጠቃላይ ከ16,000 በላይ ተማሪዎች በመደበኛው፣ እንዲሁም ከ6,000 በላይ ተማሪዎች በተከታታይ (continuing education) መርሀ ግብር እያስተማረ ይገኛል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – STEMpower የተሰኘ መቀመጫውን USA (ሳሌም፥ ማሳቹሴትስ፣ አሜሪካ) ያደረገ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ ትምህርቶችን በዩኒቨርሲቲዎች እየረዳ የሚገኝ ሲሆን በአገራችን 13 ማዕከላትን ከፍቶ በትብብር እየሠራና እየረዳ ይገኛል።

    ድርጅቱ የድጋፍ አድማሱን በማስፋት በኢትዮጵያ ተጨማሪ 10 ማዕከላትን (ሰባት ማዕከላትን በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች፣ ሶስቱን በተለያዩ ከተሞች እ.አ.አ. በ2019) ለመክፈት ከኢፌዴሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም ከሰባቱ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የትብብር ስምምነት የካቲት 14 ቀን 2011ዓ.ም. ተፈራርመዋል።

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ሂሩት ወልደማርያም (ፕ/ር) STEMpower ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ትምህርቶችን ለማበልጸግ እያደረገ ያለውን ትብብር በማመስገን፥ ዩኒቨርሲቲዎችም ዕድሉን በመጠቀም በአግባቡ ማዕከላቱን ማሳለጥ እንደሚጠበቅባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

    አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በማስተማሪያ ክፍሎቹ ውስጥ ዲጂታል ሰሌዳዎችን መጠቀም ጀመረ።

    የሳንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር) በበኩላቸው ለሰባቱ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚዳንቶች (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲአዲግራት ዩኒቨርሲቲአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲጅማ ዩኒቨርሲቲ እና ወሎ ዩኒቨርሲቲ) ማዕከሉን በመጠቀም በአካባቢዎቻቸው ያሉትን የማኅበረሰብ ችግሮች መፍታት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

    የSTEMpower አስተባባሪ ዳይሬክተርና ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ቅድስት ገብረአምላክ፥ “STEMpower ከየት ወዴት?” በሚል ርዕስ ከድርጅቱ አመሠራረት ጀምሮ ዓላማውን፣ አሁን ያለበት ሁኔታ እና የወደፊት ዕቅድ አጭር ማብራሪያ ለተሳታፊዎቹ አቅርበዋል። ለወደፊትም ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ጋር በስፋት እንደሚሠሩ ፣ በ2040 የበለጸገች ኢትዮጵያን ማየት እንደሆነ ገልጸዋል።

    አገራችን ኢትዮጵያ የራሷን የሆነ ጥንታዊ ታሪክና ባህል ያላት አገር እንደመሆኗ ድርጅቱ በማኅበራዊ ሳይንስ ላይም ትኩረት እንዲያደርግ ከተሳታፊዎቹ አስተያየት ተሰንዝሯል።

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር ማዕከሎቹ በከፍተኛ ትምህርት እና በሳይንስ ትምህርቶች አከባቢ የሚስተዋሉትን ችግሮች በመቅረፍ የአገሪቱን ብልጽግና ከማረጋገጥ ረገድ መልካም ሁኔታ እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል።

    ምንጭ፦ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    STEMpower


    Semonegna
    Keymaster

    የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት በቅርቡ ዋና ካምፓሱን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፍቼ ከተማ በምድረግ ከተመሠረተው ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ጋር አብሮ ለመሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መለሰ ማርዮ እና የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገናናው ጎንፌ ጥር 8 ቀን 2011 ዓ.ም. በኢንስቲትዩቱ አዳራሽ እውቀትን ለማሸጋገር፣ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በጋራ ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።

    የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መለሰ ማርዮ በስምምነት ፊርማው ላይ ባደረጉት ንግግር እንዳስታወቁት የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት ጋር አብሮ ሊያሠራው የሚችል ስምምነቶችን በመፈራረም የተለያዩ ተግባራትን ለማከናወን መቻሉን ገልጸዋል። ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በዱረም ስንዴ ላይ በተሠራው ሥራ ከፍተኛ ምርት የሚሰጥና ድርቅን መቋቋም የሚችል ውጤት መገኝቱን፤ ከጎንደር ዩኒቨረሲቲ ጋር በመተባበር በደን ልማት ላይ እየተሠራ መሆኑን እና ከዲላ ዩኒቨረሲቲ ጋርም በመተባበር ለምርምርና ለቱሪስት መስህብ የሚውል የቦታኒክ ጋርደን ግንባታ ሥራ ከተከናወኑ ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

    VIDEO: Ethiopia: After mandatory preparations, Selale University accepts incoming students

    የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገናናው ጎንፌ በበኩላቸው ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በቅርብ ጊዜ ሥራ የጀመረ፣ እየሰፋ የሚሂድና ለግብርና እና የአካባቢ ጥበቃ ልዩ ትኩረት የሚሰጥ ነው። የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ካለው መልካአ ምድራዊ አቀማመጡ ጋር በተያያዘም በእንስሳት ዝርያ አጠባበቅ በተለይም የተለያዩ ዝርያዎችን በማዳቀል ለአዲስ አበባ ከተማ 50 በመቶ የሆነውን የወተት ምርት የሚያቀርበው የሰላሌ አርሶ አደርን ተጠቃሚ ለማድረግ ከኢንስቲትዩቱ ጋር አብረው ለመሥራት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

    ዶ/ር ገናናው አክለውም ስምምነቱ የወረቀት ላይ ስምምነት ብቻ እንዳይሆን ለማድረግና የብዝሀ ሕይወት ጥበቃ ሥራዎችን ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ከመማር ማስተማር ሥራው ጎን ለጎን የአካባቢውን ማሕበረሰብ ተጠቃሚ የማድረግ ሥራ ለማከናወን ዩኒቨርሲቲው መዘጋጀቱን ገለጸዋል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦  

    የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ዋልታ)– ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ድርጅቶች የሚመረቱ የታሸጉ ውሃዎች ላይ ሁነኛ የሆነ የጥራት ችግር እንዳለ ተገለፀ።

    በአገሪቱ ለመጠጥ ውሃ የሚውሉት የታሸጉ ውሃዎች ላይ በሚታየው የጥራት መጓደል ምክንያትም በኅብረተሰቡ ላይ አሉታዊ የጤና ችግር መንስዔ ከመሆናቸው ባሻገር አገሪቱ ማግኘት ያለባትን ገቢ አለማግኘቷም ተገልጿል።

    የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ በውሃ ምርቶች ላይ የሚስተዋሉትን ችግሮችና የጥራት ማስጠበቅ ሥራዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ጥር 23 ቀን 2011 ዓ.ም. አካሄዷል።

    ቪዲዮ፦ የታሸጉ ውሃዎች በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ የመጣው ፍላጎት እና የውሃዎቹ ያልተመጣጠነ ዋጋ

    በመጠጥ ውሃ የፕላስቲክ ማሻጊያዎቹ ክዳን ላይ የሚለጠፉትና ከፍተኛ የውጭ ምናዛሬን የሚጠይቁ ግብዓቶች ተመሳስለው በሀገር ውስጥ የሚሠሩ በመሆኑ የማሸጊያዎችም የምርት ጥራት ላይ ችግር እየተስተዋለ በመሆኑ ይህን ለማስቀረት እየተሠራ ይገኛል።

    በሀገሪቱ እየተስፋፉ ያሉ የውሃ ማምረቻ ተቋማት ንፁ ውሃን በማቅረብ እና ኢኮኖሚውን ከመደገፍ አንጻር አበረታታች ሥራ ቢሠሩም አሁንም ግን ዘርፉ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚንስትር ዴኤታ አቶ እሸቱ አስፋው ተናግረዋል።

    በርካታ በሀገሪቱ የሚኖሩ ኤምባሲዎችና የውጭ ኮሚኒቲ አካላት የታሸጉ ውሃዎችን ወደ አገር ውስጥ እያስገቡ በመሆኑ፤ በዘርፉ ያለውን የጥራት ችግር ያሳያል።

    የምርቶቹን የጥራት ደረጃ በማሻሻል ለውጭ ገበያ እንዲቀርቡ በማድረግ ሀገሪቱን ከዘርፉ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ለማሳደግ መሥራት እንደሚገባ ሚኒስትር ዴኤታው ተናግረዋል።

    የምርቶችን የአመራረት፣ የአስተሻሸግ፣፤ የማጓጓዝ እና የአቀማመጥ ሆነ ለገበያ በሚቀርቡበት ጊዜ ያለው አያያዝ ችግር ምርቶቹን በከፍተኛ ሁኔታ የጥራት ችግር እንዲጋለጡ ማድረጉን ሚኒስትር ዲኤታው አክለው ገልጸዋል።

    አሁን በሥራ ላይ የሚገኙ ከ 65 በላይ የታሸጉ ውሃ አምራቾች አለም አቀፉን የጥራት ደረጃ በጠበቀ መልኩ እንዲያመርቱ እየተሠራ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ ዳይሬክተር አቶ ይልማ መንግስቱ ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ ዋልታ ሚዲያ / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ 
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የታሸጉ ውሃዎች


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)– የአሜሪካ ኢምባሲ 2ኛውን ‹‹SolveIT›› የተሰኘ ሀገር አቀፍ የፈጠራ ውድድርን የኢዲስ አበባ ከተማን በይፋ አስጀመረ። ኢምባሲው ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ ከጃፓን ዓለማቀፋዊ ኮኦፐሬቲቭ ኤጀንሲ (Japan International Cooperation Agency – JICA) እና ከአይኮግ ላብስ (iCog Labs) ጋር በመተባር ነው ውድድሩን ይፋ ያደረገው።

    ፕሮጀክቱ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ 15 ከተሞች የሚካሄድ ሲሆን ቴክኖሎጂ ነክ የፈጠራ ሥራዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው።
    ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂ ነክ የፈጠራ ሰራዎች ያሏቸው ወጣቶች የሚሳተፉበት ይህ ውድድር የፈጠራ ባላሙያዎቹ ሥራዎቻቸውን ሊያዳብር የሚችል ስልጠና በየከተሞቹ ይሰጣቸዋል።

    SolveIT ሀገር አቀፍ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድርን የአሜሪካ ኢምባሲና የጃፓን ዓለማቀፋዊ ኮኦፐሬቲቭ ኤጀንሲ ፕሮጀክቱን በገንዘብ ይደግፉታል። ተመሳሳይ ፕሮግራሞች በየከተሞቹ የሚዘጋጁ ሲሆን የተመረጡ ችግር ፈቺ የፈጠራ ሥራዎች ለሽልማት ይበቃሉ ተብሏል።

    VIDEO: These two Ethiopian students are working to launch their own rocket – the future Eng. Kitaw Ejigu

    የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የኢኖቬሽን ልማትና ምርምርና ዘርፍ ዳይሬክተር ጀነራል ካህሊድ አህመድ (ዶ/ር) በፕሮጀክቱ ተመርጠው የመጡ የፈጠራ ሥራዎች ገበያውን እንዲቀላቀሉ ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

    ተጨማሪ ስልጠና የሚያስፈልጋቸውን በቴክኖሎጂ ማበልፀጊያ ማዕከላት በማስገባትና የሥራ ማስጀመሪያ ገንዘብ በመደጎም ጭምር ድጋፍ እንደሚያደረግ አረጋግጠዋል።

    የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ በዋናነት ስፖንሰር የሚያደርገው SolveIT ውድድር በወጣት ኢትዮጵያውያን ዘንድ የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂ፣ የኢንጂነሪንግ፣ የአርት እና የሒሳብ (STEAM) በወጣቶች ዘንድ ይበልጥ እንዲጎለብቱ የሚያበረታታ ውድድር ሲሆን ፥ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ለሚኖሩበት ህብረተሰብ፣ ብሎም ለሀገራቸው ችግር ፈቺ የሆኑ የቴክኖሎጂ፣ የሶፍትዌርና የሀርድዌር ፈጠራዎችን በመፍጠር እንዲሳተፉ ያደርጋል።

    ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 28 ዓመት የሆነ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በሚኖሩበት ከተማ ሆነው ህብረተሰባቸው የሚያጋጥመውን ችግር ሊፈታ የሚፍል ፈጠራ ለመፍጠር ለዘጠኝ ወራት ያህል ጊዜ ተሰጥቷቸው ይሠራሉ። በዚህም ጊዜ ከአወዳዳሪዎች በተመደቡላቸው ባለሙያዎች ስልጠና ይሰጣቸዋል። ፈጠራዎቻቸው ከሞባይ አፕ (mobile app) ጀምሮ እስከ ከፍ ያለ የኮምፒዩተር ሶፍትዌር ሊሆን ይችላል። በከተሞቻቸው (በክሎቻቸው) አሸናፊ የሆኑ ተወዳዳሪዎች ከፍ ወዳለው (የፌደራል) ውድድር ያልፋሉ፤ በዚያም ለሳምንት ያህል በዳኞች ና በከፈተኛ ኤክስፐሮች እየተዳኙ ይወዳደራሉ። በዚህም የመጨረሻዎቹ አሸናፊዎች ይለያሉ።

    በአሁኑ ጊዜ ተወዳዳሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል። የበለጠ መረጃ የአይኮግ ላብስ (iCog Labs) ድረ ገጽ ላይ ማግኘት ሲችሉ (እዚህ ጋር ይጫኑ)፥ መመዝገቢያውን ደግሞ እዚህ ጋር ያገኙታል (Register)።

    ምንጭ፦ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    SolveIT ውድድር


    Semonegna
    Keymaster

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ ኃይል የሚጠቀሙ ደንበኞቹ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳባቸው በባንክ እንዲከፍሉ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ጥር 13 ቀን 2011 ዓ.ም. ተፈራርሟል።

    ስምምነቱን የተፈፀመው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ እና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የባንክ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ደረጄ ፉፋ አማካኝነት ነው።

    ኢትዮ ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ተሸካሚ ላይ የተዘረጋውን ገመድ በጋራ ለመጠቀም ተስማሙ

    የመግባቢያ ስምምነቱ ዋና ዓላማ በመጀመሪያው ምእራፍ 27 ሺህ የሚሆኑ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚጠቀሙ እንዲሁም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳባቸውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል እንዲከፍሉ ለማስቻል እና በቀጣይም በአፈጻጸም ሂደቱ የተገኙ ተሞክሮዎችን በማካተት በመላ ሀገሪቱ ያሉ ደንበኞች ላይም ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር አስታውቀዋል።

    ተቋሙ ቀድሞ ይጠቀምበት የነበርውን የፍጆታ ሂሳብ አሰባሰብ ስርዓት በመቀየር፣ ቀልጣፋና በዘመናዊ ቴክኖሎጅ የታገዘ አገልግሎት ለደንበኞቹ ለመስጠት እንደሚስያችለው አክለው ገልፀዋል። ይህም በመሆኑ ተቋሙ፣ ባንኩና ደንበኞች የፍጆታ ሂሳብ ለመክፍል ይፈጠር የነበረውን የገንዘብና የጉልበት ብክነት በከፍተኛ ደረጃ ስለሚቀንሰው፤ ሦስቱም አካላት ተጠቃሚ ይሆናሉ ሲሉ ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የተናገሩት።

    አዳዲስ የቴክኖሎጂ ዕውቀቶችና ልምዶች የተገኙበትና በምስራቅ አፍሪካ በርዝመት ቀዳሚውን ስፍራ የያዘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ህንጻ

    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የባንክ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ደረጄ ፉፋ በበኩላቸው፥ ዘመናዊ የክፍያ ስርዓት መዘርጋቱ ደንበኞች ሳይጉላሉ ካሉበት ስፍራ ሆነው ክፍያ በባንኩ አማካኝነት በቀላሉ ለመክፍል እንደሚያስችላቸው ገልፀዋል። ሲያጋጥሙ የነበሩ የአከፋፈል ስርዓት ችግሮችን እንዲቀርፍ ያስችላል፤ ደንበኞችም ያጠፉት የነበረውን ጊዜና የሚያጋጥማቸው ውጣ ውረድ ይቀንስላቸዋል ሲሉ ነው አክለው የተናገሩት።

    በስምምነቱ መሠረት እነዚህ ደንበኞች በቂ ግንዛቤ በተለያዩ አማራጮች ካገኙ በኋላ በያዝነው ዓመት ከሚያዝያ ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ እንዲሁም የዚህን ጅምር ሥራ ውጤታማነት ከታየ በኋላ ሁሉም ደንበኞች በተመሳሳይ መልኩ ክፍያ እንዲፈፅሙ በቀጣይ አንደሚደረግ ተገልጿል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት


    Semonegna
    Keymaster

    የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጅክቶቹ በገንዘብ ሚኒስቴር የ100 ቀናት ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ሲሆን ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ 798 ኪሎ ዋት የማመንጭት አቅም አላቸው። የፕሮጀክቶቹ ወጪ 795 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደሚገመት በጥናቱ ላይ ተመላክቷል።

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – በኢትዮጵያ መንግስትና በግል ድርጅቶች (ኢንቨስተሮች) አጋርነት የሚሠሩ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል።

    ጥር 9 ቀን 2011 ዓ.ም. በገንዘብ ሚኒስቴር በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተገለፀው ስድስቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በአፋር፣ በሶማሌ፣ በኦሮሚያ እና በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት ስር ይተገበራሉ ተብሏል።

    ስድስቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጅክቶች በገንዘብ ሚኒስቴር የ100 ቀናት ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ሲሆን ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ 798 ኪሎ ዋት የማመንጭት አቅም አላቸው። የፕሮጀክቶቹ ወጪ 795 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደሚገመት በጥናቱ ላይ ተመላክቷል።

    የኮምቦልቻ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ የውጪ ንግዱን ለማሳደግ እና የምርት መጠኑን ለመጨመር እየሠራ መሆኑን አስታወቀ

    የገንዘብ ሚኒስቴር ዴኤታ ተሾመ ታፈሰ (ዶ/ር) አገሪቱ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ ለመሰለፍ ያስቀመጠችውን ራዕይ ለማሳካት ከዚህም ጋር ተያይዞ በየጊዜው ሳያቋርጥ እያደገ የመጣውን የህዝብ የኃይል አገልግልት ፍላጎት ለማሟላት ከመንግስት የፋይናንስ ምንጮች በተጨማሪ ሌሎች አማራጮችን ማየት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ሲሉ ገልጸዋል።

    የመንግስትና የግል አጋርነት (መግአ) የመሠረተ-ልማት አቅርቦትን ለማሻሻል እንደ አንድ ስልት የሚወሰድ ነው ያሉት ዶ/ር ተሾመ በአግባቡ ሥራ ላይ ከዋለ የግሉን ዘርፍ የኢንቨስትመንት አቅም እንደ አስፈላጊነቱ ለመጠቀም እድል ይሳጣል ሲሉ ተናግረዋል።

    ምንጭ፦ የገንዘብ ሚኒስቴር/ ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ሌሎች ዜናዎች፦

    የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጅክቶች


Viewing 15 results - 1 through 15 (of 28 total)