Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Home Forums Search Search Results for 'ኢትዮጵያ'

Viewing 15 results - 181 through 195 (of 730 total)
  • Author
    Search Results
  • Anonymous
    Inactive

    ኢንጂነር ታከለ ኡማ በአዲስ አበባ መሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢፍትሃዊ ዕደላን በተመለከተ ላወጣው ጥናታዊ ሪፖርት የሰጡት ምላሽ

    በሀሰተኛ መረጃ ሀገር ማፍረስ ይቻል ይሆናል እንጂ ሀገር አይገነባም – የፖለቲካ ትርፍም የለውም!!

    ለዚህ ምላሽ ለመስጠት ተገቢው ቦታ ላይ ባልገኝም፥ ከዚህ የመጓተት ፖለቲካ አስተሳሰብ መውጣት አለመቻል ግን ትልቅ ህመም እንደሆነ ይሰማኛል።

    የመሬት ወረራን በተመለከተ ከመጀመሪያዋ ቀን ጀምሮ እስከ መጨረሻዋ እለት ድረስ ጠንካራ የሆነ እርምጃ ስንወስድበት የቆየንበት ጉዳይ ነው። በተለያዩ ጊዜዎች የወሰድናቸው እርምጃዎችም ህያው ምስክሮች ናቸው።

    እኛ ሕገ-ወጥ የመሬት ወረራን ለመከላከል እርምጃ ስንወስድ፥ የዛሬ ተቺዎች የሰብዓዊ መብት ተነካ፣ ዜጎች ተፈናቀሉ ብለው ዘመቻ ከከፈቱብን ውስጥ ነበሩ። ለ20ሺህ አርሶ አደሮች የተሰጡ የኮንዶሚኒየም ቤቶች በተመለከተም ከአንድ አመት ተኩል በፊት በካቢኔ የተወሰነና የተተገበረ ነው። በድብቅ የተተገበረም ሳይሆን በመንግሥት ሚዲያም በይፋ የተገለፀ ነበር።

    ከመሬታቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ ከወደቁ በራሳቸው መሬት ላይ በተሠራ ህንጻ ዘበኛ እና ተሸካሚ ሆነው ከቀሩ 67 ሺህ አባወራዎች መሃል የከፋ ችግር ላይ ለወደቁት 20 ሺህ ኮንዶሚንየም ቢያንስ እንጂ የሚበዛ አይደለም። ስህተትም ከሆነ ለ67,000ውም አለመስጠታችን ነው። ከዚህ ውጭ በሕገ-ወጥ መንገድ የተሰጠ ምንም አይነት ቤት የለም።

    ይህ ሥራችን በተደጋጋሚ በይፋ ስንናገር እንደነበረው የምናፍርበት ሳይሆን የምንኮራበት ነው። በግፍ የተገፋን፣ በግፍ ከመሬቱ የተፈናቀለን አርሶ አደር መካስ ያኮራናል!

    በዙሪያዋ ካሉት አርሶ አደሮች ጋር በፍቅር ተሳስባ የምትኖር የተሰናሰለች ከተማ እንጂ በዙሪያዋ ካሉት ሕዝቦች ጋር የተቀያየመች ከተማ እንድትኖር አንሻም ነበርና። ይህ ደግሞ የከተማዋ ነዋሪዎች ፍላጎት መሆኑንም እንገነዘባለን።

    አንድም ቀን በግፍ ለተፈናቀሉ አርሶ አደሮች የመቆርቆር ስሜት አሳይቶ የማያውቅ ቡድን ዛሬ የአርሶ አደሮችን ጉዳት ለተቀባይነት ማግኛ መጠቀሚያ ሲያደርገው ማየት ያሳዝናል። ነገር ግን በሀሰተኛ እና በተጋነነ መረጃ ጠንካራ መምሰል እንጂ መሆን አይቻልም።

    በሀሰተኛ መረጃ ድካማችንና ሥራችንን ለማጠልሸት ቢሞከርም ሥራችን ይናገራልና ፍርድ የሕዝብ ነው!

    ኢንጂነር ታከለ ኡማ በንቲ
    የማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስትር
    (የቀድሞው የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ)

    ተያያዥ ጉዳዮች፦

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ፦ በሰሞነኛ ድረገጽ የአማርኛ ፎረም (semonegna.com/forums) ላይ የሚገኝ ማንኛውም ጽሑፍ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንጸባርቅ ሲሆን፥ ጽሑፉ የሰሞነኛ ኢትዮጵያንንም ሆነ የተሳታፊዎችን አመለካከትና ምልከታ ላይወክል ይችላል።

    ኢንጂነር ታከለ ኡማ በንቲ

    Anonymous
    Inactive

    የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)
    በአዲስ አበባ ከተማ መሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢፍትሃዊ ዕደላ ጥናት አንኳር

    • የከተማው አስተዳደር እያየ እና እየሰማ፥ በሕገ ወጥ እና በተደራጀ መልኩ በወረራ የተያዙ ቦታዎች በፍጥነት ካርታና ፕላን ተሠርቶላቸው ለሦስተኛ ወገን በሽያጭ ተላልፈዋል። በማኅበር እና በግል ለማምረቻና ለንግድ አገልግሎት እንዲውሉ ተደርገዋል፤ በምንም መስፈርት የቤት ተጠቃሚ ሊሆኑ የማይገባቸው ግለሰቦችና ቡድኖች ቤት እና የነዋሪነት መታወቂያ ተሰጥቷቸዋል።
    • በዋናነት በመሬት ወረራው ላይ ግንባር ቀደም ተሳታፊ የነበሩት ሰዎች የአርሶ አደር ልጆች ነን የሚሉ፤ ቦታዎቹ ከዚህ ቀደም የቤተሰቦቻችን መሬቶች ናቸው፤ በቂ ካሳ ሳይከፈለን ከቦታችን ተነስተናል የሚሉ ግለሰቦች እና ወረራ የተፈፀመባቸው ቦታዎች አካባቢ ላይ የሚገኙ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ ኃላፊዎች ናቸው።
    • ይህ በጠራራ ፀሐይ በተደራጀ መልኩ የተፈፀመው የመሬት ወረራ በመንግሥት ሥልጣን ላይ ያሉ አመራሮች፤ የፍትህና ፀጥታ አካላት ተጠሪዎች ከፍተኛ እገዛ የተደረገበት ብቻ ሳይሆን እነዚህ አካላት የጉዳዩ ዋና ተዋንያን ነበሩ። በተለያየ መልኩ ሊጠቅሟቸው ለሚፈልጉ ግለሰቦች፣ ቡድኖች እና አደረጃጀቶች መሬቱን ወረው እንዲይዙ አመቻችተዋል፤ የመንግሥትን ሥልጣን ለሕገ ወጥ ተግባር ከለላ እና ሽፋን እንዲሆን አድርገዋል፤ ከዚህም ባስ ሲል ከግለሰቦች ጋር በመመሳጠር እራሳቸው ወረራ ፈፅመዋል።
    • በጠቅላላው 213,900 ካ.ሜ ያህል ስፋት ያለው ቦታ ጥናቱ ባያቸው ጥቂት ቦታዎች ላይ ብቻ መወረራቸውን ለማረጋገጥ ችለናል።
    • ከጋራ መኖሪያ ቤት ጋር በተገናኘም በግልፅ የታየው የመንግሥት አካላት ሕገ ወጥ ተግባር ነው። ኢፍትሐዊ ሕጎችን እና መመሪያዎችን በማውጣት እና ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ሕጎችን እና ደንቦችን በማሻሻል ለካቢኔው እና ለከንቲባው በተሰጠ ልዩ ሥልጣን ከንቲባውም ሆነ ካቢኔያቸው ቤቶችን እንደፈለጉ እንዲያድሉ ምክንያት ሆኗል።
    • በዚህ መሠረት ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ቢሮዎች ሳር ቤት አካባቢ ከሚገኘው ጽሕፈት ቤት ሁሉም የተመዘገቡ ሠራተኞች በሰኔ 12 ቀን 2012 ዓ.ም ብዙ ሺህ ቤቶች የድልደላ እጣ የወጣላቸው ሲሆን፣ የድልድል እጣ ለደረሳቸው ሰዎች ሰኔ 16 ቀን 2012 ዓ.ም ድልድል ተደርጎላቸዋል። በዚህ ቀን ሁሉም ሠራተኞች የኮንዶሚኒየም ብሎክ ቁጥር እና የቤቱን ቁጥር በስማቸው ተረጋግጦ የተሰጣቸው ሲሆን፤ በተሰጣቸው የቤት ቁጥር የነዋሪነት መታወቂያ የተዘጋጀላቸው መሆኑን ለማወቅ ችለናል።
    • የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሕንጻዎች ውስጥ የተሠሩ የንግድ ቤቶች በተመለከተ የልማት ተነሺ አርሶ አደሮች፣ ልጅ እና የልጅ ልጅ ተብለው በገፍ ስለመታደላቸው፤ በእግር ኳስ ደጋፊነት ስም ለተሰባሰቡ ማኅበራት መከፋፈላቸው ተጨባጭ ማስረጃዎች ተገኝተዋል።

    ሙሉውን ሪፖርት ያንብቡ፦ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በአዲስ አበባ መሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢፍትሃዊ ዕደላ ላይ ያደረገው ጥናት ውጤት።

    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    1. እውነታውን በማድበስበስ ከተጠያቂነት ማምለጥ አይቻልም! ― የኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት
    2. አዲስ አበባ ― ዳቦ፣ የመኖሪያ ቤት፣ መብራት እና ውሃ፣ የመሬት ቅርምት፣ ተረኝነተ፣ ሙስና፣ ግፍ፣ ወዘተ…

    ምንጭ፦ ኢዜማ

    የጋራ መኖሪያ ቤቶች

    Semonegna
    Keymaster

    በሁለቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ የልህቀት ማዕከላት የሚሹትን ትኩረት ለይቶ ለመደገፍ ያለመ ጉብኝት ተካሄደ

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ ዳይሬክተር ጄኔራሎች፣ ከፍተኛ አማካሪዎች እና ሌሎች ባለሙያዎችን የያዘ ቡድን በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና በአዳማ ሳይንስና ቴክሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የሥራ ጉብኝት አድርጓል።

    በጉብኝቱ በሁለቱም ዩኒቨርሲቲዎች በአካል በመገኘት ዩኒቨርሲቲዎቹ የልህቀት ማዕከላት ሆነው ከተፈጠሩ ጊዜ አንስቶ ‘የመንግሥትን ተልዕኮ ተሸክመው የት ደርሰዋል? ምን ውጤት አስመዝግበዋል? ያጋጠማቸው ማነቆ ካለስ ምንድን ነው?’ የሚሉትን ጉዳዮች ለመለየትና መፍትሄ ለማስቀመጥ እንደተካሄደ ተገልጿል።

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፕ/ር አፈወርቅ ካሱ የጉብኝቱ ዓላማ በሀገራችን 16 የተለያዩ የልህቀት ማዕከላትን የያዙት አዲስ አበባ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ከተቋቋሙለት ዓላማ አንፃር የሚገባቸውን ያህል እየሠሩ ነው ወይ የሚለውን ለማየት፣ ያጋጠሟቸውን ችግሮች ለመለየትና በዚያው መጠን ድጋፍ ለማድረግ መሆኑን ገልፀዋል።

    ሁለቱን ዩኒቨርሲቲዎች ሐምሌ 2006 ዓ.ም መንግሥት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተቋም እንዲሆኑ አድርጎና ተጠሪነታቸውን በወቅቱ ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አድርጎ ሲያዋቅራቸው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ስርጸት ዩኒቨርሲቲዎች ተብለው በልዩ ሁኔታ የተመሠረቱ ሲሆን፤ ከመማር-ማስተማር ሥራ ጎን ለጎን በጥናትና ምርምር ልህቀት ማዕከልነት (centers of excellence) በኢንዱስትሪ-ዩኒቨርሲቲ ትስስር (industry-university linkages) እና በኢንኩቤሽን ማዕከልነት (incubation centers) እንዲያገለግሉ ታስበው ነው ብለዋል።

    በልህቀት ማዕከላቱ ተማሪዎች ተምረው ሲወጡ ኢንዱስትሪውን በቀጥታ መቀላቀል የሚችሉበት አቅም እንዲያፈሩ ታልሞ መሠራት እንዳለበት ጠቁመው፥ ይህ እውን እንዲሆን ከመቼውም ጊዜ በተለየ ሁኔታ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ሥራዎች ጋር አገናዝበን በቋሚነት በዕቅድ እንድናግዛቸው እንሠራለን ብለዋል ፕ/ር አፈወርቅ። የልህቀት ማዕከላት በሀብት መደገፍ እንዳለባቸው ገልጸው፥ ነገር ግን ከመንግሥት ቋት ብቻ ሊሆን ስለማይቻል ሀብቶች ማፈላለግ ላይ በጋራ መሥራት ይጠበቃል ብለዋል።

    የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸው፥ የተደራጀ ተቋማዊ አሠራር በመፍጠርና ተቋማዊ አቅምን በመገንባት ተቋማቱን ወደ ትክክለኛ የልህቀት ማዕከልነት መለወጥ ይቻላል ብለዋል። በአከባቢያቸው ከሚገኙ ኢንዱስትሪዎች ጋር ትስስር በመፍጠር መሥራት እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል። የሀገራችን የቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና፣ ሳይንስና ምርምር ተቀባይ ብቻ ሆኖ መቀጠል የለበትም ያሉት ዶ/ር ሳሙኤል፥ መሪ እንዲሆኑ ሀብት አፈላልጎ ዩኒቨርሲቲ-ኢንዱስትሪ ትስስር ፈጥሮ መሥራት ሚናው የጎላ ነው ብለዋል። ቴክኖሎጂ ላይ ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ በሁሉም የልዕቀት ማዕከላት የሰው ኃይል ችግር መፍታት እንደሚገባ ጠቁመው፤ ለዚህም ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልና ለሀገር ብልጽግና ካላቸውም ፈይዳ አንጻር በየደረጃው ካሉ ባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል እንዲሚደረግላቸውም ገልፀዋል።

    ቡድኑ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በነበረው ጉብኝት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ደረጀ እንግዳ በዩኒቨርሲቲው ያለውን ነባራዊ ሁኔታ የገለፁ ሲሆን፤ ዓለምአቀፍ እውቅና ለማግኘት የሚያግዙ የአሠራር ሂደቶችን ተከትለው ለመሥራት እየጣሩ መሆኑን ገልፀው፥ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ቢያግዘን ያሏቸውን ተግዳሮቶች አቅርበው ውይይቶች ተካሂደው የመፍትሄ ኃሳቦችም ተጠቁመዋል። ዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ ያሉ የልህቀት ማዕከላት፣ ቤተ-ሙከራዎች እና የግንባታ ሥራዎችም ተጎብኝተዋል።

    በተመሳሳይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ጉብኝት ሲካሄድ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ለሚ ጉታ ዩኒቨርሲቲው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተብሎ ከተሰየመበት ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ የተሰሩ ሥራዎችን እና ያጋጠሙ ችግሮችን፥ እንዲሁም የተፈጠሩ ትስስሮችን (partnerships) እና አጠቃላይ በዩኒቨርሲቲው ያለውን የሰው ሀብትና ተማሪዎች መረጃ አቅርበው ውይይት ተካሂዷል። በዩኒቨርሲቲው ልዩ ነው ያሉትን የደብል ሜጀር እና ፋስት ትራክ የትምህርት አሰጣጥ ሁኔታንም ጨምረው አብራርተዋል። ፕሬዚዳንቱ እንዳሉት፥ በአሁኑ ጊዜ በዩኒቨርሲቲው 161 የሦስተኛ ዲግሪ (doctoral) ተማሪዎች አሉ።

    በሁለቱ ጉብኝቶች ከተነሱት ዋና ዋና ድጋፍ የሚሹ ጉዳዮች ውስጥ የግዥ ሥርዓት ችግሮች፣ የተሽከርካሪዎች እጥረት፣ ብቁ መምህራን ከገበያ ላይ በቀላሉ ያለማግኘት፣ በፋይናንስ ምክንያት የግንባታ ሥራዎች መዘግየት ይገኙበታል።

    በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በነበረው ቆይታ ማጠቃለያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሙሉ ነጋ እንዳሉት፥ የልህቀት ማዕከላት ሲባል አንድ ተቋም በአገሪቱ መሪ የሆነ የቴክኖሎጂ ማዕከል መሆን ማለት ነው። ይሄንን ደግሞ ከኢንዱስትሪ ጋር ትስስር በመፍጠር፣ ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና (TVET) ማዕከላት ጋር በመቀናጀት ኢንዱስትሪውን የሚመጥን፣ የኢንዱስትሪውን ፍላጎት ያሟላ ሰልጣኝ ለገበያ የሚያቀርብ፣ ተግባራዊ ምርምሮች የሚካሄዱበት መሆን ሲቻል ነው ብለዋል።

    ዩኒቨርሲቲዎቹ ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ድጋፍ እንፈልጋለን ብለው ያቀረቧቸውን በመውሰድ እንሠራበታለን ሲሉም ዶ/ር ሙሉ አክለዋል። ዩኒቨርሲቲዎቹ ዘመናዊ የሳይንሳዊ አስተሳሰቦች እና የቴክኖሎጂ ውጤቶች ተገናኝተው ለሀገር ብልጽግና የሚውሉባቸው እንደመሆናቸው አስፈላጊው ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።

    በሁለቱም ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ የልህቀት ማዕከላት በቡድኑ የተጎበኙ ሲሆን፤ በጉብኝቱም ዩኒቨርሲቲዎቹ የተለያዩ የሀገር ሀብት የሆኑና ምናልባትም በኢትዮጵያ ውስጥ በሌሎች ተቋማት የሌሉና በተለይ ለምርምር ትልቅ ፋይዳ ያላቸው እንደ ኤሌክትሮማይክሮስኮፕ ያሉ መሣሪያዎች መኖራቸው ተመልክቷል። ይሄንንም ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር ትስስር በመፍጠር በጋራ ለመጠቀም የሚቻልባቸው ሁኔታዎች ማመቻቸት ያስፈልጋል ተብሏል። በቀጣይም ተቋማቱ የተፈጠሩበትን ዓላማ ማሳካት እንዲችሉ እና ውጤታማ ሥራዎችን ለመሥራት እንዲቻላቸው የሚያግዙ የታቀዱ ድጋፍና ክትትሎች ከሌላው ጊዜ በተለየ ይካሄዳሉ ተብሏል።

    አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚገኙ የልህቀት ማዕከላት፦

    1. Sustainable Energy
    2. Mineral Exploration, Extraction and Processing
    3. Nano Technology
    4. Bioprocessing and Biotechnology
    5. Construction Quality and Technology
    6. High Performance Computing and Big Data Analysis
    7. Artificial Intelligence and Robotics
    8. Nuclear Reactor and Technology

    አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚገኙ የልህቀት ማዕከላት፦

    1. Space Technology Institute
    2. Institute Of Pharmaceutical Science
    3. Institute Of Water Resource and Irrigation Engineering
    4. Electrical System and Electronics
    5. Advanced Manufacturing Engineering
    6. Advanced Material Engineering
    7. Urban Housing and Development
    8. Transportation and Vehicle

    ምንጭ፦ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር

    ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ እና መቀሌ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን አስመረቁ

    ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ እና የተከታታይ ትምህርት መርሀ ግብር የድኅረ-ምረቃ ተማሪዎቹን ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም አስመርቋል። የክብር እንግዳና አስመራቂ በመሆን በቪዲዮ ኮንፍረንስ መልዕክታቸዉን ለተመራቂዎች ያስተላለፉት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤ ክፍሌ፥ ተመራቂዎች ሀገራቸዉን ከድህነትና ኋላ-ቀርነት ለማላቀቅ በያዙት ሙያ ጠንክረዉ በመሥራት የበኩላቸዉን እንዲወጡ ጥሪያቸዉን በማስተላለፍ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸዉን ለተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸዉ አስተላልፈዋል ።

    ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ (ኮቪድ-19) ጋር ተያይዞ ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በተቀመጠዉ አቅጣጫ መሠረት፥  በበይነ-መረብ (online) አማካኝነት በማስተማር የድኅረ-ምረቃ ትምህርታቸዉን ሲከታተሉ ከነበሩ ከ45 ተማሪዎች ዉስጥ 38 ተመራቂዎች በኤሌክትሪካል ፓወር ኢንጂነሪንግ (electric power engineering)፣ በሕብረተሰብ ጤና ሳይንስ (public health)፣ በቢዝነስ አድሚንስትሬሽን (business administration)፣ በአካዉንቲንግ እና ፋይናንስ( accounting and finance) በዩኒቨርሲቲዉ ሴኔት ሌጅስሌሽን መሠረት የድኅረ ምረቃ  መስፈርቱን ስላሟሉ መመረቃቸዉን የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሀብታሙ አበበ በይፋ በማስታወቅ፤ ተመራቂዎች በተማሩበት መስክ የሰዎች ልጆችን ክብር ጠብቀዉ ሀገራቸዉን በቅንነት እንዲያገለግሉ ጥሪያቸዉን አስተላልፈዋል ።

    ፕሬዝዳንቱ አክለዉም ተመራቂዎች ወደ ብልጽግና ሀገሪቱን ለሚያሸጋግሩት ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ እና ለልዩ ልዩ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶች የበኩላቸዉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ በማስተላለፍ በራሳቸዉ እና በዩኒቨርሲቲዉ ማሕበረሰብ ስም የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸዉን ለተመራቂዎች እና ለቤተሰቦቻቸዉ አስተላልፈዋል ።

    የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አቅናዉ ካዉዛ፣፥ የሀድያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ እና የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲዉ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት እና የዩኒቨርሲቲዉ የማኔጅመንትና የሴኔት አባላት የምረቃዉን ሥነ-ሥርዓት መታደማቸዉም ተመልክቷል።

    በዕለቱ ከተመረቁት ተማሪዎች መካከል ተሾመ ሊሬ በሰጠው አስተያየት፥ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ተጽዕኖ ተቋቁሞ ለምረቃ በመብቃቱ መደሰቱን ገልጿል። በሀገሪቱ መከፋፈልን የሚፈጥሩ ጉዳዮችን በመተው፥ በአንድነት ለእድገት መሰለፍ እንደሚባ አመልክቶ በሰለጠነበት ሙያ ሀገሩን ለማገልገል እንደሚጥርም ተናግሯል።

    በሀገሪቱ የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ ለማሳካት በቅንጅት መሥራት ያስፈልጋል ያለው ደግሞ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን (business administration) ሙያ የተመረቀው መስቀሉ ዳራ ነው። በሰለጠነበት ሙያ ራሱን፣ ብሎም ቤተሰቡንና ሀገሩን በመገልገል የዜግነት ግዴታውን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑንም ገልጿል።

    ከተማሪዎች ምርቃት ዜና ሳንወጣ፥ መቀሌ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች እና የዲግሪ መርሀ-ግብሮች ያስተማራቸውን ተማሪዎች በዚሁ ዕለት (ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም) በበይነ-መረብ (virtual) አስመርቋል። በዕለቱ በመጀመሪያ ዲግሪ (bachelor)፣ በሁለተኛ ዲግሪ (master) እና በሦስተኛ ዲግሪ (doctorate) እና ስፔሻሊቲ ዲግሪ (specialty degree) ትምህርታቸውን ተከታትለው ያሰመረቃቸው ተማሪዎች ቁጠር በአጠቃላይ 4,290 እንደሆነ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ፕ/ር ክንደያ ገብረሕይወት ያገኘንው መረጃ ያመለክታል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ናቸው።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)

    ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ

    Anonymous
    Inactive

    ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 4,700 ተማሪዎችን ዛሬ አስመረቀ

    ሐዋሳ (ኢዜአ/HU) – ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በበይነ-መረብ (virtual) ትምህርታቸውን እንዲጨርሱ ያስቻለቸውን የድኅረ ምረቃ (ሁለተኛ እና ሦስተኛ ዲግሪ) ተማሪዎች እንዲሁም ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት በፊት በእንስሳት ሕክምና እና በሌሎች መርሀ-ግብሮች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ የመጀመሪያ ዲግሪ 4,780 ተማሪዎችን ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም አስመረቀ።

    ዩኒቨርሲቲው ለ21ኛ ጊዜ ካስመረቃቸው መካከል 2,866 በመጀመሪያ፣ 1,900 በሁለተኛ እና 12 ደግሞ በሦስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸው መሆናቸውን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አያኖ በራሶ ገልጸዋል።

    ተማሪቂዎችና ቤተሰቦቻቸው በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ (ኮቪድ-19) ምክንያት የተፈጠረውን አስቸጋሪ ሁኔታ ተቋቁመው ለመመረቅ በመብቃታቸው እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው ወረርሽኙን ከመከላከሉ ሥራ በተጓዳኝ ችግር ፈቺ የምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎች ላይ ትኩረት በመስጠት እና የመንግሥትን የልማት እንቅስቃሴ በጥናት ለመደገፍ ጥረት እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ወረርሽኙን እየተከላከሉ መደበኛ የትምህርት ሥራቸውን ለመጀመር እየተዘጋጁ መሆኑን ገልጸዋል።

    ዶ/ር አያኖ በአዲሱ ፍኖተ-ካርታ መሠረት የምርምር ዩኒቨርሲቲ (Research University) ለመሆን ከሚጠበቁት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በቀዳሚነት ለማሰለፍ በቁርጠኝነት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።

    የዩኒቨርሲቲው ምክትል ቦርድ ሰብሳቢና የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው ተመራቂዎች የቀሰሙትን ዕውቀት በተግባር በማዋል የሀገሪቱን ዕድገት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። ተቋሙ በተደራረበ ጫና ውስጥ እያለ ተማሪዎችን ማስመረቁ፥ ምርምርና የማኅበረሰብ አገልግሎቶችን አጠናክሮ መቀጠሉ የአመራሩንና የሠራተኞችን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው ብለዋል።

    በእንስሳት ሕክምና ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የተመረቀው ዶ/ር ግርማ በዳዳ በሰጠው አስተያየት፥ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ጫና በመቋቋምና ጥናቱ ላይ በመትጋት ለምርቃ መብቃቱን ተናግሯል። ለዚህም ዩኒቨርሲቲውን አመሰግኗል።

    ሌላዋ በሶሻል ሣይኮሎጂ የሁለተኛ ዲግሪ ተመራቂ ማርታ ማጋ በበኩሏ፥ ወረርሽኙ ከመከሰቱ በፊት የክፍል ትምህርት ማጠናቀቃቸውን ጠቅሳ፤ የምርምር ሥራዋን ከዩኒቨርሲቲው ውጭ በማካሄድ ለመመረቅ እንደበቃች ገልጻለች።

    ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛና ተከታታይ የትምህርት መርሀ-ግብር የሚያስተምራቸው ከ43,000 በላይ ተማሪዎች እንዳሉት ከዩኒቨርሲቲው ድረ-ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ዩኒቨርሲቲው በአጠቃላይ ከ7,000 በላይ ሠራተኞች (staff)፣ ሰባት ካምፓሶች፣ ስምንት ኮሌጆችና ሁለት ተቋማት (institutes)፣ እና ከ200 በላይ የትምህርት መርሀ ግብራት (programs) እንዳሉት ድረ-ገጹ ያሳያል።

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)/ ዩኒቨርሲቲው (HU)

    ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ

    Semonegna
    Keymaster

    ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መርሀ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 7520 ተማሪዎች በበይነ-መረብ አስመረቀ

    (ባሕር ዳር) – ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በድኅረ ምርቃ መርሀ-ግብር በሁለተኛ ዲግሪ በመደበኛውና በተከታታይ መርሀ-ግብር 2254 ተማሪዎች፣ በሦስተኛ ዲግሪ መርሀ-ግብር 40 ተማሪዎች፣ እንዲሁም በስፔሻሊቲ መርሀ-ግብር 41 ተማሪዎች፣ በምስክር ወረቀት መርሀ-ግብር 642 ተማሪዎች በድምሩ 7520 ተማሪዎችን በበይነ-መረብ በመታገዝ ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም አስመርቋል። ከተመራቂ ተማሪዎቸ መካከል 2345 ሴቶች ሲሆኑ፤ ከእነዚህ ሴት ተመራቂ ተማሪዎች መካከል አምስቱ የሦስተኛ ዲግሪ ተመራቂ ተማሪዎች መሆናቸው ታውቋል።

    በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አባል ወ/ሮ ሰሀረላ አብዱላሂ፣ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ዋና ዳሬክተርና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አባል ፕ/ር ማስረሻ ፈጠነ፣ እንዲሁም የአማራ መልሶ ማቋቋም ልማት ድርጅት /አመልድ/ ዋና ዳሬክተርና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አባል ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ፣ የዩኒቨርሲቲው የሴኔት አባላት፣ ዲኖችና ዳይሬክተሮች እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።

    በሥነ-ሥርዓቱ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ ለተመራቂ ተማሪዎችና ለተመራቂ ቤተሰቦች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልክዕት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም ዓለምን ባስጨነቀው የኮሮና ወረርሽኝ ተግዳሮት ሳይደናቀፉ የሚጠበቅባቸውን አሟልተው ለተመረቁ ተማሪዎች አድናቆታቸውን ገልፀው ወደ ቀደምት ትልቅነታችን እና ጥበብ ለመመለስ እና አሁን የጀመርናቸውን የአባይ ግድብን ጨምሮ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለማሳካት የጋራ መድኃኒት ስለሚያስፈልገን ሁላችንም ለሀገራችን ሰላም በጋራ መሥራት እንደሚገባን አሳስበዋል።

    የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን (ኮቪድ-19) ለመከላከል እና ለመቆጣጠር እየተደረገ ባለው እንቅስቃሴ ዩኒቨርስቲዎች ሕይወትን ለመታደግ የእውቀት እና የሕዝብ ተቋምነታቸውን ማስመስከራቸውን ጠቅሰው ለዚህም ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያስችሉ ቁሳቁሶችን በማምረት እና በርካታ የፈጠራ ሥራዎችን በማበርከት ሕበረተሰቡን ከወረርሽኙ እየታደገ መሆኑን ዶ/ር ፍሬው ገልፀዋል። በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት ተማሪዎች በኮቪድ-19 ምክንያት ሙሉ በሙሉ ከትምህርት እንዳይለዩ በዩኒቨርሲቲው የICT ባለሙያዎች የበለፀገ የትምህርት አስተዳደር ሥርዓት (learning management system) ለአማራ ክልለዊ መንግሥት ትምህርት ቢሮ ማበርከቱን አውስተዋል።

    በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚንስትርና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ እንዳሉት መማር ትርጉም የሚኖረው የሕበረሰተቡን ኑሮ ማሻሻልና ለችግሮቹ መፍቻ የሚሆን አዳዲስ አሠራሮችንና ሀሳቦችን መፍጠር ሲቻል መሆኑን ጠቁመው የሀገራችን ችግር የሚፈታው የችግሮችን ስፋትና ጥልቀት በሚረዱ ምሁራን በመሆኑ የምንግዜም ጠላታችን የሆነውን ድህነትን ለማስወገድ ተመራቂ ተማሪዎች በተመረቁበት መስክ ትኩረት ሰጥተው ለመሥራት ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

    አክለውም፥ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የልሕቀት ማዕከል ለመሆን የሚያደርገውን ትጋት አድንቀው፤ በእምቦጭ ዙሪያ ብዙ ሥራ መሥራት የሚያስችል በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ትኩረት ሰጥቶ በስፋት እንዲሠራ ጥሪ አቅርበዋል። ከአባይ ፏፏቴ ጀምሮ እስከ ሰሜን ብሔራዊ ፓርክ ድረስ ትኩረት በመስጠት የቱሪዝም ኮሪደር ለማድረግ የሚቻልበትን ምርምር በመሥራት መሻሻል የሚገባቸውን ጉዳዮች ማሳየትም ከዩኒቨርሲቲው እንደሚጠበቅ ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ ተናግረዋል።

    የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱን ጥቂት ተማሪዎች አዳራሽ ውስጥ በአካል በመገኘት፥ አብዛኛዎቹ ተመራቂ ተማሪዎች ደግሞ በየቤታቸው ሆነው በአማራ ቴሌቪዥን ከጥበብ ህንፃ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በቀጥታ ስርጭት፣ በፌስቡክ (Facebook) እና ዩቲዩብ (YouTube) የተላለፈውን ታድመዋል።

    ምንጭ፦ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

    ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

     

    Semonegna
    Keymaster

    የፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሀብታቸውን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ ያልሆኑ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ተጠያቂ አደረገ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ) – የፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሀብታቸውን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ ያልሆኑ 184 የሚሆኑ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ጉዳያቸው በምርመራ እንዲጣራ እና ክስ እንዲመሠረት ነሐሴ 20 ቀን 2012 ዓ.ም ስም ዝርዝራቸውን ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን መላኩን አስታወቀ።

    ኮሚሽኑ ሀብትና ንብረት የማስመዝገብ ግዴታ ያለባቸውን ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ሀብታቸውን እንዲያስመዘግቡ በተለያየ ጊዜ በቴሌቪዥን፣ በሬድዮ እና በደብዳቤ ጥሪ ባስተላለፈው መሠረት አብዛኞቹ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ሀብትና ንብረታቸውን አስመዝግበዋል።

    ይሁን እንጂ በፌደራልና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደረጃ 184 የሚሆኑ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ኮሚሽኑ ባስቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሀብትና ንብረታቸውን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ ሆነው አልተገኙም። ሀብትን ከማስመዝገብ ግዴታ ጋር ተያይዞ ፈቃደኛ ሆኖ ያልተገኙ አካላት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት ሙስናን እና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል በወጣው የሀብት ማሳወቅና ማስመዝገብ አዋጅ ቁጥር 668/2002 መሠረት ተጠያቂ እንደሚሆኑ ተደንግጓል።

    በዚሁ መሠረት ኮሚሽኑ የሀብት ምዝገባ ሥራን በማካሄድ በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ የመንግሥት የሥራ ኃላፊነትና የግል ጥቅም ሳይቀላቀሉ በየራሳቸው መንገድ የሚመሩበትን ግልጽ ሥርዓት እንዲኖር እያደረገ ባለው ሂደት ሀብታቸውን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ ያልሆኑ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትን ተጠያቂ እንዲሆኑ እያደረገ ሲሆን፥ በቀጣይም ሀብታቸውን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ በማይሆኑ የመንግሥት ተሿሚዎችና ሠራተኞች ላይ በሕጉ መሠረት ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ የሚገደድ መሆኑን ያሳውቃል።

    ከባለስልጣናት ሀብት ምዝገባ ጋር በተያያዘ፥ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔና ምክትል አፈ-ጉባዔን ጨምሮ የምክር ቤቱ አባላት ነሐሴ 18 ቀን 2012 ዓ.ም የሀብት ምዝገባ እድሳት አካሂደዋል።

    በሀብት ምዝገባ እድሳቱ ላይ የተገኙት የምክር ቤቱ አፈ-ጉባዔ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ እንደተናገሩት፥ የፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሙስናና ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከል እየሠራቸው ካሉት በርካታ ሥራዎች መካከል የሀብት ምዝገባ ሥራ አንዱ ነው። የሀብት ምዝገባ ሥራ ሙስናን ለመከላከል ዓይነተኛ መሣሪያ እንደመሆኑ መጠን ሊደገፍና ሊጠናከር ይገባል ሲሉ አፈ-ጉባዔው አክለው ገልጸዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሁሉም አካላት ሀብታቸውን በማስመዝገብ ሙስናና ብልሹ አሠራሮችን ለመከከላከል የሚደረገውን ጥረት መደገፍ እንደሚገባቸው አፈ-ጉባዔው አሳስበዋል።

    አፈ-ጉባዔዎቹን ጨምሮ የሀብት ምዝገባ እድሳት ያካሄዱ የምክር ቤቱ አባላት ሀብታቸውን ያሳደሱበትን ሰነዶች ለፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር አቶ ፀጋ አራጌ አስረክበዋል።

    ምንጭ፦ የፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    የፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን

    Anonymous
    Inactive

    እውነታውን በማድበስበስ ከተጠያቂነት ማምለጥ አይቻልም! ― የኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት

    የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) በአዲስ አበባ ከተማ መሬት ወረራን እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢ-ፍትሃዊ ዕደላን በተመለከተ የሚደርሱትን ጥቆማዎች በመቀበል ጉዳዩን የሚመረምር ከብሔራዊ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት የተወጣጣ ኮሚቴ አቋቁሞ ጥናት ሲያደርግ ቆይቷል። የጥናቱን ውጤት ለሕዝብ እና ለመገናኛ ብዙኃን ይፋ ለማድረግ ዛሬ አርብ ነሐሴ 22 ቀን 2012 ዓ.ም ጋዜጣዊ መግለጫ ተዘጋጅቶ ነበር።

    ይህ ጋዜጣዊ መግለጫ ሲዘጋጅ ከዚህ ቀደም ጋዜጣዊ መግለጫ ስንሰጥ እንደምናደርገው ሁሉ ጋዜጣዊ መግለጫው ለሚደረግበት ራስ ሆቴል እንዲሁም በደብዳቤ ቁጥር ኢዜማ/695/12 ለኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስቴር አስቀድመን አሳውቀናል።

    ፓርቲያችን ሊሰጥ የነበረውን መግለጫ ለመከታተል እና ለሕዝብ ለማድረስ የተጠሩ ጋዜጠኞች ከተባሉት ሰዓት ቀድመው በአዳራሹ ውስጥ የተገኙ ሲሆን፥ ብዙዎቹም የቀረጻ መሣሪዎቻቸውን አሰናድተው  የመግለጫውን መሰጠት በመጠባበቅ ላይ እያሉ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አባል መሆናቸውን የገለፁ የፖሊስ አባላት መግለጫው መሰጠት እንደማይቻል በማሳወቅ፥ ጋዜጠኞቹ አዳራሹን ለቀው እንዲወጡ አድርገዋል። ፖሊሶቹ ጋዜጣዊ መግለጫውን ለማስቆም የሰጡት ምክንያት ጋዜጣዊ መግለጫው እንዲካሄድ ትዕዛዝ አልተሰጠንም የሚል ነበር።

    በስፍራው የተገኙት የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) አመራሮች ሙሉ ትብብር ያደረጉ ሲሆን፥ ስለመግለጫው ለሰላም ሚኒስቴር በደብዳቤ ማሳወቃቸውን ለፖሊስ አባላቱ አስረድተዋል። ወደ ሰላም ሚኒስቴር በመደውልም የተፈጠረውን ለሚንስትር መሥሪያ ቤቱ ያሳወቁ ሲሆን፥ የፖሊስ አባላቱን ከሰላም ሚኒስቴር ጋርም በስልክ የማገናኘት ሥራ ተሠርቷል። ነገር ግን የፖሊስ አባላቱ መልሰው “የሰላም ሚኒስቴር ሊፈቅድ የሚችለው ስብሰባዎችን እንጂ ጋዜጣዊ መግለጫዎችን አይደለም። የመግለጫ ጉዳይ የሚመለከተው ፖሊስን ነው።” በሚል መግለጫውን በመከልከል ጸንተዋል። ይህንንም ተከትሎ የኢዜማ በአዲስ አበባ ከተማ እየተፈፀመ ያለውን የመሬት ወረራ እና የጋራ መኖሪያ ቤቶች ኢ-ፍትሃዊ ዕደላን አስመልክቶ የሠራውን ጥናት ውጤት ለሕዝብ ለማሳወቅ ያዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ተስተጓጉሏል።

    ትላንት የአዲስ አበባ መሬት በሕገ-ወጥ መንገድ እየታጠረ ሲወረር እና ሲዘረፍ ማቆም ያልቻሉ የሕግ አስከባሪዎች፥ በሕጋዊ መንገድ የተጠራ ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳይሰጥ አጥር ሆነዋል። የሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነትን እና የሕግ የበላይነትን የሚያረጋግጥ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ እንደዛሬው ዓይነት እክል ትላንትናም አላስቆመንም፤ ዛሬም አያስቆመንም! የተፈጸመ ስህተት ካለ አዳምጦ ለማረም ከመዘጋጀት ይልቅ የዜጎችን እና የፖለቲካ ፓርቲዎችን ሀሳብን የመግለጽ ነፃነት በማፈን እና እውነቱን በማድበስበስ ከተጠያቂነት ለመራቅ መሞከር ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንቅፋት እንደሆነ ግልጽ ሊሆን ይገባል። ዛሬ በተከሰተው መግለጫውን የማስተጓጎል ተግባር እውነታውን ማድበስበስ እና ከተጠያቂነት ማምለጥ አይቻልም።

    ከዚህ ቀደም የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት፣ የመሬት ልማት ቢሮ እና የቤቶች ልማት ኤጀንሲ በጥናታችን የደረስንበትን ውጤት አያይዘን የእነሱን ምልከታ በጥናት ውጤታችን ውስጥ ለማካተት ምላሽ እንዲሰጡን ጠይቀን የነበረ ቢሆንም፥ ሁሉም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ካለመሆናቸው በተጨማሪ የመሬት ልማት ቢሮ እና የቤቶች ልማት ኤጀንሲ የላክንላቸውን ደብዳቤም ለመቀበል ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።

    ኢዜማ በጥናቱ የደረሰበትን ሕገ-ወጥነት እና ኢፍትሃዊነት ሰኞ ነሐሴ 25 ቀን 2012 ዓ.ም ከሰዓት 8 ሰዓት ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል። ሀሳባችንን የመግለጽ ሕገ-መንግሥታዊ መብታችንን ለማስከበር ወደኋላ እንደማንል እና ያገኘነውን ውጤት ሕዝብ ጋር እንደምናደርስ እንዲያውቁት በድጋሚ ለኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስትር እና ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ደብዳቤ ልከናል።

    የኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት

    የኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት

    Anonymous
    Inactive

    የትግራይ ሕዝብ መከራ እንዲያበቃ ህወሓት ከነግሳንግሱ መወገድ አለበት!!
    በላይ አስመላሽ
    የተጋሩ አለማቀፍ ጥምረት ለአዎንታዊ ተግባር ድርጅት (OTNAA–Worldwide) አማካሪ በሰሜን አሜሪካ

    በትግራይ ምርጫ ምርጫ ሲባል እየሰማን ነው። ነገር ግን የትግራይ ሕዝብ በትግሉ ዋጋ የከፈለበትን የፍትህ፣ የነፃነት፣ የዲሞክራሲ፣ የሕግ ልዕልና፣ የሰላምና የዳቦ ጥያቄዎች ጭራሽ አልተመለሱም። ላለፉት 50 ዓመታት በትግራይ የተካሄዱት አምስት ተከታታይ ምርጫዎችም አንዲት ኢንች ለውጥ አላመጡም። አሁንም ከ50 ዓመት በኋላ የቀረበልን የምርጫ ድግስም ያው በተመሳሳይ ‘ወጮ ቢገለብጡት ወጮ’ ሆኖ ነው የተገኘው።

    በመሆኑም የትግራይ ሕዝብ ድርብ ድርብርብ የ50 ዓመታት ሶቆቃ ሲታይ፦

    • አንድ ቀን እንኳን ተረጋግቶ የሚኖርበት እፎይታ ያላገኘ ሕዝብ ነው ያለው፤
    • አሁንም ራሱ አስመራጭ፣ ራሱ ተመራጭ፣ ራሱ መራጭ፣ ራሱ ዳኛና ራሱ ቀማኛ በሆነ ፈላጭ ቆራጭና አምባገነን የህወሓት ሥርዓት ስር ወድቆ እንደ ሞርኮኛ ተቆጥሮ በቁም እስር ላይ የሚኖር ሕዝብ ነው ያለው፤
    • አንድ ለአምስት በማደራጀት የዘመነ–ደደቢት በጫካ አገዛዝ መፈናፈኛ በማሳጣት በጅሆ (hostage) ተይዞ የሚገኝ ሕዝብ ነው ያለው፤
    • ለሚደርስበት በደል አቤት የሚልበት የዳኝነት ቦታ አጥቶ እንደ ህፃን ልጅ ‘አፍህን ያዝ!’ እየተባለ፣ እየተኮረኮመ የሚኖር፤ የፍትህ በር የተዘጋበት ሕዝብ ነው ያለው፤
    • እስካሁን ድረስ ለግማሽ ምዕተ ዓመት ያህል “ወራሪ ጠላት መጣብህ” እየተባለ በፍርሃት፣ በሽብርና በስጋት እንዲኖር የተፈረደበትና ጦርነት ያልተለየው ሕዝብ ነው ያለው፤
    • “አደንቁረህ ግዛ” በሚል የካድሬ ፈሊጥ፥ ህወሓት ሲኖር የሚኖር ህወሓት ሲጠፋ ደግሞ አብሮ የሚጥፋ በማስመሰል በአብዮታዊ ዲሞክራሲ መለኮታዊ ምትሃት እየተመራ፣ ለጥቂት መሪዎች ዘላለማዊ ስልጣን ሲባል የደም ግብር እየገበረ እንዲኖር የተፈረደበት ሕዝብ ነው ያለው፤
    • በአጠቃላይ የትግራይ ሕዝብ “ለያይተህና አናቁረህ ግዛ” በሚል ስትራተጂ፣ ሆን ተብሎ በአውራጃና በዘር በመከፋፈል ብሔራዊ ማንነቱን፣ ብሔራዊ እሴቱን፣ ወርቃዊ ባህሉን፣ ታሪኩንና አንድነቱን እንዲዳከም፣ እንዲበተንና እንዲፈርስ እየተደረገ የመጣ መሆኑን በዓይናችን ስናይ ቆይተናል፤ አሁንም እያየን ነው።

    ታዲያ ወገኖቼ ሆይ፦

    • ፍትህ በሌለባት ትግራይ – ፍትሓዊ ምርጫ ማካሄድ ይቻላልን?
    • ነፃነት በሌለባት ትግራይ – ነፃ ምርጫ ማካሄድ ይቻላልን?
    • የሕግ የበላይነት በማይከበርባት ትግራይ – ሕጋዊ ምርጫ ማካሄድ ይቻላልን?
    • በክተት አዋጅ ስር የህሊና ሰላም በሌለባት ትግራይ – ሰላማዊ ምርጫ ማካሄድ ይቻላልን?
    • አማራጭ የሌለው ሕዝብ – ማን ከማን ነው የሚመርጠው?

    ስለሆነም፥ ዛሬ በትግራይ ምድር እየተካሄደ ያለው የውሸት የምርጫ ድራማ ያለፈውን የሃምሳ ዓመት ፍዳና መከራ እንደገና በትግራይ ሕዝብ ጫንቃ ላይ መልሶ የባርነት ቀንበር ለመጫን የሚደረግ ሩጫና እሽቅድድም መሆኑን ሳይታለም የተፈታ ነው።

    መፍትሄውስ ምን ይሁን? ፦

    1. የሁሉንም ችግሮች ምንጭ የሆነው፣ ያረጀ ያፈጀ አምባገነን የህወሓት ሥርዓት ያበቃለት ስለሆነ በፍጹም የመፍትሄና የለውጥ አካል መሆን አይችልም። ባህሪውም ፈጽሞ አይፈቅድለትም። ስለዚህ ህወሓት የሕዝቡን ደመ ነብስ የሆኑት የፍትህ፣ የዲሞክራሲና የዳቦ ጥያቄዎች መመለስ የማይችል መሆኑን ላለፉት በርካታ ዓመታት በተግባር የተፈተነና የትግራይ ሕዝብን ትግል የነጠቀ ድርጅት ነው። መፍትሄውም ሥርዓቱን ከነግሳንግሱ በማስወገድ በአዲሱ ትውልድ መተካት ለትግራይ ሕዝብ የመኖርና ያለመኖር ጥያቄ ሆኖ ይገኛል።

    ስለዚህ አሁን ያለው ምርጫ ለትግራይ ሕዝብ በሰላም ወይም በባርነት የመኖርና ያለመኖር ምርጫ ነው ሲባልም አንደኛው ምርጫ የበሰበሰውን አረሜኔ የህወሓት ሥርዓት ዳግም በመምረጥ በጅሆ ተይዘው እያለቀሱ፣ እርስ በርስ እየተናቆሩና ለጥቂት መሪዎች ንፁህ ደም እየገበሩ ባርነትን አሜን ብሎ በመቀበል በጦርነት፣ በሽብርና በስጋት ደመና ስር መኖር ነው። ሁለተኛውና ወሳኙ ምርጫ ደግሞ ከኋላ-ቀርና ከጨለማው አስከፊ የአገዛዝ ሥርዓት ወጥቶ የሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ሰው በመሆን ከሁሉም ጋር በሰላም ተግባብቶና ተከባብሮ አብሮ መኖር ነው። ከሁለት መንገዶች አንዱን የመምረጥና ያለመምረጥ ደግሞ በትግራይ ሕዝብ እጅ ነው።

    ስለትግራይ ሕዝብ ሲነሳ በሚሊዮኖች ኢትዮጵያወያን ዘንድ አብረው የሚነሱ ጥያቄዎች አሉ። የነቃ የተደራጀና የታጠቀ ሕዝብ እንዴት ጠላቱንና ወዳጁን ለይቶ ማወቅ ያቅቷል? የትግራይ ሕዝብ ለባዕድ ጠላት የማይንበረክክ፣ በሀገሩ፣ በማንነቱና በነፃነቱ የማይደራደር መሆኑን ለዘመናት የቆየ ታሪኩ ይመሰክርለታል። ይህ ከሆነ ሀቁ፥ የትግራይ ሕዝብ ዛሬ ዓለም በሰለጠነበት ዘመን ለሃምሳ ዓመታት ያህል የጥቂት ገዢዎች ምርኮኛና አገልጋይ ሆኖ ለመኖር በገዛ እጁ ለምን ፈቀደ? የትግራይ ሕዝብ ዘላለም የአንድ ኋላቀር ድርጅት የግል ንብረት ሆኖ በሞኖፓልና በጅሆ ተይዞ እንዲኖር በእግዚአብሔር ለህወሓት የተፈጠረ ሕዝብ ነውን? ትግራይ በተለይም በህወሓት ዘመን ከሌሎቹ 86 የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች በተለየ መልኩ የአፈና ጉድጓድ፣ የዘር ጥላቻ ሞዴል፣ የጦርነት አውድማ፣ የግድያ ገሃነም፣ የለያይተህ ግዛ ተምሳሌትና የጭቁኖች የምድር ሲዖል ሆና እንድትታይ ያደረጋት ሚስጢሩ ምንድን ነው? በትግራይ ምድር ህወሓት በመፈጠሩ ከጦርነትና ከመፈናቀል አልፎ ለትግራይ ሕዝብ ከሌሎቹ ኢትዮጵያውያን ወገኖቹ በተለየ መልኩ ያስገኘለት ልዩ ጥቅም ምንድን ነው? እውነት ህወሓት ራሱን ያላዳነ ድርጅት በአሁኑ ጊዜ የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጪና መድኅን ሊሆን ይችላልን? የሚሉትንና ሌሎች ጥያቄዎች እስካሁን ድረስ መልስ ያላገኙ እንቆቁልሽ ሆነው ያሉት ናችው።

    1. ህወሓት በባህሪው ፀረ-ሕዝብና ፀረ-ዲሞክራሲ ብቻ አይደለም። የትግራይ ሕዝብን ክብርና ማንነት የሚያሳንስ አምባገነን፣ ጠባብና ተራ ዘራፊ ድርጅትም ጭምር ነው። ይህን ያልኩበት ምክንያት ህወሓቶች ፊደል አልቆጠሩም ማለቴ አይደለም። ራሳችው ከሚያራምዱት አመለካከትና ከሚፈፅሙት ተግባር ተነስተን ስናያችው፦ ዲሞክራሲና የሰው ልጅ ነፃነት ቃሉ እንጂ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ አያውቁትም። በዜጎች መካክል የአስተሳሰብ ልዩነት መኖር ማለት ለነሱ ጠላትነት እንጂ ለአንድ ሀገር የዲሞክራሲና የእድገት መሠረት መሆኑን አያውቁትም። ሕገ መንግሥት፣ ሕዝባዊና መንግሥታዊ ተቋማት፣ አብያተ ምእመናንንም ሳይቀር የሚጠቀሙበት የሕዝብና የሀገር ደህንነት ለመጠበቅ ሳይሆን ለመጨቆኛና ለመዝረፊያ መሣሪያነት ነው።

    ከሁሉም በላይ ደግሞ ለምን በረሃ እንደወጡና ለምን እንደታገሉም አያውቁትም። ሁሉም እኩይ ተግባሮቻችው ልብ ብሎ ለተመለከተው የታገሉበትን ዓላማ የሚፃረሩ ናችው። እስካሁን ድረስ አእምሯችውና አስተሳሰባችው የተወቀረው በዘመነ-ደደቢት የነበረ ፅንፈኛ፣ አክራሪና [ትምክህታዊ] አመለካከት ነው። ጦርነት መለኮስ፣ ግጭት መፍጠር፣ ለያይቶና አደንቁሮ መግዛት፣ የውሸት መርዝ መርጨት፣ ሽብር መፍጠርና መዝረፍ የመሳሰሉትን አፍራሽ ተግባራት እንደ ሱስና እንደ ልዩ ሙያ አድርገው ሲከተሏችው የኖሩት የባህሪያቸው መገለጫዎች ናችው። አሁን ያለው የክተት አዋጅም የቆየ ባህሪያችው አንዱ አካል ነው፤ ጭር ሲል አይወዱም። በሕዝብና በሀገር ላይ የፈፀሙበትን ወንጀል ስለሚያውቁ ዙሪያችውን ሁሉ በጠላት የታጠረ መስሎ ይታያቿል። ከዚህ የተነሳ በሕዝቡ ላይ ምንም ዓይነት አሜኔታ የላችውም። ለዚህ ነው የትግራይ ሕዝብ ሌላ አማራጭ ነገር እንዳያስብ ነጋ ጠባ በክተት አዋጅ፣ በመግለጫ፣ በስብሰባ፣ በድጋፍ ሰልፍና በሽብር እንዲናጥ የሚያደርጉት።

    ህወሓቶች የዲሞክራሲ መሃይማንና የለውጥ ፀር ናቸው ከምንልበት አንዱ ህወሓት እስካሁን ድረስ ድሮ በዘመነ-ደደቢት የነበረ የአደረጃጀት ዓይነት “ነፃ አውጪ ግንባር” ነን ብለው ነው የሚያምኑት። ህወሓት ከሌሎች የፓለቲካ ፓርቲዎች እኩል መብትና ግዴታ ያለው ድርጅት አድርጎ አያስብም፤ አሁንም ‘የአንበሳ ድርሻ ያለኝ አውራ ፓርቲ ነኝ’ ብሎ ነው የሚያምነው። የትግራይ ሕዝብና ህወሓት የማይለያዩ አንድ ናቸው ብለው ነው የሚያምኑትና የሚያስተምሩት። በየዓመቱ የሚያከብሩት የህወሓት ልደት የትግራይ ሕዝብ ልደት ነው ብሎ ነው የሚያምኑትና የሚያስተምሩት። የህወሓት ከስልጣን መወገድ ማለት የትግራይ ሕዝብ ህልውና አብሮ ያከትማል ብሎ ነው የሚያምኑትና የሚያስተምሩት። የትግራይ ሕዝብ ሓቀኛ ታሪክና ህልውና ከደደቢት ይጀምራል ብሎ ነው የሚያምኑትና የሚያስተምሩት። መንግሥትና የፓለቲካ ድርጅት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽ ናችው ብለው ነው የሚያምኑትና የሚያስተምሩት። አደንቁሮና አደንዝዞ መግዛት ማለትም ትርጉሙ ይኸው ነው።

    ልብ በሉ!! ህወሓት በሚመራው መንግሥት ሁሉም ፓሊሲዎች፣ አደረጃጀቶች፣ ሕጎችና ጠቅላላ የምሕዳሩ መመሪያ ሥርዓት የሚቀዱት ከሀገርና ከሕዝብ ፍላጎትና ጥቅም አኳያ ሳይሆን መነሻቸው ከላይ ከተጠቀሱት ኋላቀርና የድንቁርና አስተሳሰቦች የሚመነጩ ናችው። የትምህርት ሥርዓቱ፣ መምህርና ተማሪው በሙሉ በዚሁ ትውልድ ገዳይና አደንዛዥ በሆነው የድንቁርና አስተሳሰብ ነው ተቀርፀውና ተኮትኩተው ያደጉት። በወጣቱና በሕብረተሰቡ አካባቢም እስከታች ቤተሰብ ድረስ ወርዶ የዕለት ተዕለት መተዳደሪያውና የኑሮው አካል አድርጎ እንዲወስደው ይገደዳል። ከዚህ የተነሳም ሕዝቡ ህወሓትን እንደ አንድ ስጋ-ለበስ ሰዎች የተሰባሰቡበት የፓለቲካ ድርጅት ሳይሆን እንደ ረቂቃን መናፍስት አድርጎ እንደ ጣዖት እንዲያመልካችው ተደርጓል። የዚህ ሁሉ ድምር ውጤትም በሕዝቡ ሥነ ልቦና ላይ የጣለው ጠባሳ አሳዛኝ ነው። ሕዝቡ እንዳያምፅ፣ በነፃ እንዳይደራጅና የፍትህ ጥያቄ እንዳያነሳ በተለያየ ደባ ለመብቱ የማይታገል የአካልና የህሊና እስረኛ ሆኖ እንዲኖር አድርገውታል።

    በሌላ በኩል ደግሞ ከህወሓት አስርቱ ትዕዛዛት ያፈነገጠ፣ የተለየ አመለካከት የያዘ ወይም ተቃዋሚ ነው ከተባለ ደግሞ ቅጣቱ ከቤተሰቡ ይጀምራል። ትዳር ይፈርሳል፤ ቤተሰብ ይበተናል። በሕብረተሰቡ ደረጃም እሳት እንዳታስጭሩ፣ ሲሞት እንዳትቀብሩ፣ ሻይ ቡና ኣንዳትሉ፣ ቤት እንዳታከራዩ፣ ወዘተ በሚል አሰቃቂና አሳፋሪ በሆነ ሁኔታ ማኅበራዊ ውግዘት ይታወጅበታል። በመንግሥት ደረጃም የመሥራት መብቱ፣ ሀብት የማፍራትና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች ይከለከላል። የመጨረሻ ዕድሉም ሞት፣ ስደት፣ እስር ቤት ወይም የት እንደገባ በማይታወቅ መልኩ ተሰውሮ ይቀራል። ይህ ዓይነቱ ዘግናኝ ተግባር ለትግራይ ሕዝብ መናገር ማለት ለቀባሪ ማርዳት ነው የሚሆነው። ለዚህ ነው ህወሓት የሕብረተሰቡ ነቀርሳ ስለሆነ መወገድ አለበት የምንልበት ምክንያትም ተግባሩ ፀረ-ሰብዓዊ ፍጡር ስለሆነ ነው።

    ስለሆነም ለትግራይ ሕዝብ፣ ለትግራይ ምሁራን፣ ለትግራይ ወጣቶችና ታጋይ ኃይሎች በሙሉ ማስተላለፍ የምፈልገው መልዕክትም አንድና አንድ ነው። የትግራይ ሕዝብን ለጥቃት፣ ለውርደት፣ ለስደትና ለረሃብ የዳረገው ከህወሓት በላይ ሌላ ጠላት የለውም። ትግራዋይ ትግራዋይን ለማጥፋት እርስ በርሱ እንደጠላት እየተፈራረጀና እየተባላ እንዲኖር እያደረገ ያለው ምንጩ ህወሓት ራሱ በፈጠረው የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ደማዊ ሰርዓት ውጤት እንጂ ከአማራ ወይም ከውጭ የመጣ ጠላት አይደለም። በሀገሩ፣ በማንነቱና በነፃነቱ ኮርቶ ይኖር የነበረውና የጀግንነት የፍቅርና የአንድነት ተምሳሌት እየተባለ ይታወቅ የነበረውን ጀግናው የትግራይ ሕዝብ ዛሬ ትግራይን በጥላቻ የታጠረች የሽብር ደሴት ሆና እንድትቀር እያደረጋት ያለው ራሱ ህወሓት በፈጠረው የለያይተህ ግዛ መርዝ ያመጣው ጣጣ እንጂ፥ ከሌላ ጎረቤት ድንበርን ተሻግሮ የመጣብን ችግር አይደለም። ስለዚህ የችግሩ ምንጭም፣ የችግሩ ሰለባም እዚያው በትግራይ ምድር ላይ ነው ያለው። የችግሩን የመፍትሄ መድኃኒትም በራሱ በትግራይ ሕዝብ እጅ ላይ ነው ያለው።

    ለባዕዳን ወራሪዎችን ያልተንበረከከ ጀግና ሕዝብ ዛሬ እጃቸውን በደም የተነከሩ፣ ዓይናቸውን በፍቅረ-ንዋይ የታወሩ፣ አእምሯቸውን በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ምትሃት የደነዘዙ የህወሓት ጉግ ማንጉግ መሪዎችን መጫወቻ፣ ምርኮኛና የቁም እስረኛ ሆኖ ሲታይ እጅጉን ያሳዝነኛል፣ ያሳፍረኛል፣ ያስቆጣኛልም። ትናንት እንደነ ጀኔራል አሉላ አባ ነጋ፣ ሃፀይ ዮሐንስ፣ እንደነ ጀኔራል ሐየሎም አርኣያ፣ ዛሬም እንደነ ገብሩ አሥራት፣ አረጋሽ አዳነና ሌሎች በሺዎች የሚቆጠሩትን ብሔራዊ ጀግኖች የተወለዱባት ትግራይ አሁን የህወሓት ፈርጣጭ መሪዎችን መሸሸጊያና መደበቂያ ሆና የውሸት ድራማ የሚሠራባት የትርምስ አውድማ ሆና ማየቱ ውርደትና ሀፍረት ከመሆኑም በላይ የትግራይ ሕዝብን ጨዋነት፣ የሞራል እሴትና ክብር የሚያሳንስ ነው።

    ስለዚህ የትግራይ ሕዝብ መድኅን ህወሓት ሳይሆን ራሱ ሕዝቡ ነው። በአንፃሩ ህወሓትን ከሀገርና ከሕዝብ በላይ አድርጎ በማየት ጥቂት አምባገነን ገዢዎችን ከስልጣን ከማውረድ ይልቅ “የትግራይ ሕዝብ ይጥፋ፤ ሀገር ትፍረስ፤ ሚሊዮን ለጋ ወጣቶችን በማያውቁት ጉዳይ ወደ ጦርነት ይግቡ” ብሎ መንቀሳቀስ፣ የወንጀሉን ተባባሪ መሆን፣ ሕዝቡን ማስገደድና ማደናገር ማለት ያለፈውን የሃምሳ ዓመት ሶቆቃ መድገም ብቻ ሳይሆን፥ በታሪክም ሆነ በሕግ የሚያስጠይቅ የዘመናችን አስፀያፊና ወራዳ ተግባር ይሆናል።

    ስለዚህ የትግራይ ሕዝብ ማለቂያ ከሌለው ጭቆና ተላቆ ዘላቂ ሰላምና እፎይታ ማግኘት የሚችለው የሁሉንም ችግሮች ምንጭ የሆኑትን የህወሓት መሪዎች ተጠያቂነት ባለው መልኩ ለአንዴና ለመጨረሻ ከጀርባው አሽቀንጥሮ በመጣል ቦታውን ለባለተራው ለአዲሱ ታጋይ ትውልድ እንዲለቁ ሲያደርግ ብቻ መሆኑን ሊሰመርበት ይገባል። ይህ ሁኔታ በዋዛ ፈዛዛ ለጥቂት መሪዎች ዋሻ ለመሆን ሲባል ዘላቂ መፍትሄ ሳያገኝ ቀርቶ ወደ ሌላ የጥፋት ምዕራፍ ከተሸጋገረ ግን መዘዙ ከትግራይ አልፎ ሌላው ጎረቤትንም ጭምር ስለሚነካ የትግራይ ሕዝብ “ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል እየደማ ይኖራል” ነውና “ሳይቃጠል በቅጠል” ማለቱ ይበጃል እላለሁ።

    ለመላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ማስተላለፍ የምፈልገው መልዕክትም ተመሳሳይ ነው። የሩቁን ትተን የትናንትናውን የሀምሳ ዓመት የትግል ታሪካችን መለስ ብለን ስንቃኝ በትክክል የሚያሳየን ስንተባበር እንደምናሸንፍ፣ ስንበታተንና ስንለያይ ግን እንደምንሸነፍ ነው። በሌላ አነጋገር፥ ተባብረን ታግለን ያገኘነውን ድል ገና እግር ሳይተክልና ለፍሬ ሳይበቃ ተበታትነን ስናፈርሰው ነው ታሪካችንን የሚያሳየን። ዛሬም ጨቋኞች፥ በተለይም ህወሓት ደካማ ጎናችንንና ኋላቀር የፓለቲካ ባህላችንን ከኛ በላይ ጠንቅቀው ስለሚረዱ እኛን መስለው እኛን ለማጥፋት ሲጠቀሙበት ቆይቷል። ለአርባና ለሀምሳ ዓመታት ያህል በዘር፣ በሀይማኖትና በቦታ እየተሸነሸነ ሲሠራበት የቆየውን የለያይተህ ግዛ ኢንጂነሪግ በያንዳንዳችን አእምሮ ውስጥ የጥላቻ መርዝን ተክሎ አልፏል።

    በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ ቦታዎች እየተከሰቱ ያሉት አንዳንድ አላስፈላጊ ግጭቶችም መነሻቸው የዚሁ የጥላቻው መርዝ ውጤቶች መሆናቸውን እሙን ነው። በተደረገው ትግል ህወሓትን ከመሀል ሀገር ተባርሮ ወደ ትግራይ በመሄዱ ብቻ እንደ ግብ ተወስዶ ለውጥ እንደ መጣና ትግሉ ያለቀ መስሏቸው የሚዝናኑና የሚኩራሩ ጥቂቶች አይደሉም። ነገር ግን ህወሓት ዘወር አለ እንጂ አልሸሸም። መልኩን፣ ስልቱንና ስትራተጂውን ቀየረ እንጂ አልጠፋም። ህወሓት የትግራይ ሕዝብን እንደምሽግ ተጠቅሞ የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ አሁንም አለሁ አልሞትኩም እያለን ነው።

    ችግራችንን የህወሓት መኖርና አለመኖር ጉዳይ ብቻ አይደለም። ራሳችን በራሳችን ለመለወጥም አብዮት ያስፈልገናል። ሁልጊዜ ትግላችንን ውጤት አልባ ሆኖ እንዲቀር ከሚያደርጉት ጥቂት ምክንያቶች አንዱ ገና ያልተገነዘብናቸውና ያዝ ለቀቅ የምናደርጋችው መሠረታዊ ችግሮች ስላሉን ነው።

    አንደኛ – የጋራ ችግሮቻችንና የጋራ ጥቅሞቻችንን ምን እንደሆኑ ለይተን አላወቅንም፤
    ሁለተኛ – የሀገራችን እውነታና የሕዝባችንን የልብ ትርታ የተረዳ፣ የጠራ ራዕይና ዓላማ ያለው የመሪ ድርጅት ጥያቄ ገና አሁንም አልተመለሰም፤
    ሦስተኛ – ኢትዮጵያ ሦስት ሺህ ዓመት ያላት ነፃ ሀገር ናት ብለን እንፎክራለን እንጂ ሀገራዊ ንቃተ ህሊናችን ከ16ኛው የዘመነ መሳፍንት አስተሳሰብ ገና አልወጣንም፤
    አራተኛ – ከታሪካችንና ከውድቀታችን አንማርም፤
    አምስተኛ – ትልቁን ጉዳይ ትተን በጥቃቅን ጉዳዮች ላይ ነው የምንጣላውና የምናተኩረው።

    የሀገር ባለቤት መንግሥት ሳይሆን 110 ሚሊዮን ሕዝብ ነው። ሀገር ቢፈርስና ቢበታተን ተጠያቂ የሚሆነው መንግሥት ብቻ ሳይሆን ራሱ ሕዝቡም ጭምር መሆኑን በውል የሚገነዘብ ዜጋ ምን ያህል ነው? የሚለው አጠያያቂ ጉዳይ ነው። ብዙ ብዙ ማለት ይቻላል። በእነዚህ ራሳችን በምንፈጥራችው ችግሮች ምክንያት ለነፃነታችን፣ ለመብታችን፣ ለአንድነታችንና ለህልውናችን ዘብ የማንቆም፣ ለአገዛዝና ለጭቆና የተመቸን እንድንሆን አድርጎናል። ውጤቱም ትግላችን በአቋራጭ እየተነጠቀ ሁሉ ጊዜ ታጥቦ ጭቃ ሆኖ እንዲቀር አድርጎታል። ይህ በመሆኑም የሕዝባችን የመከራ ዕድሜ እንዲራዘም ከማድረጉም በላይ ከነዚህ ችግሮች በይበልጥ የጠቀመው ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሳይሆን እንደ ህወሓት ለመሳሰሉት መሰሪ መሪዎችና ገዢዎች ነው።

    ስለሆነም ትግሉ ተጀመረ እንጂ አላለቀም። መፍትሄውም ችግሮችን በተለያየ ቦታ ብልጭ ባሉ ቁጥር ከቅርጫፋቸውና ከውጤታቸው ከመታገል ይልቅ በተባበረ ኃይል ግንዱን መገርሰስ ወይም ምንጩን ማድረቅ የትግላችን ተቀዳሚ ተግባር መሆን አለበት። በመሆኑም የሁሉንም ችግሮች ምንጭ ከሆነው ህወሓት ጋር ተደራድሮ ወይም እሽሩሩ ብሎ በሀገራችን ምድር ላይ የተረጋጋ ሰላምና እድገት ይመጣል ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። የህወሓት አምባገነንነት መነሻው ከራሱ ተፈጥራዊ ባህሪይ የሚመነጭ እንጂ በግምገማ ወይም በድርድር ሊስተካከል የሚችል አይደለም።

    ስለዚህ ተበታትነን በያለንበት ጊዜያችንና ጉልበታችንን ከማባክን ይልቅ ትግላችንን በተቀናጀ መልኩ ወደ አንድ የጋራ ጠላት ማነጣጠር አለበት። ዋናው ችግር ፈጣሪ ህወሓት ቁጭ ብሎ እያለ እሱ በሚሰጠን አጀንዳ እየተመራን ከውጤቱና ከቅርጫፉ ጋር እየታገልን ከመኖር ይልቅ አልፈን መገኘት አለብን። ከወደቁት ጋር እንካ ስላንቲያ ስንል ጠላቶቻችንን መልሰው እንዲጠናከሩ ዕድል ከመስጠት አልፎ ዘላቂ መፍትሄ ማምጣት ፍፁም አይቻልም።

    የትግል አንድነታችን ይለምልም !!

    በላይ አስመላሽ
    የተጋሩ አለማቀፍ ጥምረት ለአዎንታዊ ተግባር ድርጅት (OTNAA–Worldwide) አማካሪ በሰሜን አሜሪካ

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ፦ በሰሞነኛ ድረገጽ የአማርኛ ፎረም (semonegna.com/forums) ላይ የሚገኝ ማንኛውም ጽሑፍ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንጸባርቅ ሲሆን፥ ጽሑፉ የሰሞነኛ ኢትዮጵያንንም ሆነ የተሳታፊዎችን አመለካከትና ምልከታ ላይወክል ይችላል።

    የትግራይ ሕዝብ መከራ እንዲያበቃ ህወሓት ከነግሳንግሱ መወገድ አለበት!!

    Anonymous
    Inactive

    በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን።
    የሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ እና ግድያውን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በአንዳንድ ዞኖች
    ተቀነባብረው በተፈጸሙ ጥቃቶች የተጎዱ ኦርቶዶክሳውያንን መርዳትንና መልሶ ማቋቋምን አስመልክቶ
    ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ

    አማን አማን እብለክሙ ከመ ትበክዩ ወትላህዉ አንትሙ፤ ወዓለምሰ ይትፌሣሕ፤ ወአንትሙሰ ተኃዝኑ፤ ወኃዘንክሙ ፍሥሐ ይከውነክሙ = እውነት እውነት እላችኋለኹ፤ እናንተ ታለቅሳላችኹ፤ ሙሾም ታወጣላችኹ፤ ዓለም ግን ደስ ይለዋል፤ እናንተም ታዝናላችኹ፤ ነገር ግን ኃዘናችኹ ወደ ደስታ ይለወጣል።” (ዮሐ.16፥20) ሃጫሉ ሁንዴሳ ስመ ጥምቀቱ ኃይለ ገብርኤል፣ ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ.ም. ምሽት በአዲስ አበባ መገደሉ ይታወሳል። ቤተ ክርስቲያን፥ በዚያ ድንገተኛ የልጇ ግድያ ከባድ ኃዘን ተሰምቷታል። ኾኖም፣ በግድያው የተሰማትን ኃዘን ለመወጣት ጊዜ ሳይሰጣት፣ ኃዘንተኛነቷ ተረስቶ እና እንደ ጠላት ተቆጥራ፣ በኦሮሚያ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች በክርስቲያን ልጆቿ ላይ ዘግናኝ ፍጅት እና መከራ ተፈጸመባቸው።

    በኦርቶዶክሳዊነታቸው ብቻ በአሠቃቂ መልኩ በገጀራ ተቀሉ፤ በቆንጨራ ተቆራረጡ፤ በጦር ተወግተው በጩቤ ተዘከዘኩ፤ በሜንጫ ተተለተሉ፤ በዱላ ተቀጥቅጠው እና በደንጊያ ተወግረው ተገደሉ፤ አስከሬናቸው በጎዳና እየተጎተተ ሲንገላታ ዋለ፤ ለቀናት በየቦታው ወድቆ የቆየው የሰውነት ክፍላቸው ለከርሠ አራዊት ሲሳይ ኾነ፤ ሴቶች፥ በልጆቻቸው፣ በአባቶቻቸው እና በባሎቻቸው ፊት ተደፈሩ፤ ለዘመናት የደከሙበት ቤት ንብረታቸው፣ በጥናት እና በጥቆማ እየተለየ ከተዘረፈ በኋላ ቀሪው ጋዝ እየተርከፈከፈበት በእሳት እየጋየ ወደመ፤ ብዙዎች ከሞቀ ቀዬአቸው ተፈናቅለው የክረምቱን ጨለማ በቅጽረ ቤተ ክርስቲያን በሚገኙ መቃብር ቤቶች እና አዳራሾች፣ በልዩ ልዩ መንግሥታዊ ተቋማት እንዲሁም፣ በግሰለቦች ቤቶች ተጠልለው ለማሳለፍ ተገደዱ፤ ለአስከፊ ማኅበራዊ እና ሥነ ልቡናዊ ቀውሶች ተዳረጉ።

    ቤተ ክርስቲያናችን፣ ይህንኑ የተቀነባበረ ጥቃት እንደሰማች፣ ሰኔ 24 ቀን 2012 ዓ.ም. በቋሚ ሲኖዶስ የሐዘን መግለጫ አውጥታለች፤ በአገር ውስጥ እና በውጭ በሐዘንና በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ስታመለክት ከርማለች፤ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትም፥ “አጥፊዎችን አንታገሥም፤ ተገቢውን ፍትሕ እንሰጣለን፤ የተጎዱትን እንክሳለን፤” ብለው ቃል የገቡትን ይፈጽሙ እንደ ኾነ በማለት በትዕግሥት ጠብቃ ነበር። ኾኖም፣ ዜጎችን ከጥቃት አስቀድሞ የመከላከል እና የመጠበቅ፣ ፍትሕን የማስፈንና ተጎጂዎችን በአግባቡ የመካስ ሓላፊነታቸውን በወቅቱ እና በብቃት ሲወጡ አላየችም።

    በጉዳዩ ላይ የተወያየው ቋሚ ሲኖዶስም፣ በየሥፍራው በአካል ተገኝቶ የደረሰውን ጉዳት የሚያጠና ዐቢይ ኮሚቴ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እንዲቋቋም መመሪያ ሰጥቷል። በዚኽም መሠረት ዐቢይ ኮሚቴው፣ ተጎጂዎችን፥ በጊዜያዊነት ለመርዳት እና በዘላቂነት ለማቋቋም የሚያስችሉ ልዩ ልዩ ንኡሳን ኮሚቴዎችን አደራጅቶ ወደ ሥራ ገብቷል።

    ዐቢይ ኮሚቴው ባወጣው መርሐ ግብር፣ የሥራው መጀመሪያ ያደረገው፣ ጥቃቱ የተፈጸመባቸውን አካባቢዎች በዝርዝር በመለየት፣ ተጎጅዎችን የማጽናናት እና መረጃ የማሰባሰብ ጉዞ ማካሔድ ነበር። ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን፣ የአገር ሽማግሌዎችን፣ መንፈሳውያን ማኅበራትንና በርካታ የብዙኃን መገናኛዎችን ጨምሮ 260 ያኽል ልኡካን የተሳተፉበት ይኸው ጉዞ፣ ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው አካባቢዎች ውስጥ በስድስት አህጉረ ስብከት የሚገኙ 25 ወረዳዎችን የሸፈነ ነበር።

    የዐቢይ ኮሚቴው ልኡካን፣ ተጎጂዎችንና በማነጋገር እና ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢዎች በመጎብኘት ባቀረቡት ሪፖርት መሠረት፣ የልጃችን የኃይለ ገብርኤልን ግድያ ተከትሎ፣ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች፣ የመንግሥትን መዋቅር ተገን ያደረጉ የእምነት እና የብሔር ጽንፈኞች አስቀድመው ከተደራጁ ኀይሎች ጋራ በመቀናጀት የፈጸሙት ስልታዊ እና አረመኔያዊ ጥቃት ዋና ዒላማ፣ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን እንደነበሩ ተረጋግጧል።

    ከሰኔ 22 ቀን ምሽት ጀምሮ እስከ ሰኔ 24 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ ባሉት ሦስት ተከታታይ ቀናት በተፈጸመው በዚያ ጥቃት፥ ከ67 በላይ ምእመናን በግፍ እና በአሠቃቂ ኹኔታ ተገድለዋል፤ 38 ምእመናን ቋሚ(ከባድ)፣ 29 ምእመናን ደግሞ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ከሰባት ሺሕ በላይ ምእመናን ከመኖሪያቸው ከመፈናቀላቸው ባሻገር፣ በተለያየ ደረጃ ለሚገለጽ ሥነ ልቡናዊ እና ሥነ አእምሯዊ ቀውስ ተዳርገዋል፤ ከአምስት ቢልዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረታቸውንም በዘረፋ እና በቃጠሎ ማጣታቸውን፣ ከዐቢይ ኮሚቴው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ለመረዳት ተችሏል።

    የጥቃቱን አስከፊነት በዚኽ መልኩ የተረዳው ዐቢይ ኮሚቴው፣ ተጎጅዎችን በአፋጣኝ ባሉበት ለመርዳት እና በዘላቂነት ለማቋቋም ይቻል ዘንድ፣ አደረጃጀቱን በዐዲስ መልክ በማጠናከር ተልእኮውን በአጭር ጊዜ ለማከናወን የሚያስችለውን ስልት ቀይሶ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። የጉዳቱን መጠን በነፍስ ወከፍ ደረጃ የመለየት ሥራ እየሠራ ሲኾን፣ በዚኽም መነሻነት፣ ርዳታው በቀጥታ ለተጎጂዎች እና ቤተሰቦቻቸው እንዲደርስ ይደረጋል፤ በዘላቂነት ለማቋቋምም ኹኔታዎችን ያመቻቻል።

    ዐቢይ ኮሚቴው፣ በጉዳት ጥናት መረጃው መሠረት፣ ጊዜያዊ ርዳታን ከማድረስ እና ከመልሶ ማቋቋም ባሻገር፣ መንግሥት በአስቸኳይ ሊፈጽማቸው የሚገቡ ተግባራት አሉ ብሎ ያምናል፤ እነዚኽም፤

    1. ተጎጅዎች በሃይማኖታቸው በደረሰባቸው ስልታዊ እና ዘግናኝ ጥቃት የተነሣ፣ በከፍተኛ የደኅንነት ስጋት ላይ እንደሚገኙ በቀረበው ሪፖርት እና ማስረጃ አረጋግጠናል። በወቅቱ ያሉበት ኹኔታ፣ ለኮሮና ቫይረስ እና ለሌሎችም ተላላፊ በሽታዎች የሚያጋልጣቸው እንደኾነ ለመታዘብ ተችሏል። በመኾኑም፣ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና የፌዴራል መንግሥት፣ የኦርቶዶክሳውያን ኢትዮጵያውያንን በሕይወት የመኖር እና ሀብት የማፍራት ሰብዓዊ እና ዜግነታዊ መብቶችን በማስከበር፣ የደኅንነት እና የኑሮ ዋስትና በአፋጣኝ እንዲያረጋግጥላቸው ቤተ ክርስቲያናችን አጥብቃ ታሳስባለች።
    2. መንግሥት፥ ጥቃቱን ያቀዱትን፣ የፈጸሙትንና ያስተባበሩትን ኀይሎች እንዲሁም፣ የተጣለባቸውን ሓላፊነት ወደ ጎን በማለት ጥቃቱን በዝምታ የተመለከቱትን በመዋቅሩ ውስጥ ያሉትን ሹማምንት እና የጸጥታ አካላት የኾኑ አጥፊዎችን፣ በቁጥጥር ሥር በማዋል እና በሕግ ተጠያቂ በማድረግ ፍትሕ ርትዕ እስከ መጨረሻው እንዲያሰፍን ታሳስባለች። በዚኽ ረገድ፣ መንግሥት፣ ከጥቃቱም በኋላ ቢኾን፣ ሕግን ለማስከበር እያደረገ ያለውን ጥረት፣ ቤተ ክርስቲያን በቅርበት የምትከታተለውና የምታደንቀውም ነው፤ ለውጤታማነቱም፣ ማናቸውንም የበኩሏን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መኾኗን ትገልጻለች።
    3. በአሳዛኝ ኹኔታ በደል እና ግፍ የተፈጸመባቸው ኾነው እያለ፣ በጥቃቱ ምንም ሱታፌ የሌላቸው ንጹሐን ዜጎች፣ በኦርቶዶክሳዊነታቸው ብቻ ታስረው እየተንገላቱ በመኾኑ፣ ጉዳያቸው በጥንቃቄ ታይቶ ከእስር እንዲፈቱ ታሳስባለች።
    4. አንዳንድ የመንግሥት ባለሥልጣናት እና የፖሊቲካ ፓርቲዎች፥ የግፉዓን ሰማዕታቱን መጠቃት፣ አላግባብ ለቡድናዊ እና ፖሊቲካዊ ትርፍ በመጠቀም በሐዘናችን ከመሣለቅ እንዲቆጠቡ፤ መንግሥትም፣ ተገቢውን ክትትል በማድረግ እንዲያስታግሥ ቤተ ክርስቲያን አበክራ ታሳስባለች።
    5. ከወርኀ ሰኔው ጥቃት በፊትም ኾነ በኋላ፣ በኦሮሚያ እና በሌሎችም ክልሎች አንዳንድ አካባቢዎች፣ በቤተ ክርስቲያንና በምእመናን ላይ በተደጋጋሚ እየደረሱ የሚገኙ ስልታዊ የኾኑ ግልጽ ተጽዕኖዎች እና ጥቃቶች፣ በዐይነት እና በመጠን እየጨመሩ መጥተዋል። አብዛኞቹ የክልል መንግሥታት፣ ለውይይት ባሳዩት በጎ ፈቃድ፣ ጥቃቱንና ተጽዕኖውን በተወሰነ ደረጃ ለመግታት ቢቻልም፣ በተለይ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የወቅቱ አስተዳደር ግን፣ የቀረበለትን በጋራ ችግሮችን የመፍታት ጥያቄ ችላ በማለት እና ባለመቀበል ቤተ ክርስቲያናችንን በተደጋጋሚ አሳዝኗታል። በክልሉ የተወሰኑ አህጉረ ስብከት፣ ቅዱስ ሲኖዶስ ያገደው ሕገ ወጥ ቡድን፣ ለቤተ ክርስቲያን በሕግ የተሰጧትን መብቶች ከመጋፋት ጀምሮ የአስተዳደር መዋቅሯን እስከ ማፍረስ የተዳፈረው፣ ክልላዊ መንግሥቱ ለቤተ ክርስቲያን ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ ባለመስጠት በሚያሳየው ቸልተኝነት እንደ ኾነ ለመረዳት አያዳግትም። በመኾኑም፣ የትላንቱን ችግር ለማከም፣ ይልቁንም ነገ በከፋ መልኩ ሊመጣ ያለውን ለማስቀረት እንዲቻል፣ በጋራ ከመሥራት ውጪ መፍትሔ የለም፤ ብለን እናምናለን። ስለዚህ ክልላዊ መንግሥቱ፣ ጥያቄያችንን ተቀብሎ በጋራ ለመሥራት ዝግጁ እንዲኾን ቤተ ክርስቲያናችን አጥብቃ ታሳስባለች።
    6. በ2012 ዓ.ም. መባቻ፣ በአንድ ቀን 97 ዜጎች እና ምእመናን ካለቁበት የወርኀ ጥቅምቱ ጥቃት እንዲሁም የወርኀ ጥር የበዓለ ጥምቀት አከባበር ወቅት ከተፈጸሙ ግድያዎች እና ዘረፋዎች ጀምሮ፣ በልዩ ልዩ የአገራችን አካባቢዎች፣ በቤተ ክርስቲያንና በምእመናን ላይ እየደረሱ ያሉ ግፎችንና በደሎችን መንግሥት አጣርቶ ለፍርድ እንዲያቀርብ፣ ውጤቱንም በይፋ ለሕዝብ እንዲገልጽ ቤተ ክርስቲያናችን አጥብቃ ትጠይቃለች።
    7. ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን፣ ለአገር ሰላም እና ለሕዝብ አንድነት ባበረከተችው አስተዋፅኦ፣ በገነባችው የተቀደሰ ባህል እና ባወረሰችው ዘርፈ ብዙ እሴት፣ በኢትዮጵያውያን ኹሉ ልትከበር እና ልትወደድ የሚገባት ናት። ከሞላው ጸጋዋ እና በረከቷ ያልተቋደሰ ኢትዮጵያዊ ይኖራል ተብሎ የማይገመት በመኾኑ፣ የኹሉ እናት እና ባለውለታ ናት ብለን እናምናለን።

    ኾኖም፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ፣ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እየደረሱ ያሉ ተደጋጋሚ ጥቃቶች፣ አብዝቶ እንደሚነገረው፣ “በሽግግር ወቅት የሚያጋጥሙ” ተብለው ብቻ የሚታለፉ ሳይኾኑ፣ የተሳሳቱ ርእዮተ ዓለማዊ ትርክቶችንና ጂኦ-ፖለቲካዊ ዳራዎችን መነሻ በማድረግ በተቀነባበረ እና በተደራጀ ስልት የሚፈጸሙ ኦርቶዶክሳውያንን የ‘ማጽዳት’ እንቅስቃሴዎች እንደኾኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ ግልጽ እየኾነ መምጣቱን ቤተ ክርስቲያናችን ትገነዘባለች፤ በአጭር ጊዜ ሳይታረም በዚኹ ከቀጠለም፣ የከፋ ፍጻሜ ሊያስከትል እንደሚችል ከወዲሁ ታስገነዝባለች።

    ስለዚህም፣ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታት፥ በእኒህ ስሑት አስተሳሰቦች እና ሐሳዊ ትርክቶች ማሕቀፍ፣ ኾነ ተብሎ የሚፈጸም ኦርቶዶክሳውያንን የማሣቀቅ እና የማዳከም ሃይማኖት ተኮር ጥቃትን አስቀድሞ በመከላከል፣ ፍትሕን በማስፈን፣ ተጎጂዎችን በአግባቡ በመካስ እና በማቋቋም፣ ሕገ መንግሥታዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ በአጽንዖት ታሳስባለች።

    የተወደዳችኹ ተጎጂ ምእመናንና ምእመናት የመንፈስ ልጆቻችን፤

    የግፍ ጥቃቱ የደረሰባችኹና በአሁኑ ወቅት በዐጸደ ቤተ ክርስቲያን አዳራሾች እና በግለሰቦች መኖሪያ ቤቶች ተጠልላችኹ እንደምትገኙ ይታወቃል። ይህ፣ ስለ ቀናች ሃይማኖታችኹ የተቀበላችኹት መከራ፣ በቤተ ክርስቲያናችን የሰማዕታት መዝገብ በወርቅ ቀለም ተጽፎ የሚኖር ነው። በግፈኞች ፊት ለማዕተበ ክርስትናችኹ ታምናችኹ ባሳያችኹት ጽናት እና በከፈላችኹት መሥዋዕት፣ የአገራችኹን ህልውና እና አንድነት ታድጋችኋል፤ የቤተ ክርስቲያናችኹን ልዕልና አስመሰክራችኋል። ይኸውም፣ ለትውልድ አብነት ኾኖ በምሳሌነት ሲነገር የሚኖር በመኾኑ፣ እናት ቤተ ክርስቲያናችኹ ኮርታባችኋለች። ለወደፊትም፣ መላው ኢትዮጵያውያንና ኦርቶዶክሳውያን፣ በሚያስፈልጋችኹ ኹሉ ከጎናችኹ ይቆማሉ፤ ብቻችኹን እንዳልኾናችኹም ቤተ ክርስቲያን ታረጋግጥላችኋለች። ዛሬ ባገኛችኹ መከራ ግፍ አድራሾች ቢደሰቱም፣ በጊዜው ጊዜ ፍትሕን በሕግ ተጎናጽፋችኹ እንባችኹ እንደሚታበስ እና ኃዘናችኹ ወደ ደስታ እንደሚለወጥ ቤተ ክርስቲያናችን ታምናለች።

    በአገር ውስጥ እና በውጭ የምትገኙ የተወደዳችኹ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤

    አሠቃቂው ጥቃት ከደረሰበት ሰዓት ጀምሮ፣ በኢትዮጵያዊ ነባር አስተምህሮ እና የአብሮነት ባህል እርስ በርስ በመረዳዳት፣ ዓለም አቀፉ የኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ ያሳደረው ከባድ የኑሮ ጫና ሳይበግራችኹ እና ርቀት ሳይገድባችኹ የጥቃቱን ሰለባዎች ለመታደግ እና መልሶ ለማቋቋም ያደረጋችኹትንና በማድረግ ላይ ያላችኹትን ልዩ ልዩ አስተዋፅኦ፣ ቤተ ክርስቲያናችን በከፍተኛ አንክሮ ትመለከታዋለች፤ የጎሣ እና የእምነት ልዩነት ሳይገድባችኹ እስከ ሞት ደርሳችኹ ላደረጋችኹት ሰብዓዊ እና ኢትዮጵያዊ ርዳታ እና ድጋፍ፣ ልዑል እግዚአብሔር ዋጋችኹን ይከፍላችኹ ዘንድ ዘወትር ትጸልያለች።

    በሌላ በኩል፣ በክርስቲያናዊ የትብብር መንፈስ፣ በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰው ጉዳት ተሰምቷችኹ፣ ጥቃቱን በማውገዝ አጋርነታችኹን በመግለጫ እና በልዩ ልዩ ድጋፎች ላሳያችኹ የዓለም ኦርቶዶክሳውያን አብያተ ክርስቲያናት፥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የከበረ ምስጋናዋን ታቀርብላችኋለች።

    አሁንም፣ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ተጠናክሮ የተቋቋመው ዐቢይ ኮሚቴ በሚሰጠው አቅጣጫ መሠረት፣ ተጎጅዎችን ለመርዳት እና በዘላቂነት ለማቋቋም እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ፥ በገንዘብ፣ በቁሳቁስ እና በሞያ እንድትድገፉ፤ እንዳስፈላጊነቱም በቀጣይነት ለሚያስተላልፈው ጥሪ ንቁ ምላሽ ለመስጠት እንድትዘጋጁ አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን። በዚኹ አጋጣሚ፣ በአገር ውስጥ እና በውጭ የምትኖሩ ምእመናን፥ ድጋፍ እና አስተዋፅኦ ማድረግ ያለባችኹ፣ በቋሚ ሲኖዶስ የተቋቋመው የርዳታ አሰባሳቢ አካል በከፈታቸው የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች ብቻ መኾኑን እናስታውቃለን።

    ቸሩ እግዚአብሔር፥ ለአገራችንና ለዓለም ሰላምን፣ ለሕዝባችን አንድነትን፣ በግፍ ለተገደሉት ልጆቻችን ዕረፍተ ነፍስንና ለቤተ ክርስቲያናችን መጽናናትን እንዲሰጥልን እንለምናለን።

    ወስብሐት ለእግዚአብሔር
    የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት

    ~~~

    ዐቢይ ኮሚቴው የከፈታቸው የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች፡–

    በኦርቶዶክሳዊነታቸው ምክንያት በግፍ ለተፈናቀሉ ክርስቲያኖች መርጃ እና ማቋቋሚያ
    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አጭር ቁጥር፦ 8080
    ሕብረት ባንክ የሒሳብ ቁጥር፦ 1601811299653018
    ወጋገን ባንክ የሒሳብ ቁጥር፦ 0837771210101
    ቡና ኢንተርናሽናል ባንክ የሒሳብ ቁጥር፦ 3359601000003
    ዓባይ ባንክ የሒሳብ ቁጥር፦ 146211349291701

    ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት

    ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ

    Anonymous
    Inactive

    የአቫካዶ ልማት አብዮት ተጀመረ ― ግብርና ሚኒስቴር

    አዲስ አበባ (ግብርና ሚኒስቴር)፦ “የሆርቲከልቸር ልማት በማሳለጥ የውጪ ንግዱን ለማሳደግ መጪ ጊዜ የሆርቲከልቸር ነው!” በሚል መርህ ታልሞ እየተሠራ ነው። የኢፌዲሪ ግብርና ሚኒስቴር በሰብል ልማት የተጀመረውን የኩታ-ገጠም (cluster) አመራርት ላይ የታየውን ውጤታማ ሥራ በፍራፍሬ ላይም ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል።

    በፍራፍሬ ልማት ላይ የኩታ-ገጠም (cluster) አመራረት ስልት ተግባራዊ በማድረግ የአርሶ አደሩን ገቢ ለማሳደግ እና ከሀገር-አቀፍ እስከ ዓለም-አቀፍ ገበያ ተፈላጊነት ያለውን አቮካዶን በጥራት በማምረት ተወዳዳሪ ለመሆን እየተሠራ ነው። በዘርፉ የአረንጓዴ አብዮት እንዲመጣ እየሠራ እንደሚገኝ በግብርና ሚኒስቴር የሆርቲከልቸር (horticulture) ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ወንዳለ ሀብታሙ ገልጸዋል። ዘርፉ ሰፊ የሥራ ዕድል እየፈጠረ የሚገኝ፣ የውጪ ንግድ (export) በማሳደግ ለሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ምንጭ እያሳደገና የአርሶ አደሩን የሥነ-ምግብ ችግር ከመቅረፍ አንጻር ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ የሚገኝ ዘርፍ በመሆኑ ለማስፋት እየተሠራ እንዳለ አክለው ገልጸዋል።

    ይህንኑ አጠናክሮ ለመሄድ በኦሮሚያ ክልል በምሥራቅ ሸዋ ዞን በአደኣ ወረዳ ከዚህ ቀደም በጤፍ አምራችነት ይታወቅ የነበረው አሁን ደግሞ ወረዳው ካለው 70 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ተቀንሶ 600 ሄክታር መሬት ላይ የአቫካዶ ኩታ-ገጠም (avocado cluster) ለመፍጠር በሰፊው እየተሠራበት እንደሆነ ታውቋል። ከዚህ ውስጥ ከ400 ሄክታር በላይ ላይ 1300 አርሶ አደሮች የተሳተፉበት የአቮካዶ ልማት እየተከሄደ ነው።

    አቶ ከፍያለው ለማ የምሥራቅ ሸዋ ዞን የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ኃላፊ ደንካካ እና ኡዴ የተባሉ ሁለት ቀበሌዎች ለአቮካዶ ኩታ-ገጠም (cluster) ልማት ከተመረጡ ቀበሌዎች መካከል መሆኑን ገልጸው በክላስተሩ የአቮካዶ ችግኝ ተከላ ከሀምሌ ወር 2012 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ እንደሆነ ገልጸዋል።

    ይህንን የአቦካዶ ልማት ኩታ-ገጠም የሚያጠናክር የአቮካዶ ችግኝ ተከላ የተካሄደው የግብርና ሚኒስተር ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳይሬክተሮች፣ ባለሙያዎች፣ የኦሮሚያ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ኃላፊዎች፣ የምስራቅ ሸዋ ዞን እርሻና ተፈጥሮ ሀብት መምሪያ ኃላፊዎች የአካባቢው አርሶ አደሮችና የኢትዮጵያ ሆርቲከልቸር ልማትና ኤክስፖርት ማኅበር (EHPEA) ተወካዮች በተገኙበት ነው። በአደአ ወረዳ የተጀመረው አቮካዶን በኩታ-ገጠም ማልማት ሥራ ለሀገሪቷ የአቮካዶ ኤክስፖርት እድገትተስፋ ሰጭ እንደሆነ ለማየት ተችሏል።

    በችግኝ ተከላ የተሳተፉ አካላትም አምና ተተክለው የጸደቁ አቮካዶ ማሳዎች ጉብኝተው ከገበያ የማስተሳሰር ሥራ ከወዲሁ ታስቦ መሠራት እንደሚገባ አስተያየት በመስጠት የችግኝ ተከላና የአቮካዶ ልማት ኩታ-ገጠም ጉብኝት ተጠናቅቋል።

    በተያያዘ ዜና፥ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀዝቃዛ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን በባቡርና በመርከብ አቀናጅታ ለውጭ ገበያ ማቅረብ ጀምራለች። አቮካዶ የጫነ የመጀመሪያው ኮንቴነር ነሐሴ 16 ቀን 2012 ዓ.ም. ከሞጆ ደረቅ ወደብ ወደ አውሮፓ ለሙከራ ተልኳል

    የትራንስፖርት ሚኒስቴሯ ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ ምርቶቹ ለውጭ ገበያ መቅረባቸው በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ በግብርና ዘርፍ የተሰማሩ አርሶ አደሮችና ወጣቶች ምርቶቻቸውን ለዓለም-አቀፍ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ አንዲሆኑ ያደርጋቸዋል። እንዲሁም ለውጭ ምንዛሪ ግኝት ዕድል በመፍጠር ረገድም ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

    በቀጣይም አርሶ አደሩ የግብርና ምርቶቹን ጥራታቸውን እንደጠበቁና ሳይበላሹ ለውጭ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ለማድረግ እንተጋለን ብለዋል። ለዚህም የባቡርና መርከብ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን ምርቱ በሚመረትበት ሥፍራ በትኩስነቱ እንዲመጣ የማቀዝቀዣ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎች እንደሚቀርቡ ሚኒስትሯ ወ/ሮ ዳግማዊት ገልጸዋል። በዚህም ቀጣይነት ያለው የምርት አቅርቦት እንዲኖር በማድረግ የዜጎችን ተጠቃሚነትና የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል።

    ምንጭ፦ ግብርና ሚኒስቴር / የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት

    የአቫካዶ ልማት

    Anonymous
    Inactive

    ለመጪው የትምህርት ዘመን ትምህርት ቤቶች ከነሐሴ 20 ጀምሮ ምዝገባ እንደሚጀምሩ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ

    አዲስ አበባ (ሰሞነኛ)፦ የ2013 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን ምዝገባ ከነሐሴ 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ እንደሚጀመር ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ትምህርት ቤቶች የቀጣይ ዓመት የትምህርት ምዝገባን ከነሐሴ 20 ጀምረው ማካሄድ ይችላሉ ብሏል።

    የትምህርት ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሀረጓ ማሞ፥ ትምህርት ቤቶች ምዝገባውን ሲያካሂዱ ኮሮና ቫይረስን (ኮቪድ 19) ለመከላከል በዓለም የጤና ድርጅት እና በኢፌዲሪ ጤና ሚኒስቴር የተቀመጡ ቅድመ ዝግጅቶችንና መከላከያ መንገዶችን በሚገባ በመተግበር መሆን እንዳለበት አሳስቧል።

    ትምህርት የሚጀመርበት ቀን በቀጣይ እንደሚወሰንና ይፋ እንደሚደረግም የገለፁት ዳይሬክተሯ፥ የቀጣዩ ዓመት የትምህርት ሂደት ስኬታማ እንዲሆንም ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ወላጆችና መላው የትምህርት ማኅበረሰብ ይህን አስቸጋሪ ወቅት ለማለፍ የሚተላለፉትን ገዢና አስፈላጊ መልዕክቶች ብቻ በመከታተልና ቫይረሱ ሊተላለፍ የሚችልባቸውን መንገዶች ከውዲሁ በማስወገድ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል።

    አካላዊ ርቀትን ጠብቆ ለማስተማር፣ የንፅህና መጠበቂያዎችን ከማዘጋጀትና መሰል የኮሮና ቫይረስን  የመከላከያ መንገዶችን ተግባራዊ ለማድረግ በሚያስችል መልኩ ቀድመው ዝግጅት የሚደረግባቸው ተግባራትም እንደሆኑ አክለው ገልጸዋል።

    በምን ዓይነት መልኩ ትምህርት መጀመር እንዳለበት የተለያዩ አማራጮችን ለማመላከት ሰፊ ውይይት እየተደረገባቸው ሲሆን፥ ውሳኔዎች ላይ ሲደረሱ በቀጣይ ይፋ ይደረጋሉ።

    የ8ኛና የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ጊዜን በተመለከተ ትምህርት ሚኒስቴር በቅርብ የሚያሳውቅ ሲሆን ተማሪዎች ራሳቸውን እያዘጋጁ እንዲቆዩ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

    በመጪው የትምህርት ዘመን ተማሪዎች ለኮሮና ተጋላጭ እንዳይሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ምን ዓይነት ዝግጅት እያደረገ ነው?

    በ2013 የትምህርት ዘመን ተማሪዎች ለኮሮና ተጋላጭ እንዳይሆኑ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ነሐሴ 19 ቀን 2012 ዓ.ም. አስታወቋል።

    የትምህርት ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን መኩሪያ እንደገለጹት፥ የቀጣዩ ዓመት ትምህርት ምዝገባ ከነገ ነሐሴ 20 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ በመንግሥት እና በግል ትምህርት ቤቶች እንደሚጀመር እና ትምህርት ቤቶች የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ቅደመ ዝግጅቶችንና  ተግባራትን በተገቢው መንገድ በመተግበር ምዝገባ እንዲያከናውኑ አሳስበዋል።

    የበሽታው ሁኔታ እየተስፈፋ ቢሆንም የትምህርት ዝግጅት እና እንቅስቃሴ መጀመር አስፈላጊ ሆኑ መገኘቱን ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።

    ወደ መማር ማስተማር ተግባር በሚገባበት ወቅት ለተማሪዎች ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እንደሚሠራ ገልጸው፥ የፊት መሸፈኛ ጭንብል (face mask)፣ የእጅ ማፅጃ (sanitizer) እና መሰል አቅርቦቶችን ከባላድርሻ አካላት ጋር በመሆን ለማቅረብ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

    በግልም ሆነ በመንግሥት ትምህርት ቤቶች የኮሮና ቫይረስ ስርጭት እንዳይከሰት ተማሪዎች የፊት መሸፈኛ ጭንብል በማድረግ፣ አካላዊ ርቀትን በመጠበቅ እና እጅን በተደጋጋሚ በመታጠብ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚኖርባቸው ሚኒስትሩ አሳስበዋል።

    ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ላሉት ተማሪዎች በ2012 የትምህርት ዘመን በ2ኛ ሴሚስተር ያለፋቸውን ትምህርቶች ማካካሻ ለመስጠት መታሰቡንም ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮሮፖሬሽን (EBC) ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ

    በመጪው የትምህርት ዘመን ተማሪዎች

    Semonegna
    Keymaster

    አቶ ልደቱ አያሌው ለፍርድ ቤት ያቀረበው የሕግ መከራከሪያ ነጥብና የፍትህ ሥርዓቱን ውድቀት ያሳየበት ልብ የሚነካ ንግግር*

    ክቡር ፍርድ ቤት፥

    ለመጀመሪያ ቀን በዚህ ችሎት ላይ ስገኝ ከችሎቱ ጀርባ የተፃፈውንና “ተልዕኳችን የሕግ የበላይነትን በማስከበር አርዓያ መሆን ነው” የሚለውን ሳነብ እና ከአሁን ቀደም በተመሳሳይ ሁኔታ ተከስሼ ነፃ ያወጡኝ ፍርድ ቤቶች በመሆናቸው እውነተኛ ፍትህ ከዚህ ችሎት አገኛለሁ ብዬ ተስፋ አድርጌ ነበር። ዛሬ ግን በዚህ ችሎት ፊት የተገኘሁት ሕጋዊ ግዴታዬን ለመወጣትና ለችሎቱ ያለኝን አክብሮት ለመግለፅ እንጂ፥ ፍትህ አገኛለሁ ብዬ ተስፋ በማድረግ አይደለም። ክቡር ፍርድ ቤት፥ ይህንን ማለት የተገደድኩት በሚከተሉት ምክንያቶች ነው።

    1ኛ. ለፖሊስ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ የሚሰጠው በምርመራ ሂደቱ ላይ ያሉት ለውጦች በዳኞች እየተመዘኑ ቢሆንም፥ እስካሁን በቀረብኩባቸው አራት ችሎቶች ጉዳዩን ያዩት አራት የተለያዩ ዳኞች በመሆናቸው ምንም ዓይነት የምርመራ ውጤት ለውጥ በሌለበት ሁኔታ ተከታታይ የጊዜ ቀጠሮ እየተሰጠብኝ ያለው ከሕጉ መንፈስ ውጭ በመሆኑ፤

    2ኛ. ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ውጭ አገር ለመሄድ ቀጠሮ እንዳለኝ፣ በአሁኑ ወቅትም ከፍተኛ የልብ ህመም ታማሚ እንደሆንኩ፣ ከህመሜ ጋር በተያያዘም በኮቪድ-19 ቫይረስ ብጠቃ ህይወቴ አደጋ ውስጥ ሊወድቅ እንደሚችል የሕክምና መረጃ አቅርቤ እያለና በፖሊስ የቀረበብኝ ክስ የዋስትና መብት የማያስከለክል ሆኖ እያለ ያለ አግባብ የዋስ መብት ተከልክያለሁ። ክቡር ፍርድ ቤት፥ ከምገኝበት አሳሳቢ የጤና ችግር በእስር ላይ ከምገኝበት ለኮሮና እጅግ ተጋላጭ የሆነ እስር ቤት አንፃር የተከለከልኩት የዋስትና መብት ሳይሆን የሰው ልጅ መሠረታዊ መብት የሆነውን በህይወት የመኖር መብቴን ነው። ይህም የሚያሳየው ገና ወንጀለኛ ተብዬ ሳይፈረድብኝ የሞት ፍርድ የተፈረደብኝ መሆኔን ነው፤

    3ኛ. በዚህ በተከበረው ፍርድ ቤት ፊት አሁን እየተከራከርን ያለነው አንድ መንግሥት እና አንድ ዜጋ አይደለንም። በሕጉ መሠረት ከሳሽና ተከሳሽ ነን። ክቡር ፍርድ ቤቱ ለከሳሽና ለተከሳሽ መብት መከበር እኩል መቆም ሲገባው ሁል ጊዜ የከሳሽን ምክንያታዊ ያልሆነ ጥያቄ እየተቀበለ፥ በተቃራኒው ደግሞ የእኔን በመረጃ የተደገፈ ጥያቄ ውድቅ እያደረገ አድሏዊነት እየፈፀመብኝ በመሆኑ፤

    4ኛ. በአጠቃላይ በሀገር ደረጃ ያለውን ሁኔታ ስናይም፥ ፍትህ እየተሰጠ ያለው ከችሎት አደባባይ ሳይሆን ከአራት ኪሎ ቤተ-መንግሥት መሆኑን እያየን ነው። በወቅቱ የፖለቲካ ቀውስ ምክንያት በእስር ላይ የምንገኘው ዜጎች በብዙ ሺዎች የምንቆጠር ሆኖ እያለ፥ ልክ ሁላችንም አንድ ዓይነት ወንጀል እንደሠራንና ጉዳያችን በአንድ ዳኛና ችሎት ብቻ እየታየ እንደሆነ ሁላችንም የዋስ መብት ተነፍገን በተደራራቢ የጊዜ ቀጠሮ መብታችን በጅምላ እየተጣሰ ነው።

    ክቡር ፍርድ ቤት፥ እኛ ፍትህ የምንጠብቀው ከፍርድ ቤት እንጂ ከሳሻችን ከሆነው የአራት ኪሎ መንግሥት አይደለም። የአራት ኪሎ መንግሥት ኃላፊነት ሕግ ማስፈፀም ነው እንጂ ሕግ መተርጎም አይደለም። ክቡር ፍርድ ቤት፥ በአጠቃላይ እነዚህ ከላይ የጠቀስኳቸው አራት ነጥቦች የሚያሳዩት የሕግ ሳይሆን የፖለቲካ እስረኞች መሆናችንን ነው። አሁን በመጨረሻ ፖሊስ “የሽግግር መንግሥት ጥያቄ በማቅረብ መንግሥትን የመገልበጥ ሙከራ አድርጓል” በሚል ክስ ሲያቀርብብኝ መታየቱ ይህንን የሚያረጋግጥ ነው።

    በዚህ ሁኔታ እውነተኛ ፍትህ ይገኛል ብዬ ስለማልጠብቅ በጊዜ ቀጠሮ እየተመላለስኩ እኔና ጠበቃዬ አጉል ከምንጉላላ፥ ውድ የሆነው የፖሊስ እና የፍርድ ቤት ጊዜም ያለ አግባብ ከሚባክን- መቋጫ የሌለው የፖሊስ የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ እንዲቋረጥና ጉዳዩ የፖለቲካ ውሳኔ ሲሰጠውና ፖሊስ “ምርመራዬን ጨርሻለው” ባለ ጊዜ ከእስር ቤት ወደ ችሎት እንድቀርብ እንዲወሰን በታላቅ አክብሮት እጠይቃለሁ።

    ምንጭ፦ ሀብታሙ አያሌው

    * አቶ ልደቱ አያሌው የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ምክር ቤት ሲሆኑ፥ ሐምሌ 17 ቀን 2012 ዓ.ም. ፓርቲው በፕሬዝደንቱ አቶ አዳነ ታደሰ በኩል፥ አቶ ልደቱ አያሌው የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸውና ቢሾፍቱ (ደብረ ዘይት) ከተማ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ እንደታሰሩ ገልጾ ነበር። ይህንንም አስመልክቶ ፓርቲው ሐምሌ 21 ቀን 2012 ዓ.ም. ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ፦ በሰሞነኛ ድረገጽ የአማርኛ ፎረም (semonegna.com/forums) ላይ የሚገኝ ማንኛውም ጽሑፍ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንጸባርቅ ሲሆን፥ ጽሑፉ የሰሞነኛ ኢትዮጵያንንም ሆነ የተሳታፊዎችን አመለካከትና ምልከታ ላይወክል ይችላል።

    አቶ ልደቱ አያሌው

    Semonegna
    Keymaster

    በሀገራችን ኢትዮጵያ የተፈጸመውን ግፍ እውነታ በመረጃ የማሳየትና ማስረዳት ግዴታ ሁላችንም አለብን
    (ነአምን ዘለቀ)

    ሰላም ወገኖቼ ኢትዮጵያውያን፦

    ሀገራችን ኢትዮጵያን ከምንም ችግር ለመታደግ የሚያስችል ከፍተኛ ብቃቱም የሀገር ፍቅሩም ያላችሁ አያሌ የኢትዮጵያ ልጆች በውጪው ዓለም ትኖራላችሁ። የኢትዮጵያ ችግር እንደሚያሳስባችሁና በጎዋ ደግሞ እንደሚያስደስታችሁም ግልጽ ነው። ነገር ግን አብዛኞቻችሁ በተለያየ ምክንያት የዳር ተመልካች መሆንን መምረጣችሁ ሀገራችንንና ወገኖቻችንን ብዙ ዋጋ እያስከፈለ እንደሆነ እያየን ነው። ሄዶ ሄዶ ያልተጠበቀና ከእስካሁኑም በከፋ ሁኔታ ሀገራችንንና ሕዝባችንን ለማይወጡት አደጋ ለማጋለጥ እየተመቻቸን እንደሆነ ስጋቴን ልገልጽላችሁ እፈልጋለሁ።

    በኦሮሞ ጽንፍ ኃይሎች መሪነት የኢትዮጵያ ጥላቻ ያላቸው ባዕዳን እንዲሁም የህወሓት ዲያስፓራ ሚዲያዎችና ካድሬዎች በጋራ በመሆን የአሜሪካ፣ የካናዳንና የአውሮፓን የሕግ አውጪዎችና አስፈጻሚዎች በማወናበድ ጸረ-ኢትዮጵያ አጀንዳ ለማራመድ በስፋት ጠንካራ እንቅስቃሴ እያደረጉ ይገኛሉ ። ይህም በሰፊው እየወሰዷቸው ካሉ በርካታ አፍራሽ እርምጃዎች እንዱ ብቻ ነው። እነኚህ ኃይሎች ያለማጋነን ላለፉት 27 ዓመታት የጸረ-ወያኔ ሁለንተናዊ የትግል ቆይታዬ ያላየሁትን ከፍተኛ የዓላማ አንድነት (unity of purpose)፣ ቅንጅትና መናበብ በመፍጠር ከዳር እሰከ ዳር እየሰሩ ለመሆናቸው ብዙ መረጃዎች ይገኛሉ።

    ከዚህ መልዕክት ጋር ያያያዝኩት የአሜሪካ ኮንግሬስ አባላት ለአሜሪካ ስቴት ሴክሬታሪ/የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፔዮ (Mike Pompeo) የጻፉት ደብዳቤ የዚህ ሴራ አንዱ ውጤት ነው። በተቀናጀ መልክ የሀገራችንን እውነታና ሂደት በማዛባት፣ የሃሰት ትርክቶችን በመደራረት የውጭ ኃይሎችንና መንግሥታትን ለማወናበድ ያለተቀናቃኝ በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው። ይህን ማድረግ የቻሉት ደግሞ በእነሱ ጥንካሬ ሳይሆን ለኢትዮጵያ ሀገራዊ አንድነት፣ ለፍትህ፣ ለሕዝብ እኩልነት፣ ለሕግ የበላይነት ቀናዊ የሆነው ኢትዮጵያዊ ጎራ (silent majority) የተበታተነ መሆኑና የሚያምንበትን የሀገርና ሕዝብ አንድነት እውን ለማድረግ የድርሻውን ለመወጣት ቁርጠኛ አለመሆኑ ነው።

    “ነፍጠኛን ምታ፣ አቃጥል፣ ግደል፤ ቁረጥ” የሚሉ ያልተቋረጡ የጥላቻ ዘመቻዎች በሶሻል ሚዲያና በኦኤምኤን (OMN) ሚዲያ እንደሚክያሄድ ታውቃላችሁ ብዬ አምናለሁ። የዚህ ዘመቻ ውጤትም ብዙ መቶ ወገኖቻችን በኦሮሞ ጽንፈኞች አርመኔያዊ በሆነ መንገድ መጨፍጨፍ ነው። ይህም ግፍ በቅድመ ጄኖሳይድ (pre-genocide) ደረጃ የሚመደብ የዘርና የሃይማኖት ተኮር ፍጅት ነው ማለት ከእውነቱ የራቀ አይደለም። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ይህን ሀቅ በመካድ አፈናቃይና ገዳዮቹ በተገላቢጦሽ ከሳሽ በመሆን “መንግሥት በኦሮሞ ሕዝብ ላይ የሚያደርገው አፈና” ያለ በማስመስል የተቀናጀ የሀሰት ትርክት በማሥራጨት ላይ ይገኛሉ። ዓላማቸውም የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አመንስቲ (Amnesty) እና ሂውማን ራይትስ ዎች (Human Rights Watch) የመሳሰሉ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶችን፣ የአሜሪካ፣ የአውሮፓና፣ የካናዳ የሕግና የፓሊሲ አውጪዎችን ከጎናቸው ለማሰለፍ ሲሯሯጡ ይታያሉ።

    በአሜሪካና በአንዳንድ ሀገሮች የሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ይህን የሀሰት ትርክት ለመለወጥ ጥረት ያደረጋሉ። ነገር ግን አብዛኞቹ ኢትዮጵያ ኤምባሲዎች አደጋውን መመከት በሚቻልበት ልክ የአቅምና ፓለቲካ ቁርጠኝነት ይዘው ሲንቀሳቀሱ አይታዩም። ከዚህ ከተያያዙት የተመልካችነትና ተከላካይነት ውሱን እንቅስቃሴ አልፈው የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና፣ የየሀገሩን የፓሊሲና የሕግ አውጪዎችን እውነታውን ለማስጨበጥ በቂና አጥጋቢ ሥራ መሥራት ይጠበቅባቸዋል።

    ይህ በጽንፈኞች የተቀነባበረ ርብርብና ዘመቻ በጊዜ ካልተገታ ኢትዮጵያን አንድ አድርጎ የያዘውን መንግሥት እየቦረቦረ እንዳያዳክመው ስጋት አለ። ከህወሓት እስከ ኦነግ ሽኔ በተለያዩ አፍራሽ ኃይሎች ተወጥሮ የሚገኘው በዶ/ር ዓብይ አህመድ የሚመራው መንግሥት ከተዳከመ ሀገሪቷን ለትርምስ፣ ለሁከትና ሌላም የከፋ አደጋ ሊያጋልጥ ይችላል። ስለዚህም እንደሕዝብና ሀገር ከፊታችን የተደቀነውን አደጋ በቀላሉ ማየት የለብንም።

    አደጋው በጣም የሚያስፈራው ደግሞ ቅራኔው በመንግሥትና በሕዝብ መካከል ብቻ መሆኑ ቀርቶ የ27 ዓመቱ የጥላቻ ቅስቀሳ ስር ሰዶ ሕዝብ አቃቅሯል። በየጊዜው የምናየው ግድያ፣ መፈናቀልና ንብረት መውደም የዚህ የጥላቻ ፖለቲካ ውጤት ነው። “ብሔር ለብሔር” ቅራኔዎችና ግጭቶችን እነማን ለምን ዓላማ ሲያራግቡ፣ ሲደግፉና ሲቆሰቁሱ እንደነበሩና ዛሬም ድረስ ያማያርፉበት፣ የሚተጉበት መሆኑን ሁላችንም የምናውቅም ይመስለኛል።

    እነዚህን የውስጣዊና የውጭ ከባድ አደጋዎች ድምር ለመግታትም በተደራጀ መልክ በካናዳ፣ በአሜሪካና በአውሮፓ የተናበቡ ሥራዎች መሥራት ግድ ይላል። ለየሀገራቱ የሕግ አውጪ (lawmakers) እና የሥራ አስፈጻሚ/የፓሊሲ ወሳኞች (policymakers) በሀገራችን ኢትዮጵያ የተፈጸመውን ግፍ እውነታ በመረጃ የማሳየትና ማስረዳት ግዴታ ሁላችንም አለብን። ስለዚህም ሁላችንም በየሀገሩና በየከተማው መሰባሰብ፣ መነጋገር፣ መተባበር፣ መቀናጀትና ጠንካራ የአድቮኬሲ ቡድን (advocacy group) ማቋቋም ይኖርብናል። ከዛሬ ሁለት ወር በፊት ገደማ በሀገርና በሕዝብ ላይ የመጣው አደጋ አሳስቧቸው የተሰባሰቡ በርካታ ምሁራን፣ አክቲቪስቶች፡ የፓለቲካ፣ የአድቮኬሲ፣ የድርጅታዊ ልምድና ተሞከሮ ያላቸው ኢትዮጵያውን የሚገኙበት ዓለም ኣቀፍ ኔትዎርክ እገዛ ያደርግላችኋል። ይህን መሰል እንቅስቃሴ የምታደርጉ ለማድረግ የተዘጋጃችሁ ሁሉ፣ አሰፈላጊውን የሰነድ፣ የምክር፣ የአቅጣጫ ድጋፍ ልናደርግላችሁ ፈቃደኞችና ዝግጁዎች ስለሆን በውስጥ መስመር (messenger inbox) ልታገኙን ትችላላችሁ።

    ነአምን ዘለቀ
    bit.ly/NeaminZeleke

    ሰሞነኛ ኢትዮጵያ፦ በሰሞነኛ ድረ-ገጽ የአማርኛ ፎረም (semonegna.com/forums) ላይ የሚገኝ ማንኛውም ጽሑፍ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንጸባርቅ ሲሆን፥ ጽሑፉ የሰሞነኛ ኢትዮጵያንንም ሆነ የተሳታፊዎችን አመለካከትና ምልከታ ላይወክል ይችላል።

    በሀገራችን ኢትዮጵያ የተፈጸመውን ግፍ እውነታ በመረጃ የማሳየትና ማስረዳት ግዴታ ሁላችንም አለብን

    Anonymous
    Inactive

    ድሬዳዋ፣ መዳ ወላቡ እና ሰመራ ዩኒቨርሲቲዎች ከ460 በላይ ተማሪዎችን አስመረቁ

    ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ መስኮች በድኅረ ምረቃና በቅድመ መደበኛ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸውን 118 ተማሪዎች አስመረቀ። ከተመራቂዎች መካከል 56ቱ የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች ሲሆኑ፥ 23 ተማሪዎች ደግሞ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሰለጠኑ የሕክምና ዶክተሮች እንዲሁም በቴክኖሎጂ ኢኒስቲቲዩት 39 ተማሪዎች በኪነ ህንፃ በመጀመሪያ ዲግሪ ያሰለጠናቸው ናቸው።

    የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተመራቂዎች ሃገራችን በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ ውስጥ ሆና የተመረቁ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ በተለይም የሕክምና ተመራቂዎች የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል በተጀመረው ጥረት ውስጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

    ሌሎችም በተመረቁበት ሙያ የሀገሪቱን እድገት በማረጋገጥ ረገድ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል።

    የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኡባህ አደም በበኩላቸው፥ ዩኒቨርሲቲው በምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት በመሰማራት በ2012 በጀት ዓመት 38 የምርምር ሥራዎች ፀድቀው ወደ ሥራ መግባታቸውንና ሃያ ሰባቱ መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል።

    ከዩኒቨርሲቲው ጋር በተያያዘ፥ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሙሉ ነጋ እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲን የሥራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል።

    በጉብኝቱ የዩኒቨርሲቲው ሪፈራል ሆስፒታል ያለበትን የግንባታ ደረጃና የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ በዩኒቨርስቲው እየተሠሩ ያሉ ሥራዎችንና የSTEM ማዕከሉን ጎብኝተዋል።

    ከተማሪዎች ምረቃ ዜና ሳንወጣ፥ መዳ ወላቡ እና ሰመራ ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 345 ተማሪዎች ነሐሴ 16 ቀን 2012 አስመርቀዋል።

    የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አህመድ ከሊል በምረቃው ሥነ-ሥርዓት እንደተናገሩት፥ ተቋሙ በየዓመቱ በርካታ ተማሪዎችን አሰልጥኖ ቢያስመርቅም ዘንድሮ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል። ሆኖም እንደ “ኦንላይን” ያሉ የተለያዩ አማራጭ በመጠቀም ምሩቃን ተማሪዎች የሚጠበቅባቸውን እንዲያሟሉ ማድረጉንም ገልጸዋል።

    መዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በዕለቱ በሁለተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር ያስመረቃቸው 208 ተማሪዎች አምስተኛው ዙር ሲሆኑ፥ በተፈጥሮ ሳይንስ፣ ቋንቋና ሥነ ጽሁፍ፣ ሕክምናና ጤና ሳይንስ፣ ማኅበራዊ ሳይንስ፣ የተፈጥሮ ቀመር፣ ቢዝነስና ምህንድስና የተማሩ ናቸው።

    ዶክተር አህመድ እንደገለጹት፥ ዩኒቨርሲቲው የአካባቢውን ማኅበረሰብ ከኮሮና ቫይረስ ለመጠበቅ ግንዛቤ ከማስጨበጡ በተጓዳኝ ለችግር የተጋለጡ ወገኖችን የመደገፍና ተመርምረው ራሳቸውን እንዲያውቁ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል። ተመራቂዎች በትምህርት ቆይታቸው የቀሰሙትን ዕውቀት ወደ ተግባር ቀይረው ሀገራቸውንና ሕዝባቸውን እንዲያገለግሉና ኮሮናን በመከላከሉም የድርሻቸውን እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

    ከተመራቂዎች መካከል መሐመድ አህመድ በሰጠው አስተያየት፥ ኮሮና ቫይረስ በትምህርቱ ዘርፍ ጫና ቢያሳድርም በቴክኖሎጂ ታግዘው ለምርቃት በመብቃቱ መደሰቱን ገልጾ፥ በሰለጠነበት ሙያ ሕብረተሰቡን ለማገልገል ዝግጁ መሆኑን ተናግሯል። ሌላው የእለቱ ተመራቂ ጣህር መሐመድ በበኩሉ በሙያው ሕዝቡን በማገልገል የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ገልጿል።

    በ1999 ዓ.ም 742 ተማሪዎች ተቀብሎ ሥራ የጀመረው መዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ አሁን ላይ ከ24ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎች እንዳሉት ተመልክቷል።

    በተመሳሳይ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ፣ ርቀትና ተከታታይ የትምህርት መረሃ ግብር ያሰለጠናቸው 137 ተማሪዎች አስመርቋል።

    የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አደም ቦሪ በምረቃው ሥነ-ሥርዓት እንደገለጹት፥ ያስመረቋቸው ተማሪዎች ኮሮና ቫይረስ ጫና ቢፈጥርባቸውም አማራጭ የመገናኛ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ናቸው።

    ከተመራቂዎቹ መካከል 107 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ በተለያዩ የትምህርት መስኮች የሰለጠኑ ሲሆኑ፥ ቀሪዎቹ በመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ፣ ርቀትና ተከታታይ ትምህርት የተከታተሉ መሆኑ ተመልክቷል።

    ተመራቂዎች ወደ ሥራ ሲገቡ በሰለጠኑበት ሙያ ሀገራቸውንና ሕዝባቸውን በቅንነትና ፍትሃዊነት ማገልገል እንዳለባቸው ፕሬዚዳንቱ ዶ/ር አደም ቦሪ አሳስበዋል።

    ከተመራቂዎች መካከል በሁለተኛ ዲግሪ አካውንቲንግና ፋይናንስ የትምህርት መስክ አራት ነጥብ በማምጣት የተመረቀው መሃመድ አሊ በሰጠው አስተያየት፥ ከ17 ዓመታት በኋላ ወደ ትምህርት ተመልሶ የቤተሰብ ኃላፊነትና የሥራ ጫና ተቋቁሞ ለዚህ ውጤት በመብቃቱ መደሰቱን ገልጿል። በቀጣይም እራሱን የበለጠ በማብቃት በተሰማራበት ሙያ በቅንነትና በትጋት ሀገሩን ለማገልገል እንደሚሠራ ተናግሯል።

    ድሬዳዋ፣ መዳ ወላቡ እና ሰመራ ዩኒቨርሲቲዎች ከ460 በላይ ተማሪዎችን አስመረቁ

Viewing 15 results - 181 through 195 (of 730 total)